+ ሌላ መንገድ +
ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::
ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12
ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::
መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ “ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::
በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል
"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።
ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?
ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!
ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :‐
"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"
እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 2017
ማስታወሻ :- የልደቴን ቀን አስመልክታችሁ ብዙ ምርቃትና መልካም ምኞት ላዘነባችሁልኝ ሁሉ ለእኔ የተመኛችሁትን ሁሉ ለእናንተ እጥፍ ድርብ ያድርግላችሁ:: ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስፈልገኝ ጸሎታችሁ ነውና ተክለ ማርያም ብላችሁ አስቡኝ::
#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::
ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12
ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::
መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ “ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::
በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል
"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።
ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?
ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!
ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :‐
"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"
እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 2017
ማስታወሻ :- የልደቴን ቀን አስመልክታችሁ ብዙ ምርቃትና መልካም ምኞት ላዘነባችሁልኝ ሁሉ ለእኔ የተመኛችሁትን ሁሉ ለእናንተ እጥፍ ድርብ ያድርግላችሁ:: ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስፈልገኝ ጸሎታችሁ ነውና ተክለ ማርያም ብላችሁ አስቡኝ::
#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
እኛ ስንት ክፍል ቤት ውስጥ እንኖራለን? አንድ ክፍል እንኳን ብንል ስንት ቤተሰብ ነን? ቢበዛ 10 ነው!
በሜቄዶንያ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ7ዐዐ በላይ አረጋውያን ይኖራሉ:: ሌላ ሕመማቸውን ትተን በዚህ ሁኔታ መኖር ብቻ የሚያመጣው ብዙ ሕመም አለ::
የካቲት 1 የሜቄዶንያን ሕንፃ ለመጨረስ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ የዩቲዩብ ቻናል ላይ እንዘምታለን:: በዚህም ትልቁን ሆስፒታልና የአረጋውያን ማረፊያ እንሠራለን!
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
የመቄዶንያ የክብር አምባሳደር
▫️@diyakonhenokhaile
በሜቄዶንያ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ7ዐዐ በላይ አረጋውያን ይኖራሉ:: ሌላ ሕመማቸውን ትተን በዚህ ሁኔታ መኖር ብቻ የሚያመጣው ብዙ ሕመም አለ::
የካቲት 1 የሜቄዶንያን ሕንፃ ለመጨረስ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ የዩቲዩብ ቻናል ላይ እንዘምታለን:: በዚህም ትልቁን ሆስፒታልና የአረጋውያን ማረፊያ እንሠራለን!
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
የመቄዶንያ የክብር አምባሳደር
▫️@diyakonhenokhaile
2008 ዓ.ም. ከዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ ጋር የተባበሩት ዐረብ ኢመሬትስ ሻርጃ ሰአሊተ ምሕረት አብረን ለማገልገል ተጠርተን ነበር:: ከሃያ ቀናት በላይ በየቀኑ በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ላይ ዘማሪት ሕይወት መሣሪያ በማይፈልገው የተለየ ድምፅዋ “ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ" የሚል ድንቅ መዝሙር ስትዘምር ሰማሁ::
"ስሸጥህ አቀፍከኝ ስወጋህ ዓይኔ በራ” እያለ ራስን ከይሁዳና ከሌንጊኖስ ጋር በትሕትና የሚያነጻጽረው ይህን መዝሙር በጣም ስለወደድሁት አንዲት ቃል ላይ ብቻ እርማት እንድታደርግ አስተያየት ሰጥቼ አብረን በሰነበትንበት ሻርጃ ሕዝቡ በቃሉ እስኪይዘው ድረስ 14ቱንም ቀን አስዘመርኳት::
ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ በሙያዋ ነርስ ስትሆን ቤተ ክርስቲያን ቆንጥጣ ካሳደገቻቸው ወርቅ ዘማርያን አንድዋ ናት:: ሰዓታት የምትቆም ፣ አስቀድሳ የምቆርብ ፣ መምህሩ ያስተማረውን ቁጭ ብላ ሰምታ ለትምህርቱ የሚስማማ መዝሙር የምትዘምር ፣ በጣም በትሕትናና በታዛዥነት የምታገለግል ካላት የዝማሬ ጸጋ ገና የሚገባትን ያህል ያልተሰማች (Underrated) ያወቋትና የሰሟት ደግሞ እንዴት ሳልሰማት ቀረሁ የሚሉባት የቤተ ክርስቲያን ውድ ልጅ ናት:: እግዚአብሔር ይጠብቅልንና ዘማሪት ሕይወት ከ "ረ" ፊደል በስተቀር በመዝሙር ዘርፍ ገና ለመሥራት ምንም የሚቸግራት ነገር የለም::
ሰሞኑን በአእላፋት ዝማሬ ላይ "ና ና አማኑኤል" የሚለው መዝሙር በጃን ያሬድ መዘምራን ሲዘመር የሰሙና የወደዱት ምእመናን “ይኼ መዝሙር ግጥሙ የአንተ ነው" በሚል ሲመርቁኝ ሰነበቱ:: ምርቃቱን ሳላስተባብል አሜን ብዬ ብቀበልም ይህንን በሳል መዝሙር ግጥምና ዜማ የሠራውን ሰው ግን በጸሎት እንድታስቡትና እንድትመርቁት ማሳሰብ የግድ ሆነብኝ::
የመዝሙር ርእስ :- ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ
ዘማሪዋ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
ግጥም :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
ዜማ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
"ስሸጥህ አቀፍከኝ ስወጋህ ዓይኔ በራ” እያለ ራስን ከይሁዳና ከሌንጊኖስ ጋር በትሕትና የሚያነጻጽረው ይህን መዝሙር በጣም ስለወደድሁት አንዲት ቃል ላይ ብቻ እርማት እንድታደርግ አስተያየት ሰጥቼ አብረን በሰነበትንበት ሻርጃ ሕዝቡ በቃሉ እስኪይዘው ድረስ 14ቱንም ቀን አስዘመርኳት::
ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ በሙያዋ ነርስ ስትሆን ቤተ ክርስቲያን ቆንጥጣ ካሳደገቻቸው ወርቅ ዘማርያን አንድዋ ናት:: ሰዓታት የምትቆም ፣ አስቀድሳ የምቆርብ ፣ መምህሩ ያስተማረውን ቁጭ ብላ ሰምታ ለትምህርቱ የሚስማማ መዝሙር የምትዘምር ፣ በጣም በትሕትናና በታዛዥነት የምታገለግል ካላት የዝማሬ ጸጋ ገና የሚገባትን ያህል ያልተሰማች (Underrated) ያወቋትና የሰሟት ደግሞ እንዴት ሳልሰማት ቀረሁ የሚሉባት የቤተ ክርስቲያን ውድ ልጅ ናት:: እግዚአብሔር ይጠብቅልንና ዘማሪት ሕይወት ከ "ረ" ፊደል በስተቀር በመዝሙር ዘርፍ ገና ለመሥራት ምንም የሚቸግራት ነገር የለም::
ሰሞኑን በአእላፋት ዝማሬ ላይ "ና ና አማኑኤል" የሚለው መዝሙር በጃን ያሬድ መዘምራን ሲዘመር የሰሙና የወደዱት ምእመናን “ይኼ መዝሙር ግጥሙ የአንተ ነው" በሚል ሲመርቁኝ ሰነበቱ:: ምርቃቱን ሳላስተባብል አሜን ብዬ ብቀበልም ይህንን በሳል መዝሙር ግጥምና ዜማ የሠራውን ሰው ግን በጸሎት እንድታስቡትና እንድትመርቁት ማሳሰብ የግድ ሆነብኝ::
የመዝሙር ርእስ :- ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ
ዘማሪዋ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
ግጥም :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
ዜማ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ
#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
My interview with Kal Podcast is out now. Please take your time to watch and comment on it.
https://youtu.be/nvvX4aOiQP8?si=MJ2BFqkMIeWM1Jk8
https://youtu.be/nvvX4aOiQP8?si=MJ2BFqkMIeWM1Jk8
YouTube
ፀሎት ቴራፒ ነው! የተጎዱ ሰዎች ሰዎችን ይጎዳሉ! ዮጋ ሌላ አምልኮ ነው! ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Deacon Henok Haile
በዚህ ቪዲዮ ከ መምህር ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ ጋር በነበረን ልዩ ቆይታ ስለ አእምሮ ጤና እና መንፈሳዊነት፣ ስለ ህልም፣ ስለ ቅናት፣ የህይወት ትርጉምን ስለመፈለግ፣ ስለ ዲሲፕሊን እና ስለሌሎችም የህይወታችን አንኳር ስለሆኑ ርእሰ ጉዳዮች አንስተን ተወያይተናል፤የመፍትሔ ሀሳቦችም ተንሸራሽረዋል። መልካም ቆይታ ይሁንላችሁ። ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ። ይሄ ውይይት ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ማድረጋችሁን…
+ ምሕረት የለሹ ምሕረት +
የወንድሜ የዲያቆን ምሕረት መላኩንና የሁለቱን ፓስተሮች ውይይት ዘግይቼም ቢሆን አየሁት:: ውይይቱ በጣም በሰከነው የዲያቆኑ ኦርቶዶክሳዊ ጨዋነት የተነሣ ሁለቱን የፕሮቴስታንት ዋርካዎች በትሕትና ብቻ የገነደሰ ነበረ:: ቅመሙ ዲያቆን ምሕረት ውይይቱ እንደሚቀረጽ በደንብ ስላስተዋለ ጠይቆአቸው ሳይመልሱ ያለፉትን ወይም ያልተጠየቁትን ጉዳይ ያነሡበትን ቦታ ሁሉ ልክ ነጥብ “ተመልካች ይፍረድ” በሚመስል ብልጠት እየተወ ወደ ቀጣዩ ነጥብ የሚሸጋገርበት ፍጥነት ድንገት የገባበት ውይይት ሳይሆን የተጠና (scripted) ውይይት እንዲመስል አድርጎታል:: በጣም በትሕትና ሆኖ እየጠየቀ ዕርቃናቸውን ያሳየበት መንገድ ምን ያህል ሊያናድዳቸው እንደሚችል ሳስብ ውይይቱ በሰላም አለቀ እንጂ “ከአሁን አሁን ይመቱት ይሆን?” ብዬም ተሳቅቄያለሁ::
በውይይቱ ላይ ካየኋቸው ያስገረሙኝን ጥቂት እውነታዎች ላስቀምጥ:-
1. ቤተ ክርስቲያንን የሙጥኝ ማለት
ዲያቆን ምሕረት ውይይቱን የጀመረው የፓስተሮቹን አስተምህሮ ከቤተ ክርስቲያን ቅድምና አንጻር በማንሳት ነበር:: በዚህም ለፕሮቴስታንቱ ዓለም ደካማ ጎን የሆነውን ስስ ብልት በመምታት ጀመረ::
@diyakonhenokhaile
የወንድሜ የዲያቆን ምሕረት መላኩንና የሁለቱን ፓስተሮች ውይይት ዘግይቼም ቢሆን አየሁት:: ውይይቱ በጣም በሰከነው የዲያቆኑ ኦርቶዶክሳዊ ጨዋነት የተነሣ ሁለቱን የፕሮቴስታንት ዋርካዎች በትሕትና ብቻ የገነደሰ ነበረ:: ቅመሙ ዲያቆን ምሕረት ውይይቱ እንደሚቀረጽ በደንብ ስላስተዋለ ጠይቆአቸው ሳይመልሱ ያለፉትን ወይም ያልተጠየቁትን ጉዳይ ያነሡበትን ቦታ ሁሉ ልክ ነጥብ “ተመልካች ይፍረድ” በሚመስል ብልጠት እየተወ ወደ ቀጣዩ ነጥብ የሚሸጋገርበት ፍጥነት ድንገት የገባበት ውይይት ሳይሆን የተጠና (scripted) ውይይት እንዲመስል አድርጎታል:: በጣም በትሕትና ሆኖ እየጠየቀ ዕርቃናቸውን ያሳየበት መንገድ ምን ያህል ሊያናድዳቸው እንደሚችል ሳስብ ውይይቱ በሰላም አለቀ እንጂ “ከአሁን አሁን ይመቱት ይሆን?” ብዬም ተሳቅቄያለሁ::
በውይይቱ ላይ ካየኋቸው ያስገረሙኝን ጥቂት እውነታዎች ላስቀምጥ:-
1. ቤተ ክርስቲያንን የሙጥኝ ማለት
ዲያቆን ምሕረት ውይይቱን የጀመረው የፓስተሮቹን አስተምህሮ ከቤተ ክርስቲያን ቅድምና አንጻር በማንሳት ነበር:: በዚህም ለፕሮቴስታንቱ ዓለም ደካማ ጎን የሆነውን ስስ ብልት በመምታት ጀመረ::
@diyakonhenokhaile
ነገሩ እንዲህ ነው:: መጽሐፍ ቅዱስን አሁን ባለው ቅርጽ እንዲህ አድርጋ የሠራችው ቤተክርስቲያን ናት:: ይህ እውነታ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከሐዋርያት እጅ የተቀበሉትንና ሐዲስ ኪዳን በቀኖና ወስነው ለእኛ ያስተላለፉትን የመጀመሪያዎቹን ክርስቲያኖች ትርጉምና አረዳድ እንድንቀበል ያስገድደናል:: ልክ እስራኤል ሕግን ተቀብሎ የመጣውን ሙሴን እንደ ባለ ሥልጣን እንደተቀበሉትና ስለ ሕጉ የእርሱን አሳብ ያለማወላወል እንደተቀበሉ ሁሉ ሐዲስ ኪዳንን ከሐዋርያት እጅ የተቀበሉትን የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን አባቶችም በሐዲስ ኪዳን ትርጉም ላይ ያላቸውን ሃሳብ መቀበል ግድ ይለናል:: ይህን ጠንቅቆ የተረዳው ዲያቆን ምሕረት:-
ጥምቀትና ቁርባን ተምሳሌቶች እንጂ ለድኅነት ፍቱን አይደሉም ስትሉን ነበር:: ከአንደኛ እስከ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን ያሉ ክርስቲያኖችን ሃሳብ ስናይ ደግሞ እነዚህ ነገሮች ለመዳን የግድ እስፈላጊ መሆናቸውን ጽፈው እናገኛለን:: የእኔ ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከተቀበሉትና ሐዲስ ኪዳንን በቀኖና ከደነገጉ ክርስቲያኖች ጋር ትርጓሜያችሁ ካልገጠመ ምኑን በመጽሐፍ ቅዱስ አመናችሁ ይባላል? አላቸው::
በአጭሩ መጽሐፍ ቅዱስን ያዋለዱትን አዋላጆች ካልሰማችሁ ምኑን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሆናችሁት “ድምፅህ የያዕቆብን ይመስላል ጸጉርህ ግን የኤሳው ነው” ያለው ለእናንተ አይደል ወይ? እንደማለት ያለ ነው::
@diyakonhenokhaile
ጥምቀትና ቁርባን ተምሳሌቶች እንጂ ለድኅነት ፍቱን አይደሉም ስትሉን ነበር:: ከአንደኛ እስከ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን ያሉ ክርስቲያኖችን ሃሳብ ስናይ ደግሞ እነዚህ ነገሮች ለመዳን የግድ እስፈላጊ መሆናቸውን ጽፈው እናገኛለን:: የእኔ ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከተቀበሉትና ሐዲስ ኪዳንን በቀኖና ከደነገጉ ክርስቲያኖች ጋር ትርጓሜያችሁ ካልገጠመ ምኑን በመጽሐፍ ቅዱስ አመናችሁ ይባላል? አላቸው::
በአጭሩ መጽሐፍ ቅዱስን ያዋለዱትን አዋላጆች ካልሰማችሁ ምኑን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሆናችሁት “ድምፅህ የያዕቆብን ይመስላል ጸጉርህ ግን የኤሳው ነው” ያለው ለእናንተ አይደል ወይ? እንደማለት ያለ ነው::
@diyakonhenokhaile
ዲያቆን ምሕረት በዚህ ጥያቄው ሰዎቹን ጨርሶ ወደማውቁት ጨለማ ክፍል ወስዶ ቆለፈባቸው:: የአንደኛው ክፍለ ዘመን አባቶች ሥነ ጽሑፍና ታሪክ ለእነርሱ የማያውቁት የውጊያ ዐውድ ነው:: ወደ በኋላም በምሥጢረ ቁርባን ዙሪያ ባለው ግልፅ አቋምና ከሐዋርያት ጋር በነበረው ቅርበት የተነሣ የፕሮቴስታንት ሊቃውንት “ምነው ባልተፈጠረ” የሚሉትንና አንዳንዶቹም “እሱ አልጻፈውም” ብለው መጽሐፉን ለመካድ የሚገደዱበትን ቅዱስ አግናጥዮስን በመጥቀስ አስጨንቆአቸዋል::
የሚገርመው የሠጡት መልስ :-
የምትለው እውነት ከሆነ ለምን ሚልዮኖች ሳይቀበሉት ቀሩ? የሚል ልፍስፍስ ጥያቄ ነው::
ምሕረት መለሰ :- ይህማ እጅግ ብዙ ሰዎች ወንጌልን ላለመቀበላቸውም የሚቀርብ ምክንያት ነው::
ብሎ የራሳቸውን አመክንዮ በራሳቸው ላይ መለሰው:: በሳልሽው ተመተሪ!
ፓስተሩ :- እስቲ በሁለቱም ወገን (ጥምቀትና ቁርባን ለድኅነት ያስፈልጋል አያስፈልግም) ከሚሉ ወገን አባቶችን በስም ጥቀስልኝ አለው::
“መረጃ ተጠናክሮ በሁለቱም ወገን ይቅረብልን” እንደሚል ዳኛ ውይይቱን ትቶ ዳኛ ሊሆን ተማጸነው::
“በሁለት ወገን ብሎ ነገር የለም:: ከዚህ ውጪ ሃሳብ ያለው ሰው ስለመኖሩምንም የተቀመጠ ታሪካዊ ማስረጃ የለም” አለ ምሕረት የለሹ ምሕረት::
@diyakonhenokhaile
የሚገርመው የሠጡት መልስ :-
የምትለው እውነት ከሆነ ለምን ሚልዮኖች ሳይቀበሉት ቀሩ? የሚል ልፍስፍስ ጥያቄ ነው::
ምሕረት መለሰ :- ይህማ እጅግ ብዙ ሰዎች ወንጌልን ላለመቀበላቸውም የሚቀርብ ምክንያት ነው::
ብሎ የራሳቸውን አመክንዮ በራሳቸው ላይ መለሰው:: በሳልሽው ተመተሪ!
ፓስተሩ :- እስቲ በሁለቱም ወገን (ጥምቀትና ቁርባን ለድኅነት ያስፈልጋል አያስፈልግም) ከሚሉ ወገን አባቶችን በስም ጥቀስልኝ አለው::
“መረጃ ተጠናክሮ በሁለቱም ወገን ይቅረብልን” እንደሚል ዳኛ ውይይቱን ትቶ ዳኛ ሊሆን ተማጸነው::
“በሁለት ወገን ብሎ ነገር የለም:: ከዚህ ውጪ ሃሳብ ያለው ሰው ስለመኖሩምንም የተቀመጠ ታሪካዊ ማስረጃ የለም” አለ ምሕረት የለሹ ምሕረት::
@diyakonhenokhaile