“እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” - ባለስልጣኑ
➡️ከ2015 እስከ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም በሥራ ላይ የ142 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተጠቁሟል!
የአዲስ አበባ ከተማ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከ2015 እስከ 24/10/2017 ዓ/ም ድረስ በመዲናዋ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች 121 ወንዶች፣ 21 ሴቶች በድምሩ 142 ሰዎች በህንጻ ሥራ ላይ እያሉ በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡
42 ወንዶችና 10 ሴቶች በድምሩ 52 በለሚኩራ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በንፋስ ስልክ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በቦሌ፤ 13 ወንዶችና አንዲት ሴት በድምሩ 14 ሰዎች በቂርቆስ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎቹ ክፍለ ከተሞች ህወታቸው ማለፉን የባለስልጣኑ መረጃ በዝርዝር ያስረዳል፡፡
ባለስልጣኑ ህንፃች አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ “እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” ብሏል፡፡
ባለፉት አስር አመታት በአዲስ አበባ ሰማይ ጠቀስ ህንጻዎች በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙ፣ ለአብነትም በ2017 ዓ/ም በከተማዋ 11 ሺሕ 748 አዳዲስና 12 ሺሕ 322 ነባር ግንጻዎች ክትትል እንደተደረገባቸው፣ ግንባታዎቹ ከ581 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት እንዳላቸው የባለሥልጣኑ መረጃ ይገልጻል፡፡
በከተማዋ በግንባታ ሳይቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚታዩ የአደጋ መንስኤዎች እና ስጋቶች ምንድን ናቸው?
-ከከፍታ ላይ መውደቅ
-የኤሌክትሪክ አደጋ
-የእቃ መውደቅ
-የግንባታ መዋቅር ችግር
-የሠራተኞች በቂ ስልጠና አለመውሰድ
-የግል ደህንነት መጠበበቂያ መሳሪያዎች ያለመጠቀም
-የቁጥጥር ችግር፣ የበጅት እጥረት
-ህግ የማስከበር ችግር ዋና ዋናዎቹ ናቸው ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ “በአስር አመት አማካኝ የኢንዱስትሪው እድገት 10%"፣ “በቀጥታና በተዘዋዋሪ በየዓመቱ በአማካኝ የሚፈጠረው የሥራ እድል 1.2 ሚሊዮን” መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ “በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ፈጣን ኢንዱስትሪው እድገት በሠራተኞች የሥራ ላይ ደንነነት ተመሳሳይ ለውጥና መሻሻል እየታየበት አይደለም” ብሏል፡፡
“አልሚዎች ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ወጭ ለመጨረስ በሚያደርጉት ጥረት የሥራ ላይ ደህንነት ትኩረት በመሆኑ አደጋና ጉዳት እየጨመረ ይገኛል” ብሎ፣ የኮንስትራክሽን እድገት በአጭር ጊዜና በዝቅተኛ ዋጋ ግንባታዎችን ለመጨረስ የሥራ ላይ ደህንነትን አቀናጅቶ መተግበር እንደሚገባ አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጃ ከላይ የተያያዘ ሲሆን፣ ተጣለ የተባለውን ቅጣት የተመለከተ ተጨማሪ አለን)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ከ2015 እስከ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም በሥራ ላይ የ142 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተጠቁሟል!
የአዲስ አበባ ከተማ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከ2015 እስከ 24/10/2017 ዓ/ም ድረስ በመዲናዋ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች 121 ወንዶች፣ 21 ሴቶች በድምሩ 142 ሰዎች በህንጻ ሥራ ላይ እያሉ በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡
42 ወንዶችና 10 ሴቶች በድምሩ 52 በለሚኩራ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በንፋስ ስልክ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በቦሌ፤ 13 ወንዶችና አንዲት ሴት በድምሩ 14 ሰዎች በቂርቆስ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎቹ ክፍለ ከተሞች ህወታቸው ማለፉን የባለስልጣኑ መረጃ በዝርዝር ያስረዳል፡፡
ባለስልጣኑ ህንፃች አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ “እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” ብሏል፡፡
ባለፉት አስር አመታት በአዲስ አበባ ሰማይ ጠቀስ ህንጻዎች በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙ፣ ለአብነትም በ2017 ዓ/ም በከተማዋ 11 ሺሕ 748 አዳዲስና 12 ሺሕ 322 ነባር ግንጻዎች ክትትል እንደተደረገባቸው፣ ግንባታዎቹ ከ581 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት እንዳላቸው የባለሥልጣኑ መረጃ ይገልጻል፡፡
በከተማዋ በግንባታ ሳይቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚታዩ የአደጋ መንስኤዎች እና ስጋቶች ምንድን ናቸው?
-ከከፍታ ላይ መውደቅ
-የኤሌክትሪክ አደጋ
-የእቃ መውደቅ
-የግንባታ መዋቅር ችግር
-የሠራተኞች በቂ ስልጠና አለመውሰድ
-የግል ደህንነት መጠበበቂያ መሳሪያዎች ያለመጠቀም
-የቁጥጥር ችግር፣ የበጅት እጥረት
-ህግ የማስከበር ችግር ዋና ዋናዎቹ ናቸው ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ “በአስር አመት አማካኝ የኢንዱስትሪው እድገት 10%"፣ “በቀጥታና በተዘዋዋሪ በየዓመቱ በአማካኝ የሚፈጠረው የሥራ እድል 1.2 ሚሊዮን” መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ “በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ፈጣን ኢንዱስትሪው እድገት በሠራተኞች የሥራ ላይ ደንነነት ተመሳሳይ ለውጥና መሻሻል እየታየበት አይደለም” ብሏል፡፡
“አልሚዎች ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ወጭ ለመጨረስ በሚያደርጉት ጥረት የሥራ ላይ ደህንነት ትኩረት በመሆኑ አደጋና ጉዳት እየጨመረ ይገኛል” ብሎ፣ የኮንስትራክሽን እድገት በአጭር ጊዜና በዝቅተኛ ዋጋ ግንባታዎችን ለመጨረስ የሥራ ላይ ደህንነትን አቀናጅቶ መተግበር እንደሚገባ አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጃ ከላይ የተያያዘ ሲሆን፣ ተጣለ የተባለውን ቅጣት የተመለከተ ተጨማሪ አለን)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤292😭47🕊8😡6👏4😱4😢4💔3🤔2🥰1🙏1
TIKVAH-ETHIOPIA
“እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” - ባለስልጣኑ ➡️ከ2015 እስከ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም በሥራ ላይ የ142 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተጠቁሟል! የአዲስ አበባ ከተማ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከ2015 እስከ 24/10/2017 ዓ/ም ድረስ በመዲናዋ በ11ዱም…
ያለፈቃድ የግንባታ ዲዛይን ማስፋፊያ ለሚያደርጉ አካላት በየእርከኑ የ100 ሺሕ ብር ቅጣት ተጣለ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ባደረገው የቅጣት ማሻሻያ በሕንፃ ግንባታ ህግጋት መሰረት በተጣለው የህንፃ ደህንነትና ተያያዥ ቅጣት በተለያዩ ተግባራት ከ15 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን ገልጿል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው የባለስልጣኑ መረጃ እንዲሚያስረዳው፥ የማስፋፊያ ሥራ የዲዛይን ማሻሻያን ስለሚፈልግ፣ ያልተፈቀደ ግንባታ የዲዛይን ጥራት ስለሚጎድለው የመደርመስ አደጋ ስለሚያስከትል ያለፈቃድ የማስፋፋት ሥራ ማከናወን (በየእርከኑ) 100 ሺሕ ብር ያስቀጣል።
እንዲሁም፣ ጥራት ያለው ስካፎልዲንግ፣ ሾርኒንግና መሰል መሳሪያዎችን አለመጠቀም ለአደጋ የሚያጋልጥ መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ በግንባታ ወቅት እነዚህን መስፈርቶች ለማያሟሉ አካላት (በእርከን) 50 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን አመልክቷል።
ቅጣቱ "በየእርከኑ" ሲባል ምን ማለት እንደሆነ ባለስልጣኑ ሲያስረዳም፣ "ለምሳሌ አንድ G+10 ህንጻ 26 የክትትል እርከኖች ይኖሩታል፤ 26*50,000=1,300,000 ይሆናል" ሲልም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ያለተቆጣጣሪ ማሰራት ለአደጋ አጋላጭ በመሆኑ የግንባታ ስራዎችን ያለተቆጣጣሪ የሚያሰሩ አካላት (በየእርከኑ) 25 ሺሕ ብር እንደሚቀጡም ተጠቁሟል።
ስቶር፣ ልብስ መሸጫ፣ መመገቢያና ሌሎች የቅድመ ግንባታ መስፈርቶችን ሳያዘጋጁ ሥራ ለሚጀምሩ አካላት የ15 ሺሕ ብር፤ በሚሰጥ የማስታወቂያ ትዕዛዝ መሰረት ተረፈ ምርትን በወቅቱ ለማያነሱ 15 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን የደረሰን የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል።
ሕጋዊ ተጠያቂነትን በተመለከተ የማማከር ኃላፊነትን በአግበባቡ አለመወጣት ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ30 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ፤ ደረጃውን ያልጠበቀ ግንባታ ማከናወን ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ50 እስከ 100 ሺሕ የገንዘብ ቅጣቶች መጣላቸው ተመልክቷል፡፡
እንዲሁም፣ ግባታውን በህዝብ ደህንነት አደጋ በሚጥል ሁኔታ ያከናወነ ከ5 እስከ 10 ዓመታት የእስራት እና ከ20 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት የተገለጸ ሲሆን፣ ጥፈተኛ ሆኖ የተገኘ አማካሪ/ሥራ ተቋራጭ ከ15 ዓመት እስከ ከፍተኛ የእስር ጊዜው ፈቃዱ ይታገዳል ተብሏል፡፡
(የቀድሞው እና የተሻሻለውን ቅጣት፤ የመፍትሄ ሀሳቦችን የያዘው የባለስልጣኑ መረጃ ከላይ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ባደረገው የቅጣት ማሻሻያ በሕንፃ ግንባታ ህግጋት መሰረት በተጣለው የህንፃ ደህንነትና ተያያዥ ቅጣት በተለያዩ ተግባራት ከ15 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን ገልጿል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው የባለስልጣኑ መረጃ እንዲሚያስረዳው፥ የማስፋፊያ ሥራ የዲዛይን ማሻሻያን ስለሚፈልግ፣ ያልተፈቀደ ግንባታ የዲዛይን ጥራት ስለሚጎድለው የመደርመስ አደጋ ስለሚያስከትል ያለፈቃድ የማስፋፋት ሥራ ማከናወን (በየእርከኑ) 100 ሺሕ ብር ያስቀጣል።
እንዲሁም፣ ጥራት ያለው ስካፎልዲንግ፣ ሾርኒንግና መሰል መሳሪያዎችን አለመጠቀም ለአደጋ የሚያጋልጥ መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ በግንባታ ወቅት እነዚህን መስፈርቶች ለማያሟሉ አካላት (በእርከን) 50 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን አመልክቷል።
ቅጣቱ "በየእርከኑ" ሲባል ምን ማለት እንደሆነ ባለስልጣኑ ሲያስረዳም፣ "ለምሳሌ አንድ G+10 ህንጻ 26 የክትትል እርከኖች ይኖሩታል፤ 26*50,000=1,300,000 ይሆናል" ሲልም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ያለተቆጣጣሪ ማሰራት ለአደጋ አጋላጭ በመሆኑ የግንባታ ስራዎችን ያለተቆጣጣሪ የሚያሰሩ አካላት (በየእርከኑ) 25 ሺሕ ብር እንደሚቀጡም ተጠቁሟል።
ስቶር፣ ልብስ መሸጫ፣ መመገቢያና ሌሎች የቅድመ ግንባታ መስፈርቶችን ሳያዘጋጁ ሥራ ለሚጀምሩ አካላት የ15 ሺሕ ብር፤ በሚሰጥ የማስታወቂያ ትዕዛዝ መሰረት ተረፈ ምርትን በወቅቱ ለማያነሱ 15 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን የደረሰን የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል።
ሕጋዊ ተጠያቂነትን በተመለከተ የማማከር ኃላፊነትን በአግበባቡ አለመወጣት ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ30 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ፤ ደረጃውን ያልጠበቀ ግንባታ ማከናወን ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ50 እስከ 100 ሺሕ የገንዘብ ቅጣቶች መጣላቸው ተመልክቷል፡፡
እንዲሁም፣ ግባታውን በህዝብ ደህንነት አደጋ በሚጥል ሁኔታ ያከናወነ ከ5 እስከ 10 ዓመታት የእስራት እና ከ20 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት የተገለጸ ሲሆን፣ ጥፈተኛ ሆኖ የተገኘ አማካሪ/ሥራ ተቋራጭ ከ15 ዓመት እስከ ከፍተኛ የእስር ጊዜው ፈቃዱ ይታገዳል ተብሏል፡፡
(የቀድሞው እና የተሻሻለውን ቅጣት፤ የመፍትሄ ሀሳቦችን የያዘው የባለስልጣኑ መረጃ ከላይ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤401😡86👏35🙏13😢10🕊8🥰6🤔4
ጥያቄያችን ካልተመለሰ ወደ ቤት አንገባም ያሉ ነዋሪዎች !
" መንግስት መጥቶ ጥያቄያችንን ካለመለሰልን ወደ ቤት ላለመመለስ ወስነን ሜዳ ላይ ተሰብስበናል " - ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
" ሰሚ እስክናገኝ ወደ ቤታችን አንመለስም ! "
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች " በአዲስ የመዋቅር ጥናት እና ልማታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የወረዳዉ መንግስት እንዲያነጋግን ብንጠይቅም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን በአደባባይ ወጥተን ድምፃችንን ለማሰማት ተሰብስበናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የአከባቢዉ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሀዋሳ ከተማ አዲስ የመዋቅር አደረጃጀት ጋር በተያያዘ የተናገሯቸው መረጃዎችን መነሻ በማድረግ ሕዝቡ የወረዳው መንግስት ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቋል።
ነገር ግን የሚያናግር አካል ባለመምጣቱ 18 የሚሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአከባቢው ባለሃብቶችን ያካተተ የሕብረተሰቡ ተወካዮች ተሰይመዉ በየደረጃው የመንግስት አካላትን እንዲያነጋግሩ ቢላኩም ተገቢው ምላሽ ስላልተሰጣቸው ሕዝቡ ሜዳ ላይ ተሰብስቦ መዋሉን አስረድተዋል።
የህዝቡ መሰረታዊ ጥያቄ " ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ዶሬ ባፋኖ አከባቢ ያሉ አምስት ቀበሌያት በአዲስ መልክ ይዋቀራል በተባለዉ የሀዋሳ አንድ ክፍለ ከተማ ስር ተካተዋል " መባሉ ነዉ ያሉ አንድ አስተያየት ሰጪ " ይህ የወረዳዉን አቅም ያዳክመዋል የሚል ቅሬታ ሕዝቡ ዘንድ ፈጥሯል " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዛሬዉ ዕለትም ' የሚያናግራችሁ የመንግስት አመራር ይመጣል ' ተብለን ቀኑን ሙሉ ብንጠበቅም እንደተባለው ባለመምጣቱ ሕዝቡ በነቅስ ወደ ወረዳ አስተዳዳሪዉ ቢሮ ሄዷል ' አመራሩ ተነጋግሮ ያነጋግራችኋል ' ተብለን ምላሽ ባለመምጣቱ ሕዝቡ ' የሚያነጋግረን የመንግስት አካል እስኪመጣ ወደ ቤታችን አንመለስም ' በማለት ምሽቱንም በአንድ ቦታ ላይ ተሰባስቦ ይገኛል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ መረጃ ለማግኘት ባደረገዉ ሙከራ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊን በስልክ አግኝቷቸው ነበር። ግን " የወረዳ አስተዳዳሪ አነጋግሩ " በማለታቸዉ ወደ አስተዳዳሪዉ የእጅ ስልክ ደጋግመን ብንደዉልም ምላሽ ማግኘት ባለመቻሉ ምላሻቸው ሳይካተት ቀርቷል።
ምላሻቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" መንግስት መጥቶ ጥያቄያችንን ካለመለሰልን ወደ ቤት ላለመመለስ ወስነን ሜዳ ላይ ተሰብስበናል " - ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
" ሰሚ እስክናገኝ ወደ ቤታችን አንመለስም ! "
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች " በአዲስ የመዋቅር ጥናት እና ልማታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የወረዳዉ መንግስት እንዲያነጋግን ብንጠይቅም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን በአደባባይ ወጥተን ድምፃችንን ለማሰማት ተሰብስበናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የአከባቢዉ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሀዋሳ ከተማ አዲስ የመዋቅር አደረጃጀት ጋር በተያያዘ የተናገሯቸው መረጃዎችን መነሻ በማድረግ ሕዝቡ የወረዳው መንግስት ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቋል።
ነገር ግን የሚያናግር አካል ባለመምጣቱ 18 የሚሆኑ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአከባቢው ባለሃብቶችን ያካተተ የሕብረተሰቡ ተወካዮች ተሰይመዉ በየደረጃው የመንግስት አካላትን እንዲያነጋግሩ ቢላኩም ተገቢው ምላሽ ስላልተሰጣቸው ሕዝቡ ሜዳ ላይ ተሰብስቦ መዋሉን አስረድተዋል።
የህዝቡ መሰረታዊ ጥያቄ " ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ዶሬ ባፋኖ አከባቢ ያሉ አምስት ቀበሌያት በአዲስ መልክ ይዋቀራል በተባለዉ የሀዋሳ አንድ ክፍለ ከተማ ስር ተካተዋል " መባሉ ነዉ ያሉ አንድ አስተያየት ሰጪ " ይህ የወረዳዉን አቅም ያዳክመዋል የሚል ቅሬታ ሕዝቡ ዘንድ ፈጥሯል " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዛሬዉ ዕለትም ' የሚያናግራችሁ የመንግስት አመራር ይመጣል ' ተብለን ቀኑን ሙሉ ብንጠበቅም እንደተባለው ባለመምጣቱ ሕዝቡ በነቅስ ወደ ወረዳ አስተዳዳሪዉ ቢሮ ሄዷል ' አመራሩ ተነጋግሮ ያነጋግራችኋል ' ተብለን ምላሽ ባለመምጣቱ ሕዝቡ ' የሚያነጋግረን የመንግስት አካል እስኪመጣ ወደ ቤታችን አንመለስም ' በማለት ምሽቱንም በአንድ ቦታ ላይ ተሰባስቦ ይገኛል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ መረጃ ለማግኘት ባደረገዉ ሙከራ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊን በስልክ አግኝቷቸው ነበር። ግን " የወረዳ አስተዳዳሪ አነጋግሩ " በማለታቸዉ ወደ አስተዳዳሪዉ የእጅ ስልክ ደጋግመን ብንደዉልም ምላሽ ማግኘት ባለመቻሉ ምላሻቸው ሳይካተት ቀርቷል።
ምላሻቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
❤529👏49😱41😭38🕊24😢17🤔14😡9🥰8🙏6
#SouthEthiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ የማሽንጋ ወንዝ በመሙላቱ በተከሰተ ጎርፍ የሁለት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የወላይታ ዞን አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ አቶ ዳዊት ደሳለኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወደ ገበያ እየሄዱ የነበሩ አራት አርሶአደሮችን የዉሃ ሙላቱ ወስዷቸዉ እንደነበር የገለፁት አቶ ዳዊት ሁለቱ በሕይወት መትረፋቸውን ሁለቱ ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን ገልፀዋል።
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች በመሬት ናዳ ሰዎች እንደሞቱ ተደርጎ እየተሰራጨ ያለዉ መረጃ ከእዉነት የራቄ ነዉ ያሉት ኃላፊዉ ከሰሞኑ በዞኑ በየትኛውም ቦታ በመሬት ናዳ የሞተ ሰዉ አለመኖሩን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ፤ በዛው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ አሪ ዞን ሳላማጎ ወረዳ ዲሜገሮ ቀበሌ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ለመትከል በቁፋሮ ላይ የነበሩ ሰራተኞች ላይ አፈር ተደርምሶ ሦስት ወጣቶች ወዲያውኑ መሞታቸውን የወረዳዉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዳጁ ጨነቀ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ በአከባቢው የከፍተኛ ኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ታዎር ለመትከል DCGG በተባለ ኮንትራክተር አማካኝነት በተቆፈሩ ጉድጓዶች የዝናብ ዉሃ መሙላቱን ተከትሎ ዉሃዉ በጄኔሬተር ፓንፕ እንዲወጣ ተደርጎ ሰራተኞች ግንባታ እየሰሩ በነበረበት የአፈር መደርመስ ተከስቶ እንደሆነ አስረድተዋል።
በአደጋው ሦስት ወጣቶች ሲሞቱ በሁለቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስታዉቀዋል።
የሦስቱ ወጣቶች አስከሬን በእስካቫተር ተቆፍሮ መዉጣቱንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ የማሽንጋ ወንዝ በመሙላቱ በተከሰተ ጎርፍ የሁለት ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የወላይታ ዞን አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ አቶ ዳዊት ደሳለኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወደ ገበያ እየሄዱ የነበሩ አራት አርሶአደሮችን የዉሃ ሙላቱ ወስዷቸዉ እንደነበር የገለፁት አቶ ዳዊት ሁለቱ በሕይወት መትረፋቸውን ሁለቱ ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን ገልፀዋል።
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች በመሬት ናዳ ሰዎች እንደሞቱ ተደርጎ እየተሰራጨ ያለዉ መረጃ ከእዉነት የራቄ ነዉ ያሉት ኃላፊዉ ከሰሞኑ በዞኑ በየትኛውም ቦታ በመሬት ናዳ የሞተ ሰዉ አለመኖሩን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ፤ በዛው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ አሪ ዞን ሳላማጎ ወረዳ ዲሜገሮ ቀበሌ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ምሶሶ ለመትከል በቁፋሮ ላይ የነበሩ ሰራተኞች ላይ አፈር ተደርምሶ ሦስት ወጣቶች ወዲያውኑ መሞታቸውን የወረዳዉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዳጁ ጨነቀ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ በአከባቢው የከፍተኛ ኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ታዎር ለመትከል DCGG በተባለ ኮንትራክተር አማካኝነት በተቆፈሩ ጉድጓዶች የዝናብ ዉሃ መሙላቱን ተከትሎ ዉሃዉ በጄኔሬተር ፓንፕ እንዲወጣ ተደርጎ ሰራተኞች ግንባታ እየሰሩ በነበረበት የአፈር መደርመስ ተከስቶ እንደሆነ አስረድተዋል።
በአደጋው ሦስት ወጣቶች ሲሞቱ በሁለቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስታዉቀዋል።
የሦስቱ ወጣቶች አስከሬን በእስካቫተር ተቆፍሮ መዉጣቱንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
😭245❤139💔18🕊11😢6🙏4🤔3👏1