Telegram Web Link
ለንግድ ሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ

📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት

👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ  ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።

ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35

Telegram username
@Ruthtemersales

Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
Forwarded from YeneTube
ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንደስትሪ ኃ. የተ. የግ. ማኅበር

ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንደስትሪ ኃ. የተ. የግ. ማኅበር፣ ለደንበኞቹ ካዘጋጃቸው ሽልማቶች ውስጥ ስድስተኛ የሆነው ቢዋይዲ የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ፣ በጅማ ከተማ ለዕድለኛ ወጥቷል፡፡

በጅማ ቆጬ ሰፈር ነዋሪ የሆኑት ዕድለኛው አሸናፊ አቶ ዮሐንስ ካሳ፣ ሽልማታቸውን ሰኔ 21 ቀን 2017ዓ.ም. በጅማ ከተማ በተከናወነ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡

ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንደስትሪ ኃ. የተ. የግ. ማኅበር፣ የፔፕሲ፣ ሚሪንዳ እና ሰቨን አፕ ምርቶቹን በድጋሚ ለገበያ ካቀረበ በኋላ የተለያዩ እና በርካታ አጓጊ ሽልማቶችን ለደንበኞቹ አዘጋጅቶ ዕድለኛ አሸናፊዎችን በአስገራሚና አጓጊ ሽልማቶች በማንበሽበሽ ላይ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ዕድሜያችን እየጨመረ ሲሄድ ጊዜ እየፈጠነ የሚመስለን ለምንድነው?

ለምንድነው በዕድሜ እየገፋን ስንሄድ ጊዜ የሚበር የሚመስለን? ልጅ እያለን የክረምት ዕረፍት ዘላለም ነበር የሚመስለን። አሁን ላይ ግን ዓመታት በቅጽበት የሚያልፉ ይመስላል። እዚህ ጋር ምን እየሆነ ነው? ይህ የእርስዎ ብቻ የሚሰማዎት ሳይሆን ሳይንሳዊ ማብራሪያ ያለው ነገር ነው።

ለዚህ እና ለሌሎች ጊዜን የተመለከቱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠንበትን ዝግጅት እንዲከታተሉ ጋበዝንዎ። መሰል ዝግጅቶችን ለመከታተል ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ።

https://youtu.be/K_JqeH94iBo
Forwarded from YeneTube
🎨 Graphic Design Course Registration Now Open!
Unlock your creativity and learn the skills to design stunning visuals for social media, branding, and more.
Beginner-friendly
Hands-on projects
Certificate included

📅 Limited seats – Register today!

Call us:
          ☎️
0989747878
0799331774

@merahyan
Forwarded from YeneTube
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ምሽት አይበግረንም!

ለሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት

👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።

ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35

Telegram username
@Ruthtemersales

Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
Forwarded from YeneTube
አቅመ ደካማወችን ሀረጋውያኖችን በነፃ

https://vm.tiktok.com/ZMSayMdXa
በተለያየ የጤና ችግር የሚሰቃዩትን እየ ፈወሰ
ደስታቸውን እየመለሰ የሚገኘውን የህክምና ተቋም https://vm.tiktok.com/ZMSay8eV2/
ሰወች እንዴት እንደተፈወሱ ሲመሰክሩ እንስማ እንይ ቻናሉን እንቀላቀል
https://vm.tiktok.com/ZMSaDEhoN

በስጋውይም ሆነ በመንፈስ ደውየ ከተቸገሩ መተው በመመርመር ይታከሙ ይፈወሱ
  44ት አይነት በሽታወችን እየፈወስን እንገኛለን
  አድራሻ አዲስ አበባ አየርጤና ወደካራ ናትራን ኩፓንያ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ባህርዳር ዲያስፖራ በአሮጌው አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት
☎️ 0917040506
☎️0912718883
ይደውሉ ይምጡ ይታከሙ ይፈወሱ ይመስክሩ
Forwarded from YeneTube
Ethiopian Building Code Standards
Private Sector Engagement in Code Revision: Final Week – Week 4 Sessions


We're closing out our 14-part expert-led workshop series with two crucial technical sessions in Week 4:

🧱 Concrete Design & Specifications
📏 Technical Specs & Measurement Methods


📅 Tuesday, June 24, 2025
📍 The Urban Center, Addis Ababa
🖥 Live on TUC Facebook page & Google Meet (link shared 30 min before each session)
☕️ Free sessions with refreshments

📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7

🔗 Let’s finish strong, join the conversation, contribute your perspective, and help shape Ethiopia’s future building code.

Many thanks to all our incredible partners for making this journey possible!

#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #EngineeringEthiopia #ConstructionStandards #UrbanDevelopment #ProfessionalEngagement
ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ኤክስፖርት ፕሮጀክት ሰረዘች!

👉 በምትኩ የማዕድን ሚኒስትር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ዉስጥ ፍጆታ ለመጠቀም የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና ነዉ

ኢትዮጵያ በኦጋዴን ክልል የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ ፕሮጀክት የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መዘግየትን ዋቢ በማድረግ እንደሰረዘች አስታውቃለች። በምትኩ፣ የማዕድን ሚኒስቴር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ውስጥ ፍጆታ፣ በተለይም ማዳበሪያ ለማምረትና ኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና መሆኑን ገልጿል።

የማዕድን ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያ በተለይም በኦጋዴን ተፋሰስ፣ በካሉብና ሂላላ አካባቢዎች ከፍተኛ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት ሲሆን፣ ይህም ከ50 ዓመታት በላይ ለሚሆን ጊዜ ማዳበሪያ ለማምረት፣ ኃይል ለማመንጨትና ለተለያዩ የነዳጅ ምርቶች ለማገልገል የሚያስችል እንደሆነ ቢገመትም፣ እስካሁን በጥልቀት አልተጠናም።

የጅቡቲ የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት መሰረዝ
በ2022፣ ከኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ አውጥቶ በ767 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው የቧንቧ መስመር ወደ ጅቡቲ በመላክ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ታቅዶ የነበረው ፕሮጀክት መሰረዙ ተገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ!

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በሁሉም የመፈተኛ ማዕከላት መሰጠት መጀመሩን፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ማጠናቀቂያ ፈተናው በኦንላይን እና በወረቅት በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው ዕለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ጀምሯል።

በዚህም መሠረት ዘንድሮው በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ በአጠቃላይ 608 ሺሕ 588 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የተገለጸ ሲሆን፤ 140 ሺሕ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን እንሚወሰዱ ተመላክቷል፡፡

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና በአራት ዙሮች የሚሰጥ ሲሆን፤ ከሰኔ 23 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡

በዚህ መሠረት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 23 እስከ 30 ድረስ እንዲሁም፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 1 እስከ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
በመንግስት ግዥ ሂደት ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች የይግባኝ ዉሳኔ ቢያገኙም ዉሳኔዉ ተፈፃሚ እየሆነ አይደለም ተባለ!

አንዳንድ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በይግባኝ ቦርዱ የሚሰጣቸዉን የይግባኝ ዉሳኔ እንደማይተገብሩ ተገልፆል።የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን በበጀት አመቱ 148 ይግባኝ እንደቀረበ አስታዉቋል።

ከቀረቡት ዉስጥ መረጃ ተሟልቶ ለቀረቡ ምርመራ በማድረግ ለ 142 የይግባኝ ጥያቄዎች ዉሳኔ መሰጠቱን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ተናግረዋል።የይግባኝ ጥያቄዉ በግዥ አፈፃፀም እና ንብረት ሽያጭ ላይ የመንግሥት መስሪያ ቤቱ የሕግ ጥሰት አለበት ብሎ የሚያምን ተወዳዳሪ ወይም ተጫራች እንዲመረመርለት የሚያቀርበዉ ቅሬታ ነዉ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሆኖም የቦርዱን የይግባኝ ዉሳኔ ተቀበሎ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳሉ ገልፀዋል።መስሪያ ቤቶቹ የይግባኝ ቦርዱ የተቋቋመዉ በአዋጅ እንደመሆኑ የተሰጠዉን ዉሳኔ መቀበል ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።

አያይዘዉም በይግባኝ የተሰጡ ዉሳኔዎች አተገባበር ላይ በልዩ ሁኔታ ኦዲት ተደርጎ ሪፖርት እንዲወጣ ለማድረግ መታሰቡንም ጠቁመዋል።የመንግስት ግዢ እና ንብረት አስተዳደር በህጉ መሠረት መከወኑን ለመለየት 62 ተቋማት ላይ የህጋዊነት ኦዲት መደረጉን የመንግስት ግዢ እና ንብረት ባለስልጣን አሳዉቋል።ባለስልጣኑ የበጀት አመቱን ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት በ 16 የመንግስት ተቋማት ላይ የኦዲት ጥቆማ እንደቀረበለት ሰምተናል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የመንግስታቱ ድርጅት በአማራ ክልል የረድኤት ሰራተኛ መገደሏን ተከትሎ ድርጊቱን አወገዘ፣ የረድኤት ድርጅት ሰራተኞች ከለላ እንዲሰጣቸው ጠይቋል!

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን “አንጎት” ወረዳ “በመንግስት ሃይሎች እና በአከባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መካከል” ተከስቶ በነበረው ግጭት በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስላ የነበረች የረድኤት ድርጅት ሰራተኛ ማህሌት ስጦታው አበራ መሞቷን አስታውቋል፤ ድርጊቱንም አውግዟል።

የማስተባበሪያ ቢሮው ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማህሌት “በተኩስ ልውውጡ ጉዳት የደረሰባት በአከባቢው የእርዳታ እህል አቅርቦት የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች በተመለከተ መረጃ እያሰባሰበች፣ በስራ ላይ በነበረችበት ወቅት ነው” ብሏል።

ሃላፊዋ አቢባቶ ዋነ-ፎል ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ባልደረቦቿ ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ “የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን የማስተላልፈው ለሟች ቤተሰብ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ የሰብአዊ ረድኤት ሰራተኞች ነው” ሲሉ ገልጸዋል፤ “ንጹሃንን እና ለተቸገሩ ሰዎች እርዳታ ለማቅረብ የሚጥሩ ሰራተኞችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሁሉም እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል ብለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
ቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ተጨማሪ ሁለት አባላቱ መታሰራቸውን አስታወቀ!

-ክልሉ በበኩሉ በፖለቲካ ምክንያት የታሰረ ሰው የለም ሲል አስተባብሏል

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦዴፓ) ሁለት ተጨማሪ አባላቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታወቀ፤ በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ኧርገታ ወርቁ የተባሉ በቡለን ወረዳ የፓርቲው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እና አቶ ታምራት ጉዴሶ የተባሉ የፓርቲው አባል መሆናቸው ተገልጿል።

"በዚህ ወንጀል ተብሎ የተጠረጠሩበት የደረሳቸው የወንጀል ክስ የለም" ያሉት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የፓርቲው አመራር አክለውም የፓርቲው አባል በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ለእስር ተዳርገዋል ሲሉ ገልጸዋል። በክልሉ በተለይም በቡለን ወረዳ በፓርቲያችን አባላቶች ላይ እስር እና ወከባ ቀጥሏል ያሉት አመራሩ "ይህም ለቀጣዩ አገር አቀፍ ምርጫ በቂ ዝግጅት እንዳናደርግ የታለመ ነው" ሲሉ አመልክተዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የጠየቅናቸው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰላም ግንባታና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ቢንያም መንገሻ "በክልሉ እስከአሁን በፖለቲካ ምክንያት የታሰረ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራር የለም" ሲሉ አስተባብለዋል።

“ማንኛውም ግለሰብ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣን ይሁን አልያም የተፎካካሪ ፓርቲ አመራር፣ የወንጀል ድርጊቶች ላይ ተሳታፊ ሆኖ የተገኘ ግለሰብ ላይ የክልሉ መንግስት ህግ የማስከበር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አጽንኦት ሰጥተዋል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
ሚኒስትሩ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ ተባለ!

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸው በማህበራዊ ሚዲያ መረጃ ሲሰራጭ ሰንብቷል፡፡ ሚኒስትር መ/ቤቱ በጉዳዩ ላይ በሰጠው መግለጫ ሚኒስትሩ የመጂና አደጋ እንደደረሰባቸው አረጋግጧል፡፡

ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ ከምሽቱ 1:00 አካባቢ መኖሪያ ቤታቸው የሚገኝበት ካርል አደባባይ ላይ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ደርሶባቸው ነበር ያለው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፤ በእለቱ ሚኒስትሩ ወደ ሆስፒታል አምርተው በቂ ህክምና እንዳገኙና አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡

ሚኒስትሩ ከበቂ የጤና እረፍት ቆይታ በኋላ ወደ መደበኛ ስራ ገበታቸው እንደሚመለሱም መግለጫው ጠቁሟል፡፡"እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሁነቱን ለርካሽ ፖለቲካዊ ግብ ለመጠቀም ከአውድ ውጪ ባልተረጋገጠ መረጃና በአሉባልታ የሚናፈሰው የማህበራዊ ሚዲያ ዘገባ የተሳሳተና መሰረተቢስ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ሚኒስቴር አበክሮ ለመግለጽ ይወዳል" ብሏል፤ ሚኒስቴር መ/ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መግለጫ፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ተወሰነ!

ሦስተኛ ስብሰባውን ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ያካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወሰነ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ዛሬ ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውስኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው።

"አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል።

ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳብ ሌሎች ለብሔራዊ ባንክ ቦርድ ቀርቦ መጽደቁንም መግለጫው አመልክቷል።ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ በሚያስገድደው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 2022 ጀምሮ ከአጠቃላይ ዓመታዊ ብድራቸው አምስት በመቶ የሚሆነውን ለዚህ የቦንድ ግዥ ሲያውሉ ቆይተዋል። በዚህ መመሪያ መሠረት የገዙት ቦንድ የሚመለሰው (ለቦንድ ግዢ ያዋሉት ገንዘብ ተመላሽ የሚደረግላቸው) ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሆን ፣ ባንኮቹ መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ወር አንስቶ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 30 ቀን 2024 ድረስ የገዙት የቦንድ መጠን 94 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት ዕዳ መግለጫ ያመለክታል።

በገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ያሳለፈው ሌላኛው ውሳኔ በባንኮች ላይ የተጣለውን የብድር ዕቀባ የተመለከተ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ጣሪያ እስከ መጪው መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲቀጠል ኮሚቴው ወስኗል።ለዚህም የሰጠው ምክንያት አሁን ላይ የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ እየተስተዋለ ቢሆንም ይህንን ማስቀጠል አስፈላጊ በመሆኑ በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕድገት ጣሪያ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ የሚገልጽ ነው።

Via Reporter
@YeneTube @FikerAssefa
"በ11 ወራት 815 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ሰበሰብኩ" -የገቢዎች ሚኒስቴር

የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡት ሪፖርት በበጀት ዓመቱ ከሀገር ውስጥ ታክስና ከወጪ ንግድ ቀረጥና ታክስ ከ900 ቢሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ባለፉት 11 ወራት 815 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል ፡፡

በወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ ላይ በተደረገው የቁጥጥር ስራ 19 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ፡፡

የሥነ ምግባር ጉድለት የታየባቸው 405 ሰራተኞች ከጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ ስንብት የሚደርስ ርምጃ ከመውሰድ ባለፈ በወንጀል እንዲጠየቁ መደረጉን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
2025/07/01 11:11:41
Back to Top
HTML Embed Code: