Telegram Web Link
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
"የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው" ዕብ.

13:7

A blessed meeting With His Grace Abune Fanuel, Archbishop of Washington DC Diocese. A great reunion With My beloved Spritual Father and Mentor Kesis Hibret Yeshitla, With Our Mezmur Legend, Liqë Mezemiran Yilma Hailu, With the pioneer of dogmatic books Melake

Ariyam Birhanu Gobena

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
“ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ... በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ” ፊልጵ. 2:12

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሠጥቶናል ስሙም

ድንቅ!!!!!!!

መካር ኃያል አምላክ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል" ኢሳ.6:9

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
+ ሌላ መንገድ +

ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::

ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12

ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::

መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ “ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::

በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል

"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።

ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?

ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!

ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :‐

"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"

እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 2017

ማስታወሻ :- የልደቴን ቀን አስመልክታችሁ ብዙ ምርቃትና መልካም ምኞት ላዘነባችሁልኝ ሁሉ ለእኔ የተመኛችሁትን ሁሉ ለእናንተ እጥፍ ድርብ ያድርግላችሁ:: ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስፈልገኝ ጸሎታችሁ ነውና ተክለ ማርያም ብላችሁ አስቡኝ::

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
2025/06/27 19:31:49
Back to Top
HTML Embed Code: