Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
“ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ... በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ” ፊልጵ. 2:12

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ሕፃን ተወልዶልናል ወንድ ልጅም ተሠጥቶናል ስሙም

ድንቅ!!!!!!!

መካር ኃያል አምላክ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል" ኢሳ.6:9

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
+ ሌላ መንገድ +

ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::

ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12

ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::

መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ “ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::

በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል

"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።

ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?

ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!

ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :‐

"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"

እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 2017

ማስታወሻ :- የልደቴን ቀን አስመልክታችሁ ብዙ ምርቃትና መልካም ምኞት ላዘነባችሁልኝ ሁሉ ለእኔ የተመኛችሁትን ሁሉ ለእናንተ እጥፍ ድርብ ያድርግላችሁ:: ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስፈልገኝ ጸሎታችሁ ነውና ተክለ ማርያም ብላችሁ አስቡኝ::

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
እኛ ስንት ክፍል ቤት ውስጥ እንኖራለን? አንድ ክፍል እንኳን ብንል ስንት ቤተሰብ ነን? ቢበዛ 10 ነው!

በሜቄዶንያ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ7ዐዐ በላይ አረጋውያን ይኖራሉ:: ሌላ ሕመማቸውን ትተን በዚህ ሁኔታ መኖር ብቻ የሚያመጣው ብዙ ሕመም አለ::

የካቲት 1 የሜቄዶንያን ሕንፃ ለመጨረስ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ የዩቲዩብ ቻናል ላይ እንዘምታለን:: በዚህም ትልቁን ሆስፒታልና የአረጋውያን ማረፊያ እንሠራለን!

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የመቄዶንያ የክብር አምባሳደር
▫️@diyakonhenokhaile
2008 ዓ.ም. ከዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ ጋር የተባበሩት ዐረብ ኢመሬትስ ሻርጃ ሰአሊተ ምሕረት አብረን ለማገልገል ተጠርተን ነበር:: ከሃያ ቀናት በላይ በየቀኑ በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ላይ ዘማሪት ሕይወት መሣሪያ በማይፈልገው የተለየ ድምፅዋ “ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ" የሚል ድንቅ መዝሙር ስትዘምር ሰማሁ::

"ስሸጥህ አቀፍከኝ ስወጋህ ዓይኔ በራ” እያለ ራስን ከይሁዳና ከሌንጊኖስ ጋር በትሕትና የሚያነጻጽረው ይህን መዝሙር በጣም ስለወደድሁት አንዲት ቃል ላይ ብቻ እርማት እንድታደርግ አስተያየት ሰጥቼ አብረን በሰነበትንበት ሻርጃ ሕዝቡ በቃሉ እስኪይዘው ድረስ 14ቱንም ቀን አስዘመርኳት::

ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ በሙያዋ ነርስ ስትሆን ቤተ ክርስቲያን ቆንጥጣ ካሳደገቻቸው ወርቅ ዘማርያን አንድዋ ናት:: ሰዓታት የምትቆም ፣ አስቀድሳ የምቆርብ ፣ መምህሩ ያስተማረውን ቁጭ ብላ ሰምታ ለትምህርቱ የሚስማማ መዝሙር የምትዘምር ፣ በጣም በትሕትናና በታዛዥነት የምታገለግል ካላት የዝማሬ ጸጋ ገና የሚገባትን ያህል ያልተሰማች (Underrated) ያወቋትና የሰሟት ደግሞ እንዴት ሳልሰማት ቀረሁ የሚሉባት የቤተ ክርስቲያን ውድ ልጅ ናት:: እግዚአብሔር ይጠብቅልንና ዘማሪት ሕይወት ከ "ረ" ፊደል በስተቀር በመዝሙር ዘርፍ ገና ለመሥራት ምንም የሚቸግራት ነገር የለም::

ሰሞኑን በአእላፋት ዝማሬ ላይ "ና ና አማኑኤል" የሚለው መዝሙር በጃን ያሬድ መዘምራን ሲዘመር የሰሙና የወደዱት ምእመናን “ይኼ መዝሙር ግጥሙ የአንተ ነው" በሚል ሲመርቁኝ ሰነበቱ:: ምርቃቱን ሳላስተባብል አሜን ብዬ ብቀበልም ይህንን በሳል መዝሙር ግጥምና ዜማ የሠራውን ሰው ግን በጸሎት እንድታስቡትና እንድትመርቁት ማሳሰብ የግድ ሆነብኝ::

የመዝሙር ርእስ :- ና ና አማኑኤል ና መድኃኒቴ

ዘማሪዋ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ

ግጥም :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ

ዜማ :- ዘማሪት ሕይወት ተፈሪ

#share
▫️@diyakonhenokhaile
https://www.tg-me.com/diyakonhenokhaile
"በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን"
1 ቆሮንቶስ 15:19
▫️@diyakonhenokhaile
We are now on TikTok

አሁን ቲክቶክም ላይ ያገኙናል
@diyakonhenokhaile
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የመጀመሪያው ቪድዮ ተለቀቀ

ዘወትር ዐርብ በ Henok Haile - Official Channel ይጠብቁ
#share #share
@diyakonhenokhaile
+ ምሕረት የለሹ ምሕረት +

የወንድሜ የዲያቆን ምሕረት መላኩንና የሁለቱን ፓስተሮች ውይይት ዘግይቼም ቢሆን አየሁት:: ውይይቱ በጣም በሰከነው የዲያቆኑ ኦርቶዶክሳዊ ጨዋነት የተነሣ ሁለቱን የፕሮቴስታንት ዋርካዎች በትሕትና ብቻ የገነደሰ ነበረ:: ቅመሙ ዲያቆን ምሕረት ውይይቱ እንደሚቀረጽ በደንብ ስላስተዋለ ጠይቆአቸው ሳይመልሱ ያለፉትን ወይም ያልተጠየቁትን ጉዳይ ያነሡበትን ቦታ ሁሉ ልክ ነጥብ “ተመልካች ይፍረድ” በሚመስል ብልጠት እየተወ ወደ ቀጣዩ ነጥብ የሚሸጋገርበት ፍጥነት ድንገት የገባበት ውይይት ሳይሆን የተጠና (scripted) ውይይት እንዲመስል አድርጎታል:: በጣም በትሕትና ሆኖ እየጠየቀ ዕርቃናቸውን ያሳየበት መንገድ ምን ያህል ሊያናድዳቸው እንደሚችል ሳስብ ውይይቱ በሰላም አለቀ እንጂ “ከአሁን አሁን ይመቱት ይሆን?” ብዬም ተሳቅቄያለሁ::

በውይይቱ ላይ ካየኋቸው ያስገረሙኝን ጥቂት እውነታዎች ላስቀምጥ:-

1. ቤተ ክርስቲያንን የሙጥኝ ማለት

ዲያቆን ምሕረት ውይይቱን የጀመረው የፓስተሮቹን አስተምህሮ ከቤተ ክርስቲያን ቅድምና አንጻር በማንሳት ነበር:: በዚህም ለፕሮቴስታንቱ ዓለም ደካማ ጎን የሆነውን ስስ ብልት በመምታት ጀመረ::
@diyakonhenokhaile
2025/07/05 22:41:01
Back to Top
HTML Embed Code: