ልንመርቅ ነው።
ከዚህ ቀደም ለዙፋን ልፊያ መጻሕፍ የምርቃት ፕሮግራም አስበን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ተሰርዞ ነበር። ድግስ መሰረዝ ይጎዳል፥ ቅር ያሰኛል። አሁን የተሰረዘው ዳግመኛ ተሰናድቷል።
የዙፋን ልፊያ መስከረም 14 (የፊታችን ረቡዕ) በ10:30 በወመዘክር ይመረቃል።
ማስታወሻ፥ ከዚህ ቀደም ለንባብ ያበቃሁትን ነገን ፍለጋ የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መጻሕፍ ያላገኛችሁ በዙፋን ልፊያ ምርቃት እለት ታገኛላችሁ።
ቀን ፥ መስከረም 14
ቦታ ፥ ወመዘክር
ሰአት ፥ 10፥ 30
ከዚህ ቀደም ለዙፋን ልፊያ መጻሕፍ የምርቃት ፕሮግራም አስበን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ተሰርዞ ነበር። ድግስ መሰረዝ ይጎዳል፥ ቅር ያሰኛል። አሁን የተሰረዘው ዳግመኛ ተሰናድቷል።
የዙፋን ልፊያ መስከረም 14 (የፊታችን ረቡዕ) በ10:30 በወመዘክር ይመረቃል።
ማስታወሻ፥ ከዚህ ቀደም ለንባብ ያበቃሁትን ነገን ፍለጋ የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መጻሕፍ ያላገኛችሁ በዙፋን ልፊያ ምርቃት እለት ታገኛላችሁ።
ቀን ፥ መስከረም 14
ቦታ ፥ ወመዘክር
ሰአት ፥ 10፥ 30
🔥5❤2
Tesfaab Teshome pinned «ልንመርቅ ነው። ከዚህ ቀደም ለዙፋን ልፊያ መጻሕፍ የምርቃት ፕሮግራም አስበን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ተሰርዞ ነበር። ድግስ መሰረዝ ይጎዳል፥ ቅር ያሰኛል። አሁን የተሰረዘው ዳግመኛ ተሰናድቷል። የዙፋን ልፊያ መስከረም 14 (የፊታችን ረቡዕ) በ10:30 በወመዘክር ይመረቃል። ማስታወሻ፥ ከዚህ ቀደም ለንባብ ያበቃሁትን ነገን ፍለጋ የተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች መጻሕፍ ያላገኛችሁ በዙፋን ልፊያ ምርቃት…»
ቀጠሮ እንደተጠበቀ ነው?
የዙፋን ልፊያ መስከረም 14 ይመረቃል። (መፃሕፍ ፆታው ወንድ ነው ወይስ ሴት?🤔)
በምርቃቱ በርካታ እንግዶች ይገኛሉ።
ምህረት ታሪኩ ፥ ቤተማሪያም ተሾመ ፥ ሀብታሙ ሀደራ ፥ ታዲዮስ አዲሱ ፥ አንዱ ጌታቸው ግጥም ያቀርባሉ።
ረድኤት ዳዲ የስነልቦና ባለሞያ ስትሆን የዙፋን ልፊያን በሞያዋ መነፅር ትዳስሰዋለች።
ምግባር ሲራጅ ዳሰሳ ያቀርባል።
ዋሲሁን በላይ ከመጻህፉ ይተርካል።
ዶክተር ኤርሲዶ ፥ ተስፋዬ ማሞ እና ቤጃይ ኔርሽ የክብር እንግዶች ናቸው።
መድረኩን ጋዜጠኛ ብስራት መለሰ ያጋፍረዋል።
ዝግጁ?
በእለቱ የተወሰኑ የነገን ፍለጋ ኮፒዎችን ታገኛላችሁ።
እለት ፥ መስከረም 14 (ረቡዕ)
ሰአት ፥ 1ዐ : 30
ቦታ ፥ ወመዘክር
የዙፋን ልፊያ መስከረም 14 ይመረቃል። (መፃሕፍ ፆታው ወንድ ነው ወይስ ሴት?🤔)
በምርቃቱ በርካታ እንግዶች ይገኛሉ።
ምህረት ታሪኩ ፥ ቤተማሪያም ተሾመ ፥ ሀብታሙ ሀደራ ፥ ታዲዮስ አዲሱ ፥ አንዱ ጌታቸው ግጥም ያቀርባሉ።
ረድኤት ዳዲ የስነልቦና ባለሞያ ስትሆን የዙፋን ልፊያን በሞያዋ መነፅር ትዳስሰዋለች።
ምግባር ሲራጅ ዳሰሳ ያቀርባል።
ዋሲሁን በላይ ከመጻህፉ ይተርካል።
ዶክተር ኤርሲዶ ፥ ተስፋዬ ማሞ እና ቤጃይ ኔርሽ የክብር እንግዶች ናቸው።
መድረኩን ጋዜጠኛ ብስራት መለሰ ያጋፍረዋል።
ዝግጁ?
በእለቱ የተወሰኑ የነገን ፍለጋ ኮፒዎችን ታገኛላችሁ።
እለት ፥ መስከረም 14 (ረቡዕ)
ሰአት ፥ 1ዐ : 30
ቦታ ፥ ወመዘክር
❤1👍1
ነገ ንጥቀት እንደሆነ እየተነገረ ነው። ሰሞኑን ፈረንጆችን ጨምሮ አንዳንድ አማኒያን ነገ ንጥቀት እንደሆነ እየተናገሩ ነው።
የሚያወሩት እውነት ከሆነ የተወሰኑ አማኞች ነገ ይነጠቃሉ። ሌሎቻችን ታላቁን መከራ እንቀበላለን። (ያድርግላቸው)
እንደ ሐሳብ ግን ፥ ከነገ ወዲያ የመጽሐፍ ምርቃት ስላለኝ ንጠቀቱ ሐሙስ ቢሆን ጥሩ ነው። ካልሆነ ግን ምን ይደረጋል?
ነገ ፃድቃን ከተነጠቁ በኋላ በምድር የምትቀሩ ሰዎች ሐሙስ በመጽሐፍ ምርቃት ፕሮግራሜ ተገኙልኝ
የሚያወሩት እውነት ከሆነ የተወሰኑ አማኞች ነገ ይነጠቃሉ። ሌሎቻችን ታላቁን መከራ እንቀበላለን። (ያድርግላቸው)
እንደ ሐሳብ ግን ፥ ከነገ ወዲያ የመጽሐፍ ምርቃት ስላለኝ ንጠቀቱ ሐሙስ ቢሆን ጥሩ ነው። ካልሆነ ግን ምን ይደረጋል?
ነገ ፃድቃን ከተነጠቁ በኋላ በምድር የምትቀሩ ሰዎች ሐሙስ በመጽሐፍ ምርቃት ፕሮግራሜ ተገኙልኝ
😁10❤2
በዙፋን ልፊያ መጻሕፍ ምርቃት እነማን ይገኛሉ?
ረድኤት ዳዲ
ረድኤት የስነልቦና ባለሞያ እና አሰልጣኝ ናት። በሃሴት የማማከር አግልግሎት የምክክር አገልግሎት ትሰጣለች። በዙፋን ልፊያ መጻሕፍ ምርቃት ላይ ከሚገኙ እንግዶች መካከል አንዷ ረድኤት ዳዲ ስትሆን መጻሕፉን ከሞያዋ አንፃር ትመለከታለች።
ምግባር ሲራጅ
ምግባር ሦስት መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል። ዘንባባ ፥ መንደሪን መንደሪን እና እየዳነ ኼደ ለንባብ ያበቃቸው ስራዎቹ ናቸው። ምግባር የዙፋን ልፊያ ላይ ዳሰሳ ያቀርባል።
ዋሲሁን በላይ
ገጣሚ ተዋናይ እና ደራሲ ነው። በቅርቡ ለንባብ ያበቃው የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው አልንበረከክም መጻሕፍ በአጭር ጊዜ ሁለተኛ እትም ደርሷል። ዋሲሁን ሲተረክ የተለየ ሰው ነው። የሱን ትረካ አለመውደድ አይቻልም። ዋሲሁን ከዙፋን ልፊያ አንድ ክፍል ይተርክልናል።
ተስፋዬ ማሞ
ጋሽ ተስፋዬን ማስተዋወቅ በጣም አስቸጋሪ ነው። ዘርፈ ብዙ ባለሞያ ነው ብዬ ብናገር ለ ቀ ባ ሪ ማርዳት ይሆንብኛል። በሸገር ኤፍ ኤም የሚያዘጋጀው የጥበብ መንገድ የሬዲዮ ፕሮግራም ሰቃይ ፕሮግራም ነው። ነጎድጓዳማ ድምፁ እና የንባብ ዝግጅቱ የፕሮግራሙ ድምቀት ናቸው። ከማዕበል ማዶ በቅርቡ ለንባብ ያበቃው የግለ ታሪክ መጻሕፍ ነው። ተስፋዬ ማሞ የክብር እንግዳ ነው።
ዶክተር ኤርሲዶ ለንዴቦ
የአራዳ እና የአዋቂ ቅልቅል ከፈለጋችሁ ዶክ እውነተኛ ማሳያ ነው። ኤርሲዶን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቅኹት ኑሮ ማፕ በሚለው መጻሕፍ ነው።
ኤርሲዶ አንደበቱ ርቱዕ ነው። ተራማጅ ነው። ሃሳቡን አደራጅቶ መግለፅ ያውቅበታል። ሞጋች ነው። የልጆቻችን ኢትዮጵያ የተሸኘው ተወዲጅ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅ ነው። (የአያን ራንድም ወዳጅ ነው😀) ኤርሲዶ የክብር እንግዳችን ነው።
ደግሞ በፕሮግራማችን የተዋጣላቸው ገጣሚያን አሉ።
አንዱ ጌታቸው በጣም የተለየ አፃፃፍ የሚከተል ገጣሚ ነው። አነባበቡም እንደአፃፃፉ ነው። የሚፅፍበት መንገድ ደስ ይላል።
ቤተማሪያም ተሾመ ገጣሚ ብቻ ሳይሆን የግጥም ተርጓሚም ጭምር ነው። በአንድ ወቅት እንዳለጌታ ከበደ "በአገራችን ካሉ ሦስት ምርጥ የግጥም ተርጓሚዎች መካከል ቤተማሪያም ይገኝበታል" ብሎናል።
ሀብታሙ ሀደራ ፥ ሰዎች በስምምነት በጅምላ የሚወዱት ገጣሚ ነው። ግጥሞቹን አያወሳስብም። ሁሉም ሰው እንዲረዳውና ለንባብ እንዲመች አድርጎ መፃፍ ያውቅበታል።
ታዲዮስ አዲሱን እንደማደንቀው ለብዙ ሰው ተናግሬ አውቃለሁ። ግጥሞቹ ብቻ ሳይሆን የሚያነብበትም መንገድ ይለያል። ረጃጅም ግጥሞቹ እንኳ ከጥፍጥናቸው ብዛት አጭር ይመስላሉ።
ምህረት ታሪኩ ጎበዝ ገጣሚ እንደሆነች መቶ ሰባ ሚሊዮን ጊዜ ነግሬያት አላመነችኝም። እናንተ ትነግሯታላችሁ።
ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ ግጥሞቻቸውን ያቀርባሉ።
መድረክ አጋፋሪው ጋዜጠኛ ብስራት መለሰ ነው። ብስራት በተለያዩ ሚዲያዎች ይታወቃል። በተለይ በፋና ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም በሐገሬ ቴሌቪዥን እናውቀዋለን። (በሐገሬ አመራርም ነበር)
አለም አቀፍ የፖለቲካ ትንታኔዎቹ ይወደዱለታል።
ኢንጂነር ቤጃይ ኔርሽ...
ቤጃይን አላስተዋውቅም 😎
እኒህ ሁሉ እንግዶች የናንተን መገኘት ይጠብቃሉ።
ኑ፥ የዙፋን ልፊያን እንመርቅ
ቦታ ፥ ወመዘክር
ቀን ፥ መስከረም 14 (የፊታችን ረቡዕ)
ሰአት ፥ 10:30
ይህን ለሌሎች አጋሩ
ረድኤት ዳዲ
ረድኤት የስነልቦና ባለሞያ እና አሰልጣኝ ናት። በሃሴት የማማከር አግልግሎት የምክክር አገልግሎት ትሰጣለች። በዙፋን ልፊያ መጻሕፍ ምርቃት ላይ ከሚገኙ እንግዶች መካከል አንዷ ረድኤት ዳዲ ስትሆን መጻሕፉን ከሞያዋ አንፃር ትመለከታለች።
ምግባር ሲራጅ
ምግባር ሦስት መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቷል። ዘንባባ ፥ መንደሪን መንደሪን እና እየዳነ ኼደ ለንባብ ያበቃቸው ስራዎቹ ናቸው። ምግባር የዙፋን ልፊያ ላይ ዳሰሳ ያቀርባል።
ዋሲሁን በላይ
ገጣሚ ተዋናይ እና ደራሲ ነው። በቅርቡ ለንባብ ያበቃው የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው አልንበረከክም መጻሕፍ በአጭር ጊዜ ሁለተኛ እትም ደርሷል። ዋሲሁን ሲተረክ የተለየ ሰው ነው። የሱን ትረካ አለመውደድ አይቻልም። ዋሲሁን ከዙፋን ልፊያ አንድ ክፍል ይተርክልናል።
ተስፋዬ ማሞ
ጋሽ ተስፋዬን ማስተዋወቅ በጣም አስቸጋሪ ነው። ዘርፈ ብዙ ባለሞያ ነው ብዬ ብናገር ለ ቀ ባ ሪ ማርዳት ይሆንብኛል። በሸገር ኤፍ ኤም የሚያዘጋጀው የጥበብ መንገድ የሬዲዮ ፕሮግራም ሰቃይ ፕሮግራም ነው። ነጎድጓዳማ ድምፁ እና የንባብ ዝግጅቱ የፕሮግራሙ ድምቀት ናቸው። ከማዕበል ማዶ በቅርቡ ለንባብ ያበቃው የግለ ታሪክ መጻሕፍ ነው። ተስፋዬ ማሞ የክብር እንግዳ ነው።
ዶክተር ኤርሲዶ ለንዴቦ
የአራዳ እና የአዋቂ ቅልቅል ከፈለጋችሁ ዶክ እውነተኛ ማሳያ ነው። ኤርሲዶን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወቅኹት ኑሮ ማፕ በሚለው መጻሕፍ ነው።
ኤርሲዶ አንደበቱ ርቱዕ ነው። ተራማጅ ነው። ሃሳቡን አደራጅቶ መግለፅ ያውቅበታል። ሞጋች ነው። የልጆቻችን ኢትዮጵያ የተሸኘው ተወዲጅ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅ ነው። (የአያን ራንድም ወዳጅ ነው😀) ኤርሲዶ የክብር እንግዳችን ነው።
ደግሞ በፕሮግራማችን የተዋጣላቸው ገጣሚያን አሉ።
አንዱ ጌታቸው በጣም የተለየ አፃፃፍ የሚከተል ገጣሚ ነው። አነባበቡም እንደአፃፃፉ ነው። የሚፅፍበት መንገድ ደስ ይላል።
ቤተማሪያም ተሾመ ገጣሚ ብቻ ሳይሆን የግጥም ተርጓሚም ጭምር ነው። በአንድ ወቅት እንዳለጌታ ከበደ "በአገራችን ካሉ ሦስት ምርጥ የግጥም ተርጓሚዎች መካከል ቤተማሪያም ይገኝበታል" ብሎናል።
ሀብታሙ ሀደራ ፥ ሰዎች በስምምነት በጅምላ የሚወዱት ገጣሚ ነው። ግጥሞቹን አያወሳስብም። ሁሉም ሰው እንዲረዳውና ለንባብ እንዲመች አድርጎ መፃፍ ያውቅበታል።
ታዲዮስ አዲሱን እንደማደንቀው ለብዙ ሰው ተናግሬ አውቃለሁ። ግጥሞቹ ብቻ ሳይሆን የሚያነብበትም መንገድ ይለያል። ረጃጅም ግጥሞቹ እንኳ ከጥፍጥናቸው ብዛት አጭር ይመስላሉ።
ምህረት ታሪኩ ጎበዝ ገጣሚ እንደሆነች መቶ ሰባ ሚሊዮን ጊዜ ነግሬያት አላመነችኝም። እናንተ ትነግሯታላችሁ።
ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ ግጥሞቻቸውን ያቀርባሉ።
መድረክ አጋፋሪው ጋዜጠኛ ብስራት መለሰ ነው። ብስራት በተለያዩ ሚዲያዎች ይታወቃል። በተለይ በፋና ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም በሐገሬ ቴሌቪዥን እናውቀዋለን። (በሐገሬ አመራርም ነበር)
አለም አቀፍ የፖለቲካ ትንታኔዎቹ ይወደዱለታል።
ኢንጂነር ቤጃይ ኔርሽ...
ቤጃይን አላስተዋውቅም 😎
እኒህ ሁሉ እንግዶች የናንተን መገኘት ይጠብቃሉ።
ኑ፥ የዙፋን ልፊያን እንመርቅ
ቦታ ፥ ወመዘክር
ቀን ፥ መስከረም 14 (የፊታችን ረቡዕ)
ሰአት ፥ 10:30
ይህን ለሌሎች አጋሩ
❤4
ዳሰሳ በቶፊቅ ተማም
* * *
የዙፋን ልፍያን እንዳነበብኩት
የመፅሀፉ ርእስ ፡- የዙፋን ልፍያ
የህትመት አመት ፡- ነሀሴ 2017
የታተመበት ማተሚያ ቤት ፡- ሀይማኖት ማተሚያ ቤት
የገፅ ብዛት ፡- 179
ደራሲ ፡- ተስፋአብ ተሾመ
በቶፊቅ ተማም
በማህበራዊ ሚዲያ ደርዝ ባላቸውና በተመጠኑ ፅሁፎችና በተለይ ግላዊ እይታዎችን በማጋራት ይታወቃል። ከዚህ በፊት በክልል የሬድየ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ሰርቷል ክራራዊ ህይወት እንዲሁም የአጭር ልቦለዶች ስብስብ የሆነውን ነገን ፍለጋ የተሰኘ መፅሀፍ የሰጠን ተስፋአብ ተሾመ አሁን ደግሞ አቅሙን አጠናክሮ እና በንባብ ዳብሮ የዙፋን ልፍያ የተሰኘ ሶስተኛ እና ወጥ የሆነ ልብ ወለድ ስራ ለአንባብያን ያቀረበ ሲሆን እኔም መፅሀፉን አንብቤ የተሰማኝን ከዚህ በመቀጠል አሰፍራለሁ ፡፡
የተናቀው ሽበት
የመፅኀፉ ዋና ኣላማ በተለይ የጦርነት መነሻ እና ከጦርነት በኋላ የአንድን ሀገር ብሎም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰውን ቁሳዊ ኪሳራ ማሳየት ከዚህ ባለፈም የሚታየውን የሞራል የባህል ኪሳራም ያሳያል። በዚህ ርእስ ላይ የጦርነትን ዳፋ በተለይ ለሴቶችና አረጋውያን እጅግ የባሰ መሆኑን አሳይቶናል "እባክህ ልጄ" በደፈሰ አይኑ ሲያፈጥባቸው የሚናገሩት ቸገራቸው ልባቸው ራደ እድሜአቸው ምህረት አላስገኘላቸውም›› በማለት በመቁረብያ እድሜ ስለተደፈሩት እናት ያወሳናል ይህ ፀሀፊው ያሰፈረው ሀሳብ በእውኑ ከአመት በፊት እድሜአቸው ወደ ሰማንያ በላይ የሆኑ አዛውንት ላይ እዚሁ ሀገራችን የተከሰተ ድርጊት መሆኑ ይታወሳል።
‹‹ ይህን ዘመን ላለማየት ከታላቁ መከራ በፊት ግደለኝ ብለው ቢፀልዩም ምላሽ አላገኙም ›› በማለት በጦርነቱ ሳቢያ የተደፈሩት የመብራት ኣዛውንት መጨረሻ በዚህ መልኩ መገባደዱን አየነገረን ጎን ለጎንም ጦርነት የሀገሪቱ ትውፊት የነበረውን እርስ በእርስ የመከባባር ስርአት ጦርነት እንደሚንደው አሳይቶናል ፡፡
ልፍያና ፍልሚያ
‹‹ ባለስልጣናቱ በአንደበታቸው ቃል ይዋጋሉ ወታደሮች በጠመንጃ ይጠዛጠዛሉ የሀብታሞችን ጦርነት ድሆች ይዋጋሉ የሹማምንት ልፍያ የተርታ ዜጎች ፍልሚያ ነው ››ገፅ 11 በማለት የጦርነት ደርዙ አንድም ልፍያ አሊያም ሲብስና የሻቱትን ማግኘት ግድ ሲል ፍልሚያ መሆኑን የሚነግረን ተስፋአብ፥ ካለይ እንደተገለፀው አሁንም የሴቶች መደፈር ብቻ ሳይሆን ሰይጣንን በሚያስንቅ ክፋት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ሞት እና እንግልት ለማሳየት ሞክሯል ።
"አስገድዶ መድፈር ውስጣቸው ያለውን አውሬ ማርካት ያልቻሉ በደፈሯቸው ሴቶች ላይ ጥይት አርከፈከፉ" በማለት የተደፈሩ ሴቶች በአውሬዎች መበላታቸውን ይግልፃል። ከዚህ ባለፈ ጦርነቱ የወጣቶችን ተስፋን የሚያጠፋ መሆኑን እንዲህ አስቀምጦታል ፡፡
"ተስፋ ነበራቸው ፥ ብዙ የመኖር፥ ወላጆቻቸውን የመጦር ፥ የመርዳት ታላላቆቻቸውን የማርካት ተስፋ ነበራቸው ፖለቲካው በላው " ገጽ 12
ጦርነት በተለይ ቀጣይ ሀገር ተረካቢ የሆኑ የወጣቶች ታዳጊዎች ህይወት እንደሚያጨልም ለማሳየት ሞክሯል። ጦርነት ከመጣ ሁልም ነገር የቅርብ ሩቅ መሆኑን እንዲህ በሚል ይገልፃል ፡፡ ‹‹የጦርነት እሳት ሲለኮስ ባለፀጎቹ ገንዘባቸው አላዳናቸውም። ምግብ እያለ ለተራቡ ፥ ገንዘብ እያላቸው ተቸገሩ፥ የአልጋ ቁራኛ ሲሆኑ መድሀኒት ማግኘት አልተቻላቸውም ›› ገፅ 23
የሰላም እጥረት የሚያደርሰውን ኪሳራ ለማሳየት ሞክሯል። ሌላው በመፅሀፉ ያነሳው ሀሳብ ኦሜርታ የተባለውን አቋም የሚያንፀባርቁትን አላየንም አልሰማንም አንናገርም በማለት በብዛት የሚታወቁትን ምሁራን ስለ ሀገር ሰላም እንዲሰሩ የጠቆመበት ነው ፡፡‹‹ መ ሀ ይ ም የሚያቦካው ፖለቲካ ›› በማለት ከገዛ ሀገራቸው ጉዳይ ራሳቸውን ገለል ቢያዳርጉም ከገፈቱ አላመጡም። አላዋቂዎች ያሏቸው በህይወታቸው ላይ ወሰኑ ከጎናቸው ያልተሰለፉት ለሞት እና ለመከራ ዳረጓቸው ›› ገፅ 23
ምሁራንም የገፈቱ ቀማሽ መሆናቸውን ለመጥቀስ ሲሞክር፥ ምሁራን በተለይ ሀገር ወደ ጦርነት እንዳትገባ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ለመጠቆም ሞክሯል ፡፡
በህግ አምላክ
ከጦርነት አንዱ ዳፋ የትዳር ባላጋራን ብሎም ቤተሰብን ማጣት እንዳለ ሆኖ ተደፍሮ ህይወት መበላሸትም የሚያጋጥም መሆኑን በዚህ ክፍል አሳይቶናል
‹‹ በህግ አምላክ እያለች ብትማፀንም ከመደፈር አልዳነችም። መለዮህን እክብር ብትልም አልሆነም። መደፈሯንም ተክትሎ በመጣው ፅንስ ሳቢያ ማስወረድን ብትፈልግም ማስወረድ ለጤና አደጋ በመሆኑ ሳቢያ ያልፈለገቸውን ልጅ ወልዳ ለማሳደግ ያልተረፈችው ህመሟን የምታስታግስበት የወለደችውን የአብራኳን ክፋይ በመስደብ ነው ›› ሰይጣን ዘረ ሰይጣን ዲ ላ በማለት።
ጦርነት ዳፋው ከገዛ ማህፀን የወጣ ልጅ ያሰድባል። በጦርነት ሳቢያ ተደፍረው ስንቶች አባት የሌለው ልጅ ወለዱ? ጦርነት ውብ የሆነውን እናትነት ይፈትናል። ይህ ታሪክ የብዙ ኢትዮጲያውያን ታሪክ ነው። በመደፈር ሳቢያ የሚከሰተውን ጽንስ የሚረግሙ ፥ላም እሳት ወለደች እንዲሉ... ወልደው በፍቅር ለማሳደግ ወደው ፈቅደው አልፀነሱ፥ የፀነሱትን ፅንስ ማውረድ ነፍስ ማጥፋት እየሆነባቸው...
ምነው አምና በሞትኩ
* * *
የዙፋን ልፍያን እንዳነበብኩት
የመፅሀፉ ርእስ ፡- የዙፋን ልፍያ
የህትመት አመት ፡- ነሀሴ 2017
የታተመበት ማተሚያ ቤት ፡- ሀይማኖት ማተሚያ ቤት
የገፅ ብዛት ፡- 179
ደራሲ ፡- ተስፋአብ ተሾመ
በቶፊቅ ተማም
በማህበራዊ ሚዲያ ደርዝ ባላቸውና በተመጠኑ ፅሁፎችና በተለይ ግላዊ እይታዎችን በማጋራት ይታወቃል። ከዚህ በፊት በክልል የሬድየ ጣቢያዎች በጋዜጠኝነት ሰርቷል ክራራዊ ህይወት እንዲሁም የአጭር ልቦለዶች ስብስብ የሆነውን ነገን ፍለጋ የተሰኘ መፅሀፍ የሰጠን ተስፋአብ ተሾመ አሁን ደግሞ አቅሙን አጠናክሮ እና በንባብ ዳብሮ የዙፋን ልፍያ የተሰኘ ሶስተኛ እና ወጥ የሆነ ልብ ወለድ ስራ ለአንባብያን ያቀረበ ሲሆን እኔም መፅሀፉን አንብቤ የተሰማኝን ከዚህ በመቀጠል አሰፍራለሁ ፡፡
የተናቀው ሽበት
የመፅኀፉ ዋና ኣላማ በተለይ የጦርነት መነሻ እና ከጦርነት በኋላ የአንድን ሀገር ብሎም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰውን ቁሳዊ ኪሳራ ማሳየት ከዚህ ባለፈም የሚታየውን የሞራል የባህል ኪሳራም ያሳያል። በዚህ ርእስ ላይ የጦርነትን ዳፋ በተለይ ለሴቶችና አረጋውያን እጅግ የባሰ መሆኑን አሳይቶናል "እባክህ ልጄ" በደፈሰ አይኑ ሲያፈጥባቸው የሚናገሩት ቸገራቸው ልባቸው ራደ እድሜአቸው ምህረት አላስገኘላቸውም›› በማለት በመቁረብያ እድሜ ስለተደፈሩት እናት ያወሳናል ይህ ፀሀፊው ያሰፈረው ሀሳብ በእውኑ ከአመት በፊት እድሜአቸው ወደ ሰማንያ በላይ የሆኑ አዛውንት ላይ እዚሁ ሀገራችን የተከሰተ ድርጊት መሆኑ ይታወሳል።
‹‹ ይህን ዘመን ላለማየት ከታላቁ መከራ በፊት ግደለኝ ብለው ቢፀልዩም ምላሽ አላገኙም ›› በማለት በጦርነቱ ሳቢያ የተደፈሩት የመብራት ኣዛውንት መጨረሻ በዚህ መልኩ መገባደዱን አየነገረን ጎን ለጎንም ጦርነት የሀገሪቱ ትውፊት የነበረውን እርስ በእርስ የመከባባር ስርአት ጦርነት እንደሚንደው አሳይቶናል ፡፡
ልፍያና ፍልሚያ
‹‹ ባለስልጣናቱ በአንደበታቸው ቃል ይዋጋሉ ወታደሮች በጠመንጃ ይጠዛጠዛሉ የሀብታሞችን ጦርነት ድሆች ይዋጋሉ የሹማምንት ልፍያ የተርታ ዜጎች ፍልሚያ ነው ››ገፅ 11 በማለት የጦርነት ደርዙ አንድም ልፍያ አሊያም ሲብስና የሻቱትን ማግኘት ግድ ሲል ፍልሚያ መሆኑን የሚነግረን ተስፋአብ፥ ካለይ እንደተገለፀው አሁንም የሴቶች መደፈር ብቻ ሳይሆን ሰይጣንን በሚያስንቅ ክፋት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ሞት እና እንግልት ለማሳየት ሞክሯል ።
"አስገድዶ መድፈር ውስጣቸው ያለውን አውሬ ማርካት ያልቻሉ በደፈሯቸው ሴቶች ላይ ጥይት አርከፈከፉ" በማለት የተደፈሩ ሴቶች በአውሬዎች መበላታቸውን ይግልፃል። ከዚህ ባለፈ ጦርነቱ የወጣቶችን ተስፋን የሚያጠፋ መሆኑን እንዲህ አስቀምጦታል ፡፡
"ተስፋ ነበራቸው ፥ ብዙ የመኖር፥ ወላጆቻቸውን የመጦር ፥ የመርዳት ታላላቆቻቸውን የማርካት ተስፋ ነበራቸው ፖለቲካው በላው " ገጽ 12
ጦርነት በተለይ ቀጣይ ሀገር ተረካቢ የሆኑ የወጣቶች ታዳጊዎች ህይወት እንደሚያጨልም ለማሳየት ሞክሯል። ጦርነት ከመጣ ሁልም ነገር የቅርብ ሩቅ መሆኑን እንዲህ በሚል ይገልፃል ፡፡ ‹‹የጦርነት እሳት ሲለኮስ ባለፀጎቹ ገንዘባቸው አላዳናቸውም። ምግብ እያለ ለተራቡ ፥ ገንዘብ እያላቸው ተቸገሩ፥ የአልጋ ቁራኛ ሲሆኑ መድሀኒት ማግኘት አልተቻላቸውም ›› ገፅ 23
የሰላም እጥረት የሚያደርሰውን ኪሳራ ለማሳየት ሞክሯል። ሌላው በመፅሀፉ ያነሳው ሀሳብ ኦሜርታ የተባለውን አቋም የሚያንፀባርቁትን አላየንም አልሰማንም አንናገርም በማለት በብዛት የሚታወቁትን ምሁራን ስለ ሀገር ሰላም እንዲሰሩ የጠቆመበት ነው ፡፡‹‹ መ ሀ ይ ም የሚያቦካው ፖለቲካ ›› በማለት ከገዛ ሀገራቸው ጉዳይ ራሳቸውን ገለል ቢያዳርጉም ከገፈቱ አላመጡም። አላዋቂዎች ያሏቸው በህይወታቸው ላይ ወሰኑ ከጎናቸው ያልተሰለፉት ለሞት እና ለመከራ ዳረጓቸው ›› ገፅ 23
ምሁራንም የገፈቱ ቀማሽ መሆናቸውን ለመጥቀስ ሲሞክር፥ ምሁራን በተለይ ሀገር ወደ ጦርነት እንዳትገባ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ለመጠቆም ሞክሯል ፡፡
በህግ አምላክ
ከጦርነት አንዱ ዳፋ የትዳር ባላጋራን ብሎም ቤተሰብን ማጣት እንዳለ ሆኖ ተደፍሮ ህይወት መበላሸትም የሚያጋጥም መሆኑን በዚህ ክፍል አሳይቶናል
‹‹ በህግ አምላክ እያለች ብትማፀንም ከመደፈር አልዳነችም። መለዮህን እክብር ብትልም አልሆነም። መደፈሯንም ተክትሎ በመጣው ፅንስ ሳቢያ ማስወረድን ብትፈልግም ማስወረድ ለጤና አደጋ በመሆኑ ሳቢያ ያልፈለገቸውን ልጅ ወልዳ ለማሳደግ ያልተረፈችው ህመሟን የምታስታግስበት የወለደችውን የአብራኳን ክፋይ በመስደብ ነው ›› ሰይጣን ዘረ ሰይጣን ዲ ላ በማለት።
ጦርነት ዳፋው ከገዛ ማህፀን የወጣ ልጅ ያሰድባል። በጦርነት ሳቢያ ተደፍረው ስንቶች አባት የሌለው ልጅ ወለዱ? ጦርነት ውብ የሆነውን እናትነት ይፈትናል። ይህ ታሪክ የብዙ ኢትዮጲያውያን ታሪክ ነው። በመደፈር ሳቢያ የሚከሰተውን ጽንስ የሚረግሙ ፥ላም እሳት ወለደች እንዲሉ... ወልደው በፍቅር ለማሳደግ ወደው ፈቅደው አልፀነሱ፥ የፀነሱትን ፅንስ ማውረድ ነፍስ ማጥፋት እየሆነባቸው...
ምነው አምና በሞትኩ
❤1
ምነው አምና በሞትኩ በሚለው ርእስ ስር ጦርነት ከሚያደርሰው አካላዊ ጉዳት፥ የንብረት ጉዳት፥ የስነ ልቦና ጉዳት ባለፈ ለተለያየ የአእምሮ ህመሞች እንደሚዳርግ ለማሳየት ሞክረዋል ፡፡የአእምሮ ጤና ማለት ምንም አይነት የእምሮ ህመም አለመኖር ብቻ አይደለም። የአእምሮ ጤና ችሎታችንን የምንገዘነብበት እና የመደበኛ ህይወት ጭንቀቶችን የምንሸከመበት መንገድ ነው። በአስተሳሰባችን ፥ በስሜታችን ፥ በድርጊታችን እና በህይወታችን ውሳኔዎች ላይ ተፅእኖ ያሳድራል ፡፡የአእምሮ ጤና ከአለም አቀፍ የበሽታዎች ሸክም 14 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ ህመም የሚይዘው በመሆኑ የአእምሮ ጤና አስፈላጊና የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ መብት መሆኑን የጤና ባለሙዎች ይናገራሉ ፡፡
ጉልበትና ጉድለት
በዚህ ክፍል በተለይ በጦርነት ሳቢያ የአካል ጉዳተኛ የሚሆኑ ዜጎችን በተመለከተ ያሣየበት ነው ለዚህም ‹‹ እባካችሁ ወገኖች ግራ እጁ ከክርኑ በታች ተቆሯል ቀኝ እግሩ ከጉልበቱ በታች ያለው ቀኝ አይኑ ፈሷል ጆሮ የመስማት አቅም ተዳክሟል ›› ገፅ 83
ይህ በጦርነቱ ጉዳት ያጋጠመው ወታደር ታሪክ በማድረግ ሲሆን ወታደሩ ለእለት ጉርስ እያለ ቢለምንም ቸር የነበረው የመብራት ህዝብ በጦርነተ ሳቢያ በድህነት እጅ ከወርች በመያዙ የእለት ጉርሱ ፈተና ሲሆንበት ያሳየናል ከዚህ ባለፈ በጦርነት ሰመጣ የማይነካው ቤተሰብ አለመኖሩንም እንዲህ ብሎ ያስቀምጠዋል
‹‹ የጦርነት እሳት ያልጎነኘው ቤተሰብ ለማግኘት ከሞመከር ይልቅ ፀሀይ በምእራብ በኩል ወጥታ በምስራቅ በኩል እንድትጠልቅ መመኘቱ የተሻለ ውጤት አለው
ወልዶ ለጦርነት
ኖር ለጦርነት
ሰርቶ ለጦርነት›› ገፅ 89
ጦርነት በተንሰራፋበት ልጅ ቢወለድ ለጦርነት፥ ሰርቶ ጥሪት ቢያዝ ለጦር መሳርያ መግዣ ነው ይላል ደራሲው። ይህ በፊት ባለጉልበት እና መሳርያ ታጣቂ ወታደር በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ጉልበቱ አጉድልታል። በዚህም ጦርነት ሰለማዊ ዜጋን ብቻ ሳይሆን ተፈላሚ ሀይሎችንም ድል ፊታቸውን ስታዞር ዳፋው ለነሱም መሆኑን ለማሳየት ሞክሯል ፡፡
የሁለት ህይወቶች ወግ
‹‹ በምድር የቆየችበት እድሜ ሶስት አስርተ የሚሞላ ባሆንም የእድሜዋን እጥፍ የኖረች ይመስል ተጎሳቁላለች ቀይ መልኳ ወደ ጥቁረት ጉዞ ጀምሯል ከፊቷ ማዲያት ያልጎበኘውን ስፍራ ማግኘት አይቻልም ›› ገፅ 115
ይህን የሚላት ህይወት ስለምትባል እና በጦርነቱ ከሴተነቷ ጋር ተዳምሮ ስለፈተናት እንስት ነው
‹‹የእርሰ በእርስ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ የሀገሪቱ ህግ ህገ ወጥነት እንዳይሆን አስቀርቷታል የሐይማኖት አባቶች ጆሮ ሲነፈጉ የእምነት ተቋማት አቅም ሰያጡ የመብራት ከተማ አባቶች መደመጥ፤የማይችሉ ሲሆኑ ሸንጎ መዘባበቻ ሲደረግ ስነምግባር ለጉልበት ሲገብር ህግ ለአመፅ ሲሰግድ አየን ››ገፅ 117
ጦርነት የቅርቡን ሩቅ ያደርጋል። ያለ ሰላም ዘርቶ መቃም ወልዶ መሳም ነግዶ ማትረፍ ፤መገበያየት አስቸጋሪ መሆኑን እያሳየ የጦርነትን አበሳ በዚህች ህይወት ብቻ ማሳየት ያልበቃው ተስፋ አብ ሌላዋን ህይወት ያስቃኘናል ፡፡
‹‹ ህይወት እባላለሁ ኣባቴ›› መላ አካልዋን በመገረም ቃኙት ‹‹ ህይወት ነሽ›› መገረም ፊታቸው ላይ ተጋድሞ አዎን አባቴ ›› ገፅ 122
በማለት ራሷን ያስተዋወቀችው ህይወት ያመጣትን ጉዳይ እንዲህ ትገልፃለች ‹‹ ውጊያው ሁልንም ሰዎች ስላደሀየ ሰዎች ችግራቸውን ለመርታት የተለየ መፍትሄ መፈለግ ጀመሩ ታማኝ ሰዎች ማጭበርበር ሲጀምሩ አየሁ ስርቆትን የሚጠየፉ ለሌብነት ተሽቀዳደሙ ሴትነታቸውን ያከብሩ የነበሩ ገላቸውን ለመሸጥ ፈቀዱ ›› ገጽ 124
ጦርነት የሰርክ ኖሮን ያመሰቃቅላል። ይህን ምስቅልቅል ይህንን ክፍተት ለመጠቀም የወሰነቸው ህይወት፥ ጦርነቱ ባመጣው እድል ተጠቃሚ ሆነች። ኑሮ የከበዳቸውን ቀንና ሌሊቱ አንድ የሆነባቸውን ሴቶች ገላቸውን እንዲሸጡ በማድረግ ዳጎስ ያለ ገንዘብ ብታገኝም የልጇ ከስነ ምግባር ማፈንገጥ እና በአጉል ሱስ መጠመድ መፍትሄ ፍለጋ የመብራት ከተማ ነዋሪ የሆኑት አባት ጋር መፍትሄ ፍላጋ አምርታለች።
ጦርነት በተለይ በታዳጊ ወጣቶች የስነ ምግባር ዝቅጠት የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚኖረው በሁለተኛዋ ህይወት ልጅ አማካኝነት ሊየሳየን ሞክሯል ፡፡
መፍረስና መፍረስ
በዘህ ርእሰ ስር ንፁህ ስለተባለች ገጸ ባህሪ በተለይ የጦሩ አለቃ ባለቤት ስለሆነችው ንፁህ እየነገረን በዛውም ጦርነት ሲመጣ የሹማምንት ቤተሰቦች የተሻለ መኖርያ እና ማረፍያ እንደሚዘጋጅላቸው በአንፃሩ መደዴው ህብረተሰብ ለከፋ ችግር እንደሚተው ያሳየናል ፡፡
ከዚህ ባለፈም የንፁህን የትዳር ፍለጋ ስንክሳር እያዋዛ የተረከበት መንገድ ግሩም ነው
እንደ መውጫ
ከላይ እንደተገለፀው መፅሀፉ ልብ ወለድ ይሁን እንጂ ፥ባለፉት አመታት የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ እንደ ነበረ ሀገር የጦርነትን አስከፊነት በቀላሉ እንድንገነዘብ ለማድረግ፥ አጠር ባለ መልኩ ያስቀመጠበት ሂደት መልካም ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ከዚህ ባለፈ በመፅሀፉ መቻል ስለተባው ገፀ ባህሪ ያሰፈረው እንዲሁም ስለ ምናባዊ ከተማዋ መብራት ገለፃ በማድረግ የጦርነቱን ምድር በአግባቡ እንድናውቅ ሲያስችል፥ ለጦርነቱ መነሻ ስለሆኑት ፕሬዘዳንት እና ጄነራል የመፅሀፉ ርአስ ስለሆነቸው ዙፋን የተለያዩ የስነ ፅሁፍ ቴከኒኮችን በመጠቀም... አሰቃቂውን የጦርነት ሁኔታ በሌሎች የህወይት ቅመሞች እያዋዛ አሳይቶናል።
መፅሀፉ እንከን የለሽ ነው ማለት አይደለም። ሌሎች የስነ ፅሁፍ ባለሙያዎች የሚሰጡት ሂስ እንደተጠበቀ ሆኖ ፥ የቃላት ግድፈቶች ታርመው ለቀጣይ ህትመት ቢዘጋጅ እያልኩ በዚህ ላብቃ ፡፡
ማስታወሻ፥
የዙፋን ልፊያ ነገ 11 ሰአት በወመዘክር ይመረቃል
ጉልበትና ጉድለት
በዚህ ክፍል በተለይ በጦርነት ሳቢያ የአካል ጉዳተኛ የሚሆኑ ዜጎችን በተመለከተ ያሣየበት ነው ለዚህም ‹‹ እባካችሁ ወገኖች ግራ እጁ ከክርኑ በታች ተቆሯል ቀኝ እግሩ ከጉልበቱ በታች ያለው ቀኝ አይኑ ፈሷል ጆሮ የመስማት አቅም ተዳክሟል ›› ገፅ 83
ይህ በጦርነቱ ጉዳት ያጋጠመው ወታደር ታሪክ በማድረግ ሲሆን ወታደሩ ለእለት ጉርስ እያለ ቢለምንም ቸር የነበረው የመብራት ህዝብ በጦርነተ ሳቢያ በድህነት እጅ ከወርች በመያዙ የእለት ጉርሱ ፈተና ሲሆንበት ያሳየናል ከዚህ ባለፈ በጦርነት ሰመጣ የማይነካው ቤተሰብ አለመኖሩንም እንዲህ ብሎ ያስቀምጠዋል
‹‹ የጦርነት እሳት ያልጎነኘው ቤተሰብ ለማግኘት ከሞመከር ይልቅ ፀሀይ በምእራብ በኩል ወጥታ በምስራቅ በኩል እንድትጠልቅ መመኘቱ የተሻለ ውጤት አለው
ወልዶ ለጦርነት
ኖር ለጦርነት
ሰርቶ ለጦርነት›› ገፅ 89
ጦርነት በተንሰራፋበት ልጅ ቢወለድ ለጦርነት፥ ሰርቶ ጥሪት ቢያዝ ለጦር መሳርያ መግዣ ነው ይላል ደራሲው። ይህ በፊት ባለጉልበት እና መሳርያ ታጣቂ ወታደር በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ጉልበቱ አጉድልታል። በዚህም ጦርነት ሰለማዊ ዜጋን ብቻ ሳይሆን ተፈላሚ ሀይሎችንም ድል ፊታቸውን ስታዞር ዳፋው ለነሱም መሆኑን ለማሳየት ሞክሯል ፡፡
የሁለት ህይወቶች ወግ
‹‹ በምድር የቆየችበት እድሜ ሶስት አስርተ የሚሞላ ባሆንም የእድሜዋን እጥፍ የኖረች ይመስል ተጎሳቁላለች ቀይ መልኳ ወደ ጥቁረት ጉዞ ጀምሯል ከፊቷ ማዲያት ያልጎበኘውን ስፍራ ማግኘት አይቻልም ›› ገፅ 115
ይህን የሚላት ህይወት ስለምትባል እና በጦርነቱ ከሴተነቷ ጋር ተዳምሮ ስለፈተናት እንስት ነው
‹‹የእርሰ በእርስ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ የሀገሪቱ ህግ ህገ ወጥነት እንዳይሆን አስቀርቷታል የሐይማኖት አባቶች ጆሮ ሲነፈጉ የእምነት ተቋማት አቅም ሰያጡ የመብራት ከተማ አባቶች መደመጥ፤የማይችሉ ሲሆኑ ሸንጎ መዘባበቻ ሲደረግ ስነምግባር ለጉልበት ሲገብር ህግ ለአመፅ ሲሰግድ አየን ››ገፅ 117
ጦርነት የቅርቡን ሩቅ ያደርጋል። ያለ ሰላም ዘርቶ መቃም ወልዶ መሳም ነግዶ ማትረፍ ፤መገበያየት አስቸጋሪ መሆኑን እያሳየ የጦርነትን አበሳ በዚህች ህይወት ብቻ ማሳየት ያልበቃው ተስፋ አብ ሌላዋን ህይወት ያስቃኘናል ፡፡
‹‹ ህይወት እባላለሁ ኣባቴ›› መላ አካልዋን በመገረም ቃኙት ‹‹ ህይወት ነሽ›› መገረም ፊታቸው ላይ ተጋድሞ አዎን አባቴ ›› ገፅ 122
በማለት ራሷን ያስተዋወቀችው ህይወት ያመጣትን ጉዳይ እንዲህ ትገልፃለች ‹‹ ውጊያው ሁልንም ሰዎች ስላደሀየ ሰዎች ችግራቸውን ለመርታት የተለየ መፍትሄ መፈለግ ጀመሩ ታማኝ ሰዎች ማጭበርበር ሲጀምሩ አየሁ ስርቆትን የሚጠየፉ ለሌብነት ተሽቀዳደሙ ሴትነታቸውን ያከብሩ የነበሩ ገላቸውን ለመሸጥ ፈቀዱ ›› ገጽ 124
ጦርነት የሰርክ ኖሮን ያመሰቃቅላል። ይህን ምስቅልቅል ይህንን ክፍተት ለመጠቀም የወሰነቸው ህይወት፥ ጦርነቱ ባመጣው እድል ተጠቃሚ ሆነች። ኑሮ የከበዳቸውን ቀንና ሌሊቱ አንድ የሆነባቸውን ሴቶች ገላቸውን እንዲሸጡ በማድረግ ዳጎስ ያለ ገንዘብ ብታገኝም የልጇ ከስነ ምግባር ማፈንገጥ እና በአጉል ሱስ መጠመድ መፍትሄ ፍለጋ የመብራት ከተማ ነዋሪ የሆኑት አባት ጋር መፍትሄ ፍላጋ አምርታለች።
ጦርነት በተለይ በታዳጊ ወጣቶች የስነ ምግባር ዝቅጠት የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚኖረው በሁለተኛዋ ህይወት ልጅ አማካኝነት ሊየሳየን ሞክሯል ፡፡
መፍረስና መፍረስ
በዘህ ርእሰ ስር ንፁህ ስለተባለች ገጸ ባህሪ በተለይ የጦሩ አለቃ ባለቤት ስለሆነችው ንፁህ እየነገረን በዛውም ጦርነት ሲመጣ የሹማምንት ቤተሰቦች የተሻለ መኖርያ እና ማረፍያ እንደሚዘጋጅላቸው በአንፃሩ መደዴው ህብረተሰብ ለከፋ ችግር እንደሚተው ያሳየናል ፡፡
ከዚህ ባለፈም የንፁህን የትዳር ፍለጋ ስንክሳር እያዋዛ የተረከበት መንገድ ግሩም ነው
እንደ መውጫ
ከላይ እንደተገለፀው መፅሀፉ ልብ ወለድ ይሁን እንጂ ፥ባለፉት አመታት የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ እንደ ነበረ ሀገር የጦርነትን አስከፊነት በቀላሉ እንድንገነዘብ ለማድረግ፥ አጠር ባለ መልኩ ያስቀመጠበት ሂደት መልካም ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ከዚህ ባለፈ በመፅሀፉ መቻል ስለተባው ገፀ ባህሪ ያሰፈረው እንዲሁም ስለ ምናባዊ ከተማዋ መብራት ገለፃ በማድረግ የጦርነቱን ምድር በአግባቡ እንድናውቅ ሲያስችል፥ ለጦርነቱ መነሻ ስለሆኑት ፕሬዘዳንት እና ጄነራል የመፅሀፉ ርአስ ስለሆነቸው ዙፋን የተለያዩ የስነ ፅሁፍ ቴከኒኮችን በመጠቀም... አሰቃቂውን የጦርነት ሁኔታ በሌሎች የህወይት ቅመሞች እያዋዛ አሳይቶናል።
መፅሀፉ እንከን የለሽ ነው ማለት አይደለም። ሌሎች የስነ ፅሁፍ ባለሙያዎች የሚሰጡት ሂስ እንደተጠበቀ ሆኖ ፥ የቃላት ግድፈቶች ታርመው ለቀጣይ ህትመት ቢዘጋጅ እያልኩ በዚህ ላብቃ ፡፡
ማስታወሻ፥
የዙፋን ልፊያ ነገ 11 ሰአት በወመዘክር ይመረቃል
❤1
