ጭንቀቴ በክፍሉ ውስጥ እንዳለ አንድ ሌላ ሰው ያህል እውነት ነው። እጆቼን ብዘረጋ እንደምነካው ያህል... እስትንፋሱ በጆሮዬ እንደሚሰማኝ ያህል... ሙቀቱ በጉንጮቼ ይታወቀኛል።
መኃል መኃል ላይ እየቦጨቀ ይጎርሰኛል። እሱ እየገዘፈ እኔ እኮስሳለሁ። የሰናፍጭ ቅንጣት ሆኖ ጀምሮ ተራራ ያህላል።
መጨነቅ ሀጢያት ነው፣ አይደል?
@coffeeandscribblings
(ደህና ነኝ። በአንድ ወቅት የተሰማኝ ስሜት ገርሞኝ መጻፌ ነው እንጂ አሁን በጣም ደህና ነኝ። አመሰግናለሁ። 🤗)
መኃል መኃል ላይ እየቦጨቀ ይጎርሰኛል። እሱ እየገዘፈ እኔ እኮስሳለሁ። የሰናፍጭ ቅንጣት ሆኖ ጀምሮ ተራራ ያህላል።
መጨነቅ ሀጢያት ነው፣ አይደል?
@coffeeandscribblings
(ደህና ነኝ። በአንድ ወቅት የተሰማኝ ስሜት ገርሞኝ መጻፌ ነው እንጂ አሁን በጣም ደህና ነኝ። አመሰግናለሁ። 🤗)
ጸጉር ሰሪው:- ይሄን ጸጉር ስንት አመት አወቅሁት? ሁለት አመት?
እኔ:-አዎ ይሆናል። ጸጉሬ እንግዳ አይወድም። የለመደውን እጅ ይፈልጋል።
እሱ:- ታዲያስ እውነቱን ነው እኮ። እኔ እንኳን ይህቺን ቁንጮዬን ከአንድ ሰው ውጪ ሲነካት አልወድም።
(እውነትም ቁንጮ ነው።)
ሳቅሁ።
እሱ:- ቁንጮ እኮ ጥቅሟ ምን መሰለሽ? ቁመት ትጨምርልኛለች።
ጸጉር ፖለቲካ ነው። የብዙኃን መተዳደሪያ ነው። ውሳኔዎችህ ላይ ተጽዕኖ አለው። ጸጉር ቤቶች የፖለቲካ መድረኮች ናቸው። ሌላ ጊዜ እነግርኃለሁ እንዴት እንደሆነ። አሁን ጊዜ የለኝም።
@coffeeandscribblings
እኔ:-አዎ ይሆናል። ጸጉሬ እንግዳ አይወድም። የለመደውን እጅ ይፈልጋል።
እሱ:- ታዲያስ እውነቱን ነው እኮ። እኔ እንኳን ይህቺን ቁንጮዬን ከአንድ ሰው ውጪ ሲነካት አልወድም።
(እውነትም ቁንጮ ነው።)
ሳቅሁ።
እሱ:- ቁንጮ እኮ ጥቅሟ ምን መሰለሽ? ቁመት ትጨምርልኛለች።
ጸጉር ፖለቲካ ነው። የብዙኃን መተዳደሪያ ነው። ውሳኔዎችህ ላይ ተጽዕኖ አለው። ጸጉር ቤቶች የፖለቲካ መድረኮች ናቸው። ሌላ ጊዜ እነግርኃለሁ እንዴት እንደሆነ። አሁን ጊዜ የለኝም።
@coffeeandscribblings
ሌላ ቅዳሜ።
አዳዲስ መንገዶች እንደፏፏቴ ሿ ብለው የተከፈቱ ይመስለኛል። በጨለማ እንኳ ቀስተደመናዎች ያሉ ይመስለኛል።
ከጊዜ ማለፍ በላይ መልካም ነገር የለም። ሌላው ቢቀር ቅዳሜን ሲወስድ ቅዳሜ ይተካል።
መልካም ቅዳሜ!
@coffeeandscribblings
አዳዲስ መንገዶች እንደፏፏቴ ሿ ብለው የተከፈቱ ይመስለኛል። በጨለማ እንኳ ቀስተደመናዎች ያሉ ይመስለኛል።
ከጊዜ ማለፍ በላይ መልካም ነገር የለም። ሌላው ቢቀር ቅዳሜን ሲወስድ ቅዳሜ ይተካል።
መልካም ቅዳሜ!
@coffeeandscribblings
Coffee and Scribblings pinned «https://lozadmasu.wordpress.com/2022/04/18/%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d-%e1%88%88%e1%8a%aa/»
ካፌዎች ሲዘጉ ይጨንቀኛል። ሌባ ትዝታዬን ይዞ የበረረ ይመስለኛል። 'ሌባ ሌባ' ብዬ ብጮህ እመኛለሁ።
ካፌዎች እንደፎቶግራፎች ናቸው። አሁን እንኳን አይኔን ጨፍኜ በዚያ ካፌ እኔ እና እናንተ የሆንነውን ሁሉ ማስታወስ እችላለለሁ። አቀማመጣችን፣ ሳቃችን፣ አወራራችን ምናምን ሁሉ ይታየኛል። ስትናፍቁኝ የነበርንበት ካፌ ሄጄ ከነበርንበት ቦታ ራቅ ብዬ የነበርንበትን አያለሁ። አታምኑኝም። ግን እውነት ነው።
በየግድግዳው ስለተሰቀሉ ስዕሎች... ስለአስተናጋጆች... ስለሙዚቃው... ስለመጻሕፍት... ስለሰዎቻችን... ስለነገሮቻችን... ያወራነው ሁሉ እንደቱባ ክር ከፊቴ ይተረተራል።
ካፌዎች የመንገድ ላይ ቤቶች ናቸው። እናንተ ትከፍቷቸዋላችሁ፤ እኛ እንኖርባቸዋለን። ሸጎጥ ብለን ራሳችንን ከዚህም ከዛም ሰብሰብ አድርገን የምንወጣበት። ምን ነካኝ? የምንልበት። በማኪያቶ ጥቁርነት በኩል የደፈረሰ እኛነታችንን የምናይበት።
ካፌዎች ቢሮዎች ናቸው። በመነሻ እና መድረሻችን መኃል ያሉ ሀሳቦቻችንን የምንሰድርበት። የምንከትበት። የበሰለ ሀሳባችንን በገበታ የምናቀርብበት።
አቦ ካፌ አትዝጉ! አትዝጉ በቃ!
ወይ እርማችንን እንድናወጣ ቀድማችሁ ንገሩን። ከዚህ ቀን ጀምሮ አገልግሎት አንሰጥም በሉ!! ቢያንስ ፎቶ እናነሳለን!!
የሚያቁነጠንጥ ሀሳባችንን ልናሳርፍ ያቺ ካፌ ድረስ ያቺ ካፌ ድረስ እያልን (ከባድ ሸክም ይዞ እንደሚንደረደር ጎረምሳ) ስንደርስ ዝግ! አይን ፍጥጥ! ሸክም ዝርግፍ!
የሰው እጅ እየጎተትን ቆይ ሀሳብህን ያዝ ቆይ ጨዋታህን ያዝ መታጠፊያው ላይ ካፌ አለች። ያዝ ትንሽ። እያልን ስንደርስ ባዶ! መቃቃር ያመጣል!! በወንድማማች መኃል ቂም የሚዘራ ነው ነገሩ!!
ካፌ አትዝጉ! አትዝጉ በቃ!!
መታሰቢያነቱ:-
ላ ፓሪዝየን (አለም ሲኒማ ጋር)
ብሉዝ ካፌ (ሜክሲኮ)
@coffeeandscribblings
ካፌዎች እንደፎቶግራፎች ናቸው። አሁን እንኳን አይኔን ጨፍኜ በዚያ ካፌ እኔ እና እናንተ የሆንነውን ሁሉ ማስታወስ እችላለለሁ። አቀማመጣችን፣ ሳቃችን፣ አወራራችን ምናምን ሁሉ ይታየኛል። ስትናፍቁኝ የነበርንበት ካፌ ሄጄ ከነበርንበት ቦታ ራቅ ብዬ የነበርንበትን አያለሁ። አታምኑኝም። ግን እውነት ነው።
በየግድግዳው ስለተሰቀሉ ስዕሎች... ስለአስተናጋጆች... ስለሙዚቃው... ስለመጻሕፍት... ስለሰዎቻችን... ስለነገሮቻችን... ያወራነው ሁሉ እንደቱባ ክር ከፊቴ ይተረተራል።
ካፌዎች የመንገድ ላይ ቤቶች ናቸው። እናንተ ትከፍቷቸዋላችሁ፤ እኛ እንኖርባቸዋለን። ሸጎጥ ብለን ራሳችንን ከዚህም ከዛም ሰብሰብ አድርገን የምንወጣበት። ምን ነካኝ? የምንልበት። በማኪያቶ ጥቁርነት በኩል የደፈረሰ እኛነታችንን የምናይበት።
ካፌዎች ቢሮዎች ናቸው። በመነሻ እና መድረሻችን መኃል ያሉ ሀሳቦቻችንን የምንሰድርበት። የምንከትበት። የበሰለ ሀሳባችንን በገበታ የምናቀርብበት።
አቦ ካፌ አትዝጉ! አትዝጉ በቃ!
ወይ እርማችንን እንድናወጣ ቀድማችሁ ንገሩን። ከዚህ ቀን ጀምሮ አገልግሎት አንሰጥም በሉ!! ቢያንስ ፎቶ እናነሳለን!!
የሚያቁነጠንጥ ሀሳባችንን ልናሳርፍ ያቺ ካፌ ድረስ ያቺ ካፌ ድረስ እያልን (ከባድ ሸክም ይዞ እንደሚንደረደር ጎረምሳ) ስንደርስ ዝግ! አይን ፍጥጥ! ሸክም ዝርግፍ!
የሰው እጅ እየጎተትን ቆይ ሀሳብህን ያዝ ቆይ ጨዋታህን ያዝ መታጠፊያው ላይ ካፌ አለች። ያዝ ትንሽ። እያልን ስንደርስ ባዶ! መቃቃር ያመጣል!! በወንድማማች መኃል ቂም የሚዘራ ነው ነገሩ!!
ካፌ አትዝጉ! አትዝጉ በቃ!!
መታሰቢያነቱ:-
ላ ፓሪዝየን (አለም ሲኒማ ጋር)
ብሉዝ ካፌ (ሜክሲኮ)
@coffeeandscribblings
Coffee and Scribblings pinned «ካፌዎች ሲዘጉ ይጨንቀኛል። ሌባ ትዝታዬን ይዞ የበረረ ይመስለኛል። 'ሌባ ሌባ' ብዬ ብጮህ እመኛለሁ። ካፌዎች እንደፎቶግራፎች ናቸው። አሁን እንኳን አይኔን ጨፍኜ በዚያ ካፌ እኔ እና እናንተ የሆንነውን ሁሉ ማስታወስ እችላለለሁ። አቀማመጣችን፣ ሳቃችን፣ አወራራችን ምናምን ሁሉ ይታየኛል። ስትናፍቁኝ የነበርንበት ካፌ ሄጄ ከነበርንበት ቦታ ራቅ ብዬ የነበርንበትን አያለሁ። አታምኑኝም። ግን እውነት ነው።…»