Telegram Web Link
#ግብር

" የቤተክርስቲያን ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ሊመለከተው ይገባል " - አባቶች

➡️ የሃይማኖት ተቋማት ከተቋቋሙበት ዓላማ ባሻገር የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ሲሳተፉ ታክስ መክፈል እንዳለባቸው መወሰኑ ይታወቃል !

ቤተ ክርስቲያን የተጨማሪ ገቢ ግብር መክፈል እንዳለባት በተላለፈ ውሳኔ ላይ ውይይት መደረጉን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገለጸች።

ውይይቱ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የተካሄደ ሲሆን፦
- ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣
- ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የደቡብ ምስራቅ ትግራይና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
- ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስአበባ እና የሐድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
- ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ ፕሬዘዳንትና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሊቀ ጳጳስ ተገኝተው ነበር።

ከመንግሥት በኩል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ የሥራ ኀላፊዎች እና መጋቢ ታምራት የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ በውይይቱ ተካፍለዋል።

የሃይማኖት ተቋማት ከተቋቋሙበት ዓላማ ባሻገር የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ሲሳተፉ ታክስ መክፈል እንዳለባቸው የሚደነግገውን አዋጅ ላይ በከተማ አስተዳደሩ የተጋበዙ የሥራ ኀላፊዎች ዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል።

ከቤተክርስቲያን ወገን የተገኙ መሪዎችና የሥራ ኃላፊዎች ፤ ጉዳዩ ዙሪያ መለስ ውጤቶችን ከግምት ባስገባ መልኩ ተጨማሪ ምክክር ሊደረግበት የሚገባ መሆኑን አሳውቀዋል።

በተጨማሪ የቤተክርስቲያን ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ሊመለከተው እንደሚገባ መጠቆማቸውም ተገልጿል።

ውይይቱ ቀጣይነት እንዳለው ተጠቁሟል።

መረጃው የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

@tikvahethiopia
926😡352👏66🤔36😢30😱20😭15💔14🕊12🥰5🙏3
" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።

አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር  እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።

አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።

ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።

አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።

ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።

እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።

አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።

ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።

በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።

አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ

@tikvahethiopia
1.02K👏49🕊21😡15😭13🙏11🤔9🥰7😱1
" ሦስት 5Lሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት ፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል " - ባለንብረቶቹ

ትላንት (ረቡዕ ለሐሙስ) ከሌሊቱ 9 ሰዓት ገደማ ፓርክ ከተደረጉበት ሦስት 5L ሚኒባሶች እንደተወሰዱባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቹን ያየ ሁሉ እንዲጠቁማቸው በአጽንኦት ተማጽነዋል።

ባለንብረቶቹ " ሦስት 5L ሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል። ሁለቱ 'ተኝተን ነበር' አሉ። ከተቀጠረ ሦስት ቀናት የማይሞላው ጥበቃ ነው ከተሽከርካሪዎቹ ጋር አብሮ የጠፋው " ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

" ጥበቃው የተቀጠረው በኤጀንሲ ነበር። ኤጄንሲው ተመሳጥሮ እንዳይሆን የሚል ጥርጣሬ አለን። ምክንያቱም ኤጀንሲው የተሟላ ዶክሜንት አልያዘም ጥቃውን ሲቀጥረው፤ ዋስትና አልያዘም 'መጣል' በሚል" ብለዋል።

አክለው፣ "ኮሚቴዎች ደግሞ 'አይቻልም' ብለው ሲመልሱ አማላጅ ፓሊስ ጠርቶ 'ፓሊሱ እኔ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ፤ በሦስት ቀናት ያመጣል ይስራ' እንዳላቸው ነው ኮሚቴዎቹ የነገሩን። የኤጀንሲው ሰውም፣ ፓሊሱም፣ ሁለቱ ጥበቃዎችም ተይዘዋል" ነው ያሉት።

ሦስቱም ተሽከርካሪዎች ከአንድ ፓርኪንግ ከቆሙበት እንደተወሰዱ፣ የተወሰዱትም ቃሊቲ ቶታል ጨፌ ኮንዶሚኒየም እንደሆነ፣ አንዱ መኪና ኦሮ ኮድ 03 34021 መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላኛው የጠፋው ተሽከርካሪ ኦሮ ኮድ 03 ኦሮ 41867 እንደሆነ፣ ከጠፉት ከሦስቱ አንዱ እንደተገኘ በዚህ ዘገባ ታርጋቸው የተገለጹት እንዳልተገኙ ገልጸው፣ ተሽከርካሪዎቹን ያየ በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንዲጠቁማቸው ተማጽነዋል።

የባለንብረቶቹ ስልክ ቁጥሮች 0912049042፤ 0965206720
ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አዲስ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
 
@tikvahethiopia
1.31K😢240🙏78😱62💔62🤔40😭35🕊22🥰20😡13
💎 ትልቁ ይገባዎታል!

በፀሐይ ባንክ "ዳይመንድ የቁጠባ ሒሳብ" ተጠቃሚ ይሁኑ!

9.5% እስከ 10% የሚደርስ የወለድ መጠን የሚያስገኝ ልዩ የቁጠባ ሒሳብ!

እርስዎ በርትተው ይቆጥቡ፤ እኛ ዳጎስ ባለ የወለድ ምጣኔ እንደግፍዎታለን! አሁኑኑ የፀሐይ ባንክ "ዳይመንድ የቁጠባ ሒሳብ" ይክፈቱ!

ለበለጠ መረጃ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ ወይም ወደ 921 ነጻ የጥሪ ማዕከላችን ይደውሉ፡፡

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!


የፀሐይ ባንክ የቴሌግራም ገጽን ይቀላቀሉ 👇 https://www.tg-me.com/tsehaybanksc
179🙏7🥰5😡3😢2🤔1😭1
" በአነስተኛ ጀልባዎች ለመሻገር የሚደረጉ ሙከራዎች ከንቱ ይሆናሉ "- የዩናይትድ ኪንግደም ጠ/ሚ

ዩናይትድ ኪንግደም ከፈረንሳይ በአነስተኛ ጀልባዎች ወደ አገሪቱ የሚገቡ ስደተኞችን በሳምንታት ጊዜ ውስጥ አዲስ በተወጠነ እቅድ መሰረት መመለስ እንምትጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪር ስታመር መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በእቅዱ መሰረት አገር ውስጥ የሚገቡ አንዳንድ ስደተኞች ወደ ፈረንሳይ ሲመለሱ፤ ዩናይትድ ኪንግደም ደግሞ ተመጣጣኝ ቁጥር ያላቸውን ጥገኛ ጠያቂዎች የደኅንነት ፍተሻ አድርጋ ትቀበላለች።

የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለሦስት ቀናት የሥራ ጉብኝት ለንደን ይገኛሉ።

መሪዎቹ በጋራ በሰጡት መግለጫ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ስታመር " በአነስተኛ ጀልባዎች ለመሻገር የሚደረጉ ሙከራዎች ከንቱ ይሆናሉ " ብለዋል።

እቅዱ በሳምንት እስከ 50 የሚደርሱ ሰዎች እንዲመለሱ እንደሚያደርግ የተዘገበ ቢሆንም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን አሃዙን አላረጋገጡም።

" ለውጥ አምጪው " እቅድ የሰዎች ዝውውር ላይ የተመለደውን አካሄድ ለመስበር የሚያግዝ እና ውጤታማ ከሆነ በስፋት የሚሰራበት ነውም ብለዋል።

ሕገ-ወጥ ስደት " ዓለም አቀፍ ቀውስ፣ የአውሮፓ ሕብረት ቀውስ እና የሁለቱ አገሮቻችን ቀውስ ነው " ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
372😭50🙏14😢10💔8🕊5🤔3
አዲሱ የዩትዩብ ሞኒታይዤሽን መመሪያ ምን ይዟል ?

ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ዩትዩብ፤ ዩትዩብን ተጠቅመው ገቢ በሚያስገቡ ላይ ጥብቅ መመሪያ አውጥቷል።

መመሪያው ምን ይላል ?

- ከአሁን በኋላ ዩትዩብ ክፍያ የሚፈጽመው አዲስና የራሳቸው ፈጠራ ብቻ ለሆኑ ፤ በብዛት ወይም በድጋሚ በዩትዩብ ላይ ላልዋሉ ስራዎች ነው።

- ክፍያ የሚፈጸምላቸው ቪድዮዎች እውነት እና የራስ ስራ ላይ የተመሰረቱ ብቻ መሆን አለባቸው።

- አርተፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ተጠቅመው የሚሰሩ ሰዎች ክፍያ አይከፈላቸውም።

- በድምፅና ትንሽ የቪድዮ ስራ ብቻ ተጨማምሮባቸው የሚቀርቡ የሌላ ሰዎች ስራዎች ክፍያ አያገኙም።

- በተለያዩ ተንቀሳቃሽ ቪድዮዎች ወይም የሰው ቪድዮዎች ላይ reaction መስጠት እና የሰው ቪድዮዎችን እየሰበሰቡ ማቅረብ ከዩትዩብ ክፍያ ውጭ ይደረጋሉ።

- የራሳቸው ስራ ያልሆነ ቪድዮ ማለትም እዛው ዩትዩብ ላይ በሌሎች የተሰሩ ቪድዮ የሚያቀርቡ ሰዎች የራሳቸውን ሃሳብ እንዲጨምሩና እንዲሰሩ የሚጠየቁበት መንገድ ቢኖርም ያለማስጠንቀቂያም ሊታገዱ ይችላሉ።

ዩትዩብ በአዲሱ መመሪያው ኦሪጅናል ለሆኑ እና ሰዎች በራሳቸው ጥረት ለሰሯቸው ስራዎች ክፍያ ይከፍላል። ክፍያ ለማግኘት የራስን የፈጠራ ስራ ዩትዩብ ላይ መጫን ግዴት ይሆናል።

ዩትዩብ ይህን ወደማድረግ የገባው ሰዎች የራሳቸውን የፈጠራ ስራ እንዲሰሩ ለማበረታታ ነው።

ዩትዩብ ክፍያ ለመክፈል ከዚህ ቀደም ያስቀመጠው አስገዳጁ 1 ሺህ ሰብስክራይበር እንዲሁም 4,000 የዕይታ ሰዓት በ12 ወራት ውስጥ ማግኘት አሁንም እንደ ግዴታ ይቀጥላል ተብሏል።

#YouTube #TheVerge

@tikvahethiopia
984😢130👏117🙏27😡16😱14😭12🤔8🕊8🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tax ዩትዩብ ወይም ቲክቶክ የመሳሰሉ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ገንዘብ የሚያገኙ ግለሰቦች እና ተቋማት ታክስ እንዲከፍሉ ሊደረግ ነው። በክፍያ የሚቀርቡ ወይም በሚያቀርቡት አገልግሎት ገንዘብ ከሚያገኙ የድረገጽ እና የመተግበሪያ ውጤቶች ላይ መንግሥት ታክስ ሊሰበስብ መዘጋጀቱን አሰራሩን ለመተግበር ከወጣው የመንግሥት ሰነድ መመልከቱን ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል። በድረገጽ የሚቀርቡ የሚዲያ አገልግሎቶች ፖድካስት፣…
#Ethiopia🇪🇹

ከዩቲዩብ ፣ ቲክቶክና ከሌሎች የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ሊጣል ነው።

በኢትዮጵያ ለ9 ዓመታት ስራ ላይ የቆየውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ለመጣል የሚያስችል ንዑስ አንቀጽ ተካቷል።

በታቀደው የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ መሰረት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ የሚገኝ ገቢ ለምሳሌ ፦
- ከዩቲዩብ፣
- ፌስቡክ፣
- ኢንስታግራም፣
- ቲክቶክና ሌሎችም መድረኮች
- በኢንተርኔት ከሚሰራጩ መረጃዎች
- በኢንተርኔት ከሚፈፀሙ ግብይቶች፣
- ከስፖንሰርሺፕ ከመሳሰሉት የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር እንደሚጣልባቸው በዝርዝር ያስቀምጣል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዉይይት እየተደረገበት የሚገኘዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ፤ እነዚህ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች በመደበኛነት የሚከናወኑ ከሆነ፣ የሚገኘው ገቢ በንግድ ስራ ገቢ ስር የሚመደብ ሲሆን፣ የንግድ ስራ ገቢ ግብርም የሚከፈልበት መሆኑን ይገልጻል።

ሆኖም፣ በአዋጁ የተቀመጡትን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ፣ ገቢው " ሌሎች ገቢዎች "  በሚለው ስር ተመድቦ ከጠቅላላ ገቢው ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፈልበት ይደረጋል ይላል።

ከዚህ በተጨማሪም፣ ለዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ክፍያ የሚያመቻቹ መድረኮች ለእያንዳንዱ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ የተከፈለውን ገንዘብ የሚያሳይ ሪፖርት ለታክስ ባለስልጣን የመላክ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ያስቀምጣል።

ይህን ተከትሎም፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የማውጣት ፣ ገቢያቸውን የማስታወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎችን የመወጣት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው ያስገድዳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው። #CAPITAL

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.14K😭430😡301👏107🤔72🕊30😱23🙏18💔15🥰13😢8
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል !

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የጭካኔ የግድያ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኞች ተብለው የፍርድ ውሳኔ ተላለፈባቸው።

ተከሳሾቹ ለፍርድ ውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል በማለት " የቆየ ህመም አለብን " ቢሉም የመቐለ ዓይደር ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሃኪሞች የምርመራ ማስረጃ " የቆየ ህመም የለባቸውም " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

የመቐለ ማእላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ ግድያ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

የተጠርጣሪ ጠበቆች ትናንት ሀምሌ 3 " ደምበኞቻችን የቆየ ህመም አለባቸው ይህንን ለማረጋገጥ የህክምና ማስረጃ ለአርብ ሀምሌ 4 እናቀርባለን " ብለው ነበር።

ፍርድ ቤቱ ይህን ተቀብሎ ለዛሬ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።

ዛሬ አርብ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም ከመንግስት ሰራተኞች የስራ ሰዓት በፊት ቤተሰብ የሚገኙባቸው የሚድያና የሴቶች መብት ተቆርቋሪዎች በፍርድ ቤቱ በራፍ ደርሰው ተሰባስበዋል።

ተከሳሾች ለውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል ብለው የጠየቁት የህክምና ማስረጃ የቆየ ህመም እንደሌለባቸው አረጋግጧል።

ዳኞችም ይህን ካረጋገጡ በኋላ በተከሳሾች ላይ ውሳኔ ሰጥተዋል።

አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሾች ያሬድ ገብረስላሰ በላይ እና ኣንገሶም ሃይለማርያም በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ አለመርካታቸው የገለፁት አስተያየት ሰጪዎች የወንጀል ደርጊቱን ከማጠራት እስከ ምርመራና ውሳኔ ድረስ በችግሮች የተተበተበ እንደነበር በመግለፅ ማረሚያ ቤት የፍርድ ውሳኔውን በጥብቅ እንዲተገብረው ጠይቀዋል። 

" የጭካኔ ግድያው የሞት ፍርድ ያሰጥ ነበር " ያሉ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የተበዳይ ቤተሰቦች ወደ ቀጣዩ የፍርድ ቤት ይግባኝ ይጠይቁ " ብለዋል።

ከነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም የተጓዘው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ በዚሁ ተቋጭቷል ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የእንስቷን ግድያ ከመነሻው እስከ ፍርድ ሂደቱ ሲከታተል ቆይቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
2.01K👏435🙏115😡69😭50🕊41😢17😱15💔11🥰5🤔1
ባለንበት ሆነን ወርሃዊ የውሃ ፍጆታችንን በቀላሉ በቴሌብር በመክፈል ጊዜያችን መቆጠብ እንችላለን።

ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ ክፍያ ➡️ የውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ➡️ ክፍያ
*127# ደውለን ወይም ቴሌብርን በስልካችን በዚህ ሊንክ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!

#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
135🙏10👏5😢3
#AmazonFashion

ሙሉ ልብስ ሽያጭና ኪራይ   የአመቱ የማጣሪያ ሽያጭና ታላቅ ቅናሽ ሙሉ ልብስ(ሱፍ) ሽያጭ ከ 12 ሺ -15 ሺ ብቻ፤ በርካታ አማራጭ ስላለን ለብዛት ፈላጊዎች ለሚዜዎች ለተመራቂ ተመራቂዎች በብዙ አማራጭ አለን። በተጨማሪም የሙሉ ልብስ ኪራይም  በሌላኛው ብራንቻችን አለን።

አድራሻ: ፒያሳ downtown ህንፃ ምድር ላይ 

☎️ 0919339250 / 0911072936 /0939721321

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w
130😭11🙏3
2025/07/12 19:54:57
Back to Top
HTML Embed Code: