ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፧ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም ኣይደለም፡፡
1 የዮሐንስ ወንጌል 4:18
"የእግዚአብሄርን ቃል የወለድሽልን መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ ከዕሴይ ሥር የወጣሽ መዐዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ።"
ቅዱስ ኤፍሬም
ዓለምን የናቀው ማን ነው?

-የከተማ ቤተክርስቲያን አስተዳደር መነኮሳት ደመወዝ 35,000፣ ጳጳሳት 35,000 እስከ 200,000 እንደ ሀገረ ስብከት ብዛት ይወሰናል። በምንኩስና ሕይወት ዓለምን ትቸ እግዚአብሔርን መከተል እፈልጋለሁ ነው። የመነኮሳት የቀን አበል ከ5,000 እስከ 50,000 ብር ነው። ሁሉንም ትቼ ጌታን ተከተልኩት ሰይሆን ሁሉንም ሰብሰቤ ጌታን ተከተልኩት የሚል ይመስለኛል። የመንግሥት የቀን አበል በአማካኝ 350 ብር አካባቢ ነው።

-የአንድ ፕሮፌሰር ደመወዝ በወር net 13,560 ብር ይበልጣል?
የአንድ ሕክምና ዶክተር 11,000 ብር ይበልጣል?
የአንድ መምህር 9,000 ብር ይበልጣል?
በደማቸው ና አፅማቸው ሀገርን የሚጠብቁ ወታደሮች 5,000 እስከ ደረጃቸውን አንፃር የተጨመረ
የሀገር ሰለም የሚጠበቁ ፖሊሶች 5,000 እስከ ደረጃቸውን አንፃር የተጨመረ .....

-ስለዚህ ነገሩ መነኮሳት ሁሉንም ትተው ጌታን ተከተሉት ወይስ ሁሉን ሰብስበው ጌታን ተከተሉት ነው ? አሁን አሁን የቤት ብዛት፣ የሙስና መቃብያ ውድድር ውስጥ የገቡ ብዙዎች ናቸው። ለሥልጣን መሸሚያ በጎሳ፣ በጎጥ ፣ በቡድን፣ በብሔር ተከፋፍሎ ሌላ ፈተነ ቤተክርስቲያን ለይ የጨመሩ ፤ በዚህም ምክንያት ምዕመናን የተረበሹ ነው። እነሱ በተግባር ያስተማሩት በብሔር ኮታ የተሾሙ ይያሉ ሌለውን ይሰድበሉ።

-ዓለማዊ ሥራ በዝቅተኛ ደሞዝ ፣ መነኮሳት ከፍተኛ ደሞዝ መከፈላቸው አይገርምም? የሚቻል ቢሆን የመነኮሳቱ ደመወዝ በተቃራኒው ለዓለማዊ ሠራተኞች መክፈል አይገባም? ለመነኮሳቱ ደግሞ የመንግሥት ሠራተኛ ሐኪም፣ መምህር ... ደመወዝን መክፈል አይሻልም?

-ዓለማዊ ሥራ የተሠማሩ በአንጻራዊነት አሥራት፣ በኩራት፣ መባዕ ... ለእግዚአብሔር ይሰጣሉ። የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እንብዛም አይደለም። ስለዚህ በፈቃድ ባይሆንም ዓለምን የናቀው ማን ነው? ለእኔ በፈቃዳቸው ባይሆንም ዓለምን የናቁት አብዛኛው የመንግሥት ሠራተኛ ነው! የከተማ መነኮሳትን ደመወዝ የሚያውቅ "መመንኮስ አማረኝ" እያሉ ነው አሉ።

በአሁኑ ጊዜ አስተዳደር ሆኖ ለመደብ ግዴታ መነኮሴ ግድ በሆነበት ዘመን ነው። በ2009 ዓ ም የንስሐ አባቴ ቤተሰብ እና ምስቱን ትቶ መነኮሴ ሆነ ። ትንሽ ቆይቶ ቆሞስ ሆኖ እንደ እልሙ አስተዳደር ሆነ። ያትዳር ጉዳይ ፈተና ለይ ወደቀ ። በአስተዳደር ሰበብ ቤተሰብ ተበተነ። ቤተክርስቲያን በብዙ ነገር የተፈታነች ነው።

ትውልድ የጠፋ፣ አገልጋዮች ግን ሌለ ሥራ እና ውድድር ለይ ናቸዉ።
ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ pinned «ገዳማዊ ሕይወት በግብፅ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በየበረሃው ለሚገኙ አበው ሁለት የመንፈሳዊ ሕይወት መመሪያዎች ነበሯቸው ፩ ቅዱሳት መጻሕፍት ፪ ከቀድሞ አበው የሚገኘው መንፈሳዊ ጥበብ ነው፡፡ ይህ መንፈሳዊ ጥበብ ከኑሯቸዉ የሚገኝ ነበር፡፡ በየገዳማቱ ለመንፈሳዊ ተጋድሎ የተሰለፉ የእነዚህን አበው ሕይወትና ንግግር ለማሰባሰብ ብዙ ሊቃውንት በየበረሃው ተጉዘው ነበር፡፡ አባ ሄሮኒመስ ፡ የታሪክ ጸሐፊው…»
እንኳን ለቤዛዊተ ዓለም ድንግል ማርያም በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል ይሁንልን!
እንደ ሰዶምና እንደ ገሞራ ጠፍተን እንዳንቀር እግዚአብሔር ያስቀረልን ንጽሕት ዘር እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ኢሳ.1፥9

በድንግልና ወንድ ልጅ ትወልዳለች ተብሎ ትንቢት የተነገረላትና ለመዳናችን ምልክት ሆና የተጠቀሰችው ድንግል ዛሬ ልደቷ ነው።
ኢሳ.7፥14

የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ የተባለላት እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥27

"መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደ እርስዋ ገብቶ።
ደስ ይበልሽ፥
ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥
ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤
አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ ያላት እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥28

ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ተራቁቶ በነበረበት በዚያ ዘመን፦
በጸጋ እግዚአብሔር ተሞልታ
በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻል የተባለችቱ ድንግል ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥30

"መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥
የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፥
ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል የተባለላት እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡ ሉቃ.1፥35

እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ በማለት ከሰማይ የመጣውንና በእርሷ በኩል ለሰው ልጆች ሊደረግ በእግዚአብሔር የታቀደውን ነገረ ድኅነት አሜን ብላ የተቀበለችቱ ድንግል ዛሬ ልደቷ ነው፡፡ ሉቃ.1፥38

ቅድስት ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ፦
ያለስስት በታላቅ ድምፅም ጮኻ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥
የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው
ብላ የመሰከረችላትና ያመሰገነቻት ድንግል ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥42

"ኤልሳቤጥ ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።"
በማለት ስለ ብፅዕናዋ ያመሰገነቻት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥45

"እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤" ያለችቱ እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡ ሉቃ.1፥48

"ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።"
በማለት ብርቱ የሆነው እርሱ በእርሷ ታላቅ ሥራ እንደ አደረገና ይህንን ያደረገው እርሱ ስሙ ቅዱስ አንደሆነ ለዓለም የመሰከረችቱ ድንግል ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
ሉቃ.1፥49

✿የሚበላውን የሕይወት ምግብ ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿የሚጠጣውን የሕይውት መጠጥ ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿መንፈሳችን የተረጋጋበትን ሰላም ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿ከህመማችን የተፈወስንበትን መድኃኒት ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡
󞠊
✿ከድቅድቅ ጨለማ የወጣንበትን ብርሃን ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿ሕይወታችን ክርስቶስን የወለደችልን እርሷ ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿እግዚአብሔር የመረጣት፤
ትውልድ ሁሉ የሚያመሰግናት
ድንግል ማርያም ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿የነቢያት ትንቢታቸው
የሐዋርያት የስብከታቸው ሞገሥ
የሰማዕታት እናታቸው
የመላእክት እኅታቸው ድንግል ማርያም ዛሬ ልደቷ ነው፡፡

✿ከሰማይ የምትገዝፍ ሁለተኛይቱ ሰማይ ዛሬ ልደቷ ነው።

✿ፀሐያችን ክርስቶስን ያየንባት እውነተኛይቱ ምሥራቅ ዛሬ ልደቷ ነው።

ልዑል እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን ምክንያት ያደረጋት ድንግል ማርያም በ16 ዓ.ዓ ግንቦት 1 ቀን ከኢያቄምና ከሐና እንድትወለድ ፈቃዱ ሆነ፡፡

እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደቷ መታሰብያ ቀን በሰላም አና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን!

መልካም በዓል!!!
╭✥✥✥✥✥✥✥✥✥╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
. አባ ኒቆዲሞስ (ጳጳስ)
. 01/09/2017 ዓ.ም
. ከሕይወት ተራራ ላይ
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰✥✥✥✥✥✥✥✥✥╯
"ከቤተልሔም እስከ ቀራንዮ ነገረ ክርስቶስን ስንሰብክ እመቤታችን የሌለችበት የለም"
አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

"እመቤታችን ሆይ ከፍጡራን ሁሉ ሰይጣን አንቺን ይጠላሻል ካንቺ የተወለደው እራስ እራሱን ብሎ ቀጥቅጦታልና"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ዘተወለድኪ ማርያም እምነ ቡርክት ማኅፀን፥
አድኅንኒ እምነገሮሙ ለሰብአ ዓማፂት ዘመን፥
እለ ይትናገሩ በክልኤ ልሳን።
-----------
ከተባረከች ማኅፀን የተወለድሽ ማርያም ሆይ:- በሁለት ቢላ ከሚበሉ የዐመፃ ዘመን ሰዎች አድኚኝ!

መልክዐ ልደታ
Forwarded from ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት አገው ምድር እንጅባራ ( Felege Hiwot Gubae Bet ) (ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት ዘአዊ)
“ዓለማዊ ትምህርት እና መንፈሳዊ ትምህርት”
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
*
1. 
ምድራዊያን ባለ ሥልጣናት በሚገባ ማገልገል ይችሉ ዘንድ ልጆቻቸውንን የዚህን ዓለም ሳይንሳዊ እውቀት ለማስተማር የማናፈሰው ሃብተ እና ጉልበት የለም፡፡ እኔ ግን እያልኩ ያለውት በእኛ ዘንድ እንደ ቂል ነገር የማይቆጠረውን ስለ ተቀደሰ ሃይማኖት ሊኖር የሚገባውን እውቀት እና የሰማያዊውን ንጉስ አገልግሎት በተመለከተ ነው፡፡ ትርኢቶችን እንዲመለከቱ እናደርጋቸዋለን፤ወደ ቤተክርስትያን ስለ መሄዳቸውና በዚያ በፈሪሃ እግዚአብሔር ስለ መቆማቸው ግን ብዙም ግድ አይሰጠንም፡፡ በምድራዊ የትምህርት ተቋሞቻቸው ውስጥ ምን እንደ ተማሩ እንጠይቃቸዋለን፤በእግዚአብሔር ቤት ስለ ሰሙት ነገርስ ለምን አንጠይቃቸውም?
2. ተገቢውን ምክርና ተግሳጽ ከተናገረ በኋላ ሐዋርያው አባቶችንም እንዲህ በማለት ይናገራቸዋል፡- “እናንተም አባቶች ሆይ፣ ልጆቻቸሁን በጌታ ምክርና በተግሳጽ አሳድጓቸው እንጂ አታስቆጧቸው” ልጅህ ታዛዥ እንዲሆን ትፈልጋለህን? እንዲህ እንዲሆንልህ ከፈለግህ ከመጀመርያው ጀምሮ በጌታ ምክርና ተግሳጽ አሳድገው፡፡ “ለልጅ ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማትና መማር አስፈላጊ ነው? ብለህ አታስብ፤ ከቅዱሳን መጻሕፍት በመጀመሪያ የሚሰማው እናትና አባትህን አክብር የሚለውን ነው፡፡ በዚህም ወላጆችን የሚያከብር ስለሚሆን ዋጋህን ወዲያዉኑ መቀበል ትጀምራለህ፡፡
3. ቅዱሳት መጻሕፍትን መስማት ሲጀምር መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ ለመነኮሳት ነው፤ልጄን መነኩሴ ላደርገው ነውን? አትበል፤አይደለም መነኩሴ መሆን የግድ አያስፈልገውም፡፡ ክርስቲያን አድርገው፤ እንዲህ በጣም ጥሩ የሆነን ነገር ለምን ትፈራዋለህ እያንዳንዱ ሰው የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርት ያውቅ ዘንድ ያስፈልገዋል፤ ይህም ለሕፃናት የበለጠ እውነታነት ያለው ነገር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጡ መለኮታዊ እውነታዎችን ካለማወቃቸው የተነሳ የመመለኪያ ጣኦትና አስደናቂ ታሪክ አላቸው የሚባሉ የዓለማውያን ሰዎችን ነገር ሲሰሙ አሳፋሪ ለሆኑ ሥጋዊ ፍላጎቶቻቸውና ፍትወታቸው የተገዙትንና ምኞቶቻቸውን ያገለገሉትን ሰዎች በእነርሱ ዘንድ እንደ ጀግኖች እና ታላላቅ ሰዎች አድርገው ያዩዋቸዋል፡፡ ስለዚህም አእምሮን ለሚያቆሽሹና ሕሊናን ለሚያበላሹ  የተለያዩ ዓለማዊ ታሪኮችና መላምቶች የመርዝ ማርከሻ ይሆናቸው ዘንድ ልጆቻቸሁ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቃልና ትምህርት በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል፡፡
4.  ለልጆቻችን ትምህርት ተገቢውን ትኩረት ሰጥተናል የሚባለው በጌታችን ትምህርትና ተግሳጽ ለማሳደግ በእኩል ሁኔታ የምንተጋና የምንቀና ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ልጆቻችን ስለ ሃይማኖት ነገር የማይገዳቸው ግዴለሽና ባለጌዎች ሆነው እንዲያድጉ እያደረግን እንዲህ አይነት መራራ ፍሬን እንዴት ልናጭድ እንደቻልን ለምን እንገረማለን፤ ይህ እንዳይደርስብንና እንዳይሆንብን ይልቁንም በጌታችን ተግሳጽና ትምህርት እንዲያድጉ ለማድረግ የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርትና ተግሳጽ ሁልጊዜ ልብ እናድርግ፡፡ አርአያ የሚያደርጉትን እናሳያቸው ከመጀመርያው ዘመናቸው ጀምሮ መጽሐፍ ቅዱስን እንዲያጠኑ እናስተምራቸው ፡፡ እናንተ ይህን ነገር ብዙ ጊዜ ይደጋገምብናል፣ እኛም መስማት ሰለቸን ትሉ ይሆናል፡፡ እኔ ማድረግ ያለብኝ ተግባር ከማድረግ መቼም ቢሆን አላቆምም፡፡

ምንጭ፡- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅር ስለ ልጅ አስተዳደግ ካስተማረዉ የተወሰደ
#እንኳን ለመምህረ ዓለም ለዮሐንስ አፈርቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ጀማሪ አገልጋይ ራሱን የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያን ጠባቂ አድርጎ ይቆጥራል፤ በማስተዋልና በመንፈሳዊነት ብስለት እናገልግል፤ ወቅታዊ አጀንዳን ስናመነዥክ የቤተ ክርስቲያን ዘለዓለማዊ ተልእኮ ይዳከማል። ጊዜያችንን፣ ገንዘባችንን፣ ጉልበታችንን እና ትኩረታችንን ሁሉ በዋናው የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ በስብከተ ወንጌል ላይ እናድርግ!

መጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር
"እንግዲህ ሞትን የምታለብስና ወደ ሲኦል የምታወርድ ትዕቢትን መታጀርንም ጌጥ አናደርግ፡፡ እንግዲህ የሥጋ ንጽሕና ብቻ ያይደለ ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናደርግ መንፈስን ንጹሕ በማድረግ ነብያትእግዚአብሔርን አይተውታልና ፊት ለፊትም ተያይተዋሉና፡፡ እንግዲህ እንደ ሐዋርያት ፍቅርን የዋህነትንም ገንዘብ እናደርግ"
           አባ ሕርያቆስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
. . . ኆኅትም (ደጅም) መድኃኒታችንን የወለደች ድንግል ናት። እርሱን ከወለደች በኋላ እንደ ቀድሞው በድንግልና ኖራለችና መጥቶ ምሕረት ከሌለው ጠላት እጅ ያዳነን ጌታን የወለድሽ ሆይ የማኅፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው። አንቺ ፍጽምትና የተባረክሽ ነሽ የእውነት አምላክ በሆነ በክብር ባለቤት ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና በምድር ላይ ከሚኖሩ ሁሉ ይልቅ ገናንነትና ክብር ለአንቺ ይገባል የአብ ቃል መጥቶ በአንቺ ሰው ሆነ ከሰው ጋርም ተመላለሰ፤መሓሪ ይቅር ባይ ሰውን ወዳጅ ነውና በልዩ አመጣጡ አዳነን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን: :
ከቁርባን በኋላ አፋችንን ለምን እንሸፍናለን?

ቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ድርጊቶች ሁሉ የራሳቸው የሆነ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት አላቸው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ጌታችን ነፍሱን ከሰጠ በኋላ ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው እያለቀሱና "አቤቱ ይቅር በለን" እያሉ በአዲስ መቃብር ውስጥ እንዳኖሩት አይተናል።

ዛሬም ካህናት ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ከቅዳሴ በኋላ አፍዓዊ እድፋቸውን በሳሙና አፅድተው ልቡናቸውን በንስሐ በወለወሉ ምዕመናን ልብ ውስጥ
ይቀብሩታል።

የምዕመናን ልቡና ያንጊዜ መቃብረ ክርስቶስ ይሆናል

ለዚህ ነው ኦርቶዶክሳውያን ሥጋውን እንደበሉና ደሙን እንደጠጡ አፋቸውን የሚሸፍኑት።

የመሸፈናቸው ምስጢርም፦
፩ኛ. ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ጌታን በአዲስ መቃብር ከቀበሩት በኋላ መቃብሩን በድንጋይ የመግጠማቸው
ምሳሌ

፪ኛ. ለእኛ ስትል የተቀበልከውን መከራ ከመናገር በላይ ነው ሲሉ

፫ኛ. ክርስቶስ በውስጤ አለ ሲሉ

፬ኛ. ከአሁን በኋላ ለኃጢአት የተዘጋው ነኝ ሲሉ

እኛንም አምላካችን ለንስሐ አብቅቶን የቅዱስ ሥጋውና የክቡር ደሙ ምስጢር ተካፋዮች ያድርገን።
"ነገር ኹሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን!"

አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን። የሚያስፈልገንና የማይጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው።"

አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ረሀብና ጥማት፣ ኅዘንና ትካዜ፣ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሜ እንደ ኾነ አድርገን እናስባለን ነገር ግን ይህን የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚ ላይኾን ይችላል።

እንደ ራሳችን ሐሳብ ሳይኾን እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ስንጓዝ ግን ነገር ኹሉ ለበጎ ነው። ነገር ኹሉ ሲባልም በእኛ እይታ በጎ ነው የምንለው ብቻ አይደለም፡ ክፉ ነው የምንለውም ጭምር እንጂ። እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ሲሆን ማግኘትም፣ ማጣትም፣ ጤንነትም፣ በሽታም ለበጎ ነው።

እግዚአብሔር ለእኛ መልካም የሚያደርግልን በጎ ነው ብለን በምናስበው ነገር ብቻ አይደለም። እጅግም ክፉና አስቸጋሪ መስለው ከሚታዩን ኹኔታዎችም ለእኛ ለልጆቹ እጅግ የሚደንቅ በጎ ነገርን ማድረግ ይችልበታል።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ስለ መንፈስ ቅዱስ

ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ከወንድሙ ከታላቁ ባስልዮስና ከወዳጁ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ጎን በመቆም፣ ለሥላሴ አስተምህሮ የማይናወጥ አውታር የዘረጋ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆኖ “ፈላስፋው” በመባል የተጠራና የመጠቀ ፍልስፍናን ለረቀቀው መለኮታዊ ምስጢር ማስተማሪያ አድርጎ የተጠቀመ አባት ነው።

ታላቁ ባስልዮስ የቤተክርስቲያን መሪና አስተዳዳሪ፣ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ደግሞ ነባቤ መለኮት ከሆኑ፣ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ደግሞ የቀጰዶቃውያን ትምህርት ልብና አእምሮ ነበር ማለት ይቻላል።

የእርሱ ብዕር ደረቅ ክርክርን ወደ ሕያው ምስል፣ የተወሳሰበ ፍልስፍናን ደግሞ ወደ ተጨባጭ እውነት የለወጠ ነው። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲያስተምር፣ ከክርክር በላይ በመሄድ የመለኮትን አንድነትና ሦስትነት በሰው አእምሮ ውስጥ ለመሳል ሞክሯል።

የማይነጣጠለው የሥላሴ ሥራ (The Inseparable Operation)

ይህ የጎርጎርዮስ ዘኑሲስ አስተምህሮ ቁልፍ የሆነ ክፍል ነው። መናፍቃን "መንፈስ ቅዱስ ከወልድ ያንሳል፣ ወልድም ከአብ ያንሳል" በማለት የሥልጣን ተዋረድ ለመፍጠር ሲሞክሩ፣ ጎርጎርዮስ መልሱን ያመጣው ከአምላክ ሥራ በመነሳት ነበር። እንዲህ ሲል አስተማረ፦

“የእግዚአብሔር ሥራ ሁሉ እንደ አንድ መለኮታዊ ሥርዓተ ዜማ ነው። ድርጊቱ ከአብ ይነሳል፣ በወልድ በኩል ይከወናል፣ በመንፈስ ቅዱስ ደግሞ ፍጹም ሆኖ ይጠናቀቃል።”

ይህ ማለት ፍጥረትን ስናይ፣ ድኅነትን ስናስብ፣ ወይም ቅድስናን ስንመረምር፤ አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ተለያይተው አይሠሩም። አንዱ ከሌላው ቀድሞ ወይም አንዱ ከሌላው በልጦ አይንቀሳቀስም። ሥራቸው አንድ እንደሆነ ሁሉ፣ ባሕርያቸውም አንድ ነው። መንፈስ ቅዱስ የፈጣሪን ሥራ የሚያጠናቅቅና ፍጹም የሚያደርግ ከሆነ፣ እንዴት ራሱ ፍጡር ሊሆን ይችላል? በፍጹም ሊሆን አይችልም።

ሕያው ምሳሌዎች፡

የጎርጎርዮስ ልዩ ስጦታው፣ “በባሕርይ አንድ፣ በአካል ሦስት” የሚለውን ለሰብአዊ ምናብ የማይጨበጥ ጥልቅ ምሥጢር ሰው ሊረዳው በሚችለው ምሳሌ ማስረዳትና ማሳየት መቻሉ ነው። ከመናፍቃን ክርክር ወጥቶ ወደ ተፈጥሮና ወደ ሰው ልምድ በመመልከት እንዲህ ሲል ያብራራል፦

ምንጩ፣ ወንዙና መጠጡ፡

አብ የማይታይ፣ የማያልቅ ምንጭ ነው።
ወልድ ከዚህ ምንጭ የሚፈልቅ፣ የሚታይና የሚፈስ ወንዝ ነው።
መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ከምንጩና ከወንዙ የሆነው፣ እኛ ቀድተን የምንጠጣውና ሕይወት የሚሆነን የሕይወት መጠጥ ነው።

በዚህ ምሳሌ፣ ሦስቱም በባሕርይ አንድ (ውሃ) ናቸው፤ ነገር ግን በኩነታዊ ህልውናቸውና በሥራቸው በሦስትነት ይታወቃሉ። ምንጩ፣ ወንዙና መጠጡ የተለያዩ ቢሆኑም፣ አንዱ ከሌላው ውጭ ሊኖር አይችልም። እንዲሁ፣ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ የተለየ አካል ቢሆንም፣ ከእነርሱ የተለየ ባሕርይ የለውም።

የሥርዓት እንጂ የተዋረድ አይደለም

ጎርጎርዮስ "አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ" የሚለው አጠራር የሥልጣን ተዋረድን ሳይሆን፣ የመለኮታዊውን ግንኙነት ሥርዓት እንደሚያሳይ በብልሃት ያስተምራል።

“አብን ስናስብ፣ ወዲያውኑ አእምሯችን ወደ ወልድ ይሄዳል፤ ወልድንም ስናስብ፣ ከመንፈስ ቅዱስ አንለየውም። በመካከላቸው የጊዜ፣ የክብር፣ ወይም የባሕርይ ክፍተት የለም። ልዩነታቸው በአምላክነት ደረጃ ሳይሆን፣ በአካላዊ ግንኙነታቸው ነው፤ አብ ያልተወለደ፣ ወልድ የተወለደ፣ መንፈስ ቅዱስ የሰረፀ (የወጣ)መሆኑ ብቻ ነው።”

ይህ ትምህርቱ ሥላሴን እንደ ሦስት የተለያዩ አማልክት ወይም እንደ አንድ አምላክ ሦስት የተለያዩ ገጽታዎች ከማየት አደጋ አውጥቶ፣ ፍጹም አንድነትና ፍጹም ሦስትነት እንዴት በአንድ ጊዜ እውነት ሊሆኑ እንደሚችሉ አመላክቷል።

ማጠቃለያ

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ የመንፈስ ቅዱስን መለኮትነት ለማረጋገጥ የፍልስፍናን ጥልቀት፣ የተፈጥሮን ውበትና ምስል የሚሰጥ ዘዴን አጣምሮ ያቀረበ አባት ነው። እርሱ የሰጠው ማብራሪያ፣ በቁስጥንጥንያ ጉባኤ ላይ ለጸደቀው የሃይማኖት አንቀጽ ዓምድ ሆኗል። ትምህርቱ ዛሬም ድረስ ሥላሴን በየውሀትና በተከፈተ ልብ ማወቅ ለሚሹ ሁሉ የጠራ የብርሃን ምንጭ ሆኖ ያገለግላል፤ ምክንያቱም እርሱ ክርክሩን አሸንፎ ብቻ አላቆመም፣ ነገር ግን የአሸነፈበትን እውነት በሰው ልብ ውስጥ በላቀ ጥበብ ስሏልና።

#GregoryOfNyssa #ጎርጎርዮስዘኑሲስ #ጰራቅሊጦስ #Pentecost
ለሞቱት ብቻ አናልቅስ፥ በቆሙት ብቻም አንደሰት፤ ታዲያ ምን እናድርግ? ለኃጢአተኞች በሞቱ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በቁማቸውም እናልቅስ፤ ስለ ጻድቃን ደግሞ በቁማቸው ብቻ ሳይሆን በሞቱም ጊዜ ደስ ይበለን። ምክንያቱም ኃጢአተኞች ቆመውም ሞተዋል። ጻድቃን ግን ሞተውም ሕያዋን ናቸው

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
2025/06/29 18:45:10
Back to Top
HTML Embed Code: