Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢራን የኢራን ፕሬዝዳንት የሆኑት ኢብራሂም ራኢሲ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር " #በአደገኛ_ሁኔታ " መሬት ላይ ማራፉን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የሀገሪቱ ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሂሊኮፕተሩ በአደገኛ ሁኔታ አርፎበታል ወደተባለበት ስፍራ ላይ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንዳለ ገልጿል። የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ ቦታው ለመድረስ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል። ፕሬዝዳንቱ ሀገራቸው ከአዘርባጀን…
#IRAN🇮🇷

የኢራኑ ፕሬዝዳንት እና አብረዋቸው የነበሩ ከፍተኛ ባለስልጣናት (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እየተፈለጉ ነው።

ህዝቡ መሪዎቹ ምንም ሳይሆኑ በህይወት ተርፈው ይመለሱ ዘንድ ፈጣሪውን እየለመነ ይገኛል።

ፕ/ት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ባለስልጣናት ኢራን ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ ላይ የተገነቡ 2 ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ በሂሊኮፕተር ወደ ታብሪዝ ከተማ ሲያመሩ ነው ደብዛቸው የጠፋው።

ሄሊኮፕተሯ በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ ሳቢያ ከተራራ ጋር እንደተጋጨች ተነግሯል።

ሂሊኮፕተሯ ተጋጭታለች የተባለበት #ትክክለኛው ቦታ እስካሁን ድረስ ባይለይም ተጋጭታለች ተብሎ በታሰበበት እያንዳንዱ ቦታ ላይ ግን የነፍስ አድን ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

የአየር ሁኔታው ግን እጅግ በጣም ከባድ እንደሆነ ተሰምቷል።

ቪድዮ፦ ቀን እና ማታ ላይ የነበረውን የህዝቡን ሁኔታ የያሳያል።

@tikvahethiopia
ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ - ለአንቺ የሚገባሽ!

ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ ከመደበኛው የቁጠባ ሒሳብ ላቅ ያለ ወለድ የምታገኚበት!

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃ እንዲርሶ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጫኑ፡፡
ቴሌግራም- https://www.tg-me.com/HibretBanket
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
ዌብሳይት- https://www.hibretbank.com.et/
#Hibretbank
#Tecno #Camon30Pro5G

ቪድዮዎች እና ምስሎችን በከፍተኛ ጥራት ማንሳት እንዲያስችል Sony Imx890 የካሜራ ሴንሰርን የተገጠመለት አዲሱ Tecno Camon Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
TIKVAH-ETHIOPIA
#IRAN🇮🇷 የኢራኑ ፕሬዝዳንት እና አብረዋቸው የነበሩ ከፍተኛ ባለስልጣናት (የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ጨምሮ) እየተፈለጉ ነው። ህዝቡ መሪዎቹ ምንም ሳይሆኑ በህይወት ተርፈው ይመለሱ ዘንድ ፈጣሪውን እየለመነ ይገኛል። ፕ/ት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ባለስልጣናት ኢራን ከአዘርባጀን ጋር በምትዋሰንበት አካባቢ ላይ የተገነቡ 2 ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ በሂሊኮፕተር ወደ ታብሪዝ ከተማ ሲያመሩ ነው…
#ኢራን

የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል።

ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት አረጋግጧል።

ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል።

ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር #ሙሉ_በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

" የፕሬዜዳንት ኢብራሂም ራይሲ ሄሊኮፕተር በአደጋው ሙሉ በሙሉ ተቃጥላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሁሉም ተሳፋሪዎች ሳይሞቱ አልቀሩም " ብለዋል ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣን።

#ሮይተርስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢራን የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራይሲ ተሳፍረውባት በነበረው ሄሊኮፕተር በደረሰው አደጋ ህይወታቸው አልፏል። ይህንንም የሀገሪቱ የመንግሥት አረጋግጧል። ከሳቸው በተጨማሪ በሂሊኮፕተር ውስጥ አብረው የነበሩት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴይን አሚር አብዶላሂያን እና ሌሎች በርካታ ሰዎች ሞተዋል። ሮይተርስ በአደጋው ፕሬዚዳንቱ ሲጓዙባት የነበረችው ሄሊኮፕተር #ሙሉ_በሙሉ መቃጠሏን " አንድ የኢራን…
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ?

- የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ
- የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን
- የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ
- የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ
- የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ
- የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣
- የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ
- ቦዲጋርድ
- የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር አደጋ ሞተዋል።

የፕሬዜዳንት ራይሲን ሞት ተከትሎ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ሞሀመድ ሞክበር በ50 ቀናት ውስጥ በምርጫ አዲስ ፕሬዜዳንት እስኪመረጥ ድረስ የፕሬዜዳንቱን ቦታ ተክተው ይሰራሉ።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢንጂነር አይሻ መሀመድ እና ዶ/ር አብርሃም በላይን የስልጣን ቦታ ቀያየሩ።

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህም ፦

1. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣

2. ዶ/ር አብረሃም በላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር ፣

3. ዶ/ር መሀመድ እንድሪስ ደግሞ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል አድርገው ሾመዋቸዋል።

ኢ/ር አይሻ መሀመድ በ2011 ዓ/ም የመጀመሪያዋ ሴት የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙ በኃላ 6 ወር እንዳገለገሉ ከቦታው ተነስተዋል።

ዶ/ር አብርሃም በ2014 ነበር የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት።

ዶ/ር አብርሃም በላይ የአሁኑ ሹመት እስኪሰጥ ድረስ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴርን በሚኒስትርነት እያገለገሉ የነበሩ ሲሆን አሁን በኢ/ር አይሻ መሀመድ ተተክተው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር ሆነዋል።

@tikvahethiopia
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture

የዘመናዊነት ተምሳሌት!


አድራሻችን

1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727
2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686
3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282

👉 Telegram:  https://www.tg-me.com/yonatanbt_furniture
👉 Facebook:  https://www.facebook.com/profile.php?id=100087238034736
👉 TikTok: https://www.tiktok.com/@yonatanbtfurniture
👉 Instagram: https://www.instagram.com/yonatanbtfurniture/
#AddisAbaba

አምስት (5) ፓርኮችን ለማልማት ከ10 ቢሊዮን ብር ላይ የሚፈጅ የፕሮጀክት ጥናት መደረጉ ተነገረ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ መዝናኛ ኮርፓሬሽን ከሚያስተዳድራቸው 10 ፓርኮች መካከል 5ቱ በንጉሱ እና በደርግ ጊዜ የተሰሩና ከስታንዳርድ በታች በመሆናቸው ለማልማት / ደረጃቸውን ለማሻሻል ታቅዶ ለ3ቱ ዲዛይን ተሰርቶ አንዱን ማልማት መጀመሩን አስታውቋል።

ኮርፓሬሽኑ ይህንን ያለው ባለፈው ቅዳሜ በሰጠው መግለጫ ሲሆን የሚታደሱትም ፦
- ኩባ ፓርክ፣
- ሐምሌ 19፣
- ብሔረ ፅጌ፣
- ኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ፣
- አዲስ ዙ (ፒኮክ) ፓርኮች መሆናቸውን ገልጿል።

ለማልማት ምን ያህል በጀት ያስፈልጋል ? ተብሎ ጥያቄ የቀረበለት ኮርፖሬሽኑ ፥ “ Estimation በጀቱ ትልቅ ነው። የኮንስትራክሽን በጀቶቹ ቀላል አይደሉም ” ብሏል።

“ አሁን አዲሱ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ፕሮጀክት ነው የተጠናው። በተግባር ሲገባ ስንት ይሆናል ? የሚለው በወቅቱ የምናሳውቅ ይሆናል። ኮሪያ ፓርክ ላይም እየሰራን ያለነው ከ100 ሚሊዮን ብር ባለፈ ወጪ ያለው ነው ” ሲልም አክሏል።

' ስድስት ኪሎ ' ያለው ፓርክ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ በመሆኑ ሲታደስ የታሪክ ትዝታዎቹ አይጠፉም ወይ ? ተብሎ ለቀረበው ጥያቄም፣ “ 6 ኪሎም ሆነ ሌሎቹን በፊት ያለውን መሠረታዊ ነገር እንዲለቅ አይፈለግም ” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

“ የፓርኮች ልማት ጤናማ የሆነ ማህበረሰብ እንዲኖር የማድረግ እድል ይኖረዋል። ስለዚህ በእኛ በኩል ከማንኛውም ልማት በላይ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው፣ ሕዝብንና ተፈጥሮን የማገናኘት ጉዳይ ነው የፓርክ ጉዳይ ” ብሏል ኮርፖሬሽኑ።

“ የፓርክ ልማት ለአዲስ አበባ የህልውና ጉዳይ ነው። ትርፍ ስራ አይደለም ፤ የ Prioritization ስራም አይደለም ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ነው ፤ አለበለዚያ ከተማው በአንድ ጀንበር የመጥፋት እድል ነበረው ” ሲል ገልጿል።

“ በዛ መልክ የማንሰራ ከሆነ የከተማው ህልውና አደጋ ላይ ነው ያለው። የማህበረሰቡ አኗኗር ለበሽታ የመጋለጥ እድሉ በጣም ከፍተኛ ነው። ፓርክ መስራት ማለት ለሕዝቡ ኦክስጂን መስጠት ነው ” ነው ያለው።

በቀጣይም በኮሪደር ልማት ስራ በርካታ ፓርኮች እና መዝናኛ ቦታዎች እንደሚሰሩ ያመለከተው ኮርፖሬሽኑ እነዚህንም በማካተት " የህዝቡን የመዝናኛ እና ንጹህ ቦታ የመኖር ፍላጎት እንዲሟላ እንሰራለን " ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ? - የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን - የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ - የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ - ቦዲጋርድ - የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር…
#ኢራን

" ...አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ ላይ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " - ሙሐመድ ጃቫር ዛሪፍ

የኢራን የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ የኢራን ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት ላይ ለደረሰው የሄሊኮፕተር አደጋ አሜሪካን ተጠያቂ አድርገዋል።

ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ " #አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " ብለዋል፡፡

ከኢራን ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ ደረጉት ዛሪፍ ፣ " ማዕቀቡ ኢራን #አዳዲስ የአቪየሽን ምርቶችን መግዛት እንዳትችል አድርጓታል " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ጥሩ የሚባል ግንኙነት እንደሌላት ይታወቃል።

ትላንት የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ እና ሌሎች ባለልስጣናት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ታብሪዝ እያመሩ ሳሉ የነበሩበት ሂሊኮፕተር ከተራራ ጋር ተጋጭቶ ሁሉም ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው በደረሰበት አካባቢ ላይ እጅግ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንደነበርም ተገልጿል።

More ➡️ @thiqaheth
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት እነ ቀሲስ በላይ መኮንን ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ አዟል።

በዋስ ጥያቄያቸው ዛሬም ውድቅ ተደርጓል።

ቀሲስ በላይ መኮንን በችሎቱ ፥ " ፖሊስ ይዞኝ ሳይሆን እራሴ ነው የሄድኩት " ብለዋል፡፡

" #ብዙ_የሀገር_ጉዳይ በእጄ ስላሉ ጥፋ ብባል እንኳ የምጠፋ ስላልሆንኩ ፤ በጤናዬ ላይ በደረሰው እክልና በቤተሰቦቼ ላይ በደረሰው ችግር ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብት ይጠብቅልኝ " ሲሉ ጠይቀዋል።

የብዙ ልጆች አሳዳጊና የቤተሰብ አስተዳዳሪ እንደሆኑ ጠቅሰው በዋስ ከእስር እንዲወጡ ጠይቀው ነበር።

ፍርድ ቤት ግን ሁሉም ተከሳሾች በፖሊስ ጣቢያ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ አዟል።

ቀሲስ በላይ መኮንን በሀሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ላይ #ከ6_ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማውጣት ሙከራ አድርገዋል ተብለው አብረዋቸው ከነበሩት ሰዎች ጭምር መታሰራቸው አይዘነጋም።

ያንብቡ : https://telegra.ph/DW-05-20 #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
#Hawassa

በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ።

ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር።

አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው ግራ እንዳጋባቸውና ልክ እንደባለፈዉ ጊዜ ከስራቸዉ ተስተጓጉለው ቤት መዋል መጀመራቸው እንዳሳዘናቸው ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል ፥
° ቤቶቹን ለምን ታሸጉ ?
° መፍትሄውስ ምንድን ነው ? ሲል የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለን ጠይቋል።

እሳቸውም ፤ " #በሲዳማ_ክልል_ስር የወጣ አንድም የንግድ ፈቃድ የለም " ብለዋል።

" ከወራት በፊት ከነዚህ አካላት (ቤቲንግ ቤቶች) ጋር በነበረን ውይይት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ህጋዊ እንዲሆኑ ተግባብተን ነበር " ሲሉ አስታውሰዋል።

" ይሁንና ከረዥም ጊዜ በኋላ ዳግም ስናጣራ አሁንም ህጋዊ መሆን አልቻሉም " ያሉት ሀላፊው " ከዚህ ባለፈም እነዚህ ቤቶች በትምህርት ቤት ፣ በሀይማኖት ተቋማትና በመኖሪያ ሰፈሮች እንዲሰሩ አይፈቀድም ሌላዉ የመዘጋታቸዉ ምክኒያት ይኸው ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

ለግለሰቦቹ በሰላማዊ መንገድ ምክንያቱ ተነግሯቸው ቤታቸዉ እየተዘጋ መሆኑን የገለጹት አዛዡ ፤ " ከዚህ ዉጭ ' ገንዘብ ተወሰደብኝ ' እንዲሁም ' የአላግባብ ህገወጥ የሆነ ተግባር ተፈጽሞብኛል ' የሚል አካል በማንኛዉም ሰአት ወደ ሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመምጣት ሊያመለክት ይችላል " ብለዋል።

ቤቶቹ ተመልሰው #የመከፈት እድል አላቸዉ ወይ ? ተብለው የተጠየቁት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ " መጀመሪያ ህጋዊ ይሁኑ ከዛ በኋላ ከፖሊስ በተጨማሪ የሚመለከታቸዉ አካላት የሚመለከቱት ጉዳይ ይሆናል " ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
2024/05/21 00:31:09
Back to Top
HTML Embed Code: