በአዲስ አበባ የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ይፋ ይደረጋል።

የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 194 የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠቱ ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ወስኗል።

በከተማ አስተዳደሩ በ2017 ዓ.ም 70,525 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ፈተናን ወስደዋል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ስር በሚገኘው ሃኪም ግዛው ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።

በሆስፒታሉ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶ/ር አዲሱ ግርማ የ38 ዓመቷ እናት የባሶና ወራና ወረዳ መምጣቷን ገልጸው÷ በህክምና ባለሙያዎች በተደረገላት እገዛ አራት ሴት ልጆችን በሰላም መገላገሏን ተናግረዋል፡፡

በሆስፒታሉ ታሪክ አንዲት እናት አራት ልጆችን ስትገላገል ይህ የመጀመሪያው ነው ያሉት ዶ/ር አዲሱ÷ ሁሉም ህጻናት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ህጻናቱ ከ1 ነጥብ 3 ኪሎ ግራም እስከ 1 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም ክብደት እንዳላቸው አብራርተዋል፡፡

እናታቸውም ቀደም ሲል በተለያዩ ጊዜያት የወለዷቸው አራት ወንድ እና ሁለት ሴት በአጠቃላይ ስድስት ልጆች እንዳሏቸው አስታውሰው÷ አሁን ደግሞ አራት ልጆችን በአንድ ጊዜ በመውለዳቸው ደስተኛ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

አቅም ያላቸው በጎ አድራጊዎች ልጆቻቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍ እንዲያደርጉላቸውም ጠይቀዋል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#ማትሪክ_ደርሷል!
አትጨነቁ!
ለዝግጅታችሁ አሪፍ መፍትሄ እኛ ጋር አለ!

#ESSLCE_With_Model_Exams: ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም የማትሪክ ፈተና ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸውና ሙሉ ማብራርያ፣

#Concise_Summary_With_Model_Exams: ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ያሉትን ትምህርቶች አጫጭር ማስታወሻዎች፣

#Ethiopian_New_Curriculum_All_Subjects: በከፍተኛ ጥራት የተቀረጹ  ቪዲዮዎች፣ Virtual Labs  ፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ(AI) የታገዙ ትምህርቶች፣ እና እየተዝናኑ የሚማሩበትን ጌሞችን ያካተተ።

#Short_Notes: ለእያንዳንዱ ትምህርት  ዋና ነጥቦችን አጠቃሎ የያዘ

ይፍጠኑ ይህ እድል እንዳያልጥዎ
www.selectacademy.edu.et በመመዝገብ ዝግጅቶን አሁኑኑ ይጀምሩ።
መልካም እድል ለመላው ተፈታኞች

ለበለጠ መረጃ
+251 926 913 404 | 9521

Join Our Telegram

@Select_Academy
💡Big ideas start small. Like Bill Gates, you can build the next big thing. Ready?

Apply here 👉 https://www.tg-me.com/Founderacademyapplicationguide
ውድ ደንበኞቻችን ከዚህ በታቹ ካሉት website ላይ ማዘዝ የምትፈልጉትን ማንኛውንም እቃ photo  screenshots በinbox  ይላኩልን 

👨‍💻  Aliexpress.com
👨‍💻  Amazon.ae
👨‍💻  shein.com  

በ 7 ቀን ውስጥ ያሉበት ቦታ ድረስ በነፃ እናደርሳለን

📞0946362749( @eden16mg)

join our telegram channel 🫴🫴
https://www.tg-me.com/edmart24
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ12ኛ ክፍል ፈተናን በበይነ መረብ ለሚወስዱ ተማሪዎች  የሙከራ ፈተና ተሰጠ

የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሃገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሰጥ ይታወቃል ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፈተናው  በበይነ መረብ እና በተለመደው የወረቀት ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ በመሆኑም ፈተናቸውን በበይነ መረብ ለሚወስዱ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ሰኔ 17/2017 ዓ.ም እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ይህም ተፈታኞች በበይነ መረብ መፈተንን እንዲለማመዱ እና  ምንም አይነት ችግር ሳይገጥማቸው ፈተናቸውን በተሳካ ሁኔታ ለመውሰድ የሚያችላቸውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲው በበይነ መረብ የመፈተን አቅም ዝግጅት የሚገመገምበት መሆኑ ተገልጿል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።

ከ60 ዓመታት በላይ ዕድሜ በትምህርት ተቋምነት ያስቆጠረው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን ስድስት ምሁራን ሰሞኑን አስመርቋል። ከስድስቱ ተመራቂዎች አንድ ሴት ይገኙበታል።

በመስከረም 2014 ዓ.ም በአዲስ መልክ የተደራጀው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ የመጀመሪያዎቹን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የትምህርት ተመራቂዎች ዘንድሮ ማስመረቁም ተገልጿል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ተማሪ የአፕል የትምህርት መተግበሪያ /Apple Award for Education App/ውድድርን በማሸነፍ ተሸላሚ ሆኗል።
=======================

በዮርክ ዩኒቨርሲቲ የአራተኛ አመት የኮምፒውተር ምህንድስና ተማሪ የሆነው ናሆም ወርቁ ውስን የኢንተርኔት አገልግሎት ያላቸውን ተማሪዎች ለመደገፍ በተዘጋጀው "Access Ed"አክሰስ ኢድ በተሰኘው የትምህርት አፕሊኬሽኑ አለም አቀፍ እውቅናን አትርፏል።

የተማሪ ናሆም ወርቁ የፈጠራ ስራ በቅርቡ የተከበረውን የአፕል ስዊፍት ተማሪዎች ፈተናን በማሸነፍ በአለም ዙሪያ አፕሊኬሽኑን ለአፕል ዋና ስራ አስፈፃሚ ቡድን በካሊፎርኒያ አፕል ፓርክ እንዲያቀርቡ ከተጋበዙት 11 ተማሪዎች መካከል አንዱ አድርጎታል።

በዝግጅቱ ላይም ከአፕል ኩባንያ ሃላፊ ቲም ኩክ ጋር የተገናኘ ሲሆን የፈጠራ ስራውንም አብራርቷል።

ተማሪው ከCP 24 ጋር በነበረው ቆይታ በልጅነቱ በትውልድ አካባቢው የኢንተርኔት እጥረት በተደጋጋሚ ሲያጋጥመው እንደነበር ጠቅሶ ለዚህ ችግር የኢንተርኔት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎችን ችግር ለመቅረፍ ፈጠራው ከኢንተርኔት ውጭ /ከመስመር ውጭ/ የመማሪያ መሳሪያዎችን ለማቅረብ አክሰስ ኢድ የተሰኘውን መተግበርያ ምፍጠሩን ጠቅሷል።

ተማሪ ናሆም ወደ ቴክኖሎጅ ጉዞ የጀመረው የኮረና ወረርሽኝ በተከሰተበት ወቅት እራሱን በተለያዩ አማራጮች በኮዲንግ በማብቃት እንደሆነ ይናገራል።

በዚህ ፈጠራውም በዓለም ዙሪያ ያሉ ተማሪዎች በመጥፎ የኢንተርኔት ግንኙነት ምክንያት የሚመጡትን የትምህርት መሰናክሎች እንዲያሸንፉ ለመርዳት ተስፋ እንዳለው ይናገራል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#ማትሪክ_ደርሷል!
አትጨነቁ!
ለዝግጅታችሁ አሪፍ መፍትሄ እኛ ጋር አለ!

#ESSLCE_With_Model_Exams: ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም የማትሪክ ፈተና ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸውና ሙሉ ማብራርያ፣

#Concise_Summary_With_Model_Exams: ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ያሉትን ትምህርቶች አጫጭር ማስታወሻዎች፣

#Ethiopian_New_Curriculum_All_Subjects: በከፍተኛ ጥራት የተቀረጹ  ቪዲዮዎች፣ Virtual Labs  ፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ(AI) የታገዙ ትምህርቶች፣ እና እየተዝናኑ የሚማሩበትን ጌሞችን ያካተተ።

#Short_Notes: ለእያንዳንዱ ትምህርት  ዋና ነጥቦችን አጠቃሎ የያዘ

ይፍጠኑ ይህ እድል እንዳያልጥዎ
www.selectacademy.edu.et በመመዝገብ ዝግጅቶን አሁኑኑ ይጀምሩ።
መልካም እድል ለመላው ተፈታኞች

ለበለጠ መረጃ
+251 926 913 404 | 9521

Join Our Telegram

@Select_Academy
💡Big ideas start small. Like Bill Gates, you can build the next big thing. Ready?

Apply here 👉 https://www.tg-me.com/Founderacademyapplicationguide
ውድ ደንበኞቻችን ከዚህ በታቹ ካሉት website ላይ ማዘዝ የምትፈልጉትን ማንኛውንም እቃ photo  screenshots በinbox  ይላኩልን 

👨‍💻   Amazon.ae
👨‍💻    Shein.com
👨‍💻    Zara.com
👨‍💻   Noon.com
👨‍💻   Sephora.com

በ 7 ቀን ውስጥ ያሉበት ቦታ ድረስ በነፃ እናደርሳለን

📞0946362749( @eden16mg)

join our telegram channel 🫴🫴
https://www.tg-me.com/edmart24
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ከ15 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት 40.1 ሚሊዮን ብር አለመሰብሰቡ ተገለጸ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2016 የበጀት ዓመት የፋይናንስ ህጋዊነት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት በትላንትናው እለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡

በትምህርት እና ስልጠና ወቅት መሥሪያ ቤቱ ያወጣውን ወጪ በወቅቱ የገበያ ዋጋ ለሥልጠና የላኳቸው ባለሙያዎች በገቡት ውል መሰረት ግዴታቸውን መወጣታቸውን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ 15 ዩኒቨርሲቲዎች እና 109 መምህራን የውል ግዴታቸው ሳይወጡ ዩኒቨርሲቲውን መልቃቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ ተናግረዋል፡፡

በውላቸው መሰረት ተመላሽ ካላደረጉ ተቋማት ውስጥ አርባምንጭ  7.1 ሚሊዮን ብር፤ መቀሌ  6.2 ሚሊዮን ብር ፤ አክሱም 5.5 ሚሊዮን ብር፤ ጂንካ 4.1 ሚሊዮን ብር እና ጅማ ዩንቨርስቲ 3.2 ሚሊዮን ብር ከፍተኛው ድርሻ የያዙ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ከዩንቨርስቲዎቹ ብቻ በድምሩ 40.1 ሚሊዮን ብር ለመንግስት ገቢ እንዳልተደረገ ዋና ኦዲተሯ ጠቁመዋል፡፡

ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሳይፈቀድ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት ውስጥ፤ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ ነው ወ/ሮ መሰረት የገለጹት።
   
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በፌድራል ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ መንግሥት በወሰነው መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች በተመደበላቸው በጀት መሰረት ክፍያ የፈፀሙ መሆኑን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ የጋንቤላ ዩንቨርስቲ፤ የሃሮማያና የሚዛን ቴፒ ዩንቨርስቲ፤ በጠቅላላ  ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ለተፈታኞች የአልጋ እና የምግብ አገልግሎቶች ከዩንቨርስቲዎቹ መደበኛ በጀት ክፍያ የፈፀሙ መሆኑን ዋና ኦዲተሯ አስታውቀዋል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉ የትምህርት ተቋማትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ይፋ አድርጓል።


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።


በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።


በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር አሳውቋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ውጤትን ይፋ አድርጓል።

በአስተዳደሩ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁ ተፈታኞች ውጤታችሁን ከታች ያለውን ሊንክ በመጫንና የመለያ ቁጥራችሁን በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ።

ውጤት ለማየት 👇
https://www.geight.diresrms.org/View_Result/get_result

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
2025/06/26 03:36:53
Back to Top
HTML Embed Code: