Telegram Web Link
የ12ኛ ክፍል ፈተና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ108 የማስፈተኛ ጣቢያዎች ሙሉ ለሙሉ በበይነ መረብ በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፈተናው ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ቀደም ሲል ተማሪዎቹ የልምምድ ፈተና እንዲወስዱ መደረጉን እና በቂ ኦረንቴሽን መሰጠቱ እንዲሁም በየመፈተኛ ጣቢያው መሰረተ ልማቶቹን ዝግጁ የማድረግ ስራን ጨምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱ ይታወቃል።

በዛሬው የመጀመሪያ ዙር ፈተና ከ13ሺ በላይ ተማሪዎች በ108 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናውን በበይነ መረብ በመውሰድ ላይ የሚገኙ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዴታ ከወይዘሮ አየለች እሸቴ እና ከምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ዲናኦል ጫላ ጋር በመሆን ፈተናው ከሚሰጥባቸው ጣቢያዎች መካከል አንዱ በሆነው አብረሆት ተገኝተው የፈተናውን አጀማመር በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ መሰጠቱ ተማሪዎቹ ፈተናውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲፈተኑ ከማስቻሉ ባሻገር ከኩረጃ ነጻ የሆነ የፈተና ስርአት እንዲሰፍን የሚያስችል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ጠቁመው ቢሮው ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን ፈተናው ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን በመግለጽ ለተፈታኝ ተማሪዎች የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን የተመደቡ ተማሪዎች ፈተናቸውን የጀመሩ ሲሆን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር የፈተና አጀማመሩን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

በዚህም ለፈተና የሚያግዙ መሰረተ ልማቶቹ መሟላታቸውን ተፈታኞችም በፈተና ቦታቸው ላይ መገኘታቸው ተገልጿል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
ልጇን በሰላም ተገላግላ የ12ኛ ክፍል ፈተናን በመውሰድ ላይ የምትገኝ ተማሪ


ሙስተሪያ ሙሳ ትባላለች፤ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በሚገኘው ጤና ጣቢያ ልጇን በሰላም ተገላግላ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየወሰደች ትገኛለች።

ሙስተሪያ ልጇን በሰላም ከተገላገለች በኋላ አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደምትገኝና ልጇም በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ተማሪ ሙስተሪያ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከግራዋ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣችው፡፡

ለፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲው በገባችበት ወቅት አርብ ምሽት 3 ሰዓት አካባቢ ልጇን በሰላም እንደተገላገለች የምትገልፀው ሙስተሪያ፤ 2.8 ኪ.ግ የምትመዝን ሴት ልጅ በሰላም መገላገሏን ተናግራለች።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በወረቀትና በበይነ መረብ እየተሰጠ የሚገኘውን ፈተና በዛሬው እለት መስጠት ጀምሯል።

በዩኒቨርሲቲው ከተመደቡ 7 ሺህ 29 ተማሪዎች መካከል 4 ሺህ 271 ወንድ እና 2 ሺህ 375 ሴት በድምሩ 6 ሺህ 646 ተማሪዎች ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ።

ለፈተና መጥታ ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ጤና ጣቢያ ውስጥ ልጇን በሰላም የተገላገለች ሙስተሪያም ፈተናውን እየወሰደች ትገኛለች፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
2025/07/05 13:32:36
Back to Top
HTML Embed Code: