"የዙፋን ልፊያ" ገበያ ላይ ቀርቧል።
መፅሐፌ ገበያ ላይ ውሏል። ይህን በ2 ምክኒያቶች እንድታስተዋውቁ እፈልጋለሁ።
ምክንያት አንድ ፥ መፅሐፌ አልተመረቀም። የምርቃት ፕሮግራም ለማስታወቂያ ቀጥተኛ ጥቅም አለው። ለኔ ግን አልሆነልኝም። ስለዚህ የእናንተን ማስታወቂያ እፈልጋለሁ
ምክንያት ሁለት ፥ ፌስቡክ ሊገባኝ ባልቻለ ሰበብ ቀጥቶኛል። ተደራሽነቴ ላይ ገደብ አድርጓል። ስለዚህ ይህን ለማካካስ የናንተ ማስታወቂያ ያስፈገኛል።
ይህን ስለምታደርጉ አመሰግናለሁ
አሳታሚና አከፋፋይ ጃፋር መፃሕፍት
መፅሐፌ ገበያ ላይ ውሏል። ይህን በ2 ምክኒያቶች እንድታስተዋውቁ እፈልጋለሁ።
ምክንያት አንድ ፥ መፅሐፌ አልተመረቀም። የምርቃት ፕሮግራም ለማስታወቂያ ቀጥተኛ ጥቅም አለው። ለኔ ግን አልሆነልኝም። ስለዚህ የእናንተን ማስታወቂያ እፈልጋለሁ
ምክንያት ሁለት ፥ ፌስቡክ ሊገባኝ ባልቻለ ሰበብ ቀጥቶኛል። ተደራሽነቴ ላይ ገደብ አድርጓል። ስለዚህ ይህን ለማካካስ የናንተ ማስታወቂያ ያስፈገኛል።
ይህን ስለምታደርጉ አመሰግናለሁ
አሳታሚና አከፋፋይ ጃፋር መፃሕፍት
❤11👍3🔥1
የዙፋን ልፊያ ልብወለድ ነው።
ከዚህ ቀደም እንዳልኩት ፥ ስነ-ፅሑፍ ለፖለቲካ ጉዳይ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል። ስነ-ፅሁፍ ከሰው ለሰው በሰው ነው። ሰው ይፅፋል ፥ በሰው በኩል ለሰው ይቀርባል። በአንድም በሌላም ትኩረቱ ስለ ሰው ነው።
ፖለቲካ ደግሞ በእያንዳንዱ ሰው ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ ያሳደራል። ብንወድም ባንወድም በፖለቲካ ተፅዕኖ ስር ነን።
"ነገን ፍለጋ" በሚለው መፅሐፌ ያልኩትን እዚህ ልድገም። ፖለቲካ የማግባት ወይም ያለመግባባት ሁኔታችንን ይወስናል። እውነት መስሎ ባይታይም ፖለቲካ የዜጎችን ትዳር እስመወሰን ድረስ ጉልበት አለው።
"ፖለቲካ በሩቁ" ባዮች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ መሆን አይችሉም። ሰው ፖለቲካን ይሸሽ ይሆናል። ፖለቲካ ግን ሰውን አይሸሽም። ስለዚህ ለፖለቲካ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል።
የዙፋን ልፊያ ልብወለድ ነው። ፖለቲካ የተርታ ሰዎች ህይወት ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ የሚያሳይ የልብወለድ...
በመፅሐፌ ከመንግሥት ወይም ከተቃዋሚዎች ጋር ቃላት መወራወር አልፈለግኩም። መንግስትም ሆነ ተቃዋሚዎች ትኩረቴ አይደሉም። ትኩረቴ ፖለቲካ ግለሰብ ህይወት ላይ ያለው ቀጥተኛ ተፅዕኖ ነው።
የዙፋን ልፊያ ሁነኛ ትከረቱ ቀጣይ ነጥቦች ናቸው
ፖለቲካ በተርታ ሰው ህይወት ላይ ያለው ተፅዕኖ ምንድነው?
ጦርነት እና የግለሰብ ህይወት ምን አገናኘው?
የፖለቲከኞች ግላዊ ባህሪ እና የዜጎች የእለት ተዕለት ህይወት እንዴት ይገናኛል?
ከላይ ያነሳኋቸው ጥያቄዎች "የዙፋን ልፊያ" መፅሐፌ ትኩረት ናቸው።
በተቻለኝ መጠን ከቀደመው ስራዬ የተሻለ ስራ ለማምጣት የሞከርኩ ይመስለኛል።
መፅሐፌ ገበያ ላይ ውሏል። ይህን በ2 ምክኒያቶች እንድታስተዋውቁ እፈልጋለሁ።
ምክንያት አንድ ፥ መፅሐፌ አልተመረቀም። የምርቃት ፕሮግራም ለማስታወቂያ ቀጥተኛ ጥቅም አለው። ለኔ ግን አልሆነልኝም። ስለዚህ የእናንተን ማስታወቂያ እፈልጋለሁ
ምክንያት ሁለት ፥ ፌስቡክ ሊገባኝ ባልቻለ ሰበብ ቀጥቶኛል። ተደራሽነቴ ላይ ገደብ አድርጓል። ስለዚህ ይህን ለማካካስ የናንተ ማስታወቂያ ያስፈገኛል።
ይህን ስለምታደርጉ አመሰግናለሁ
@Tfanos
ከዚህ ቀደም እንዳልኩት ፥ ስነ-ፅሑፍ ለፖለቲካ ጉዳይ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል። ስነ-ፅሁፍ ከሰው ለሰው በሰው ነው። ሰው ይፅፋል ፥ በሰው በኩል ለሰው ይቀርባል። በአንድም በሌላም ትኩረቱ ስለ ሰው ነው።
ፖለቲካ ደግሞ በእያንዳንዱ ሰው ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ ያሳደራል። ብንወድም ባንወድም በፖለቲካ ተፅዕኖ ስር ነን።
"ነገን ፍለጋ" በሚለው መፅሐፌ ያልኩትን እዚህ ልድገም። ፖለቲካ የማግባት ወይም ያለመግባባት ሁኔታችንን ይወስናል። እውነት መስሎ ባይታይም ፖለቲካ የዜጎችን ትዳር እስመወሰን ድረስ ጉልበት አለው።
"ፖለቲካ በሩቁ" ባዮች ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ መሆን አይችሉም። ሰው ፖለቲካን ይሸሽ ይሆናል። ፖለቲካ ግን ሰውን አይሸሽም። ስለዚህ ለፖለቲካ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል።
የዙፋን ልፊያ ልብወለድ ነው። ፖለቲካ የተርታ ሰዎች ህይወት ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ የሚያሳይ የልብወለድ...
በመፅሐፌ ከመንግሥት ወይም ከተቃዋሚዎች ጋር ቃላት መወራወር አልፈለግኩም። መንግስትም ሆነ ተቃዋሚዎች ትኩረቴ አይደሉም። ትኩረቴ ፖለቲካ ግለሰብ ህይወት ላይ ያለው ቀጥተኛ ተፅዕኖ ነው።
የዙፋን ልፊያ ሁነኛ ትከረቱ ቀጣይ ነጥቦች ናቸው
ፖለቲካ በተርታ ሰው ህይወት ላይ ያለው ተፅዕኖ ምንድነው?
ጦርነት እና የግለሰብ ህይወት ምን አገናኘው?
የፖለቲከኞች ግላዊ ባህሪ እና የዜጎች የእለት ተዕለት ህይወት እንዴት ይገናኛል?
ከላይ ያነሳኋቸው ጥያቄዎች "የዙፋን ልፊያ" መፅሐፌ ትኩረት ናቸው።
በተቻለኝ መጠን ከቀደመው ስራዬ የተሻለ ስራ ለማምጣት የሞከርኩ ይመስለኛል።
መፅሐፌ ገበያ ላይ ውሏል። ይህን በ2 ምክኒያቶች እንድታስተዋውቁ እፈልጋለሁ።
ምክንያት አንድ ፥ መፅሐፌ አልተመረቀም። የምርቃት ፕሮግራም ለማስታወቂያ ቀጥተኛ ጥቅም አለው። ለኔ ግን አልሆነልኝም። ስለዚህ የእናንተን ማስታወቂያ እፈልጋለሁ
ምክንያት ሁለት ፥ ፌስቡክ ሊገባኝ ባልቻለ ሰበብ ቀጥቶኛል። ተደራሽነቴ ላይ ገደብ አድርጓል። ስለዚህ ይህን ለማካካስ የናንተ ማስታወቂያ ያስፈገኛል።
ይህን ስለምታደርጉ አመሰግናለሁ
@Tfanos
❤5👏2👍1
በዚህ ምሽት ይህን መፃፌ ትክክል ይሆን? እንጃ!
ከምሽቱ 3 ተኩል አከባቢ ልብሴን እንድታጥብልኝ የሰጠኋት ሴትጋ ሄድኩ። ተቀብያት በመውጣት ፋንታ ቤቷ ገባሁ። አንዳንድ ጉዳዮችን አወራን።
ታሪኳን በአጭሩ።
ከጅማ ወደ አዲስ አበባ ከመጣች 11 አመት ሆኗታል። አዲሳባ የፍቅር ህይወት ጀመረች።
ግኑኝነት ከጀመረች በኋላ ፀነሰች። እርግዝና ተፈጠረ። ከእርግዝናው በኋላ በየኋህነት ተስፋ ያደረገችው የፍቅር ግኑኝነት አልቀጠለም። በአጭሩ ተቀጨ። ፅንስ ማቋረጥ ስላልፈለገች ልጅ ወለደች። ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ!
አራስ ሆና ጡቷ ወተት አልነበረውም። ምግብ ስለማትበላ ጡቷ ወተት ማምረት አልቻለም ነበር። ወልዳ ሳምንት ሳይሞላት የሰው ልብስ ለማጠብ ተገደደች። የሰው ልብስ አጥባ ገንዘብ ካላገኘች በረሃብ መሞቷ ስለሆነ ገና የሳምንት አራስ ሳለች የጉልበት ስራ ጀመረች። ጠያቂ የላትም። አልባሽ አጉራሽ የላትም። እሷ እና ልጇ ብቻ ናቸው።
መገናኛ አከባቢ በጠባብ የቆርቆሮ ቤት እየኖረች ጎመን ትሸጥ ነበር። ጎመንና መሰል ነገሮች መገናኛ ሰፈር ስትሸጥ ደንቦች አስቸገሯት። የምትሸጠውን ይበትኑባታል ፥ ይደበድቧታል ፥ ይነጥቋታል። መገናኛ ለሽያጭ አስቸጋሪ ሲሆንባት በአንፃራዊነት የተሻለ ሰፈር ፈለገች። ጎሮ ድረስ ሄዳ ሸጣ ሲመሽ ወደ መገናኛ ቤቷ ትመለሳለች።
ከእለታት በአንዱ አምሽታ ወደ ሰፈሯ ተመለሰች። ለመሸጥ የወሰደችው ንብረት አልተሸጠላትም። ልጇንና ያልተሸጠ ንብረቷን በጀርባ አዝላ ወደ ሰፈሯ ብትደርስ ቤቷ ፈርሷል። የቆርቆሮ ቤቷ ለልማት ፈርሷል....
ቤቷ ሲፈርስ የት አረፈች? ጎዳና! ልጇን ይዛ ጎዳና ወጣች!
አሁን ከልጇጋ የምትኖረው ተጀምሮ ባላለቀ ኮንዶሚኒየም ነው። ከጎዳና ወጥታ ባላለቀ እና አስተማማኝ ባልሆነ ኮንዶሚኒየም እየኖረች "ተመስገን" ትላለች። ልብስ ታጥባለች ፥ ፅዳት ትሰራለች። በምታገኘው ገንዘብ ልጇን ትመግባለች።
ልጇ 5 አመት ሞልቶታል። ነገ ልደቱ ነው።
ይህን መፃፍ ምንም ትርጉም ላይኖረው ይችላል። ከእናትና ልጅ የተለየሁት ከደቂቃዎች በፊት ነው። ስለነሱ እኔ አቅመቢስነት ተሰማኝ።
@Tfanos
ከምሽቱ 3 ተኩል አከባቢ ልብሴን እንድታጥብልኝ የሰጠኋት ሴትጋ ሄድኩ። ተቀብያት በመውጣት ፋንታ ቤቷ ገባሁ። አንዳንድ ጉዳዮችን አወራን።
ታሪኳን በአጭሩ።
ከጅማ ወደ አዲስ አበባ ከመጣች 11 አመት ሆኗታል። አዲሳባ የፍቅር ህይወት ጀመረች።
ግኑኝነት ከጀመረች በኋላ ፀነሰች። እርግዝና ተፈጠረ። ከእርግዝናው በኋላ በየኋህነት ተስፋ ያደረገችው የፍቅር ግኑኝነት አልቀጠለም። በአጭሩ ተቀጨ። ፅንስ ማቋረጥ ስላልፈለገች ልጅ ወለደች። ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ!
አራስ ሆና ጡቷ ወተት አልነበረውም። ምግብ ስለማትበላ ጡቷ ወተት ማምረት አልቻለም ነበር። ወልዳ ሳምንት ሳይሞላት የሰው ልብስ ለማጠብ ተገደደች። የሰው ልብስ አጥባ ገንዘብ ካላገኘች በረሃብ መሞቷ ስለሆነ ገና የሳምንት አራስ ሳለች የጉልበት ስራ ጀመረች። ጠያቂ የላትም። አልባሽ አጉራሽ የላትም። እሷ እና ልጇ ብቻ ናቸው።
መገናኛ አከባቢ በጠባብ የቆርቆሮ ቤት እየኖረች ጎመን ትሸጥ ነበር። ጎመንና መሰል ነገሮች መገናኛ ሰፈር ስትሸጥ ደንቦች አስቸገሯት። የምትሸጠውን ይበትኑባታል ፥ ይደበድቧታል ፥ ይነጥቋታል። መገናኛ ለሽያጭ አስቸጋሪ ሲሆንባት በአንፃራዊነት የተሻለ ሰፈር ፈለገች። ጎሮ ድረስ ሄዳ ሸጣ ሲመሽ ወደ መገናኛ ቤቷ ትመለሳለች።
ከእለታት በአንዱ አምሽታ ወደ ሰፈሯ ተመለሰች። ለመሸጥ የወሰደችው ንብረት አልተሸጠላትም። ልጇንና ያልተሸጠ ንብረቷን በጀርባ አዝላ ወደ ሰፈሯ ብትደርስ ቤቷ ፈርሷል። የቆርቆሮ ቤቷ ለልማት ፈርሷል....
ቤቷ ሲፈርስ የት አረፈች? ጎዳና! ልጇን ይዛ ጎዳና ወጣች!
አሁን ከልጇጋ የምትኖረው ተጀምሮ ባላለቀ ኮንዶሚኒየም ነው። ከጎዳና ወጥታ ባላለቀ እና አስተማማኝ ባልሆነ ኮንዶሚኒየም እየኖረች "ተመስገን" ትላለች። ልብስ ታጥባለች ፥ ፅዳት ትሰራለች። በምታገኘው ገንዘብ ልጇን ትመግባለች።
ልጇ 5 አመት ሞልቶታል። ነገ ልደቱ ነው።
ይህን መፃፍ ምንም ትርጉም ላይኖረው ይችላል። ከእናትና ልጅ የተለየሁት ከደቂቃዎች በፊት ነው። ስለነሱ እኔ አቅመቢስነት ተሰማኝ።
@Tfanos
😢22❤7
አጋን ንት በሰው ጭካኔ ተገርመው እጃቸውን በአፋቸው አኖሩ፡፡ ሰው ከሰ ይጣን ሊስተካከል ጥረት የሚያደርግ መሰለ፡፡ የሞት መልዓክ ፋታ አጣ፣ ዲ ያ ቢ ሎስ ስራ በዛበት፡፡
ሐገር ሞት የሚታጨድባት ማሳ ሆነች፡፡
መሽቶ ፀሐይ ወደ ዘወትር ማደሪያዋ ስትከተት የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ፡፡ ጨረቃ የጠለቀችውን ፀሐይ ለመተካት አልወደደችም፡፡
‹‹ጧ…ጧ… ጧ›› የተኩስ ድምፅ በየአቅጣጫው ተሰማ፡፡
ጥይት በየሰው ገላ ተሰነቀረ፣ ወጣቶች እየተገነደሱ ወደቁ፣ ቤቶች በእሳት ጋዩ፣ እንስሳት በየአቅጣጫው ተሯሯጡ፣ ወፎች የጥይት ሲሳይ ሆኑ፡፡፡
‹‹ጧ ጧ ጧ››
ውሾች ያላዝናሉ፣ ጅቦች ከጎሬያቸው የሚሻል መሸሸጊያ ፈለጉ፡፡ የሌሊት ወፎች ሐገር ጥለው ለመሰደድ መብረር ጀመሩ፡፡ ሐገር ተተራመሰ፡፡
መሽቶ ፀሐይ ስትጠልቅ ብሄራዊ ጨለማ ተፈጠረ
‹‹ብወልድህ አደርስሃለሁ፣ እናትህ ነኝ›
የተዳፈነ እሳት ከማጀት እየቆሰቆሱ ሳለ ብሄራዊ እሳት ነደደ፡፡ ከአምስት ዓስርት ዓመታት በፊት የሰሙትን ታላቁን መከራ ተጋፈጡት፡፡
‹‹መብራታዊያን ታላቁ መከራን የሚጋፈጡበት ዘመን ይመጣል፡፡ የደም ጎርፍ ወደ መብራት ሐይቅ ይፈሳል፣ የመብራት ጎዳናዎች በሬሳ ይሞላሉ፣ የመብራት ተራራ ግርማውን ያጣል›› ተብሎ ነበር፡፡
‹‹ልጄ አታዋርደኝ››
ፀጉራቸው በሽበት የተወረሰ ነው። በእድሜ የልጅ ልጃቸው የሚሆን ጎረምሳ እግር ስር ተደፍተው ይለምኑታል።
‹‹እባክህን ልጄ››
በደፈረሰ ዐይኑ ሲያፈጥባቸው የሚናገሩት ቸገራቸው፤ ልባቸው ራደ።
እድሜያቸው ምሕረት አላስገኘላቸውም፣ እናትነታቸው ከጭካኔ አላዳናቸውም፣ ልመናቸው ከጎረምሳ ጥፊ አልታደጋቸውም። በጠንካራ መዳፉ በጥፊ ሲመታቸው በጀርባቸው ወደቁ፡፡
ጊዜ አላጠፋም። ተስገብግቦ ቀሚሳቸውን ለመግለብ ታገለ፡፡
‹‹ልጄ እናትህ ነኝ። ፈጣሪን አታሳዝነው››
በእንባ የራሰ ፊታቸው ሌላ ጥፊ ተቀበለ።
‹‹ፈጣሪህን አትፈራም?››
ከዐይናቸው የሚፈሰው እንባ በጆሮ ግንዳቸው በኩል ወረደ፡፡ ለዓመታት ተከብረው በኖሩበት፣ ልጆቻቸውን ወልደው ባሳደጉበት፣ ያሳደጓቸውን በዳሩበት ፣ እንግዶች በተቀበሉበት መኖሪያ ቤታቸው የልጅ ልጃቸው እኩያ አጎደፋቸው።
የዘመናት ፀሎታቸው ሳይሰማ ቀረ፡፡ ‹‹ታላቁን መከራ ሳላየው ልሙት›› የሚል ፀሎት ነበራቸው፡፡ ያልተሰማ ፀሎት…
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 1
ሐገር ሞት የሚታጨድባት ማሳ ሆነች፡፡
መሽቶ ፀሐይ ወደ ዘወትር ማደሪያዋ ስትከተት የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ፡፡ ጨረቃ የጠለቀችውን ፀሐይ ለመተካት አልወደደችም፡፡
‹‹ጧ…ጧ… ጧ›› የተኩስ ድምፅ በየአቅጣጫው ተሰማ፡፡
ጥይት በየሰው ገላ ተሰነቀረ፣ ወጣቶች እየተገነደሱ ወደቁ፣ ቤቶች በእሳት ጋዩ፣ እንስሳት በየአቅጣጫው ተሯሯጡ፣ ወፎች የጥይት ሲሳይ ሆኑ፡፡፡
‹‹ጧ ጧ ጧ››
ውሾች ያላዝናሉ፣ ጅቦች ከጎሬያቸው የሚሻል መሸሸጊያ ፈለጉ፡፡ የሌሊት ወፎች ሐገር ጥለው ለመሰደድ መብረር ጀመሩ፡፡ ሐገር ተተራመሰ፡፡
መሽቶ ፀሐይ ስትጠልቅ ብሄራዊ ጨለማ ተፈጠረ
‹‹ብወልድህ አደርስሃለሁ፣ እናትህ ነኝ›
የተዳፈነ እሳት ከማጀት እየቆሰቆሱ ሳለ ብሄራዊ እሳት ነደደ፡፡ ከአምስት ዓስርት ዓመታት በፊት የሰሙትን ታላቁን መከራ ተጋፈጡት፡፡
‹‹መብራታዊያን ታላቁ መከራን የሚጋፈጡበት ዘመን ይመጣል፡፡ የደም ጎርፍ ወደ መብራት ሐይቅ ይፈሳል፣ የመብራት ጎዳናዎች በሬሳ ይሞላሉ፣ የመብራት ተራራ ግርማውን ያጣል›› ተብሎ ነበር፡፡
‹‹ልጄ አታዋርደኝ››
ፀጉራቸው በሽበት የተወረሰ ነው። በእድሜ የልጅ ልጃቸው የሚሆን ጎረምሳ እግር ስር ተደፍተው ይለምኑታል።
‹‹እባክህን ልጄ››
በደፈረሰ ዐይኑ ሲያፈጥባቸው የሚናገሩት ቸገራቸው፤ ልባቸው ራደ።
እድሜያቸው ምሕረት አላስገኘላቸውም፣ እናትነታቸው ከጭካኔ አላዳናቸውም፣ ልመናቸው ከጎረምሳ ጥፊ አልታደጋቸውም። በጠንካራ መዳፉ በጥፊ ሲመታቸው በጀርባቸው ወደቁ፡፡
ጊዜ አላጠፋም። ተስገብግቦ ቀሚሳቸውን ለመግለብ ታገለ፡፡
‹‹ልጄ እናትህ ነኝ። ፈጣሪን አታሳዝነው››
በእንባ የራሰ ፊታቸው ሌላ ጥፊ ተቀበለ።
‹‹ፈጣሪህን አትፈራም?››
ከዐይናቸው የሚፈሰው እንባ በጆሮ ግንዳቸው በኩል ወረደ፡፡ ለዓመታት ተከብረው በኖሩበት፣ ልጆቻቸውን ወልደው ባሳደጉበት፣ ያሳደጓቸውን በዳሩበት ፣ እንግዶች በተቀበሉበት መኖሪያ ቤታቸው የልጅ ልጃቸው እኩያ አጎደፋቸው።
የዘመናት ፀሎታቸው ሳይሰማ ቀረ፡፡ ‹‹ታላቁን መከራ ሳላየው ልሙት›› የሚል ፀሎት ነበራቸው፡፡ ያልተሰማ ፀሎት…
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 1
😢3
‹‹ዲ ቃ ላ፣ የሰይጣን ልጅ››
ጦርነቱ የተጀመረባትን የተረገመች ቀን እያሰበች የአብራኳን ክፋይ ትሰድበዋለች።
‹‹አታልቅስ!... ዲ ቃ ላ››
ጦርነቱ የጀመረ ምሽት ባሏ ተባራሪ ጥይት በላው። ለታሪኩ ማንም ግድ ባይሰጠውም ባሏ በእርስ በእርስ ጦርነቱ የሞተ የመጀመሪያው የሀገሪቱ ሲቪል ሆነ። አባቷ በወጣበት ሲቀር ወንድሟ አካሉ ጎደለ።
‹‹ዲ ቃ ላ››
ባሏ በሞተበት ምሽት፣ ወንድሟ አካሉ በጎደለበት ምሽት፣ አባቷ በወጣበት በቀረበት ምሽት እርሷ ለጥቃት ተላልፋ ተሰጠች። በወታደር ተደፈረች።
ደፋሪዋ ከማን ወገን እንደሆነ አታውቅም። ከጀነራሉ አሊያም ከፕሬዝዳንቱ ወገን ቢሆን ግድ አይሰጣትም፡፡ የምታውቀው በወታደር መደፈሯን ነው።
በሰደፍ ሲመታት ተዘለፍልፋ ወደቀች። የለበሰችውን ሰማያዊ ጂንስ ሱሪ ለመቅደድ ሲታገል ‹‹በሕግ አምላክ›› አለች።
የሐገሪቱ አድራጊ ፈጣሪ የሆኑ ሁለት ሹማምንት ከተጣሉ በኋላ ሕገ-አራዊት እንደሰፈነ ስላላወቀች ‹‹በሕግ አምላክ›› በማለት ራሷን ለመታደግ ፈለገች።
ከምንም ሳይቆጥራት ሱሪዋን ለማውለቅ ሲታገል ‹‹መለዮህን አታከብርም?›› አለችው።
ስለመለዮ ክብር እየሰማች ስላደገች የፈጣሪን ስም ጠርቶ ከመማፀን ይልቅ ለአንደበቷ የቀረበው መለዮ ነበር፡፡
ለጥያቄዋ ቡጢ መለሰላት። ሁሉም ነገር ብዥ አለባት… እይታዋ ተጋረደ… አፏ በደም ተሞላ.. አፍንጫዋ እንደ አንዳች ባዕድ ነገር ከበዳት… ከአፏ ውስጥ ጠጣር ነገር አገኘች… ጥርሷን ተፋችው፡፡
‹በሕግ አምላክ› የሚል ተማፅእኖ ለማሰማት ጉልበት አጣች፡፡ አቅም ከዳት፡፡
ቆንጆ ነበረች፡፡ በአጭር የምትቆረጠው ፀጉሯ ከክብ ፊቷ ጋር የውበት ኪዳን ፈፅመዋል፡፡ የጥቁር ቆዳዋ ልስላሴ ድህነቷን መሰወር ተችሎታል፡፡ ጥርሶቿ፣ የጥርስ ውበት ማነፃፀረሪያ ናቸው፡፡ የረጃጅም እጅ ጣቶችዋ ከፊል በረጃጅም ጥፍር ያጌጣሉ፡፡ ከቀኝ ጣቶችዋ የቀለበት ጣትዋን እና የትንሽ ጣትዋን ጥፍሮች ታሳድጋለች፡፡ ከግራ እጇ ጣቶች መካከል ከአውራ ጣቷ እና የመሃል ጣቷ በቀር የሦስቱ ጣቶችዋ ጥፍሮች ሁሌም እንዳደጉ ናቸው፡፡
ቆንጆ ነበረች፡፡ በአንድ ቦክስ ውበቷ ከዳት፡፡
‹‹በሕግ አምላክ›› ብላ እየለመነች ውበትዋን በተነጠቀች አፍታ ክብሯንም ተቀማች፡፡
‹‹መለዮህን አክብር›› የሚለው ማሳሰቢያዋ ረብ እንደሌለው ሲገባት አቅሟን አስተባብራ ልታጠቃው ፈለገች፡፡ በደህናው ጊዜ ለውበት ዓላማ ያሳደገቻቸውን ጥፍሮች የአደጋ ጊዜ መከላከያ ልታደርግ ሞከረች፡፡ በጥፍሮቿ ልታጠቃው ታገለች፡፡ ጉልበተኛውን በጥፍሯ ልትቧጭረው መሞከሩ ከጥፍር መሰበር ውጭ ምንም አልፈየደላትም፡፡
‹‹በሕግ አምላክ›› በተሸነፈ ድምፅ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጠችው፡፡
በጉልበት ተገናኛት፤ ተደፈረች። የመጀመሪያም የመጨረሻዋም ከሆነው ባሏ ውጭ ለመጀመሪያ ጊዜ ወንድ ገባባት፡፡
ማሕጸኗ ባዕድ ነገር የገባበት ይመስል አመማት። እላይዋ ላይ ተከምሮ የቆየበት ጥቂት ደቂቃ የዘላለም ያህል ረዘመባት።
‹‹በሕግ አምላክ›› እያለች መደፈሯ እንደ እግር እሳት ለበለባት፤ ‹መለዮ አክብር› የተባለ ወታደር የጀመረውን ክፋት ሁሉ እርግፍ አድርጎ እንደሚተው እየሰማች አድጋ ተቃራኒው ቢገጥማት ሃዘን ሰረሰራት፡፡
ከራሷ ተጣልታ ፣ የገዛ እሷነቷን ተፀይፋ መኖር ጀመረች።
‹‹ሁለት ባለሥልጣናት ለመንበር ሲሉ በመጣላታቸው የተነሳ የእኔ ማሕጸን ጦር ሜዳ ሆነ›› ትላለች ሆድ እየባሳት።
የወር አበባዋ እንደቀረ ያወቀች ሰሞን፣ ፅንስ የማቋረጥ ሃሳብ አልተፈጠረባትም ነበር።
የመጀመሪያውን ስድስት ወር ያሳለፈችው የተደፈረችበትን ቅፅበት በማሰብ እያለቀሰች ነው። ግማሽ ዓመት ያለ እረፍት አነባች።አዛኝ የለሽ ለቅሶ …
በሆዷ የተሸከመችው ፅንስ ስድስት ወር ሲሞላው በረገገች። ‹‹የጠላቴን ልጅ አልወልድም›› ብላ ወደ ሆስፒታል ሄደች።
‹‹ማስወረድ አትችይም›› አላት ዶክተሩ
‹‹ለምን ሲባል?››
‹‹ለሕይወትሽ አደገኛ ነው››
‹‹ይሁና››
‹‹ገብቶሻል? ልትሞቺ ትችያለሽ››
ልቧ በጦር የተወጋ መሰላት። ደነገጠች።
መሞት አትፈልግም። ሕይወቷ ባያጓጓትም አለመኖርን አትመኝም። መኖሯን የጠላች ሆና ሳለ መሻቷ በህይወት መቆየት ነው።
ደመ-ከልብ ሆኖ የቀረ ሟች ባሏ መታሰቢያ የሆነውን የበኩር ልጇን ትታ መሞት አትፈልግም።
ከ #የዙፋን_ልፊያ መጻሕፍ የተወሰደ
@Tfanos
ጦርነቱ የተጀመረባትን የተረገመች ቀን እያሰበች የአብራኳን ክፋይ ትሰድበዋለች።
‹‹አታልቅስ!... ዲ ቃ ላ››
ጦርነቱ የጀመረ ምሽት ባሏ ተባራሪ ጥይት በላው። ለታሪኩ ማንም ግድ ባይሰጠውም ባሏ በእርስ በእርስ ጦርነቱ የሞተ የመጀመሪያው የሀገሪቱ ሲቪል ሆነ። አባቷ በወጣበት ሲቀር ወንድሟ አካሉ ጎደለ።
‹‹ዲ ቃ ላ››
ባሏ በሞተበት ምሽት፣ ወንድሟ አካሉ በጎደለበት ምሽት፣ አባቷ በወጣበት በቀረበት ምሽት እርሷ ለጥቃት ተላልፋ ተሰጠች። በወታደር ተደፈረች።
ደፋሪዋ ከማን ወገን እንደሆነ አታውቅም። ከጀነራሉ አሊያም ከፕሬዝዳንቱ ወገን ቢሆን ግድ አይሰጣትም፡፡ የምታውቀው በወታደር መደፈሯን ነው።
በሰደፍ ሲመታት ተዘለፍልፋ ወደቀች። የለበሰችውን ሰማያዊ ጂንስ ሱሪ ለመቅደድ ሲታገል ‹‹በሕግ አምላክ›› አለች።
የሐገሪቱ አድራጊ ፈጣሪ የሆኑ ሁለት ሹማምንት ከተጣሉ በኋላ ሕገ-አራዊት እንደሰፈነ ስላላወቀች ‹‹በሕግ አምላክ›› በማለት ራሷን ለመታደግ ፈለገች።
ከምንም ሳይቆጥራት ሱሪዋን ለማውለቅ ሲታገል ‹‹መለዮህን አታከብርም?›› አለችው።
ስለመለዮ ክብር እየሰማች ስላደገች የፈጣሪን ስም ጠርቶ ከመማፀን ይልቅ ለአንደበቷ የቀረበው መለዮ ነበር፡፡
ለጥያቄዋ ቡጢ መለሰላት። ሁሉም ነገር ብዥ አለባት… እይታዋ ተጋረደ… አፏ በደም ተሞላ.. አፍንጫዋ እንደ አንዳች ባዕድ ነገር ከበዳት… ከአፏ ውስጥ ጠጣር ነገር አገኘች… ጥርሷን ተፋችው፡፡
‹በሕግ አምላክ› የሚል ተማፅእኖ ለማሰማት ጉልበት አጣች፡፡ አቅም ከዳት፡፡
ቆንጆ ነበረች፡፡ በአጭር የምትቆረጠው ፀጉሯ ከክብ ፊቷ ጋር የውበት ኪዳን ፈፅመዋል፡፡ የጥቁር ቆዳዋ ልስላሴ ድህነቷን መሰወር ተችሎታል፡፡ ጥርሶቿ፣ የጥርስ ውበት ማነፃፀረሪያ ናቸው፡፡ የረጃጅም እጅ ጣቶችዋ ከፊል በረጃጅም ጥፍር ያጌጣሉ፡፡ ከቀኝ ጣቶችዋ የቀለበት ጣትዋን እና የትንሽ ጣትዋን ጥፍሮች ታሳድጋለች፡፡ ከግራ እጇ ጣቶች መካከል ከአውራ ጣቷ እና የመሃል ጣቷ በቀር የሦስቱ ጣቶችዋ ጥፍሮች ሁሌም እንዳደጉ ናቸው፡፡
ቆንጆ ነበረች፡፡ በአንድ ቦክስ ውበቷ ከዳት፡፡
‹‹በሕግ አምላክ›› ብላ እየለመነች ውበትዋን በተነጠቀች አፍታ ክብሯንም ተቀማች፡፡
‹‹መለዮህን አክብር›› የሚለው ማሳሰቢያዋ ረብ እንደሌለው ሲገባት አቅሟን አስተባብራ ልታጠቃው ፈለገች፡፡ በደህናው ጊዜ ለውበት ዓላማ ያሳደገቻቸውን ጥፍሮች የአደጋ ጊዜ መከላከያ ልታደርግ ሞከረች፡፡ በጥፍሮቿ ልታጠቃው ታገለች፡፡ ጉልበተኛውን በጥፍሯ ልትቧጭረው መሞከሩ ከጥፍር መሰበር ውጭ ምንም አልፈየደላትም፡፡
‹‹በሕግ አምላክ›› በተሸነፈ ድምፅ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጠችው፡፡
በጉልበት ተገናኛት፤ ተደፈረች። የመጀመሪያም የመጨረሻዋም ከሆነው ባሏ ውጭ ለመጀመሪያ ጊዜ ወንድ ገባባት፡፡
ማሕጸኗ ባዕድ ነገር የገባበት ይመስል አመማት። እላይዋ ላይ ተከምሮ የቆየበት ጥቂት ደቂቃ የዘላለም ያህል ረዘመባት።
‹‹በሕግ አምላክ›› እያለች መደፈሯ እንደ እግር እሳት ለበለባት፤ ‹መለዮ አክብር› የተባለ ወታደር የጀመረውን ክፋት ሁሉ እርግፍ አድርጎ እንደሚተው እየሰማች አድጋ ተቃራኒው ቢገጥማት ሃዘን ሰረሰራት፡፡
ከራሷ ተጣልታ ፣ የገዛ እሷነቷን ተፀይፋ መኖር ጀመረች።
‹‹ሁለት ባለሥልጣናት ለመንበር ሲሉ በመጣላታቸው የተነሳ የእኔ ማሕጸን ጦር ሜዳ ሆነ›› ትላለች ሆድ እየባሳት።
የወር አበባዋ እንደቀረ ያወቀች ሰሞን፣ ፅንስ የማቋረጥ ሃሳብ አልተፈጠረባትም ነበር።
የመጀመሪያውን ስድስት ወር ያሳለፈችው የተደፈረችበትን ቅፅበት በማሰብ እያለቀሰች ነው። ግማሽ ዓመት ያለ እረፍት አነባች።አዛኝ የለሽ ለቅሶ …
በሆዷ የተሸከመችው ፅንስ ስድስት ወር ሲሞላው በረገገች። ‹‹የጠላቴን ልጅ አልወልድም›› ብላ ወደ ሆስፒታል ሄደች።
‹‹ማስወረድ አትችይም›› አላት ዶክተሩ
‹‹ለምን ሲባል?››
‹‹ለሕይወትሽ አደገኛ ነው››
‹‹ይሁና››
‹‹ገብቶሻል? ልትሞቺ ትችያለሽ››
ልቧ በጦር የተወጋ መሰላት። ደነገጠች።
መሞት አትፈልግም። ሕይወቷ ባያጓጓትም አለመኖርን አትመኝም። መኖሯን የጠላች ሆና ሳለ መሻቷ በህይወት መቆየት ነው።
ደመ-ከልብ ሆኖ የቀረ ሟች ባሏ መታሰቢያ የሆነውን የበኩር ልጇን ትታ መሞት አትፈልግም።
ከ #የዙፋን_ልፊያ መጻሕፍ የተወሰደ
@Tfanos
🔥5
ስለዙፋን ልፊያ የመጀመሪያ የአንባቢ አስተያየት
(አስተያየት ሰጭ ፥ የስነልቦና ባለሞያ በሀሴት የማማከር አገልግሎት አማካሪ ረድኤት ዳዲ)
ከረጅም ጊዜ በኋላ ልብ ወለድ መፅሀፍ አነበብኩ።
አሹ ደግ አረኩ ብያለሁ!
ገና የመጀመሪያዋቹን ገፅ ማንብብ እንደጀመርኩ ነው ሳላስበው ብዙ ደቂቃዋች ያለፉት።
በመፅሀፉ ላይ ያሉት አብዛኞቹ ታሪኮች ልብ ወለድ ከመሆናቸው በላይ በተላያየ ጊዜ በማማክርበት ወቅት ቢሮዬን ያንኳኩ፤ ዕንባዬን ከዓይኔ ያፈሰሱ ታሪኮች ጋር የተዛመዱ ታሪኮቸ መሆናቸው ተስፋኣብ ተሾመ ፀሀፊ ብቻ ሳይሆን ጥሩ የስነልቦና ባለሙያ ሊሆን እንደሚችል የታዘብኩበት ነው።
የተለያዩ የግለሰቦች ታሪክ እና ስሜትን በጥልቀት የሚተርክ፤ የተለያዩ ስነልቦናዊ ጉዳዮችን በይበልጥ እንድናስተውል በተለይም “The child is a father of the man” የሚለውን ትልቅ ስነልቦና ሀሳብ በእያንዳንዱ በዙፋን ልፊያ ታሪኮች ውስጥ የሚያስኮመኩም ነው።
ራሳችንን እና ልባዊ መሻቶችን ከልጅነት ታሪካችን ጋር ያለውን ዝምድና እንድንመረምር ፍንጭ የሚሰጥ ነው።
የግለሰቦች ፀብም የህዝብን ዕጣ ፈንታ እንደሚወስን አስተውዬበታለሁ።
ሁላችሁም እየገዛችሁ አንብቡት ታተርፋበታላችሁ።
ተስፍሽ እጆችክ ከፅሁፍ አይንጠፋ ብያለሁ🙌
@Tfanos
(አስተያየት ሰጭ ፥ የስነልቦና ባለሞያ በሀሴት የማማከር አገልግሎት አማካሪ ረድኤት ዳዲ)
ከረጅም ጊዜ በኋላ ልብ ወለድ መፅሀፍ አነበብኩ።
አሹ ደግ አረኩ ብያለሁ!
ገና የመጀመሪያዋቹን ገፅ ማንብብ እንደጀመርኩ ነው ሳላስበው ብዙ ደቂቃዋች ያለፉት።
በመፅሀፉ ላይ ያሉት አብዛኞቹ ታሪኮች ልብ ወለድ ከመሆናቸው በላይ በተላያየ ጊዜ በማማክርበት ወቅት ቢሮዬን ያንኳኩ፤ ዕንባዬን ከዓይኔ ያፈሰሱ ታሪኮች ጋር የተዛመዱ ታሪኮቸ መሆናቸው ተስፋኣብ ተሾመ ፀሀፊ ብቻ ሳይሆን ጥሩ የስነልቦና ባለሙያ ሊሆን እንደሚችል የታዘብኩበት ነው።
የተለያዩ የግለሰቦች ታሪክ እና ስሜትን በጥልቀት የሚተርክ፤ የተለያዩ ስነልቦናዊ ጉዳዮችን በይበልጥ እንድናስተውል በተለይም “The child is a father of the man” የሚለውን ትልቅ ስነልቦና ሀሳብ በእያንዳንዱ በዙፋን ልፊያ ታሪኮች ውስጥ የሚያስኮመኩም ነው።
ራሳችንን እና ልባዊ መሻቶችን ከልጅነት ታሪካችን ጋር ያለውን ዝምድና እንድንመረምር ፍንጭ የሚሰጥ ነው።
የግለሰቦች ፀብም የህዝብን ዕጣ ፈንታ እንደሚወስን አስተውዬበታለሁ።
ሁላችሁም እየገዛችሁ አንብቡት ታተርፋበታላችሁ።
ተስፍሽ እጆችክ ከፅሁፍ አይንጠፋ ብያለሁ🙌
@Tfanos
🔥10
"ሁላችንም ራሳችንን ማሰልጠን አለብን! ሳይቋሰሉ መለያየትን ራሳችንን ማሰልጠን አለብን! ሳይጎዳዱ ግኑኝነታትን ማቋረጥን ራሳችንን ማሰልጠን አለብን! እንደ አ ው ሬ ሳይነካከሱ መሰነባበትን ራሳችንን ማሰልጠን አለብን!"
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 163
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 163
👍6🔥4❤1
ባለሥልጣናቱ በአንደበታቸው ቃል ይዋጋሉ። ወታደሮች በጠመንጃ ይጠዛጠዛሉ። የሀብታሞችን ጦርነት ድሆች ይዋጋሉ። የሹማምንት ልፍያ የተርታ ዜጎች ፍልሚያ ነው።
ፀሐይ ወደ ዘወትር ማደሪያዋ ስትከተት የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ። ጨረቃ የጠለቀችውን ፀሐይ ልትተካ አልወደደችም። ሰማዩ ፅልመት ሲለብስ ሰይፍ ከሰገባ ተመዘዘ።
መልዓከ-ሞት ስራ በዛበት።
አንገቶች እየተቀሉ ወደቁ፣ አንጎሎች ተበረቀሱ፣ እልፍ ደረቶች የጥይት ናዳ ወረደባቸው፣ እጆች ተቀነጠሱ፣ እግሮች ተቆርጠው ሜዳ ላይ ወደቁ።
ለወራት ዝናብ ጠምቶት የነበረ ደረቅ መሬት በሰው ደም ራሰ፣በረሃው በደም ጨቀየ።
ጦርነቱ በጀመረ የሰዓታት ውስጥ እድሜ አ ጋ ን ን ት ተፈትተው የተለቀቁ መሰለ፣ ተቆጥሮ የማያልቅ ነውር ተፈፀመ፣ ባልተገራ ሰውነት ውስጥ ተሸሽጎ የከረመ ሰ ይ ጣ ን ተገለጠ።
ከመምሸቱ በፊት እንዲህ አልነበረም።
ፀሐይ ስትጠልቅ የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ። ሰዎች ወደ አ ው ሬ ነ ት ተለወጡ፣ አ ጋ ን ን ት አካል ለብሰው ተንቀሳቀሱ፣ ወሲብን አጣጥመው የማያውቁ ወጣቶች ከእናቶቻቸው በእድሜ የሚበልጡ ሴቶችን በማስገደድ ተገናኙ፣ ወንዶች በወንዶች ተደፈሩ፣ ወጣት ሴቶች ወደ ማሕጸቸው ብረት ገባ።
አስገድዶ በመድፈር ብቻ በውስጣቸው ያለውን አውሬ ማርካት ያልቻሉ፣ በደፈሯቸው ሴቶች ብልት ላይ ጥይት አርከፈከፉ።
ሐገሪቱ እንዲህ አልነበረችም።
ፀሐይ ከመጥለቋ የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ።
አብሮ በኖረ፣ ክፉና ደጉን በጋራ ባሳለፈ፣ ከዘመድ ይልቅ ቅርብ በተባለ ጎረቤት መዘረፍ የማያስደነግጥ ሆነ። ብዙ ዜጎች በአንዲት ምሽት ገሀነም ምን እንደሚመስል አወቁ።
‹‹አንድ ጥይት ይበቃኛል፣ በአንዲት ጥይት ብቻ ገላግሉኝ›› ይላሉ ሞት የራባቸው ወጣቶች።
ተስፋ ነበራቸው። ብዙ የመኖር፣ ወላጆቻቸውን የመጦር፣ ልጆቻቸውን ለወግ ማዕረግ የማብቃት ፣ ታናናሾቻቸውን የመርዳት ፣ ታላላቆቻቸውን የማኩራት... ተስፋ ነበራቸው። ተስፋቸውን ፖለቲካ በላው።
ጥይት ያጎደለው አካላቸው ስቃይ ፈጥሮባቸዋል። የውሃ ጥማቱን፣ የቁስሉን ጥዝጣዜ መቋቋም ሲያቅታቸው ሕይወታቸውን ንቀው ሞትን ናፈቁ።
በየአቅጣጫው የተበተነውን ጦረኛ ‹ግ ደ ሉን › ይላሉ። ሞትን ይለምናሉ።
‹‹ጠብታ ውሃ ይበቃናል››
‹‹በአንዲት ጥይት አሰናብቱኝ››
‹‹እማዬ ነደድኩልሽ››
‹‹ልጄ ናፈቀኝ››
‹‹ሚስቴን ሳልሰናበት››
የሰቆቃ ድምፆች በየአቅጣጫው ይሰማሉ።
ከመምሸቱ በፊት ቀኑ ከሌላው ቀን የሚለይ አይመስልም ነበር።
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 11
@Tfanos
ፀሐይ ወደ ዘወትር ማደሪያዋ ስትከተት የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ። ጨረቃ የጠለቀችውን ፀሐይ ልትተካ አልወደደችም። ሰማዩ ፅልመት ሲለብስ ሰይፍ ከሰገባ ተመዘዘ።
መልዓከ-ሞት ስራ በዛበት።
አንገቶች እየተቀሉ ወደቁ፣ አንጎሎች ተበረቀሱ፣ እልፍ ደረቶች የጥይት ናዳ ወረደባቸው፣ እጆች ተቀነጠሱ፣ እግሮች ተቆርጠው ሜዳ ላይ ወደቁ።
ለወራት ዝናብ ጠምቶት የነበረ ደረቅ መሬት በሰው ደም ራሰ፣በረሃው በደም ጨቀየ።
ጦርነቱ በጀመረ የሰዓታት ውስጥ እድሜ አ ጋ ን ን ት ተፈትተው የተለቀቁ መሰለ፣ ተቆጥሮ የማያልቅ ነውር ተፈፀመ፣ ባልተገራ ሰውነት ውስጥ ተሸሽጎ የከረመ ሰ ይ ጣ ን ተገለጠ።
ከመምሸቱ በፊት እንዲህ አልነበረም።
ፀሐይ ስትጠልቅ የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ። ሰዎች ወደ አ ው ሬ ነ ት ተለወጡ፣ አ ጋ ን ን ት አካል ለብሰው ተንቀሳቀሱ፣ ወሲብን አጣጥመው የማያውቁ ወጣቶች ከእናቶቻቸው በእድሜ የሚበልጡ ሴቶችን በማስገደድ ተገናኙ፣ ወንዶች በወንዶች ተደፈሩ፣ ወጣት ሴቶች ወደ ማሕጸቸው ብረት ገባ።
አስገድዶ በመድፈር ብቻ በውስጣቸው ያለውን አውሬ ማርካት ያልቻሉ፣ በደፈሯቸው ሴቶች ብልት ላይ ጥይት አርከፈከፉ።
ሐገሪቱ እንዲህ አልነበረችም።
ፀሐይ ከመጥለቋ የሐገሪቱ ጨለማ ጀመረ።
አብሮ በኖረ፣ ክፉና ደጉን በጋራ ባሳለፈ፣ ከዘመድ ይልቅ ቅርብ በተባለ ጎረቤት መዘረፍ የማያስደነግጥ ሆነ። ብዙ ዜጎች በአንዲት ምሽት ገሀነም ምን እንደሚመስል አወቁ።
‹‹አንድ ጥይት ይበቃኛል፣ በአንዲት ጥይት ብቻ ገላግሉኝ›› ይላሉ ሞት የራባቸው ወጣቶች።
ተስፋ ነበራቸው። ብዙ የመኖር፣ ወላጆቻቸውን የመጦር፣ ልጆቻቸውን ለወግ ማዕረግ የማብቃት ፣ ታናናሾቻቸውን የመርዳት ፣ ታላላቆቻቸውን የማኩራት... ተስፋ ነበራቸው። ተስፋቸውን ፖለቲካ በላው።
ጥይት ያጎደለው አካላቸው ስቃይ ፈጥሮባቸዋል። የውሃ ጥማቱን፣ የቁስሉን ጥዝጣዜ መቋቋም ሲያቅታቸው ሕይወታቸውን ንቀው ሞትን ናፈቁ።
በየአቅጣጫው የተበተነውን ጦረኛ ‹ግ ደ ሉን › ይላሉ። ሞትን ይለምናሉ።
‹‹ጠብታ ውሃ ይበቃናል››
‹‹በአንዲት ጥይት አሰናብቱኝ››
‹‹እማዬ ነደድኩልሽ››
‹‹ልጄ ናፈቀኝ››
‹‹ሚስቴን ሳልሰናበት››
የሰቆቃ ድምፆች በየአቅጣጫው ይሰማሉ።
ከመምሸቱ በፊት ቀኑ ከሌላው ቀን የሚለይ አይመስልም ነበር።
#የዙፋን_ልፊያ ገፅ 11
@Tfanos
❤3
የምስር ወጥ እንቁጣጣሽ...
ቂጣ በጎመን አልወድም። ከምግቦች ሁሉ በቁጥር አንድ የምጠላው ሳይሆን አይቀርም። (በእርግጥ ቁጥር አንድ የሚለው ግነት ነው😀)
"97 አመተ ምህረት ሲባል ከምርጫ 97 ቀድሞ ቂጣ በጎመን ትዝ ይለኛል" ብዬ ብናገር ጥቂት ግነት ያለው ሐቅ ነው። ያኔ ብዙውን ጊዜ ቂጣ በጎመን ነበር የምንበላው። ቁርስ ቂጣ በጎመን ፥ ምሳ ቂጣ በጎመን ፥ ራት ቂጣ በጎመን።
በእርግጥ አልፎ አልፎ ለውጥ አለ። ፎቼ ፥ ድንች ፥ ቦሎቄ ፥ ሩዝ ...
ከድንች በቀር የያኔው ምግባችን ያስጠላኛል።
97 አ.ም የ 3ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ። ትምህርት ቤት ሆኜ ስለምሳ አስቤ እበሳጫለሁ። ቤት ውስጥ እንጀራ እንደማይኖር እርግጠኛ ስለምሆን እናደዳለሁ። ቂጣ ወይ ቦሎቄ አሊያም ሩዝ እንደምበላ ሳስብ እበሽቅ ነበር።
አመቱ አልቆ አዲስ አመት መጣ። 98 አ.ም ሆነ። "የጎመን ድስት ውጣ ፥ የገንፎ ድስት ግባ" ተባለ። ለአንድ ቀን የጎመን ድስት ወጣልንና የምስር ወጥ ድስት ገባልን።
98 አ.ም እንቁጣጣሽን በምስር ወጥ አከበርን። በጣም ደስ አለኝ።
ፀልዬ ነበር። "ጌታ ሆይ ለአመት በአሉ አስበን" ብዬ ፀልዬ ነበር። ለቁርስ ምስር ወጥ ሲቀርብ "ፀሎቴ ተመለሰ" አልኩ። ፀሎቴን ለእናቴ ነገርኳት። ስስ ቅሬታ አየሁባት።
አውዳመትን በምስር ወጥ ያከበርንባቸው ሌሎች አጋጣሚዎች አሉ። በስጋም ፥ በዶሮም አክብረን እናውቃለን። ግን የ98 አ.ም እንቁጣጣሽ አይረሳኝም። ምስር ወጥ ስለበላሁ ደስ የተሰኘሁበት እንቁጣጣሽ ነበር።
ለአውዳመት ስሜቴ ምውት ነው። አያጓጓኝም ፥ አያስደስተኝም ፥ አያስከፋኝም። አንዳንዴ ግን ለአውዳመት ምስር ወጥ ብርቅ የሚሆንባቸውን ማሰብ ያምረኛል።
የዛሬ 20 አመቱን የቤታችንን እንቁጣጣሽ አስታውሼ ፈገግ ባልኩበት አፍታ ፥ በአሉን በረሃብ የሚያሳልፉ ኢትዮጵያን ትውስ ይሉኛል
@Tfanos
ቂጣ በጎመን አልወድም። ከምግቦች ሁሉ በቁጥር አንድ የምጠላው ሳይሆን አይቀርም። (በእርግጥ ቁጥር አንድ የሚለው ግነት ነው😀)
"97 አመተ ምህረት ሲባል ከምርጫ 97 ቀድሞ ቂጣ በጎመን ትዝ ይለኛል" ብዬ ብናገር ጥቂት ግነት ያለው ሐቅ ነው። ያኔ ብዙውን ጊዜ ቂጣ በጎመን ነበር የምንበላው። ቁርስ ቂጣ በጎመን ፥ ምሳ ቂጣ በጎመን ፥ ራት ቂጣ በጎመን።
በእርግጥ አልፎ አልፎ ለውጥ አለ። ፎቼ ፥ ድንች ፥ ቦሎቄ ፥ ሩዝ ...
ከድንች በቀር የያኔው ምግባችን ያስጠላኛል።
97 አ.ም የ 3ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ። ትምህርት ቤት ሆኜ ስለምሳ አስቤ እበሳጫለሁ። ቤት ውስጥ እንጀራ እንደማይኖር እርግጠኛ ስለምሆን እናደዳለሁ። ቂጣ ወይ ቦሎቄ አሊያም ሩዝ እንደምበላ ሳስብ እበሽቅ ነበር።
አመቱ አልቆ አዲስ አመት መጣ። 98 አ.ም ሆነ። "የጎመን ድስት ውጣ ፥ የገንፎ ድስት ግባ" ተባለ። ለአንድ ቀን የጎመን ድስት ወጣልንና የምስር ወጥ ድስት ገባልን።
98 አ.ም እንቁጣጣሽን በምስር ወጥ አከበርን። በጣም ደስ አለኝ።
ፀልዬ ነበር። "ጌታ ሆይ ለአመት በአሉ አስበን" ብዬ ፀልዬ ነበር። ለቁርስ ምስር ወጥ ሲቀርብ "ፀሎቴ ተመለሰ" አልኩ። ፀሎቴን ለእናቴ ነገርኳት። ስስ ቅሬታ አየሁባት።
አውዳመትን በምስር ወጥ ያከበርንባቸው ሌሎች አጋጣሚዎች አሉ። በስጋም ፥ በዶሮም አክብረን እናውቃለን። ግን የ98 አ.ም እንቁጣጣሽ አይረሳኝም። ምስር ወጥ ስለበላሁ ደስ የተሰኘሁበት እንቁጣጣሽ ነበር።
ለአውዳመት ስሜቴ ምውት ነው። አያጓጓኝም ፥ አያስደስተኝም ፥ አያስከፋኝም። አንዳንዴ ግን ለአውዳመት ምስር ወጥ ብርቅ የሚሆንባቸውን ማሰብ ያምረኛል።
የዛሬ 20 አመቱን የቤታችንን እንቁጣጣሽ አስታውሼ ፈገግ ባልኩበት አፍታ ፥ በአሉን በረሃብ የሚያሳልፉ ኢትዮጵያን ትውስ ይሉኛል
@Tfanos
❤6
አሮጌ እንቁጣጣሽ
* * *
መሶቡ ታጥሮበት ፥ የአገር ልጅ ተርቦ
ዘመን ላይሰረይ ፥ ህይወት ጭዳ ቀርቦ
ለቆሸሸ መንፈስ
ለአሮጌ እንቁጣጣሽ ፥ ቄጤማ ጎዝጉዘን
እንዳምና ካቻምነው ፥ ሬ ሳ ላይ ቆመን
በአረጀ እንቁጣጣሽ...
ግፍ የታተመበት ፥ የማያልፍ ዘመን
አለፈ እንላለን ፥ ህይወት እያሳለፍን
(በድሉ ዋቅጅራ ፥ የወይራ ስር ፀሎት ገፅ 80)
@Tfanos
* * *
መሶቡ ታጥሮበት ፥ የአገር ልጅ ተርቦ
ዘመን ላይሰረይ ፥ ህይወት ጭዳ ቀርቦ
ለቆሸሸ መንፈስ
ለአሮጌ እንቁጣጣሽ ፥ ቄጤማ ጎዝጉዘን
እንዳምና ካቻምነው ፥ ሬ ሳ ላይ ቆመን
በአረጀ እንቁጣጣሽ...
ግፍ የታተመበት ፥ የማያልፍ ዘመን
አለፈ እንላለን ፥ ህይወት እያሳለፍን
(በድሉ ዋቅጅራ ፥ የወይራ ስር ፀሎት ገፅ 80)
@Tfanos
❤4
ዳሰሳ በፍልስፍና መምህር ዮናስ ታደሰ
የተስፋአብ ተሾመ ተስፋኣብ ተሾመ <<የዙፋን ልፊያ>> መፅሐፍን አነበብኩት። ወደድኩትም።
ዋና ገፀ ባህሪውን ሰው ሳይሆን "መብራት" የምትባል በአንዲት "ምናባዊት አገር"😁 ውስጥ የምትገኝ ምናባዊት ከተማ ያደረገ ልብ ወለድ መፅሐፍ ነው። መፅሐፉን ስናነብ በዋናነት የሰው ገፀ ባህሪ የውጣ ውረድ ሰንሰለትን እየተከተልን ሳይሆን ግኡዝ በሆነ የከተማ ዋና ገፀባህሪነት ውስጥ ባሉ የተለያዩ ገፀ ባህርያት (በዋናነት መብራታውያን) ውጣ ውረዶች ሰንሰለት ተከትለን ነው። ምናልባት አንባቢ ይሄ እስኪገለጥለት ድረስ፤ የተለያየ አይነት እርስ በርሱ የሚገናኝ የማይመስል የገፀ ባህርያት ግለ ታሪክ ሲያነብብ፣ "ይሄ ነገር የአጫጭር ልብ ወለዶች ጥርቅም ሊሆን ነው እንዴ?" ብሎ ግር ሊሰኝ ይችላል። ግዴለም ንባቦትን ይቀጥሉ ይገለጥሎታል። ደራሲው በመጀመሪያው የረዥም ልብ ወለድ ድርስት ስራው እንዲህ አይነቱን ነገር መሞከሩ በራሱ የሚደነቅ ነው።
በእርግጥ የልብ ወለዱ ዘውግ ነገሮችን በአሪስቶትል ቋንቋ፣ ሊሆኑ ይችሉ በነበሩበት (as it might be) ወይም ሊሆኑ በሚገባቸው (as it ought to be) ሳይሆን፤ በስብሐት ገብረ እግዚአብሔር አገላለፅ ታሪኩ የልብ ወለድ ድርሰት ቅርፅ ለማስያዝ እንዲረዳ ብቻ የታሪኩ ፍሰትን በተወሰነ ምናባዊ ቅርፅ አስተካክሎ ነገሮችን በሆኑበት ልክ (as it is) ሊተርክ የሚሞክር የ naturalist school አፃፃፍ የተከተለ ነው። በግሌ የዚህ ዓይነቱ መንገድ አድናቂ ባልሆንም በጭብጣቸው (theme) ምክንያት ልክ እንደ የስብሐት "ትኩሳት" እና "ሌቱም አይነጋልኝ"፣ እንደ የበአሉ ግርማ "ኦሮማይ" አይነቶች አንብቤ የምወዳቸው አሉ—የተስፋአብ የዙፋን ልፊያም ይዞት ከተነሳው ጭብጥ አንፃር ወድጄዋለሁ።
በእንደዚህ አይነት የድርሰት ዘውግ ውስጥ በብዙ የአማርኛ ድርሰቶች ላይ የማስተውለውን ምንም አስፈላጊነት በሌለው ቦታ ላይ፣ "መፃፍ እችላለሁኮ" ለማለት የሚመስል ግን ታኝከው የተተፉ፣ "ሰማዩ ጠቁሮ ነበር"፣ "ጭጋጉ እንዲህ መስሎ ነበር"፣ "አውሎ ነፋሱ እንዲያ ሲሆን ነበር"... በሚል የሚጀምሩ አሰልቺ ማጀቢያ ገለፃዎችን ሳይጠቀም፤ አሁን አሁን ደግሞ እድሜ ለድህረ-ዘመናዊነት ንቃተ-ህሊና ያመጣልህን፣ ትርጉም ይስጥ አይስጥ ሳትጨነቅ፣ የአንባቢ አእምሮ ሰብስቦ ለመያዝ የሚቸገርባቸው የቃላት ሰላጣ መአት የማፍሰስ እና የመፍሰስ አባዜ ሳይጠናወተው፤ ደራሲው ነገሮችን በተመጠኑ እና በተዋቡ ቃላት፣ የነገሮችን ሁኔታ በማያሻማ መልኩ ጥርት ባለ ቋንቋ ከሽኖ የሚገልፅበት ድርሰት ሆኖ አጊኝቼዋለሁ—የዙፋን ልፊያ።
አንዳንድ ሰዎች፣ "የዙፋን ልፊያ የእርስ በርስ ጦርነት ያለውን አስከፊ ገፅታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ድርሰት ነው" ብለው ሲገልፁት ተመልክቼአለሁ። ትክክል ነው፣እውነት አላቸው። ከዚያም ባሻገር ግን በስፋት ባይሄድበትም የእርስ በርስ ጦርነት አስከፊ ገፅታ ምንጭን የሚጠቁምበት—ማህበረሰባዊ የስነ-ምግባር ልሽቀትና ከዚህ የተነሳም የምሑራዊ ሐቀኝነት መጥፋት—ሐሳብም ቋጥሮአል። ለምሳሌ ንፁህ የምትባል ገፀ ባህሪ የታዘበችውን እንመልከት:-
<<ጦርነት አስጀማሪ ፊሽካ ከተነፋ በኋላ የሰውን ክፋት ልክ አየች። የሀገሪቱ ዜጎች እርስ በርስ ሲጠላሉ ኖረው ለመጠፋፋት አጋጣሚ እየጠበቁ እንደቆዩ አመነች። ጦርነቱ በጀመረ ማግስት ያደፈጠ ክፋት ተገለጠ፣ የተሰወረ ነውር ለአደባባይ ዋለ። "ክፉዎች ነበርን" ትላለች የሆነው ሁሉ እየደነቃት። "ክፉዎች ነበርን። የክፋታችንን ጥልቀት ጦርነት ገለጠው። የእርስ በርሱ ጦርነት ገመናችንን አደባባይ ላይ አዋለው" ትላለች ለራሷ።>> (ገፅ 142-143 አፅንኦት የራሴ)
በሌላ በኩል ደግሞ፣ "ፖለቲካና ኮረንቲ በሩቁ" የሚለው የተለመደ ብሂል የሚያዋጣ አይደለም ብሎ ሊገዳደር የሚሞክርም ነው:-
<<ምሁራን እውቀታቸው አላዳናቸውም። ፖለቲካ ምን እንደሆነ የማያውቁት በፖለቲካ እሳት አለመቃጠል አልሆነላቸውም።...>> (ገፅ 15 አፅንኦት የራሴ)
በዙፋን ልፊያ ከወደድኳቸው ነገሮች ውስጥ ከመፅሐፉ ርእስ ጀምሮ አርእስት አመራረጥና የገፀ ባህርያቱ (የአብዛኞቹ) ስሞች ከታሪክ ፍሰቱ ጋር የተሰናሰሉ መሆናቸውን ነው። ምናልባት መፅሐፉ ገና እየተነበበ ስለሆነ spoiler እንዳይሆንብኝ እንጂ፤ ለምሳሌ፣ <<የዙፋን ልፊያ>> የሚለው የመፅሐፉ አርእስት ራሱ ምን ለማለት እንደተፈለገ እንዲሁ በቀላሉ የሚጠቁመን ገላጭ አርእስት ቢመስለንም ቅሉ፤ ከገፀ ባህሪ ስምና ባህርያት ጋር ተሰናስሎ የተሸከመውን ያልጠበቅነውን ቅኔአዊ ትርጓሜ መጨረሻ ላይ ሲገለጥልን ደሞ፣ "አሃ!" ብለን መገረማችንና ደራሲውን ማድነቃችን አይቀርም። "ጉልበትና ጉድለት"፣ "መፍረስና መፍረስ" የሚሉ አርእስቶች፤ "ህይወትና ህይወት"—ሁለቱ ህይወቶች፣ "ንፁህ"፣ "ዙፋን" የሚሉ የገፀ ባህርያት ስሞች ምፀት እና ቅኔ ያዘሉ ሐሳቦችን ያረገዙ ሆነው ስናገኛቸው ደግሞ ሌላ አድናቆት ያጭርብናል።
በመጨረሻም በ"የዙፋን ልፊያ" ላይ ያለኝ ቅሬታ የነገሮችን ሁኔታ በቃላት ትረካ (ወደ መስበክ የሚያጋድል) ለመግለፅ ከሚሞክረው naturalist የአፃፃፍ ስታይል ይልቅ፤ የነገሮችን ሁኔታ በተግባራት የመንስኤና ውጤት ሰንሰለት ሴራ (a plot having a series of events with a causal chain of actions) ለመግለፅ በሚያስችለው የromanticism የአፃፃፍ ስታይል ቢፃፍ ኖሮ እንደ "ፍቅር እስከ መቃብር" ዘመን የሚሻገር ድርሰት ይሆን ነበር እላለሁ። በቀጣዩ መፅሐፍ (ተከታይ እንደሚኖር ወፊቱ ሹክ ብላኛለች😁) ደግሞ ይሄኛውን የ romantic school መንገድ እንዲሞክረው እመኛለሁ።
አንዳንድ ከመፅሐፉ የቀነጫጨብኳቸውና የወደድኳቸውን አባባሎች/አገላለፆች ላስቀምጥና ላብቃ:-
— "ለሰው ወለድ ችግር መለኮታዊ መፍትሔ መሻት መፈረካከስን ሊያዋልድ ሆነ።... ፈጣሪ ይጠብቀናል ከማለት በላይ አይጠብቀንም ብሎ ማመኑ መልካም ነው።"😁
— "ከፖለቲካ ራሳችንን ባገለልን ቁጥር ከእኛ በስነ-ምግባር እና በእውቀት ባነሱ ሰዎች ለመመራት እንገደዳለን።" ይሄኛው ከፕሌቶ የተዋሰው ፍልስፍናዊ ሐሳብ መሆኑን ወድጄዋለሁ።
— "ምልጃ ፋይዳ የለውም። መከራውን ማክሸፊያ የሰው አእምሮ ብቻ ነው..."
— " 'ውሸት ነው' ማለታቸው የለየለት ቅጥፈት እንደሆነ እያወቁ ራሳቸውን ሸነገሉ።"
— " 'አልዋሽህም...' አለች ለውሸት እየተዘጋጀች።"
— "አንድ ገንዘብ የሚጠቀም በሁለት መንግስታት የሚተዳደር ህዝብ ተፈጠረ።"
—"መከራን እንደ መልመድ ያለ መከራ ከወዴት ይገኛል?"
— "ትላንት ዛሬ ላይ እንዲያዝዝ ተፈቀደ፣ ነገ ለትላንት እንዲገብር ተወሰነ።"👌
— "ዙፋን ይህን ሁሉ ታውቃለች"😁
እና ሌሎች ብዙ ኮርኳሪ አገላለፆች...
እስቲ እናንተ ደግሞ አንብቡና የተሰማችሁን አካፍሉ።
እያነበብን እንጂ ጎበዝ!!
* * *
ዳሰሳ አቅራቢያችን ዮናስ ታደሰ በዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና ትምህርት ቤት የፍልስና መምህር ነው።
@Tfanos
የተስፋአብ ተሾመ ተስፋኣብ ተሾመ <<የዙፋን ልፊያ>> መፅሐፍን አነበብኩት። ወደድኩትም።
ዋና ገፀ ባህሪውን ሰው ሳይሆን "መብራት" የምትባል በአንዲት "ምናባዊት አገር"😁 ውስጥ የምትገኝ ምናባዊት ከተማ ያደረገ ልብ ወለድ መፅሐፍ ነው። መፅሐፉን ስናነብ በዋናነት የሰው ገፀ ባህሪ የውጣ ውረድ ሰንሰለትን እየተከተልን ሳይሆን ግኡዝ በሆነ የከተማ ዋና ገፀባህሪነት ውስጥ ባሉ የተለያዩ ገፀ ባህርያት (በዋናነት መብራታውያን) ውጣ ውረዶች ሰንሰለት ተከትለን ነው። ምናልባት አንባቢ ይሄ እስኪገለጥለት ድረስ፤ የተለያየ አይነት እርስ በርሱ የሚገናኝ የማይመስል የገፀ ባህርያት ግለ ታሪክ ሲያነብብ፣ "ይሄ ነገር የአጫጭር ልብ ወለዶች ጥርቅም ሊሆን ነው እንዴ?" ብሎ ግር ሊሰኝ ይችላል። ግዴለም ንባቦትን ይቀጥሉ ይገለጥሎታል። ደራሲው በመጀመሪያው የረዥም ልብ ወለድ ድርስት ስራው እንዲህ አይነቱን ነገር መሞከሩ በራሱ የሚደነቅ ነው።
በእርግጥ የልብ ወለዱ ዘውግ ነገሮችን በአሪስቶትል ቋንቋ፣ ሊሆኑ ይችሉ በነበሩበት (as it might be) ወይም ሊሆኑ በሚገባቸው (as it ought to be) ሳይሆን፤ በስብሐት ገብረ እግዚአብሔር አገላለፅ ታሪኩ የልብ ወለድ ድርሰት ቅርፅ ለማስያዝ እንዲረዳ ብቻ የታሪኩ ፍሰትን በተወሰነ ምናባዊ ቅርፅ አስተካክሎ ነገሮችን በሆኑበት ልክ (as it is) ሊተርክ የሚሞክር የ naturalist school አፃፃፍ የተከተለ ነው። በግሌ የዚህ ዓይነቱ መንገድ አድናቂ ባልሆንም በጭብጣቸው (theme) ምክንያት ልክ እንደ የስብሐት "ትኩሳት" እና "ሌቱም አይነጋልኝ"፣ እንደ የበአሉ ግርማ "ኦሮማይ" አይነቶች አንብቤ የምወዳቸው አሉ—የተስፋአብ የዙፋን ልፊያም ይዞት ከተነሳው ጭብጥ አንፃር ወድጄዋለሁ።
በእንደዚህ አይነት የድርሰት ዘውግ ውስጥ በብዙ የአማርኛ ድርሰቶች ላይ የማስተውለውን ምንም አስፈላጊነት በሌለው ቦታ ላይ፣ "መፃፍ እችላለሁኮ" ለማለት የሚመስል ግን ታኝከው የተተፉ፣ "ሰማዩ ጠቁሮ ነበር"፣ "ጭጋጉ እንዲህ መስሎ ነበር"፣ "አውሎ ነፋሱ እንዲያ ሲሆን ነበር"... በሚል የሚጀምሩ አሰልቺ ማጀቢያ ገለፃዎችን ሳይጠቀም፤ አሁን አሁን ደግሞ እድሜ ለድህረ-ዘመናዊነት ንቃተ-ህሊና ያመጣልህን፣ ትርጉም ይስጥ አይስጥ ሳትጨነቅ፣ የአንባቢ አእምሮ ሰብስቦ ለመያዝ የሚቸገርባቸው የቃላት ሰላጣ መአት የማፍሰስ እና የመፍሰስ አባዜ ሳይጠናወተው፤ ደራሲው ነገሮችን በተመጠኑ እና በተዋቡ ቃላት፣ የነገሮችን ሁኔታ በማያሻማ መልኩ ጥርት ባለ ቋንቋ ከሽኖ የሚገልፅበት ድርሰት ሆኖ አጊኝቼዋለሁ—የዙፋን ልፊያ።
አንዳንድ ሰዎች፣ "የዙፋን ልፊያ የእርስ በርስ ጦርነት ያለውን አስከፊ ገፅታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ድርሰት ነው" ብለው ሲገልፁት ተመልክቼአለሁ። ትክክል ነው፣እውነት አላቸው። ከዚያም ባሻገር ግን በስፋት ባይሄድበትም የእርስ በርስ ጦርነት አስከፊ ገፅታ ምንጭን የሚጠቁምበት—ማህበረሰባዊ የስነ-ምግባር ልሽቀትና ከዚህ የተነሳም የምሑራዊ ሐቀኝነት መጥፋት—ሐሳብም ቋጥሮአል። ለምሳሌ ንፁህ የምትባል ገፀ ባህሪ የታዘበችውን እንመልከት:-
<<ጦርነት አስጀማሪ ፊሽካ ከተነፋ በኋላ የሰውን ክፋት ልክ አየች። የሀገሪቱ ዜጎች እርስ በርስ ሲጠላሉ ኖረው ለመጠፋፋት አጋጣሚ እየጠበቁ እንደቆዩ አመነች። ጦርነቱ በጀመረ ማግስት ያደፈጠ ክፋት ተገለጠ፣ የተሰወረ ነውር ለአደባባይ ዋለ። "ክፉዎች ነበርን" ትላለች የሆነው ሁሉ እየደነቃት። "ክፉዎች ነበርን። የክፋታችንን ጥልቀት ጦርነት ገለጠው። የእርስ በርሱ ጦርነት ገመናችንን አደባባይ ላይ አዋለው" ትላለች ለራሷ።>> (ገፅ 142-143 አፅንኦት የራሴ)
በሌላ በኩል ደግሞ፣ "ፖለቲካና ኮረንቲ በሩቁ" የሚለው የተለመደ ብሂል የሚያዋጣ አይደለም ብሎ ሊገዳደር የሚሞክርም ነው:-
<<ምሁራን እውቀታቸው አላዳናቸውም። ፖለቲካ ምን እንደሆነ የማያውቁት በፖለቲካ እሳት አለመቃጠል አልሆነላቸውም።...>> (ገፅ 15 አፅንኦት የራሴ)
በዙፋን ልፊያ ከወደድኳቸው ነገሮች ውስጥ ከመፅሐፉ ርእስ ጀምሮ አርእስት አመራረጥና የገፀ ባህርያቱ (የአብዛኞቹ) ስሞች ከታሪክ ፍሰቱ ጋር የተሰናሰሉ መሆናቸውን ነው። ምናልባት መፅሐፉ ገና እየተነበበ ስለሆነ spoiler እንዳይሆንብኝ እንጂ፤ ለምሳሌ፣ <<የዙፋን ልፊያ>> የሚለው የመፅሐፉ አርእስት ራሱ ምን ለማለት እንደተፈለገ እንዲሁ በቀላሉ የሚጠቁመን ገላጭ አርእስት ቢመስለንም ቅሉ፤ ከገፀ ባህሪ ስምና ባህርያት ጋር ተሰናስሎ የተሸከመውን ያልጠበቅነውን ቅኔአዊ ትርጓሜ መጨረሻ ላይ ሲገለጥልን ደሞ፣ "አሃ!" ብለን መገረማችንና ደራሲውን ማድነቃችን አይቀርም። "ጉልበትና ጉድለት"፣ "መፍረስና መፍረስ" የሚሉ አርእስቶች፤ "ህይወትና ህይወት"—ሁለቱ ህይወቶች፣ "ንፁህ"፣ "ዙፋን" የሚሉ የገፀ ባህርያት ስሞች ምፀት እና ቅኔ ያዘሉ ሐሳቦችን ያረገዙ ሆነው ስናገኛቸው ደግሞ ሌላ አድናቆት ያጭርብናል።
በመጨረሻም በ"የዙፋን ልፊያ" ላይ ያለኝ ቅሬታ የነገሮችን ሁኔታ በቃላት ትረካ (ወደ መስበክ የሚያጋድል) ለመግለፅ ከሚሞክረው naturalist የአፃፃፍ ስታይል ይልቅ፤ የነገሮችን ሁኔታ በተግባራት የመንስኤና ውጤት ሰንሰለት ሴራ (a plot having a series of events with a causal chain of actions) ለመግለፅ በሚያስችለው የromanticism የአፃፃፍ ስታይል ቢፃፍ ኖሮ እንደ "ፍቅር እስከ መቃብር" ዘመን የሚሻገር ድርሰት ይሆን ነበር እላለሁ። በቀጣዩ መፅሐፍ (ተከታይ እንደሚኖር ወፊቱ ሹክ ብላኛለች😁) ደግሞ ይሄኛውን የ romantic school መንገድ እንዲሞክረው እመኛለሁ።
አንዳንድ ከመፅሐፉ የቀነጫጨብኳቸውና የወደድኳቸውን አባባሎች/አገላለፆች ላስቀምጥና ላብቃ:-
— "ለሰው ወለድ ችግር መለኮታዊ መፍትሔ መሻት መፈረካከስን ሊያዋልድ ሆነ።... ፈጣሪ ይጠብቀናል ከማለት በላይ አይጠብቀንም ብሎ ማመኑ መልካም ነው።"😁
— "ከፖለቲካ ራሳችንን ባገለልን ቁጥር ከእኛ በስነ-ምግባር እና በእውቀት ባነሱ ሰዎች ለመመራት እንገደዳለን።" ይሄኛው ከፕሌቶ የተዋሰው ፍልስፍናዊ ሐሳብ መሆኑን ወድጄዋለሁ።
— "ምልጃ ፋይዳ የለውም። መከራውን ማክሸፊያ የሰው አእምሮ ብቻ ነው..."
— " 'ውሸት ነው' ማለታቸው የለየለት ቅጥፈት እንደሆነ እያወቁ ራሳቸውን ሸነገሉ።"
— " 'አልዋሽህም...' አለች ለውሸት እየተዘጋጀች።"
— "አንድ ገንዘብ የሚጠቀም በሁለት መንግስታት የሚተዳደር ህዝብ ተፈጠረ።"
—"መከራን እንደ መልመድ ያለ መከራ ከወዴት ይገኛል?"
— "ትላንት ዛሬ ላይ እንዲያዝዝ ተፈቀደ፣ ነገ ለትላንት እንዲገብር ተወሰነ።"👌
— "ዙፋን ይህን ሁሉ ታውቃለች"😁
እና ሌሎች ብዙ ኮርኳሪ አገላለፆች...
እስቲ እናንተ ደግሞ አንብቡና የተሰማችሁን አካፍሉ።
እያነበብን እንጂ ጎበዝ!!
* * *
ዳሰሳ አቅራቢያችን ዮናስ ታደሰ በዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና ትምህርት ቤት የፍልስና መምህር ነው።
@Tfanos
❤1👍1