Telegram Web Link
መልካምነት ማለት
===
ፍሬው የማይደርቅ ፣ቅጠሉ የማይጠወልግ፣ በቦታና በጊዜ የማይገደብ ከፈጣሪ የተሰጠ ልዩ ስጦታ ሲሆን፣
==
ይሄን የተቸሩ ደጋግ ሰዎች ደግሞ ፊታቸው በደግነት የሚያበራ፣ልባቸው በእዝነት የተሞላ፣ ዛሬ  ከመሬት በላይ ሁነው_ ሰላም ያለበት ረ ሃ የሆነ Life የሚኖሩ ሲሆን ፣
ነገ ደግሞ ከሰዎች ተለይተው በድቅድቅ ጨለማ ፣በሰውነት ልክ በተቆፈረች ቀብር፣ዙሪያዋ ጨለማ ፣መብራት የለ ፣ድምፅ አይሰማ ለዚህ ከባድ ቀን ዛሬ ላይ መልካም ስራን ይሰራሉ!
"ብልጥ ማለት ከሞት በኃላ ላለው ህይወቱ ዛሬ ላይ መልካም ስራን የሰራ ነው..."
ነገ የቂያማ ቀን ደግሞ ሰው ሁሉ ነፍሴ ነፍሴ ሲል እነሱ በአረህማን አርሽ ጥላ ስር የሚጠለሉ መልካም የአላህ ባሮች ናቸው።
በየትኛውም ክፍለ ዘመናት እንደ በራሪ ስማቸውና ዝናቸው ከፍ ብሎ በሰማይ በወርቅ ብእር የሚፃፍ፣
ዘመን ተሻጋሪ ፣ድንበር የማይገድባቸው ፣ውስጣቸው በቅንነት የተሞላ ፣ሀሳባቸው ወገኔ ተቸገረ፣ተራበ፣ተጠማ፣ታመመ ብለው ሀሳብ ጭንቀት የሚይዛቸው የምድራችን የተከበሩ ፍጡሮች ናቸው።
ምድር በእነሱ ሰበብ ታብባለች፣ቡቃያ ታበቅላለች 
ሰማይም ዝናብን ታዘንባለች፣

የዚህ ሚስጥሩ ለሚስኪኖች ለደሃዎች በሚችሉት ሮጥ ሮጥ በማለታቸው ነው።


መልካምነት ዘመን የማይሽረው፣ ጊዜ የማይቀይረው ፣ድንብር የማይገድበው ፣እምነት ፣ብሄር ፣ዘር ፣ቀለም ፣ቋንቋ የማይለይ ልባዊ ስጦታ ነው!!
ደግነት ማለት የአላህን እዝነት የሚያወርድ፣ቁጣና ቅጣቱን የሚመልስ ስራ ነው!
እድለኞች እንጂ ማንም ሰው ሊቸረው አይችልም!

ስለ ነገ ዛሬ ላይ መልካም እንሁን እላለሁ!👌
👍72
የቀረበ ሁሉ ወዳጅ አይደለም
     ከሚቀርቡን ሰዎች ውስጥ ጥቂቶች ብቻ ናቸው በመልካም ንያ መልካም የሚያስተምሩን እና የሚጠቅሙን

ብዙዎች ግን ሊፈትኑን ሊያጠፉን እና ሊያዳክሙን ይቀርቡናል

ከሚቀርቡን ሰዎች ውስጥ
          -ኢማናችንን  የሚያዳክሙ
          -ቀልባችንን የሚያቆሹ
          -ብራችንን የሚዘርፉ
እናም  -ልባችን የሚሰብሩ አስመሳዮች
          -ይኖራሉ
ለሁሉም ነገር ራስን መጠበቅ አስፈላጊ ነው  የቀረበን ሁሉ ወዳጅ አይደለም !!
         
ስለ ህመማችን አልቅሰን የምንነግረው   አላህ ምስጋና ይገባው እሱ በርግጥም
       ትክክለኛ ፈዋሽ ነው
👍4
መስጂዶች በኳስ የተነሳ ባዶ መሆን የለባቸውም

فَوَيْلٌ لِّلْمُصَلِّينَ

ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡

الَّذِينَ هُمْ عَن صَلَاتِهِمْ سَاهُونَ

ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡
10👍3
"ለልብህ በሰዎች ሙገሳ አንዲሞቀው እና በሰዎች ወቀሳ እንዲሰበር አትፍቀድለት!!"

ኢማም አል-ገዛሊ
👍72
...
አላህ ብቻ ከአንተ ጋር ይሁን እንጂ
ፊትህን ማየት የጠሉ ሁሉ ጀርባህን
ማየት ይናፍቃሉ!

በርታ በል ሀቢቢ👌
👍6🔥6👌1
የህይውት  ትልቁ መከራ  ሞት ሳይሆን

በሕይወት  እያለ  አላህን  የመፍራት

ስሜት  ከውስጣችን  ሲሞት ነወ  አላህ ይጠብቅን  🤲
10👍2
የዓለማችን ውዱ ዱቄት የሚገኘው በ ጋዛ ነው።
ክፍያውም የሰው ልጅ ህይወት ነው።💔

አንድ አባት አንዲትን ከረጢት ዱቄት ለማግኘት ከ አንድ በላይ ልጆቹን ሊሰዋ ይችላል።💔

የሞተ ልጁን በአንድ ትካሻው፤ በደም የተጨማለቀ ዱቄቱን በአንድ ትካሻው ለቀሩት ቤተሰቦቹ ይዟት ይሄዳል😭💔


እኛ ግን ማድረግ የምንችለው ዱዓ ማድረግ ብቻ ነው። በዱዓችን አንርሳቸው😭💔
💔151👍1
☀️ልትተኛ ነው??

እንግዲያውስ………
  ጠዋት ፍራሽህ ላይ ሆነህ የፈጅር አላርም ይቀሰቅስሃል??
ወይስ ቀብርህ ውስጥ ሆነህ ነኪርና ሙንከር ይቀሰቅሱሃል? አታውቅም።

እናም፦
  ከስህተቶችህ ሁሉ #ተውበት አድርገህ ተኛ!!
👍113
ከነዚህ አራት በሽታዎች አንድ ሰው ራሱን ነጻ ካወጣ፣ በርግጥም ድኗል

ቅናት፣ እዩልኝ፣ በራስ መደነቅ፣ ሰውን በንቀት አይን ማየት።

ኢማሙ ነወዊይ رحمه الله
10👍1
ረሱል ((ሰ.ዐ.ወ)) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ثَلاثٌ مَن كُنَّ فيه وجَدَ حَلاوَةَ الإيمانِ: أنْ يَكونَ اللَّهُ ورَسولُهُ أحَبَّ إلَيْهِ ممّا سِواهُما، وأَنْ يُحِبَّ المَرْءَ لا يُحِبُّهُ إلّا لِلَّهِ، وأَنْ يَكْرَهَ أنْ يَعُودَ في الكُفْرِ كما يَكْرَهُ أنْ يُقْذَفَ في النّارِ﴾

“ሶስት ነገሮች በሱ ላይ ያለበት ሰው የኢማንን ጥፍጥና አግኝቷል። አላህና መልዕክተኛውን ከማንም በላይ እርሱ ዘንድ የተወደዱ ሊሆኑ። አንድን ሰው ሲወድ ለአላህ ብሎ እንጂ አለመውደድ። ወደ ክህደት (ኩፍር) መመለስን ወደ እሳት መግባትን እንደሚጠላ ሊጠላ ነው።”

📚 ቡኻሪ ዘግበውታል፡ 6941
5👍1
⭐️ቆንጆ ቤት ስላለህ ሰላም አታገኝም።

⭐️ምቹ መኪና ስላለህ ሰላም አታገኝም።

⭐️ብዙ ጓደኛ ስላለህ ሰላም አታገኝም።

⭐️ቀንጆ ልብስ ስለለበስክ ሰላም አታገኝም።

⭐️ብዙ ብር ስላለህ ሰላም አታገኝም።

⚡️⚡️ሰላም የሚገኘውም ከአንድ ፈጣሪ አላህን በመገዛት ብቻ ነው።

አለም ከምትሠጠን ደስታ ይልቅ ፈጣሪያችን የሚሰጠው ደስታ ይበልጣል።

ፈጣሪያችን ለሁላችንም የደስታ ህይወት ይስጠን አሚን ያረብ !
7👍2
​"አላህﷻ ከአንተ ጋር በሚያደርገው ነገር ሁሉ ተደሰት። በእርግጥም እሱ ሊሰጥህ እንጂ አይከለክልህም። ሊጠብቅህ እና ሊያድንህ እንጂ አይፈትንህም። ሊፈውስህ ቢሆን እንጂ በሽታን አያስነካህም ።”

ኢብኑል ቀይም አልጀውዚይ
መዳሪጅ አስ-ሳሊኪን [2/208]
👍6
🌸አዝካሩል መሳእ🌺

بِسمِ اللهِ الَّذِي لَا يَضُرُّ مَعَ اسْمِهِ شَيءٌ في الأرْضِ وَلَا في السَّمَاءِ وَهـوَ السَّمِيعُ العَلِيمُ [ثَلاثَ مَرَّاتٍ]

በአላህ ስም፣ እርሱ አላህ ከስሙ ጋር በስሙ የተጠበቁትን በሰማይም በምድርም ምንም ነገር አይጎዳቸውም፡፡ እርሱ ሰሚም አዋቂም ነው፡፡ (ሦስት ጊዜ)

ቢስሚልላሂል ለዚ ላየዱርሩ መዐኢስሚሂ ሸይኡን ፊል አርዲ ወላ ፊስሰማኢ ወሁወስሰሚዑል ዓሊይም

رَضِيْتُ بِاللهِ رَبًّا، وَبِالإسْلامِ دِيْناً، وَبِمُحَمَّدٍ نَبِيًّا [ثَلاثَ مَرَّاتٍ]

በአላህ፣ አምላክነት በኢስላም ሀይማኖትና በሙሀመድ ነብይነት ረክቻለሁ፡፡ (ሦስት ጊዜ)

ረዲይቱ ቢልላሂ ረብበን፣ ወቢል ኢስላሚ ዲነን፣ ወቢ ሙሀመዲን ነቢየን (3X)
5👍2
كُلُّ نَفْسٍ ذَائِقَةُ الْمَوْتِ ۗ وَإِنَّمَا تُوَفَّوْنَ أُجُورَكُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۖ فَمَن زُحْزِحَ عَنِ النَّارِ وَأُدْخِلَ الْجَنَّةَ فَقَدْ فَازَ ۗ وَمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا مَتَاعُ الْغُرُورِ

ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት፡፡ ምንዳዎቻችሁንም የምትሞሉት በትንሣኤ ቀን ብቻ ነው፡፡ ከእሳትም የተራቀና ገነትን የተገባ ሰው በእርግጥ ምኞቱን አገኘ፡፡ ቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ መሳሪያ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
👍5
"ቀልብህ ውስጥ ያለውን በሽታ በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ ዶክተሮች እንዲያስወግዱልህ ብትሯሯጥ እነደ ቁርኣን ያለ ፈውስ በፍፁም አታገኝም።"
【ሸይኽ ዑሰይሚን(ረሂመሁላህ)】
6👍1
ከምታስመስለው መላዕክትነት ይልቅ የዕውነት የምትተገብረው ሰይጣንነት ይሻላል ። አትመለከትም , ሙናፊቆች የማስመሰል ሸሃዳ ይይዛሉ ፣ ይሰግዳሉ ፣ ይፆማሉ ፣ ቁርዐን ይቀራሉ ፣ ሶደቃም ይሰጣሉ ፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ በአስመሳይነት ማልያ የተጫወቱት ነውና ፉርሽ ይደረግባቸዋል ፡፡ በአኺራም , ዱንያ ላይ  አሏህን በግልፅ  ሲክዱ  በአደባባይም ኢስላምን የሚፃረር ተግባራቶችን ሲፈፅሙ ከነበሩ ካፊሮች የበለጠ ቅጣት ሙናፊቆች ይቀጣሉ  ፡፡

إِنَّ ٱلْمُنَٰفِقِينَ فِى ٱلدَّرْكِ ٱلْأَسْفَلِ مِنَ ٱلنَّارِ وَلَن تَجِدَ لَهُمْ نَصِيرًا
መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡ ለእነሱም ረዳትን አታገኝላቸውም ፡፡
[{ ሱረቱ አል ኒሳዕ 145 }]

የምትናገረው ንግግር ኖረህ አሳየን ተግባራቹ ሌላ የምትናገሩት ሌላ በተለይ ቲክቶክ መንደር ላይ ነገ አሏህ ፊት መቆም አለና... ሰዎች ስላጨበጨቡልህ አላህ ዘንድ ዋስትና ይሆንሃል ማለት አይደለም ። ሰዎች ክህደት ፣ ወንጀልን በይፋ መስራት ፣ ክፋትና ሰይጣንነት መልካም ነው እያልኩ አይደለም ፡፡ ነገር ግን አስመሳይነት ከነዚህም ይባሳልና እንጠንቀቀው ! አላህ ይጠብቀን !
5👍1
ኢብኑል ቀይም አል-ጀውዚያ እንዲህ ይላሉ:-

"ከድንቁርና ሁሉ ክፉ፣ ከበደልም ሁሉ ከባዱ ለራስህ በሰዎች ዘንድ ሙገሳን እና አድናቆትን እየፈለክ፣ ያንተ ልብ ግን አላህን ከማሞገስና ከማተለቅ ሲዘናጋ ነው።"
📚በዳኢዑል ፈዋኢድ ገፅ 272]
👍7
ርምጃዎች ሁሉ በእሾህ ላይ ሲሆኑ ህመም አላቸው ...መንገዱ በረዘመ ቁጥር ህመሙ እየጨመረ ..ስቃዩ እየበረታ ይሄዳል ። ድነትን ስንሻ...ማገገም ሲያሰኘን ያለን አማራጭ ከእሾሁ ንጣፍ መንገዳችንን መቀየስ ነው ።
የአሁን ስቃያችን ሰበብ ሁሉ የእሳቤ መንገዳችን ላይ ያለው እሾህ ነው ...የዚህ ሁሉ ስቃይ የግባችን መንገድ መበላሸት ነው ። ከአላህ የራቀች ነፍስ መንገዷ ተቀይሯል...ወደአላህ የማይወስድ መንገድ ሁሉ አሳማሚ ...ከሱ የሚያርቅ መንገድ ሁሉ የሚያደማ...ከሱ የራቀ መንገድ ሁሉ አደጋ ነው ።
ከአላህ በራቅን ቅፅበት ...የልብ ምታችን ከዚችኛው አለም ጋር የተቋጠረች ቀን ...መኖራችን ለሰው ብቻ የሆነ ለት የስቃይ መንገዳችንን ሪባን ቆርጠናል ።

አንቀየስም ?
5👍1
ጥበብ ማለት ምን መናገርና ምን መናገር እንደሌለብህ ፥ መቼ መናገርና መቼ ደግሞ ዝም ማለት እንዳለብህ ለይተህ ማወቅ ነው ፡፡ ብዙ ግንኙነቶች የሚደፈርሱት ብዙ ወዳጅነቶችም የሚፈርሱት በጥበብ ጉድለት ነው ፡፡ 

ሲሆን ሲሆን ተናግረህ ከምታስቀይም ዝም ብለህ ቢከፉብህ ይሻላል ፡፡ ነገር ግን የተሟላ ጥበበኛ መሆን ከትኩረት የዘለለ ብዙ ዋጋ አይጠይቅምና ደንታ ቢሶች አንሁን !
7👍1
ዛሬ ወዳንተ ወሬን ይዞ የመጣ...
ነገ ደግሞ ካንተ ወሬ ይዞ እንደሚሄድ እወቅ

[حسن البصري]
🍓6👍2
2025/10/20 02:22:23
Back to Top
HTML Embed Code: