ዛሬ ነገ ነው!
“አባዬ ዛሬ ነገ ነው?” አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ አባት እየተበሳጨ “ምንድን ነው የምትለኝ? አለ፡፡ ዛሬ ነገ ነው ወይ? አባት እንቅልፉ ስላልቀቀው “ሂድና እናትህን ጠይቃት በቃ ልተኛበት አለና እየተበሳጨ ፊቱን ሸፈነ፡፡
ልጅ ወደ እናት ሔዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት"እማዬ ዛሬ ነገ ነው" እናት አለች
“ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?” አለች የልጅዋን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች “ትናንት አስተማሪያችን “ነገ ትምህርት የለም” ብላን ነበር ፤ ዛሬ ነገ ነው? እናት እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው” አለች እየሳቀች፡፡
ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው፡፡ ለነገ እንማራለን ፣ ለነገ እንሠራለን ፣ ይህ ለሕጸኑ ጥያቄ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም። ለነገ እንገነባለን፡፡ የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ፡፡ ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን፡፡ ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን፡፡ እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን፡፡ መጽሐፍ “ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና, “ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ! ይላል፡፡ /ያዕ 4፡15 ፤ ማቴ 6፡34/
ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሣሪያም አንዱ “ነገ በሚል ቃል ማዘናጋት ነው፡፡ ነገ እማራለሁ ፣ ነገ እሔዳለሁ ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ ፣ ነገ ንስሓ እገባለሁ ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሠራለሁ ነገ ነገ ነገ ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉሥ በመቅሠፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር፡፡ በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ ፦ ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው፡፡
ፈርኦንም ፦ ነገ አለ፡፡ እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው፡፡ ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት ክፉ አመል አለብህ ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ ፣ አልስተካከል ያለህ ድክመት ፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? 'አቤቱ እሁን አድን' ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ።
ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ : ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ : ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም፡፡ ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግሥቱም መልሳችን ነገ ነው፡፡ 'ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሠራ የማንፈልገውን እየሠራን እንኖራለን፡፡ ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም “የተወደደው ሰዓት አሁን ነው, መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትሥጥ፡፡ ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው፡፡ ማንም ሊሠራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት፡፡
አሁኑኑ ተነሥ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመሥራት ፣ ክፉውን ነገር ለመተው አደርገዋለሁ ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅህ “ነገ አደርገዋለሁ” ብለህ ነበር ፤ ዛሬም ነገ አትበል ምክንያቱም ሕጻኑ እንዳለው “ዛሬ ነገ ነው”
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
“አባዬ ዛሬ ነገ ነው?” አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ አባት እየተበሳጨ “ምንድን ነው የምትለኝ? አለ፡፡ ዛሬ ነገ ነው ወይ? አባት እንቅልፉ ስላልቀቀው “ሂድና እናትህን ጠይቃት በቃ ልተኛበት አለና እየተበሳጨ ፊቱን ሸፈነ፡፡
ልጅ ወደ እናት ሔዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት"እማዬ ዛሬ ነገ ነው" እናት አለች
“ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?” አለች የልጅዋን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች “ትናንት አስተማሪያችን “ነገ ትምህርት የለም” ብላን ነበር ፤ ዛሬ ነገ ነው? እናት እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው” አለች እየሳቀች፡፡
ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው፡፡ ለነገ እንማራለን ፣ ለነገ እንሠራለን ፣ ይህ ለሕጸኑ ጥያቄ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም። ለነገ እንገነባለን፡፡ የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ፡፡ ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን፡፡ ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን፡፡ እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን፡፡ መጽሐፍ “ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና, “ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ! ይላል፡፡ /ያዕ 4፡15 ፤ ማቴ 6፡34/
ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሣሪያም አንዱ “ነገ በሚል ቃል ማዘናጋት ነው፡፡ ነገ እማራለሁ ፣ ነገ እሔዳለሁ ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ ፣ ነገ ንስሓ እገባለሁ ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሠራለሁ ነገ ነገ ነገ ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉሥ በመቅሠፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር፡፡ በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ ፦ ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው፡፡
ፈርኦንም ፦ ነገ አለ፡፡ እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው፡፡ ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት ክፉ አመል አለብህ ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ ፣ አልስተካከል ያለህ ድክመት ፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? 'አቤቱ እሁን አድን' ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ።
ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ : ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ : ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም፡፡ ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግሥቱም መልሳችን ነገ ነው፡፡ 'ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሠራ የማንፈልገውን እየሠራን እንኖራለን፡፡ ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም “የተወደደው ሰዓት አሁን ነው, መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትሥጥ፡፡ ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው፡፡ ማንም ሊሠራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት፡፡
አሁኑኑ ተነሥ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመሥራት ፣ ክፉውን ነገር ለመተው አደርገዋለሁ ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅህ “ነገ አደርገዋለሁ” ብለህ ነበር ፤ ዛሬም ነገ አትበል ምክንያቱም ሕጻኑ እንዳለው “ዛሬ ነገ ነው”
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#ኅዳር_6
#ደብረ_ቁስቋም
ኅዳር ስድስት በዚህች ዕለት ክብርት እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ከስደት በሚመለሱበት ጊዜ ደብረ ቁስቋም ገብተው ካገኛቸው ድካም ዐረፉ፡፡
አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ከስደት በተመለሰች ጊዜ እንዲህ ሆነ፡- የብርሃን እናቱ ክብርት እመቤታችን ልጇን ይዛ ከእነ ዮሴፍ ጋር ወደ ምድረ ግብፅ ስትሰደድ ግብፅ ደርሰው በዚያ ቢቀመጡም ነገርን ግብፅ አልተመቸቻውም፡፡ ሕዝቡም በሰላም አልተቀበላቸውም፡፡ እንዲያውም በምድረ ግብፅ ብዙ ተሠቃይተዋል፡፡ ከግብፅም ተነሥተው ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ግን ኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በሰላምና በፍቅር ተቀበላቸው፡፡ ከመንገዱና ከርሃብ ጥሙ ጽናት የተነሣ እጅግ ደክማለችና የኢትዮጵያ ሰዎች እመቤታችንን አይተው እጅግ አዘኑላት፡፡ ‹‹ይህችስ የነገሥታት ዘር ትመሥላለች ነገር ግን አንዳች ችግር አጋጥሟት ተሰዳ ወደ ሀገራችን መጥታለች..›› ብለው እንክብካቤን አደረጉላት፡፡ እግራቸውን አጥበው በክብር ማረፊያዎች ላይ አሳረፏቸው፡፡ መልካም መስተንግዶም አደረጉላቸው፡፡ እመቤታችንም ከድካሟ ካረፈች በኋላ ሀገሪቱን በእጅጉ ወደደቻትና የተወደደ ልጇን ‹‹ይህን ሀገርና ሕዝቧን በመላ ወድጃቸዋልሁና በዚህ እስከ መጨረሻው እንኑር›› አለችው፡፡ ጌታችንም ክብርት እናቱን ‹‹ይህች ቅድስት ሀገር ናት፣ በኋለኛው ዘመን የቅዱሳን መነኮሳት ቦታ ትሆናለች፡፡ በውስጧም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እመሰገንባታለሁ፤ የአንቺም ስም ሳይጠራ አይውልባትም›› አላት፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን ደመና ጠቅሶ በእርሷ ላይ ተቀመጡ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም መጣና እየመራቸው መላ ኢትዮጵያን ጎበኟት፡፡ እመቤታችንም ሀገሪቱንና ሕዝቦቿን ወዳቸዋለች ደስም ተሰኝታባቸዋለችና ጌታችን ለክብርት እናቱ ‹‹ይህችን ቅድስት ሀገር አሥራት አድርጌ ሰጠሁሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም እጅግ ተደስታ ‹‹ልጄ አምላኬ›› ብላ አመሰገነችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ እየተዘዋወሩ መላዋ ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባረኳት፡፡ ጌታችንም ‹‹በዚህ ቦታ እንዲህ ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ እከሌ የሚባል እንዲህ ዓይነት ቅዱስ ይነሣል…›› እያለ ብዙ ምሥጢራትን ለክብርት እናቱ ነገራት፡፡ ከዚህም በኋላ የስደቱ ዘመን ሲያልፍ ሄሮድስም በመጨረሻ ክፉ አሟሟትን ሲሞት መልአኩ ወደ ገሊላ አውራጃ እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡ እመቤታችንም ‹‹ከዚህች ሀገርስ ባንሄድ እመርጣለሁ›› ስትለው የተወደደ ልጇ ግን ‹‹እናቴ ሆይ ጽድቅንና ፈቃድን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናል›› ብሎ አጽናናትና ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡
ተመልሰውም ሊሄዱ ሲነሡ የኢትዮጵያ ሰዎች ልዩ ልዩ አምሐ እጅ መንሻ ሰጧቸው፡፡ ልዩ ልዩ ልብሶች፣ ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ፣ ሽቱ እና ሥንቀቸውን በግመሎች ላይ ጭነው እመቤታችንንና የተወደደ ልጇንም በበቅሎ ላይ አስቀምጠው በክብር ሸኟቸው፡፡ እመቤታችንም ልጇን ታቅፋ በበቅሎ ተቀምጣ በበረሃው በመጓዝ ወደ መጣችበት አገር ሄደች፡፡ ኢትዮጵያንም የሰጧትን ብዙ እጅ መንሻዎች በግመሎች ጭና ይዛ ወደ አገሯ በተመለሰች ጊዜ ከአንድ ባሕር ዳር ደረሰች፡፡ ከዚያም የጀልባውን ባለቤት ‹‹እግዚአብሔርን ስለመውደድ አሻግረኝ›› ብላ ለመነችው፡፡ ባለጀልባውም ‹‹እነሆ ዕቃ የተጫኑ አምስት ግመሎችና ከአንቺ ጋር ከዚህም ሕፃን ጭምር አምስት ሰዎች እመለከታለሁ፣ አንቺ የተቀመጥሽባት በቅሎም አለች፡፡ ጀልባዋም ታናሽ ናት፣ የመቀመጫ ክፍሏም በውስጧ የተሳፈሩት ሰዎችም ተጨናንቀው ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ እንዴት ላሻግርሽ እችላለሁ? ነገር ግን እመቤቴ ሆይ! ይቅርታ አድርጊልኝ ይህን በክፋት አላደረግሁትምና›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችንም የጀልባው ባለቤት ሊያሻግራት እንዳልቻለ በተረዳች ጊዜ ‹‹ልጄ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ እንደመሆንህ ይህን ትልቅ ወንዝ ለመሻገር የአምላክነትህን ሥራ ትሠራ ዘንድ እለምንሃለሁ›› ስትል ማለደችው፡፡ ያንጊዜም ጌታችን ክብርት እናቱን ‹‹የወለደሽኝ እናቴ ሆይ! አትዘኝ›› ብሎ አረጋጋት፡፡ ዳግመኛም ‹‹በእኔ ፈቃድ በአባቴ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ካንቺ ሰው ሆኛለሁና ሰው መሆኔንም ከአባቴ በቀር መስተፍሥሒ ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስም በቀር ያወቀ የለም፡፡ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ለሁሉም እንደየሥራው እከፍለው ዘንድ እመጣለሁ፡፡ ያችንም ሰዓት የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ የአዳም ልጆችም ቢሆኑም ከእኔና ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስም በቀር የሚያውቃት የለም፡፡ ያንጊዜ ‹ዐመፅን የሚናገር አንደበት ሁሉ ይዘጋል› ብሎ አባትሽ ዳዊት እንደተናገረ እከራከራለሁ የሚል አንደበት እንደድዳ ምላሽ ያጣል›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችን ማርያምም ይህንን ሁሉ ምሥጢር የተወደደ ልጇ የነገራትን ታስተውለው በልቧም ትጠብቀው ነበር፡፡ ጌታችንም አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለክብርት እናቱ ይህንን ከነገራት በኋላ ቀኝ እጁን ዘርግቶ ከወንዙ ማዶ ጢር በሚባል ተራራ ያሉትን ድንጋዮች ጠቀሳቸው፡፡ ያንጊዜም እነዚህ ድንጋዮች እየተገለባበጡ መጥተው እንደ ጀልባ ሆነው በወራጁ ወንዝ ላይ ተንሳፈፉ፡፡ ከዚያም እመቤታችንን ከሕፃኑ ጋር ከነቤተሰቧና ከነጓዟ አሻገረሯት፡፡
እነዚህንም ድንጋዮች ያዩ ሰዎች ሁሉ እጅግ አድንቀው ‹‹ብቻውን ድንቅ ተአምራት ያደረገ፣ እስራኤልን የፈጠረ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን የጌትነቱም ስም የተመሰገነ ነው›› እያሉ አመሰገኑ፡፡ እነዚህም የተባረኩ ሰዎች ወንዙን ከተሻገሩ በኋላ በዚህች አገር ለስምንት ቀን ተቀመጡ፡፡ ከዚህም በኋላ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ስለደረገላት መልካም ሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽማ እያመሰገነች ወደ አባቷ ወደ ዳዊት አገር ተመለሰች፡፡
ዳግመኛም በኋለኛው ዘመን ጌታችን በዚህ በደብረ ቍስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸውና ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንን አክብሮ የቍርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው፡፡ ለዚህም ነገር የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮቹ ሆኑ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#ደብረ_ቁስቋም
ኅዳር ስድስት በዚህች ዕለት ክብርት እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ከስደት በሚመለሱበት ጊዜ ደብረ ቁስቋም ገብተው ካገኛቸው ድካም ዐረፉ፡፡
አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ከስደት በተመለሰች ጊዜ እንዲህ ሆነ፡- የብርሃን እናቱ ክብርት እመቤታችን ልጇን ይዛ ከእነ ዮሴፍ ጋር ወደ ምድረ ግብፅ ስትሰደድ ግብፅ ደርሰው በዚያ ቢቀመጡም ነገርን ግብፅ አልተመቸቻውም፡፡ ሕዝቡም በሰላም አልተቀበላቸውም፡፡ እንዲያውም በምድረ ግብፅ ብዙ ተሠቃይተዋል፡፡ ከግብፅም ተነሥተው ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ግን ኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በሰላምና በፍቅር ተቀበላቸው፡፡ ከመንገዱና ከርሃብ ጥሙ ጽናት የተነሣ እጅግ ደክማለችና የኢትዮጵያ ሰዎች እመቤታችንን አይተው እጅግ አዘኑላት፡፡ ‹‹ይህችስ የነገሥታት ዘር ትመሥላለች ነገር ግን አንዳች ችግር አጋጥሟት ተሰዳ ወደ ሀገራችን መጥታለች..›› ብለው እንክብካቤን አደረጉላት፡፡ እግራቸውን አጥበው በክብር ማረፊያዎች ላይ አሳረፏቸው፡፡ መልካም መስተንግዶም አደረጉላቸው፡፡ እመቤታችንም ከድካሟ ካረፈች በኋላ ሀገሪቱን በእጅጉ ወደደቻትና የተወደደ ልጇን ‹‹ይህን ሀገርና ሕዝቧን በመላ ወድጃቸዋልሁና በዚህ እስከ መጨረሻው እንኑር›› አለችው፡፡ ጌታችንም ክብርት እናቱን ‹‹ይህች ቅድስት ሀገር ናት፣ በኋለኛው ዘመን የቅዱሳን መነኮሳት ቦታ ትሆናለች፡፡ በውስጧም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እመሰገንባታለሁ፤ የአንቺም ስም ሳይጠራ አይውልባትም›› አላት፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን ደመና ጠቅሶ በእርሷ ላይ ተቀመጡ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም መጣና እየመራቸው መላ ኢትዮጵያን ጎበኟት፡፡ እመቤታችንም ሀገሪቱንና ሕዝቦቿን ወዳቸዋለች ደስም ተሰኝታባቸዋለችና ጌታችን ለክብርት እናቱ ‹‹ይህችን ቅድስት ሀገር አሥራት አድርጌ ሰጠሁሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም እጅግ ተደስታ ‹‹ልጄ አምላኬ›› ብላ አመሰገነችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ እየተዘዋወሩ መላዋ ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባረኳት፡፡ ጌታችንም ‹‹በዚህ ቦታ እንዲህ ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ እከሌ የሚባል እንዲህ ዓይነት ቅዱስ ይነሣል…›› እያለ ብዙ ምሥጢራትን ለክብርት እናቱ ነገራት፡፡ ከዚህም በኋላ የስደቱ ዘመን ሲያልፍ ሄሮድስም በመጨረሻ ክፉ አሟሟትን ሲሞት መልአኩ ወደ ገሊላ አውራጃ እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡ እመቤታችንም ‹‹ከዚህች ሀገርስ ባንሄድ እመርጣለሁ›› ስትለው የተወደደ ልጇ ግን ‹‹እናቴ ሆይ ጽድቅንና ፈቃድን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናል›› ብሎ አጽናናትና ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡
ተመልሰውም ሊሄዱ ሲነሡ የኢትዮጵያ ሰዎች ልዩ ልዩ አምሐ እጅ መንሻ ሰጧቸው፡፡ ልዩ ልዩ ልብሶች፣ ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ፣ ሽቱ እና ሥንቀቸውን በግመሎች ላይ ጭነው እመቤታችንንና የተወደደ ልጇንም በበቅሎ ላይ አስቀምጠው በክብር ሸኟቸው፡፡ እመቤታችንም ልጇን ታቅፋ በበቅሎ ተቀምጣ በበረሃው በመጓዝ ወደ መጣችበት አገር ሄደች፡፡ ኢትዮጵያንም የሰጧትን ብዙ እጅ መንሻዎች በግመሎች ጭና ይዛ ወደ አገሯ በተመለሰች ጊዜ ከአንድ ባሕር ዳር ደረሰች፡፡ ከዚያም የጀልባውን ባለቤት ‹‹እግዚአብሔርን ስለመውደድ አሻግረኝ›› ብላ ለመነችው፡፡ ባለጀልባውም ‹‹እነሆ ዕቃ የተጫኑ አምስት ግመሎችና ከአንቺ ጋር ከዚህም ሕፃን ጭምር አምስት ሰዎች እመለከታለሁ፣ አንቺ የተቀመጥሽባት በቅሎም አለች፡፡ ጀልባዋም ታናሽ ናት፣ የመቀመጫ ክፍሏም በውስጧ የተሳፈሩት ሰዎችም ተጨናንቀው ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ እንዴት ላሻግርሽ እችላለሁ? ነገር ግን እመቤቴ ሆይ! ይቅርታ አድርጊልኝ ይህን በክፋት አላደረግሁትምና›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችንም የጀልባው ባለቤት ሊያሻግራት እንዳልቻለ በተረዳች ጊዜ ‹‹ልጄ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ እንደመሆንህ ይህን ትልቅ ወንዝ ለመሻገር የአምላክነትህን ሥራ ትሠራ ዘንድ እለምንሃለሁ›› ስትል ማለደችው፡፡ ያንጊዜም ጌታችን ክብርት እናቱን ‹‹የወለደሽኝ እናቴ ሆይ! አትዘኝ›› ብሎ አረጋጋት፡፡ ዳግመኛም ‹‹በእኔ ፈቃድ በአባቴ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ካንቺ ሰው ሆኛለሁና ሰው መሆኔንም ከአባቴ በቀር መስተፍሥሒ ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስም በቀር ያወቀ የለም፡፡ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ለሁሉም እንደየሥራው እከፍለው ዘንድ እመጣለሁ፡፡ ያችንም ሰዓት የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ የአዳም ልጆችም ቢሆኑም ከእኔና ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስም በቀር የሚያውቃት የለም፡፡ ያንጊዜ ‹ዐመፅን የሚናገር አንደበት ሁሉ ይዘጋል› ብሎ አባትሽ ዳዊት እንደተናገረ እከራከራለሁ የሚል አንደበት እንደድዳ ምላሽ ያጣል›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችን ማርያምም ይህንን ሁሉ ምሥጢር የተወደደ ልጇ የነገራትን ታስተውለው በልቧም ትጠብቀው ነበር፡፡ ጌታችንም አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለክብርት እናቱ ይህንን ከነገራት በኋላ ቀኝ እጁን ዘርግቶ ከወንዙ ማዶ ጢር በሚባል ተራራ ያሉትን ድንጋዮች ጠቀሳቸው፡፡ ያንጊዜም እነዚህ ድንጋዮች እየተገለባበጡ መጥተው እንደ ጀልባ ሆነው በወራጁ ወንዝ ላይ ተንሳፈፉ፡፡ ከዚያም እመቤታችንን ከሕፃኑ ጋር ከነቤተሰቧና ከነጓዟ አሻገረሯት፡፡
እነዚህንም ድንጋዮች ያዩ ሰዎች ሁሉ እጅግ አድንቀው ‹‹ብቻውን ድንቅ ተአምራት ያደረገ፣ እስራኤልን የፈጠረ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን የጌትነቱም ስም የተመሰገነ ነው›› እያሉ አመሰገኑ፡፡ እነዚህም የተባረኩ ሰዎች ወንዙን ከተሻገሩ በኋላ በዚህች አገር ለስምንት ቀን ተቀመጡ፡፡ ከዚህም በኋላ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ስለደረገላት መልካም ሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽማ እያመሰገነች ወደ አባቷ ወደ ዳዊት አገር ተመለሰች፡፡
ዳግመኛም በኋለኛው ዘመን ጌታችን በዚህ በደብረ ቍስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸውና ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንን አክብሮ የቍርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው፡፡ ለዚህም ነገር የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮቹ ሆኑ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የምንኩስና ሕይወት አጀማመርና ዕድገት
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂድና ያለህን ሁሉ ሸጠህ ለድሆች ስጥና ተከተለኝ» «ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ካጣ ምን ይጠቅመዋል?» ብሎ የተናገራቸውን ቃል እንደ እቃ ጦር ታጥቀው የዚህን ዓለም ኃላፊነትና ጠፊነት በሚገባ ተረድተው አእምሯቸውን ጥበብ መንፈሳዊ ማለትም ይህንን ዓለም በመናቅ አበልጽገው የኖሩ የሚኖሩ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ሃይማኖትና ምግባር እንደ ነፍስና ሥጋ የተዋሐደላቸው እግዚአብሔር የሚወደውን ብቻ የሚወዱ እርሱ ባዘጋጀላቸው መንገድ ተጉዘው ከመርገመ ኃጥአው እና ከፍትወታት እኩያት ታግሰው ያሸነፉና ሕጉንና ትእዛዙን የፈጸሙ ለመፈጸም በቦታ ተወስነው የሚኖሩት መነኮሳት ይባላሉ፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ወፍ ዘራሽ የመጣ ሳይሆን ትንቢት ተነግሮለት ምሳሌ ተመስሎለት የመጣ ነው እንጂ፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር ምሳሌ በሕገ ልቡናና በብሉይ ኪዳን ዘመን
ምንም እንኳን ሕግ ወጥቶለት ሥርዓት ተሠርቶለት የተጀመረው በዘመነ ሐዲስ ቢሆንም በቀድሞ ዘመን በሕገ ልቡና በዘመነ ብሉይ ለምንኩስና ሕይወት ምሳሌ የሚሆኑ ከሴት ርቀው ንጽሕና ጠብቀው በምስጋና ጸንተው በደብር ቅዱስ ሲኖሩ የነበሩት ደቂቀ ሴት፣ ሄኖክ በዚህ ዓለም ልጆችን ከወለደ በኋላ ይህ አናኗር ለመንፈሳዊ ፍላጎቱ አጥጋቢ ሆኖ ስላላገኘው የብሕትውና ኑሮ ጀምሯል፡፡ ዘፍ.5÷24 በተጨማሪም መልከጼዴቅ፤ ኤልያስ፣ መጥምቁ ዮሐንስ። ከሴት ወገን በምንኩስና ሕይወት የምትታወቀው ነብይት ሃና ሉቃስ 2÷36 በአጠቃላይ በሕገ ልቡና ለምንኩስና ሕይወት ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር በሐዲስ ኪዳን
በዘመነ ሐዲስ ለገዳማዊ ሕይወት ለምንኩስናና ለብሕትውና ጀማሪውና መሪው መምህረ ትህትና ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይኸውም እንደተጠመቀ ወዲያው ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ምንም ነገር ሳይቀምስ በተባሕትዎ ቆይቷል። በዚህም ለባሕታውያን ብሕትውናን ባርኮና ቀድሶ ሰጥቶአል፡፡ እንዲሁም በድንግልና በመኖር ለደናግልና ለመነኮሳት አብነትና መምህር ሆኗል።
ጌታችን በሚያስተምርበት ዘመን ካደረበት የሚያድሩ ከዋለበት የሚውሉ ከእርሱ የማይለዩ መቶ ሃያ ቤተሰብ እንዲሁም የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ለምንኩስና ሕይወት በዘመነ ሐዲስ ምሳሌ ናቸው፡፡
የሥርዓተ ምንኩስና አጀማመር
ምንኩስና ማለት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም በዓለም ያለውን ማንኛውም ነገር ትቶ በቆብ ቃልኪዳን የገባ የሞተ፣ የተለየ፣ ዓለምን የረሳ፣ ራሱን የጠላ ማለት ነው፡፡ በተመሳሳይ ዓላማና ሕይወት በአንድነት የሚኖሩ «ማኅበረ መነኮሳት» ይባላሉ፡፡ በማኅበር ሲራዱና ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ከሰው ተለይተው ቦታ ወስነው ብቻቸውን የሚኖሩት ባሕታውያን ይባላሉ፡፡ ከአንድነት ገዳም ርቀው በሚገኙ አንዳንድ ጫካዎችና ዋሻዎች እንደ መልከጼዴቅና እንደ ዮሐንስ መጥምቅ ከሰው ጋራ ሳይገናኙ የሚኖሩ የተለየ አለባበስና አስፈሪ ግርማ ሞገስ ያላቸው ባሕታውያንም አሉ፡፡ እነዚህ ዓይነቱ ባሕታውያን በኅብረተሰቡ አጠራር «ግሑሳን» ይባላሉ፡፡ «ግሑስ» ማለት ከሰው ርቆ የሚኖር ባሕታዊ ማለት ነው፡፡
በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያው ባሕታዊ ቅዱስ ጳውሊ ሲሆኑ ነገር ግን ሕግና ሥርዓት አውጥተውለት እንዲሰፋ ያደርጉት አባ እንጦንዮስ ናቸው፡፡ አባ ጳኩሚስ፤ መቃርስ፣ ዮሐንስ ሐፂር ተነስተው ለምንኩስና መስፋፋት ከፍተኛውን አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ፍጹም ልትሆን ብትወድ ሂድና ያለህን ሁሉ ሸጠህ ለድሆች ስጥና ተከተለኝ» «ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ካጣ ምን ይጠቅመዋል?» ብሎ የተናገራቸውን ቃል እንደ እቃ ጦር ታጥቀው የዚህን ዓለም ኃላፊነትና ጠፊነት በሚገባ ተረድተው አእምሯቸውን ጥበብ መንፈሳዊ ማለትም ይህንን ዓለም በመናቅ አበልጽገው የኖሩ የሚኖሩ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ሃይማኖትና ምግባር እንደ ነፍስና ሥጋ የተዋሐደላቸው እግዚአብሔር የሚወደውን ብቻ የሚወዱ እርሱ ባዘጋጀላቸው መንገድ ተጉዘው ከመርገመ ኃጥአው እና ከፍትወታት እኩያት ታግሰው ያሸነፉና ሕጉንና ትእዛዙን የፈጸሙ ለመፈጸም በቦታ ተወስነው የሚኖሩት መነኮሳት ይባላሉ፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ወፍ ዘራሽ የመጣ ሳይሆን ትንቢት ተነግሮለት ምሳሌ ተመስሎለት የመጣ ነው እንጂ፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር ምሳሌ በሕገ ልቡናና በብሉይ ኪዳን ዘመን
ምንም እንኳን ሕግ ወጥቶለት ሥርዓት ተሠርቶለት የተጀመረው በዘመነ ሐዲስ ቢሆንም በቀድሞ ዘመን በሕገ ልቡና በዘመነ ብሉይ ለምንኩስና ሕይወት ምሳሌ የሚሆኑ ከሴት ርቀው ንጽሕና ጠብቀው በምስጋና ጸንተው በደብር ቅዱስ ሲኖሩ የነበሩት ደቂቀ ሴት፣ ሄኖክ በዚህ ዓለም ልጆችን ከወለደ በኋላ ይህ አናኗር ለመንፈሳዊ ፍላጎቱ አጥጋቢ ሆኖ ስላላገኘው የብሕትውና ኑሮ ጀምሯል፡፡ ዘፍ.5÷24 በተጨማሪም መልከጼዴቅ፤ ኤልያስ፣ መጥምቁ ዮሐንስ። ከሴት ወገን በምንኩስና ሕይወት የምትታወቀው ነብይት ሃና ሉቃስ 2÷36 በአጠቃላይ በሕገ ልቡና ለምንኩስና ሕይወት ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው፡፡
የምንኩስና ሕይወት አጀማመር በሐዲስ ኪዳን
በዘመነ ሐዲስ ለገዳማዊ ሕይወት ለምንኩስናና ለብሕትውና ጀማሪውና መሪው መምህረ ትህትና ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይኸውም እንደተጠመቀ ወዲያው ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ምንም ነገር ሳይቀምስ በተባሕትዎ ቆይቷል። በዚህም ለባሕታውያን ብሕትውናን ባርኮና ቀድሶ ሰጥቶአል፡፡ እንዲሁም በድንግልና በመኖር ለደናግልና ለመነኮሳት አብነትና መምህር ሆኗል።
ጌታችን በሚያስተምርበት ዘመን ካደረበት የሚያድሩ ከዋለበት የሚውሉ ከእርሱ የማይለዩ መቶ ሃያ ቤተሰብ እንዲሁም የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ለምንኩስና ሕይወት በዘመነ ሐዲስ ምሳሌ ናቸው፡፡
የሥርዓተ ምንኩስና አጀማመር
ምንኩስና ማለት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም በዓለም ያለውን ማንኛውም ነገር ትቶ በቆብ ቃልኪዳን የገባ የሞተ፣ የተለየ፣ ዓለምን የረሳ፣ ራሱን የጠላ ማለት ነው፡፡ በተመሳሳይ ዓላማና ሕይወት በአንድነት የሚኖሩ «ማኅበረ መነኮሳት» ይባላሉ፡፡ በማኅበር ሲራዱና ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ከሰው ተለይተው ቦታ ወስነው ብቻቸውን የሚኖሩት ባሕታውያን ይባላሉ፡፡ ከአንድነት ገዳም ርቀው በሚገኙ አንዳንድ ጫካዎችና ዋሻዎች እንደ መልከጼዴቅና እንደ ዮሐንስ መጥምቅ ከሰው ጋራ ሳይገናኙ የሚኖሩ የተለየ አለባበስና አስፈሪ ግርማ ሞገስ ያላቸው ባሕታውያንም አሉ፡፡ እነዚህ ዓይነቱ ባሕታውያን በኅብረተሰቡ አጠራር «ግሑሳን» ይባላሉ፡፡ «ግሑስ» ማለት ከሰው ርቆ የሚኖር ባሕታዊ ማለት ነው፡፡
በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያው ባሕታዊ ቅዱስ ጳውሊ ሲሆኑ ነገር ግን ሕግና ሥርዓት አውጥተውለት እንዲሰፋ ያደርጉት አባ እንጦንዮስ ናቸው፡፡ አባ ጳኩሚስ፤ መቃርስ፣ ዮሐንስ ሐፂር ተነስተው ለምንኩስና መስፋፋት ከፍተኛውን አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#በስድብ_ፈንታ_አመስግኑ
ብዙ ጊዜ ስንሳደብ እና መጥፎ ቋንቋ ስንጠቀም “እኔ ይህን አለማድረግ አልችልም ልማዴ ነው" እንላለን፡፡ እናም ሲጎዱን አንድ ነገር መናገር ካለብንም፣ በስድብ ፈንታ ምስጋና መናገርን እራሳችንን እናስተምር።
ነገር ግን፣ ሰው እያሰቃየኝ ዝም ማለት አልችልም ትላለህ፡፡ ከመናገርም አልከለክልህም፡፡ ሆኖም ከመሳደብ ይልቅ ምስጋናን ተናገር፡፡ ከመበሳጨት ይልቅ ምስጋናህን ግለጽ፡፡
ለጌታህ መናዘዝ ትችላለህ፡፡ በጸሎትህ ውስጥ ጩኽ፤ እንዲሁ መከራህን ያቀልልሃል፣ ፈታኙም ሰይጣን በምስጋናህ ውስጥ ይሸሻል፣ የእግዚአብሔርም እርዳታ ወዳንተ ይቀርባል። ከተሳደብክ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ ትከለክላለህ፤ እናም ፈታኙ በአንተ ላይ እንዲበረታ ታደርጋለህ፤ በዚያም እራስህን የበለጠ በህመም ውስጥ ታስገባለህ፡፡ ብታመስግን ግን የክፉ መንፈስን ጥቃት ትቃወማለህ፡፡
ነገር ግን ምላስ ብዙውን ጊዜ በልማድ ኃይል አንዳንድ መጥፎ ቃላትን ከመናገር ወደኋላ ማለት አይችልም። ከዚያም በምትወድቅበት ጊዜ ኹሉ ቃሉ ከመናገርህ በፊት ጥርሶችህን ጠብቀው ይዘጉ፡፡ ምላስህ የደም ጠብታ ብታፈስስ ይሻላታል፤ ከስድብም በኋላ የማያቋርጥ ቅጣት ከምትቀበል በጊዜው ሥቃይን ብትታገሥ ይሻልሃልና፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ብዙ ጊዜ ስንሳደብ እና መጥፎ ቋንቋ ስንጠቀም “እኔ ይህን አለማድረግ አልችልም ልማዴ ነው" እንላለን፡፡ እናም ሲጎዱን አንድ ነገር መናገር ካለብንም፣ በስድብ ፈንታ ምስጋና መናገርን እራሳችንን እናስተምር።
ነገር ግን፣ ሰው እያሰቃየኝ ዝም ማለት አልችልም ትላለህ፡፡ ከመናገርም አልከለክልህም፡፡ ሆኖም ከመሳደብ ይልቅ ምስጋናን ተናገር፡፡ ከመበሳጨት ይልቅ ምስጋናህን ግለጽ፡፡
ለጌታህ መናዘዝ ትችላለህ፡፡ በጸሎትህ ውስጥ ጩኽ፤ እንዲሁ መከራህን ያቀልልሃል፣ ፈታኙም ሰይጣን በምስጋናህ ውስጥ ይሸሻል፣ የእግዚአብሔርም እርዳታ ወዳንተ ይቀርባል። ከተሳደብክ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ ትከለክላለህ፤ እናም ፈታኙ በአንተ ላይ እንዲበረታ ታደርጋለህ፤ በዚያም እራስህን የበለጠ በህመም ውስጥ ታስገባለህ፡፡ ብታመስግን ግን የክፉ መንፈስን ጥቃት ትቃወማለህ፡፡
ነገር ግን ምላስ ብዙውን ጊዜ በልማድ ኃይል አንዳንድ መጥፎ ቃላትን ከመናገር ወደኋላ ማለት አይችልም። ከዚያም በምትወድቅበት ጊዜ ኹሉ ቃሉ ከመናገርህ በፊት ጥርሶችህን ጠብቀው ይዘጉ፡፡ ምላስህ የደም ጠብታ ብታፈስስ ይሻላታል፤ ከስድብም በኋላ የማያቋርጥ ቅጣት ከምትቀበል በጊዜው ሥቃይን ብትታገሥ ይሻልሃልና፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#የተቀደደ_መጽሐፍ
መጽሐፍት ሙሉ መልዕክት የሚኖራቸው ሙሉውን ክፍል እስካነበብን ድረስ ነው። የአንድን መጽሐፍ አንድ ገጽ መቅደድ የመልዕክቱን ሙሉነት ያሳንሰዋል። ብዙ መጽሐፍ ማንበብ የሚወዱ ሰዎች መጽሐፍ ሲቀደድ ሲያዩ የመታገስ ጽዋቸው ሞልቶ ለቁጣ ይጋበዛሉ። ያነበብቱ በዚህ ልክ ከተሰማቸው የመጽሐፉ ጸሓፊ ደግሞ እንዴት ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም። አንዳንድ ጸሓፊዎች መጽሐፋቸውን ልጄ ብለው በመጥራት ለልጃቸው የሚያደርጉትን ጥንቃቄ ሁሉ ለመጽሐፋቸው ሲያደርጉ ይስተዋላሉ።
እግዚአብሔር ቃሉ እንዲጻፍ ለምን የፈለገ ይመስላችኋል? ሳይጻፍ ቀርቶ በንግርት ወይም ከሰዎች ምላስ ላይ እንዲደመጥ አድርጎስ ቢሆን? እንዲ ቢሆን ኖሮ በዚህ ዘመን የምንሰማው ቃል ጥቂት የእግዚአብሔር ይሆንና እልፍ የሰዎች ይሆናል። የተወሰኑ 20 ሰዎችን ደርድረን ለመጀመሪያው ረዘም ያለ መልዕክት ነግረነው ለሁለተኛው እንዲነግረው ሁለተኛውም ለሶስተኛው..... 20ኛው ሰው እስኪ የሰማኸውን ንገረን ብንለው ከዋናው መልዕክት በጣም ጥቂት ቃላት ከ19ኙ ሰዎች ብዙ ስህተት የሆነ ቃላትን ገጣጥሞ ይነግረናል።
በንግርት የሚያልፍ መልዕክት አይደለም ከትውልድ ወደ ትውልድ በሙሉነቱ ሊሸጋገር ቀርቶ በአንድ ትውልድ ውስጥ ባሉ ሰዎች እንኳን በትክክል ለመተላለፍ ይቸገራል። የእግዚአብሔር ቃሉ በንግርት የተቀመጠ ቢሆን ነገስታት ያራቸውን ክብር ለመጨመር ቃሉ ላይ በጨመሩ ነበር፣ ተናጋሪዎቹ የሰሙትን እንደሚረዱት መጠን ባስተላለፉት ነበር። ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል መጻፍ ዋና ጉዳይ መልዕክቱ ትክክለኛነቱን እንደጠበቀ ዘመናትን እንዲሻገር ነው።
ይኸው ስለተጻፈ በዚህ ዘመን ያለን ሰዎች በዛ ዘመን የተሰበከውን የእውነት ቃል ለማንበብ እና በቅዱሱ መንፈስ አማካኝነት ደግሞ ለመረዳት በቅተናል። እረ እንኳንም ተጻፈ። የመልዕክቱ ርዕስ የተቀደደ መጽሐፍ ስለሚል ከርዕሴ እንዳልወጣ ስለመጻፉ አስፈላጊነት ብዙ አልበል። ብዙ ሰዎች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ቅዱሱን የእግዚአብሔር ቃል በመቅደድ ተግባር ላይ ናቸው። መርጠው ይሰማሉ፣ ከፍለው ያነባሉ፣ ቆንጽለው ይረዳሉ፣ የተመቻቸውን ክፍል ብቻ ልክ ይላሉ፣ እንደልባቸው ይተረጉማሉ ይሄ ነው መጽሐፉን መቅደድ የሚባለው።
አሁን አሁንማ ከሰዎችም አልፎ ተርፎ ቤተ እምነቶችም ለራሳቸው አስተምህሮ እንዲመች አድርገው መጽሐፉን ይቀዳሉ ግሪኩ እንዲ ይላል በማለት የራሳቸውን ያስቀምጣሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ የአፍ መፍቻ ቋንቋ የዕብራስጥ እና የግሪክ ቋንቋ እንደሆነ መረዳት ያሻል። መጽሐፉ ልክ ሲጻፍ እንዲ ይላል ብሎ ሌላ መጽሐፍ መጽሐፉን መቅደድ ካልተባለ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም።
ከመሃል መርጠን የተረዳነውን ቃል እስኪ ከነሙሉ መልዕክቱ ለመረዳት ልባችንን ክፍት እናድርግ ያኔ የቀደድናቸው ክፍሎች ይታዩናል። አንድ ጸሓፊ የጻፈው መጽሐፍ ሲቀደድበት ማያትን ካልፈለገ የመጽሐፍ ቅዱስ ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር መጽሐፉ ሲቀደድ ምን ይሰማው ይሆን? የእግዚአብሔር ከሆነው ነገር ከመጉደል በላይ መጉደል ወዴት አለ? የእግዚአብሔርን ሃሳብ በሙሉነቱ ካልመረዳት በላይ መጎዳትስ ከዬት ይገኛል?
ስለእግዚአብሔር ቃል ያለን መረዳት ስለዘላለማችን ይወስናልና መረዳታችን በተገቢው መልኩ መፈተሽ ያስፈልጋል። የእግዚአብሔር ሆኖ የማይገባን ነገር እንዳይኖር መትጋት በጣም አስፈላጊ ነው። የእግዚአብሔር የልቡ ሃሳብ ያለው የትም አይደለም ቅዱሱ መጽሐፍ ላይ ነው። ከዚህ ክፍል አንዱን ገጽ መቅደድ በእግዚአብሔር በልቡ ሃሳብ ላይ ማሾፍ ነው። እናማ አትቅደዱ አንቅደድ። በተቻለን ሁሉ ከዚህ ቃል የማይገባን እንዳይኖር እግዚአብሔር መረዳታችንን እንዲረዳው መጸለይ እና ቃሉን ማንበብ የሁል ጊዜ ስራችን ይሁን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
መጽሐፍት ሙሉ መልዕክት የሚኖራቸው ሙሉውን ክፍል እስካነበብን ድረስ ነው። የአንድን መጽሐፍ አንድ ገጽ መቅደድ የመልዕክቱን ሙሉነት ያሳንሰዋል። ብዙ መጽሐፍ ማንበብ የሚወዱ ሰዎች መጽሐፍ ሲቀደድ ሲያዩ የመታገስ ጽዋቸው ሞልቶ ለቁጣ ይጋበዛሉ። ያነበብቱ በዚህ ልክ ከተሰማቸው የመጽሐፉ ጸሓፊ ደግሞ እንዴት ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም። አንዳንድ ጸሓፊዎች መጽሐፋቸውን ልጄ ብለው በመጥራት ለልጃቸው የሚያደርጉትን ጥንቃቄ ሁሉ ለመጽሐፋቸው ሲያደርጉ ይስተዋላሉ።
እግዚአብሔር ቃሉ እንዲጻፍ ለምን የፈለገ ይመስላችኋል? ሳይጻፍ ቀርቶ በንግርት ወይም ከሰዎች ምላስ ላይ እንዲደመጥ አድርጎስ ቢሆን? እንዲ ቢሆን ኖሮ በዚህ ዘመን የምንሰማው ቃል ጥቂት የእግዚአብሔር ይሆንና እልፍ የሰዎች ይሆናል። የተወሰኑ 20 ሰዎችን ደርድረን ለመጀመሪያው ረዘም ያለ መልዕክት ነግረነው ለሁለተኛው እንዲነግረው ሁለተኛውም ለሶስተኛው..... 20ኛው ሰው እስኪ የሰማኸውን ንገረን ብንለው ከዋናው መልዕክት በጣም ጥቂት ቃላት ከ19ኙ ሰዎች ብዙ ስህተት የሆነ ቃላትን ገጣጥሞ ይነግረናል።
በንግርት የሚያልፍ መልዕክት አይደለም ከትውልድ ወደ ትውልድ በሙሉነቱ ሊሸጋገር ቀርቶ በአንድ ትውልድ ውስጥ ባሉ ሰዎች እንኳን በትክክል ለመተላለፍ ይቸገራል። የእግዚአብሔር ቃሉ በንግርት የተቀመጠ ቢሆን ነገስታት ያራቸውን ክብር ለመጨመር ቃሉ ላይ በጨመሩ ነበር፣ ተናጋሪዎቹ የሰሙትን እንደሚረዱት መጠን ባስተላለፉት ነበር። ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል መጻፍ ዋና ጉዳይ መልዕክቱ ትክክለኛነቱን እንደጠበቀ ዘመናትን እንዲሻገር ነው።
ይኸው ስለተጻፈ በዚህ ዘመን ያለን ሰዎች በዛ ዘመን የተሰበከውን የእውነት ቃል ለማንበብ እና በቅዱሱ መንፈስ አማካኝነት ደግሞ ለመረዳት በቅተናል። እረ እንኳንም ተጻፈ። የመልዕክቱ ርዕስ የተቀደደ መጽሐፍ ስለሚል ከርዕሴ እንዳልወጣ ስለመጻፉ አስፈላጊነት ብዙ አልበል። ብዙ ሰዎች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ቅዱሱን የእግዚአብሔር ቃል በመቅደድ ተግባር ላይ ናቸው። መርጠው ይሰማሉ፣ ከፍለው ያነባሉ፣ ቆንጽለው ይረዳሉ፣ የተመቻቸውን ክፍል ብቻ ልክ ይላሉ፣ እንደልባቸው ይተረጉማሉ ይሄ ነው መጽሐፉን መቅደድ የሚባለው።
አሁን አሁንማ ከሰዎችም አልፎ ተርፎ ቤተ እምነቶችም ለራሳቸው አስተምህሮ እንዲመች አድርገው መጽሐፉን ይቀዳሉ ግሪኩ እንዲ ይላል በማለት የራሳቸውን ያስቀምጣሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ የአፍ መፍቻ ቋንቋ የዕብራስጥ እና የግሪክ ቋንቋ እንደሆነ መረዳት ያሻል። መጽሐፉ ልክ ሲጻፍ እንዲ ይላል ብሎ ሌላ መጽሐፍ መጽሐፉን መቅደድ ካልተባለ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም።
ከመሃል መርጠን የተረዳነውን ቃል እስኪ ከነሙሉ መልዕክቱ ለመረዳት ልባችንን ክፍት እናድርግ ያኔ የቀደድናቸው ክፍሎች ይታዩናል። አንድ ጸሓፊ የጻፈው መጽሐፍ ሲቀደድበት ማያትን ካልፈለገ የመጽሐፍ ቅዱስ ባለቤት የሆነው እግዚአብሔር መጽሐፉ ሲቀደድ ምን ይሰማው ይሆን? የእግዚአብሔር ከሆነው ነገር ከመጉደል በላይ መጉደል ወዴት አለ? የእግዚአብሔርን ሃሳብ በሙሉነቱ ካልመረዳት በላይ መጎዳትስ ከዬት ይገኛል?
ስለእግዚአብሔር ቃል ያለን መረዳት ስለዘላለማችን ይወስናልና መረዳታችን በተገቢው መልኩ መፈተሽ ያስፈልጋል። የእግዚአብሔር ሆኖ የማይገባን ነገር እንዳይኖር መትጋት በጣም አስፈላጊ ነው። የእግዚአብሔር የልቡ ሃሳብ ያለው የትም አይደለም ቅዱሱ መጽሐፍ ላይ ነው። ከዚህ ክፍል አንዱን ገጽ መቅደድ በእግዚአብሔር በልቡ ሃሳብ ላይ ማሾፍ ነው። እናማ አትቅደዱ አንቅደድ። በተቻለን ሁሉ ከዚህ ቃል የማይገባን እንዳይኖር እግዚአብሔር መረዳታችንን እንዲረዳው መጸለይ እና ቃሉን ማንበብ የሁል ጊዜ ስራችን ይሁን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የፍቅር ሥራ ይህች ናት
ባልንጀራውን የሚረዳውን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ይረዳዋል፡፡ ለወንድሙ የሚነቀፍበትን ስም የሚያወጣውን ፈታሒ በርትዕ እግዚአብሔር እንዲሰደብ ያደርገዋል፡፡ ክፉ ስለ ሠራ ወንድሙን በቤቱ ለብቻው ሆኖ የሚመክረው ሰው ግን በምክሩ ዐዋቂ ይሆናል፡፡ ወንድሙን በዐደባባይ የነቀፈ ግን ኀዘን ያጸናበታል፡፡ ከሰው ተለይቶ ወንድሙን የሚመክር ሰው እነሆ የፍቅሩን ብዛት ያስረዳል፤ በባልንጀሮቹ ፊት የሚነቅፈው ግን የቅናቱን ጽናት ያስረዳል፣ የምቀኝነቱን ጽናት አስረዳ፡፡
ወዳጁን ተሠውሮ የሚመክር ሰው ብልህ ባለመድኃኒት ነው:: ያ እንዳዳነው መክሮ አስተምሮ ያድነዋልና፡፡ ወንድሙን በብዙ ሰው ፊት የሚያመሰግነው ሰው እሱ እውነተኛ ጠላቱ ነው፣ በውዳሴ ከንቱ ይጎዳ ብሎ ነውና።
ኀዘን ያለበት የርሕራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለት ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው፡፡ ወደ ክብር የሚያደርስ ረብህ ጥቅም ያግኝ ብሎ የሚመክር፣ የሚያስተምር በፍቅር ይመክረዋል፣ ያስተምረዋል፡፡ ቂም በቀል የሚሻ ሰው ፍቅር የለውም፡፡ አንድም እበቀለዋለሁ ብሎ የሚመክር ከፍቅር የተለየ ነው፡፡
ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር በፍቅር ይመክራል፣ ያስተምራል፣ እበቀላለሁ ብሎ ያይደል፡፡ እሱስ በምሳሌው የተፈጠረው ሰውን ለማዳን ይገሥጻል፡፡ አንድ ጊዜስ እንኳን ቂም አይዝም፣ መዓትን አያዘጋጅም፡፡ የፍቅር ሥራ ይህች ናት፣ በቅንነት ትገኛለች፡፡ ቂም ለመያዝ እበቀላለሁ አትልም፣ በፍቅር ሰውን መናገር ነው።
ብልህ የሚሆን ቅን ሰው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይመስለዋል፡፡ ሰውን ክፉ ስላደረገ እበቀለዋለሁ ብሎ አይገሥጸውም፣ ሊመክረው ወዶ ነው እንጂ ሌሎችንም ለማስፈራት ነው እንጂ። ተግሣጽስ በፍቅር ካልሆነ ተግሣጽ አይባልም፡፡ በጎ ነገር ያደርግልኛል ብሎ በጎ የሚሠራ ኋላ ፈጥኖ ይተዋል፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ባልንጀራውን የሚረዳውን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ይረዳዋል፡፡ ለወንድሙ የሚነቀፍበትን ስም የሚያወጣውን ፈታሒ በርትዕ እግዚአብሔር እንዲሰደብ ያደርገዋል፡፡ ክፉ ስለ ሠራ ወንድሙን በቤቱ ለብቻው ሆኖ የሚመክረው ሰው ግን በምክሩ ዐዋቂ ይሆናል፡፡ ወንድሙን በዐደባባይ የነቀፈ ግን ኀዘን ያጸናበታል፡፡ ከሰው ተለይቶ ወንድሙን የሚመክር ሰው እነሆ የፍቅሩን ብዛት ያስረዳል፤ በባልንጀሮቹ ፊት የሚነቅፈው ግን የቅናቱን ጽናት ያስረዳል፣ የምቀኝነቱን ጽናት አስረዳ፡፡
ወዳጁን ተሠውሮ የሚመክር ሰው ብልህ ባለመድኃኒት ነው:: ያ እንዳዳነው መክሮ አስተምሮ ያድነዋልና፡፡ ወንድሙን በብዙ ሰው ፊት የሚያመሰግነው ሰው እሱ እውነተኛ ጠላቱ ነው፣ በውዳሴ ከንቱ ይጎዳ ብሎ ነውና።
ኀዘን ያለበት የርሕራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለት ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው፡፡ ወደ ክብር የሚያደርስ ረብህ ጥቅም ያግኝ ብሎ የሚመክር፣ የሚያስተምር በፍቅር ይመክረዋል፣ ያስተምረዋል፡፡ ቂም በቀል የሚሻ ሰው ፍቅር የለውም፡፡ አንድም እበቀለዋለሁ ብሎ የሚመክር ከፍቅር የተለየ ነው፡፡
ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር በፍቅር ይመክራል፣ ያስተምራል፣ እበቀላለሁ ብሎ ያይደል፡፡ እሱስ በምሳሌው የተፈጠረው ሰውን ለማዳን ይገሥጻል፡፡ አንድ ጊዜስ እንኳን ቂም አይዝም፣ መዓትን አያዘጋጅም፡፡ የፍቅር ሥራ ይህች ናት፣ በቅንነት ትገኛለች፡፡ ቂም ለመያዝ እበቀላለሁ አትልም፣ በፍቅር ሰውን መናገር ነው።
ብልህ የሚሆን ቅን ሰው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይመስለዋል፡፡ ሰውን ክፉ ስላደረገ እበቀለዋለሁ ብሎ አይገሥጸውም፣ ሊመክረው ወዶ ነው እንጂ ሌሎችንም ለማስፈራት ነው እንጂ። ተግሣጽስ በፍቅር ካልሆነ ተግሣጽ አይባልም፡፡ በጎ ነገር ያደርግልኛል ብሎ በጎ የሚሠራ ኋላ ፈጥኖ ይተዋል፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#ሺ_ጊዜ
ሺ ጊዜ ኃጢያት ስራ ነገር ግን ንስሃ ከመግባት አትቦዝን። የፈጠረህ እግዚአብሔር ጨርሶ አንተን መማር አይሰለችምና። እልፍ ጊዜ በድል ነገር ግን ከእግዚአብሔር አትኮብልል። ምክንያቱም እግዚአብሔር የደበሉ ወደ እርሱ የሚሸሸጉበት ዕሩሩህ እንጂ የሚሸሹት ጨካኝ አይደለምና።
በጣም ለቁጥር እንኳን በሚታክት ጥፋት ውስጥ ሁን ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከእግሩ ስር አትጥፋ። እግሩ ስር ስትሆን ክብር አለህና በጥፋትህ ብዛት እኔ እንዴት ወደ እግዚአብሔር እቀርባለሁ ብለህ አትራቅ። እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንድትቀርብ ልጁን ለአንተ ሲል በመስቀል ሰውቶታልና።
ጉድ የሚያስብል ጉድ ውስጥም ሁን ነገር ግን ገበናህን ከሚሸሸግልህ ከእግዚአብሔር አትሸፍት። የሁሉ ሰው ተግባር በእግዚአብሔር ፊት ግልጥ ነው። እግዚአብሔር ሁሉንም ነገርህን እያወቀ ዝም የሚልህ ስለሚምርህ ነው እንጂ ለኃጢአትህ መዝገብ አዘጋጅቶ አይደለም።
ኃጢአቴ ብዙ ነው ብትልም የኃጢአትህ ክምር በጭራሽ እግዚአብሔርን እንዳይሸሽግህ። ከበደልህ ይልቅ የሞተልህን ተመልከት። እግዚአብሔር የኃጥዓን መፍትሔ ነው። ችግር ውስጥ እንዳለህ በተሰማ ቁጥር ወደ ባለመፍትሔው ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እጅግ ማትረፊያ ነው። ኃጢአት የሰው ልጅ ሁሉ ችግር ነውና።
የራስህን መንገድ ብትከተል ጨርሶ ልትወጣው ወደማትችለው መስመር ልትገባ ትችላለህ ከዚህ ይልቅ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” (ማቴዎስ 11፥28) የሚለውን መለኮታዊ ቃል አምነህ ከነሸክምህ ወደ እግዚአብሔር ቅረብ። እርሱ እንዳለውም ያሳርፍሃልና።
የራስህን ኃጢአት እና የእግዚአብሔርን ጽድቅ እያመዛዘንክ አትኑር። በምንም መልኩ በእግዚአብሔር ልክ ጻድቅ ልትሆን እና የእርሱን የጽድቅ ጥማትም ልታረክ አትችልም። እንዲህ እስክሆን ወደ እርሱ አልቀርብም፣ ይሄንን ልማዴን እስከተው አልጠጋውም አትበል ያንን ልማድህን የሚያስክድ እና የሚያስተው አቅም እና ጸጋ በእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ እራስህ ጋር አታገኘውምና።
እና ወዳጄ እሩጫ የሚሻለው ወደ እግዚአብሔር ሲሆን ነው። ጌታ እግዚአብሔር የማያሳፍርህ ተቀባይ፣ የማያሸማቀቅህ አዛኝ፣ ፊት የማይነሳህ አቃፊ ነው። እና ወደ እርሱ መምጣት የሁሉ ነገር መፍትሔ ነው።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ሺ ጊዜ ኃጢያት ስራ ነገር ግን ንስሃ ከመግባት አትቦዝን። የፈጠረህ እግዚአብሔር ጨርሶ አንተን መማር አይሰለችምና። እልፍ ጊዜ በድል ነገር ግን ከእግዚአብሔር አትኮብልል። ምክንያቱም እግዚአብሔር የደበሉ ወደ እርሱ የሚሸሸጉበት ዕሩሩህ እንጂ የሚሸሹት ጨካኝ አይደለምና።
በጣም ለቁጥር እንኳን በሚታክት ጥፋት ውስጥ ሁን ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከእግሩ ስር አትጥፋ። እግሩ ስር ስትሆን ክብር አለህና በጥፋትህ ብዛት እኔ እንዴት ወደ እግዚአብሔር እቀርባለሁ ብለህ አትራቅ። እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንድትቀርብ ልጁን ለአንተ ሲል በመስቀል ሰውቶታልና።
ጉድ የሚያስብል ጉድ ውስጥም ሁን ነገር ግን ገበናህን ከሚሸሸግልህ ከእግዚአብሔር አትሸፍት። የሁሉ ሰው ተግባር በእግዚአብሔር ፊት ግልጥ ነው። እግዚአብሔር ሁሉንም ነገርህን እያወቀ ዝም የሚልህ ስለሚምርህ ነው እንጂ ለኃጢአትህ መዝገብ አዘጋጅቶ አይደለም።
ኃጢአቴ ብዙ ነው ብትልም የኃጢአትህ ክምር በጭራሽ እግዚአብሔርን እንዳይሸሽግህ። ከበደልህ ይልቅ የሞተልህን ተመልከት። እግዚአብሔር የኃጥዓን መፍትሔ ነው። ችግር ውስጥ እንዳለህ በተሰማ ቁጥር ወደ ባለመፍትሔው ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እጅግ ማትረፊያ ነው። ኃጢአት የሰው ልጅ ሁሉ ችግር ነውና።
የራስህን መንገድ ብትከተል ጨርሶ ልትወጣው ወደማትችለው መስመር ልትገባ ትችላለህ ከዚህ ይልቅ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” (ማቴዎስ 11፥28) የሚለውን መለኮታዊ ቃል አምነህ ከነሸክምህ ወደ እግዚአብሔር ቅረብ። እርሱ እንዳለውም ያሳርፍሃልና።
የራስህን ኃጢአት እና የእግዚአብሔርን ጽድቅ እያመዛዘንክ አትኑር። በምንም መልኩ በእግዚአብሔር ልክ ጻድቅ ልትሆን እና የእርሱን የጽድቅ ጥማትም ልታረክ አትችልም። እንዲህ እስክሆን ወደ እርሱ አልቀርብም፣ ይሄንን ልማዴን እስከተው አልጠጋውም አትበል ያንን ልማድህን የሚያስክድ እና የሚያስተው አቅም እና ጸጋ በእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ እራስህ ጋር አታገኘውምና።
እና ወዳጄ እሩጫ የሚሻለው ወደ እግዚአብሔር ሲሆን ነው። ጌታ እግዚአብሔር የማያሳፍርህ ተቀባይ፣ የማያሸማቀቅህ አዛኝ፣ ፊት የማይነሳህ አቃፊ ነው። እና ወደ እርሱ መምጣት የሁሉ ነገር መፍትሔ ነው።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
👆🏾 ኦ ሚካኤል!
ሚካኤል ሆይ፤ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም አጠራርህ ጋር ለተባበረ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡ የእግዚብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ፤ የተቸገሩትን፣ የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ሁሉ፤ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ በፍጥነት ድረስልኝ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ለሰው ልጅ ይቅርታን ለማስገኘት ወደ ልዑል እግዚአብሔር አሻቅበው ለሚማልዱ ዓይኖችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ሚካኤል ሆይ፤ በጠላት ተማርከው ለሚጨነቁና ለሚሰቃዩት ዋስ ጠበቃቸው አንተ ነህና፡፡ በእኔ ላይ የሚተበትቡትን የጠላቶቼን የምክር መረብ በጣጥሰህ ጣልልኝ፡፡ ነፍሴንም ሥጋዬንም ለአንተ አደራ ሰጥቻለሁና፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ክርክር በተደረገ ጊዜ የዘለፋ ቃል ላልተናገረ አንደበትህ ሰላም እላለሁ፡፡ ክቡር መልአክ ሆይ፤ ክብርህ ከመላእክት ሁሉ ክብር ከፍ ያለ ነውና፤ በሥነ ሥዕልህ ፊት ቆሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ሁሉ አይዞህ አለሁልህ በማለት ፈጥነህ ድምጽህን አሰማኝ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ የፍጥረታት ሁሉ መጠለያ ለሆኑ ክንፎችህ ሰላም እላለሁ፡፡ ክቡር የሰማውያን ካህናት አለቃ ሆይ፤ ከእለት እኪት አድነን፤ ከጥፋት ሁሉ ሰውረን፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ የመብረቅ መስቀል ምልክት ያለበት በትረ ወርቅ ለጨበጡ እጆችህ ሰላም እላለሁ፡፡ ሊቀ መላእክት ሆይ፤ በገዳመ ራማ የምትኖር የዋህ ርግብ ወይም ዋልያ አንተ ነህና፤ የሕጻናት እድገት በነጋው በነጋው እንዲጨምር ጽድቅህ በእኔ በባርያህ ላይ እድገቷን ታሳይ፤ ትግለጽ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ቂም በቀል የሌለበት የርህራሄ እና የየዋህነት መዝገብ ለሆነ ልቡናህ ሰላም እላለሁ፡፡ የሰማያዊያን ኃያላት አለቃ ሚካኤል ሆይ፤ የእስራኤልን ልጆች ባሕሩን ከፍለህ በባሕር መካከል እንዳሳለፍካቸው፤ እኔንም አገልጋይህን ከስውር ወጥመድ ሰውረህ በሰላም አሳልፈኝ፡፡
አማላጃችን ሚካኤል ሆይ፣ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ፣ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህኮ፡፡ የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህኮ፡፡ ይልቁንም የልዑላን ልዑል አንተ ነህና፤ በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታህ በቸርነትህ ድረስልኝ፣ አትራቀኝ፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ሚካኤል ሆይ፤ የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም አጠራርህ ጋር ለተባበረ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡ የእግዚብሔር የምክሩ አበጋዝ ሆይ፤ የተቸገሩትን፣ የተጨነቁትን ዘወትር እንደምትረዳቸው ሁሉ፤ እኔንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ በፍጥነት ድረስልኝ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ለሰው ልጅ ይቅርታን ለማስገኘት ወደ ልዑል እግዚአብሔር አሻቅበው ለሚማልዱ ዓይኖችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ሚካኤል ሆይ፤ በጠላት ተማርከው ለሚጨነቁና ለሚሰቃዩት ዋስ ጠበቃቸው አንተ ነህና፡፡ በእኔ ላይ የሚተበትቡትን የጠላቶቼን የምክር መረብ በጣጥሰህ ጣልልኝ፡፡ ነፍሴንም ሥጋዬንም ለአንተ አደራ ሰጥቻለሁና፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ክርክር በተደረገ ጊዜ የዘለፋ ቃል ላልተናገረ አንደበትህ ሰላም እላለሁ፡፡ ክቡር መልአክ ሆይ፤ ክብርህ ከመላእክት ሁሉ ክብር ከፍ ያለ ነውና፤ በሥነ ሥዕልህ ፊት ቆሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ሁሉ አይዞህ አለሁልህ በማለት ፈጥነህ ድምጽህን አሰማኝ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ የፍጥረታት ሁሉ መጠለያ ለሆኑ ክንፎችህ ሰላም እላለሁ፡፡ ክቡር የሰማውያን ካህናት አለቃ ሆይ፤ ከእለት እኪት አድነን፤ ከጥፋት ሁሉ ሰውረን፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ የመብረቅ መስቀል ምልክት ያለበት በትረ ወርቅ ለጨበጡ እጆችህ ሰላም እላለሁ፡፡ ሊቀ መላእክት ሆይ፤ በገዳመ ራማ የምትኖር የዋህ ርግብ ወይም ዋልያ አንተ ነህና፤ የሕጻናት እድገት በነጋው በነጋው እንዲጨምር ጽድቅህ በእኔ በባርያህ ላይ እድገቷን ታሳይ፤ ትግለጽ፡፡
ሚካኤል ሆይ፤ ቂም በቀል የሌለበት የርህራሄ እና የየዋህነት መዝገብ ለሆነ ልቡናህ ሰላም እላለሁ፡፡ የሰማያዊያን ኃያላት አለቃ ሚካኤል ሆይ፤ የእስራኤልን ልጆች ባሕሩን ከፍለህ በባሕር መካከል እንዳሳለፍካቸው፤ እኔንም አገልጋይህን ከስውር ወጥመድ ሰውረህ በሰላም አሳልፈኝ፡፡
አማላጃችን ሚካኤል ሆይ፣ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ፣ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህኮ፡፡ የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህኮ፡፡ ይልቁንም የልዑላን ልዑል አንተ ነህና፤ በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታህ በቸርነትህ ድረስልኝ፣ አትራቀኝ፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በዚህ ምድር ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር ካልተዛመድን በሰማያት ልንዛመደው አንችልም፤ የመንግሥቱ ጣዕም ያለው በዚህ ነውና። ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ዝምድና እዚህ ምድር ላይ ይጀምራል። ይህም እንደ እግዚአብሔር እንደ ራሱ "ልጄ ሆይ ልብህን ስጠኝ።" ምሳ 23፥26 በሚለው ጥያቄ ይጀምራል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ልብን አንጽቶ በፍቅር ከሞላው በኋላ በዚያ ራሱን ያሳድራል። ወንጌል "የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና።"ሉቃ 17፥21 ብሎ እንደሚናገር ይህ የእግዚአብሔር መንግሥት ማረጋገጫ ይሆናል።
ስለዚህ የሰማያትን መንግሥት ከማግኝት በፊት ሰው በውስጡ ያለውን የእግዚአብሔርን መንግሥት ማግኝት መቻል አለበት። ይህ ይሁን እንጂ አንድ ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያገኝ የሚችለው እንዴት ነው? ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ኅብረት ሊያገኝ የሚችለውስ እንዴት ነው? ሁል ጊዜ ከእርሱ ጋር የሚሆነውስ እንዴት ነው? በዚህ ዙሪያ የምሰጣችሁ ምክር ምንጊዜም ቢሆን በእርሱ እንድትጠመዱ ሲሆን ይህም በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላለው ስለ እርሱ ሥራና ስለ ራሱ በማንበብ የሚከናወን ይሆናል።
ከቅዱሳኑ ጋር ስላለው ዝምድና ስለ ድንቅ ባሕርያቱና በማንኛዎቹም አጋጣሚዎች ውስጥ ስላለው ስለ እርሱ እጅ አንብቡ። በዚህ ጊዜ ልባችሁ በእርሱ ፍቅር ይንቀሳቀሳል። በማንኛውም ጊዜ ውስጥም ከእርሱ ጋር ይገናኝ ዘንድ ዝግጁ ነው ።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ስለዚህ የሰማያትን መንግሥት ከማግኝት በፊት ሰው በውስጡ ያለውን የእግዚአብሔርን መንግሥት ማግኝት መቻል አለበት። ይህ ይሁን እንጂ አንድ ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያገኝ የሚችለው እንዴት ነው? ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ኅብረት ሊያገኝ የሚችለውስ እንዴት ነው? ሁል ጊዜ ከእርሱ ጋር የሚሆነውስ እንዴት ነው? በዚህ ዙሪያ የምሰጣችሁ ምክር ምንጊዜም ቢሆን በእርሱ እንድትጠመዱ ሲሆን ይህም በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላለው ስለ እርሱ ሥራና ስለ ራሱ በማንበብ የሚከናወን ይሆናል።
ከቅዱሳኑ ጋር ስላለው ዝምድና ስለ ድንቅ ባሕርያቱና በማንኛዎቹም አጋጣሚዎች ውስጥ ስላለው ስለ እርሱ እጅ አንብቡ። በዚህ ጊዜ ልባችሁ በእርሱ ፍቅር ይንቀሳቀሳል። በማንኛውም ጊዜ ውስጥም ከእርሱ ጋር ይገናኝ ዘንድ ዝግጁ ነው ።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#እግዚአብሔር_መፍራት
ወደ ፍቅር መንገድ ለመድረስ የሚረዳን የመጀመርያው መንገድ ፍርሃት ነው። ምክንያቱም በመጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ መጽሐፈ ምሳሌ ላይ "የጥበብ መጀመርያ #እግዚአብሔርን መፍራት ነው፥…"(ምሳ9፡10) የሚል ቃል አለ፡፡ በዳዊት የመዝሙር መጽሓፍ ውስጥም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቃል አለ፥ መዝ 110 ፡10። ይህ እንዴት ነው የሚሆነው? በፍርሃትና በፍቅር መካከል ያለው ግንኝነት ምንድር ነው? ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ ግን እንዲህ ይለናል፡- " ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም . . ."/1ኛ ዮሐ 4 ÷18/
ልክ መፍራት ስትጀምሩ ለእግዚአብሔር ትታዘዛላችሁ ትዕዛዛቱንም ትፈጽማላችሁ።
ቢያንስ-ቢያንስ የእርሱን ቅጣት ትፈራላችሁ፥ አስፈሪውን የፍርድ ቀን ትፈራላችሁ፥ ዘላለማዊ ስቃይ ትፈራላችሁ። የእርሱን ትዕዛዛት የምትቀበሉ ከሆናችሁ ግን ለሕይወታችሁ ደስታንና ታላቅ ጥቅምን ታገኛላችሁ። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙራቱ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር ትእዛዛት ፥ ስለ ሥርዓቶቹና ስለ ሕግጋቱ እንዲህ እያለ ዘምሯል፡- "የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል።"፥ "የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፡ ልብን ደስ ያሰኛል፥ . . ." ፥ " ሕፃናት ጠቢባን ያደርጋል።" ፥ "ከወርቅ እና ከክቡር እንቁ ይልቅ ይወደዳል ከማር ወለላም ይጣፍጣል፡፡" መዝ18፡ 7- 10። ከዚህ በተጨማሪ ዳዊት በረዥሙ መዝሙሩ ውስጥ እንዲህ ብሏል ፡- " ለባርያህ ተስፋ ያደረግኸውን ቃልህን አስብ፡፡ ቃልህ ሕያው አድርጎኛልና ይህቺ በመከራዬ ደስ አሰኘችኝ።"፥ "እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ።" ፥ " እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል።"፥ " የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ ትእዛዛህ ግን እጅግ ሰፊ ነው፡፡"፥ " አቤቱ፡- ሕግህ እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው።" መዝ 118 ።
#የእግዚአብሔር_ትዕዛዛትን በመውደድ መልካም የሆነውን እንወዳለን። መልካም የሆነውን በመውደድ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር እንደርሳለን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ወደ ፍቅር መንገድ ለመድረስ የሚረዳን የመጀመርያው መንገድ ፍርሃት ነው። ምክንያቱም በመጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ መጽሐፈ ምሳሌ ላይ "የጥበብ መጀመርያ #እግዚአብሔርን መፍራት ነው፥…"(ምሳ9፡10) የሚል ቃል አለ፡፡ በዳዊት የመዝሙር መጽሓፍ ውስጥም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቃል አለ፥ መዝ 110 ፡10። ይህ እንዴት ነው የሚሆነው? በፍርሃትና በፍቅር መካከል ያለው ግንኝነት ምንድር ነው? ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ ግን እንዲህ ይለናል፡- " ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም . . ."/1ኛ ዮሐ 4 ÷18/
ልክ መፍራት ስትጀምሩ ለእግዚአብሔር ትታዘዛላችሁ ትዕዛዛቱንም ትፈጽማላችሁ።
ቢያንስ-ቢያንስ የእርሱን ቅጣት ትፈራላችሁ፥ አስፈሪውን የፍርድ ቀን ትፈራላችሁ፥ ዘላለማዊ ስቃይ ትፈራላችሁ። የእርሱን ትዕዛዛት የምትቀበሉ ከሆናችሁ ግን ለሕይወታችሁ ደስታንና ታላቅ ጥቅምን ታገኛላችሁ። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙራቱ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር ትእዛዛት ፥ ስለ ሥርዓቶቹና ስለ ሕግጋቱ እንዲህ እያለ ዘምሯል፡- "የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል።"፥ "የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፡ ልብን ደስ ያሰኛል፥ . . ." ፥ " ሕፃናት ጠቢባን ያደርጋል።" ፥ "ከወርቅ እና ከክቡር እንቁ ይልቅ ይወደዳል ከማር ወለላም ይጣፍጣል፡፡" መዝ18፡ 7- 10። ከዚህ በተጨማሪ ዳዊት በረዥሙ መዝሙሩ ውስጥ እንዲህ ብሏል ፡- " ለባርያህ ተስፋ ያደረግኸውን ቃልህን አስብ፡፡ ቃልህ ሕያው አድርጎኛልና ይህቺ በመከራዬ ደስ አሰኘችኝ።"፥ "እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ።" ፥ " እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል።"፥ " የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ ትእዛዛህ ግን እጅግ ሰፊ ነው፡፡"፥ " አቤቱ፡- ሕግህ እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው።" መዝ 118 ።
#የእግዚአብሔር_ትዕዛዛትን በመውደድ መልካም የሆነውን እንወዳለን። መልካም የሆነውን በመውደድ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር እንደርሳለን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#ጾመ_ነቢያት
እግዚአብሔር አምላካችን ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ መልበሱን፣ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ግብር መሰደዱን፣ በባሕረ ዮርዳኖስ መጠመቁን፣ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ማብራቱን፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲል ልዩ ልዩ ዓይነት መከራ መቀበሉን፣ መሰቀሉን፣ መሞቱን፣ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም ለፍርድ የሚመጣ መኾኑን በአጠቃላይ የማዳን ሥራውን በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አስቀደመው በትንቢት ተናግረዋል፡፡ ትንቢቱ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው ኾኖ ዓለምን የሚያድንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔር ሰው መኾን ፍጻሜ አግኝቷል፡፡
ይህን ምሥጢር በማሰብ በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዋይዜማ ድረስ እንድንጾም አባቶቻችን መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሠርተውልናል፡፡ ይህ ጾም፣ ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ሲኾን፣ በስያሜም #ጾመ_ነቢያት (የነቢያት ጾም) እየተባለ ይጠራል፡፡ ወቅቱ ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ የተፈጸመበት ስለ ኾነም #ጾመ_አዳም (የአዳም ጾም) ይባላል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም #ጾመ_ስብከት (የስብከት ጾም) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ #ጾመ_ልደት (የልደት ጾም) በመባል ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም #ጾመ_ሐዋርያት እየተባለ ይጠራል፤ ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት "በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?" በማለት ነቢያት በጾሙበት ማለት ከልደተ ክርስቶስ በፊት ባለው ወቅት ጾመዋልና፡፡
በሌላ አጠራር ይኸው ጾመ ነቢያት #ጾመ_ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም) በመባል ይታወቃል፤ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያ እና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ተሰወረባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ በዓት ዘግተው፣ ሱባዔ ገብተው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ቢለምኑት ልመናቸውን ተቀብሎ ሱባዔ በያዙ በ፫ኛው ቀን የቅዱስ ፊልጶስን ሥጋ (በድን) መልሶላቸው በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት 'ጾመ ፊልጶስ' እየተባለ ይጠራል፡፡
ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ካበሠራት በኋላ "ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?" በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ እመቤታችን ጾማዋለችና ይህ ጾም #ጾመ_ማርያም በመባልም ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ በጾመ ነቢያት፣ ነቢያትም ሐዋርያትም፣ ቀደምት አባቶቻችንም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባናል፡፡
ጾሙን ጾመ ሥርየት፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግል!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
እግዚአብሔር አምላካችን ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ መልበሱን፣ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ግብር መሰደዱን፣ በባሕረ ዮርዳኖስ መጠመቁን፣ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ማብራቱን፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲል ልዩ ልዩ ዓይነት መከራ መቀበሉን፣ መሰቀሉን፣ መሞቱን፣ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱን፣ ማረጉንና ዳግም ለፍርድ የሚመጣ መኾኑን በአጠቃላይ የማዳን ሥራውን በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አስቀደመው በትንቢት ተናግረዋል፡፡ ትንቢቱ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው ኾኖ ዓለምን የሚያድንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔር ሰው መኾን ፍጻሜ አግኝቷል፡፡
ይህን ምሥጢር በማሰብ በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዋይዜማ ድረስ እንድንጾም አባቶቻችን መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሠርተውልናል፡፡ ይህ ጾም፣ ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ሲኾን፣ በስያሜም #ጾመ_ነቢያት (የነቢያት ጾም) እየተባለ ይጠራል፡፡ ወቅቱ ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ የተፈጸመበት ስለ ኾነም #ጾመ_አዳም (የአዳም ጾም) ይባላል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም #ጾመ_ስብከት (የስብከት ጾም) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ #ጾመ_ልደት (የልደት ጾም) በመባል ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም #ጾመ_ሐዋርያት እየተባለ ይጠራል፤ ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት "በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?" በማለት ነቢያት በጾሙበት ማለት ከልደተ ክርስቶስ በፊት ባለው ወቅት ጾመዋልና፡፡
በሌላ አጠራር ይኸው ጾመ ነቢያት #ጾመ_ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም) በመባል ይታወቃል፤ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያ እና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ተሰወረባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ በዓት ዘግተው፣ ሱባዔ ገብተው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ቢለምኑት ልመናቸውን ተቀብሎ ሱባዔ በያዙ በ፫ኛው ቀን የቅዱስ ፊልጶስን ሥጋ (በድን) መልሶላቸው በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት 'ጾመ ፊልጶስ' እየተባለ ይጠራል፡፡
ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ካበሠራት በኋላ "ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?" በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ እመቤታችን ጾማዋለችና ይህ ጾም #ጾመ_ማርያም በመባልም ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ በጾመ ነቢያት፣ ነቢያትም ሐዋርያትም፣ ቀደምት አባቶቻችንም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባናል፡፡
ጾሙን ጾመ ሥርየት፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግል!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሠርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሠርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሠርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡
በሌላ አገላለጽ ብነግራችኁ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በሌላ አገላለጽ ብነግራችኁ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"ብዙዎች ቢጾሙም ለእነርሱ መጾም ማለት የጾም ምግብ መብላት ማለት ነው። እነርሱ በጾም ወቅት ለራሳቸው የሚበሏቸውን በጣም ጣፋጭና ገንቢ ምግቦችን ያዘጋጃሉ አልፎ ተርፎም ውድና የማይገኙ ቅመማ ቅመም ይጨምሩባቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የጾም ቅቤ፤ የጾም አይብ፤ የጾም ቸኮላታ እንዲያገኙ ይጠይቃሉ። በአጠቃላይ የጾም ምግቦቻችን ብዛትና ዓይነት ከልክ እጅግ ያለፈ ነው።
በዚህም ነብዩ ዳንኤል ስለ ጾም የተናገረውን ይዘነጉታል። "በዚያ ወራት እኔ ዳንኤል ሦስት ሳምንት ሙሉ ሳዝን ነበርሁ። ማለፊያ እንጀራ አልበላሁም ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም ሦስቱንም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም።" (ዳን 10፥2-3) በዚህ አባባሉ ውስጥ "ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም" የሚለው ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ። አንድ ሰው በጾም ወራት በየዕለቱ ጥሩ ጥሩ ምግቦች እየበላና የሚናፍቀውን ምግብ ለሰውነቱ እየሰጠ የሥጋውን ፈቃድ እንዴት ሊቆጣጠር ይችላል? አይችልም።
መንፈሳዊው ሰው የጾም ትክክለኛ ፍቺ ሥጋን በማዋረድ የምግብን ፋላጎት ድል ለማድረግ ካበቃ በኋላ ከቁሳዊው ዓለም በላይ ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ያውቃል ። በመሆኑም የጾም ምግቦችን መብላት ብቻ መሆን የለበትም እርሱ በሚጾምበት ጊዜ ግድ የሚለው መታቀብ ነው ። ይህም ማለት የሚመገበው ሙሉ ለሙሉ የጾም ምግብ ቢሆንም ሥጋው ሊያገኛቸው የሚናፍቃቸውን ነገሮች በሙሉ መከልከል ማለት ነው ።
ብዙ ሰዎች የሚጾሙት በልምድ ወይም በፊደል ስለሆነ ምንም የሚጠቀሙት ነገር የለም ። እነዚህ ሰዎች ጾምን መለኮታዊ ዓላማውን በመገንዘብ ስለማይጀምሩት ወደ ጾም መንፈሳዊነት ወይም ስለ ትእዛዙ መንፈሳዊነት ሊገቡ አይችሉም። በመሆኑም ሰውነታቸው ይጹም እንጂ መንፈሳቸው አይጾምም።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በዚህም ነብዩ ዳንኤል ስለ ጾም የተናገረውን ይዘነጉታል። "በዚያ ወራት እኔ ዳንኤል ሦስት ሳምንት ሙሉ ሳዝን ነበርሁ። ማለፊያ እንጀራ አልበላሁም ሥጋና ጠጅም በአፌ አልገባም ሦስቱንም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ዘይት አልተቀባሁም።" (ዳን 10፥2-3) በዚህ አባባሉ ውስጥ "ማለፊያ እንጀራም አልበላሁም" የሚለው ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ። አንድ ሰው በጾም ወራት በየዕለቱ ጥሩ ጥሩ ምግቦች እየበላና የሚናፍቀውን ምግብ ለሰውነቱ እየሰጠ የሥጋውን ፈቃድ እንዴት ሊቆጣጠር ይችላል? አይችልም።
መንፈሳዊው ሰው የጾም ትክክለኛ ፍቺ ሥጋን በማዋረድ የምግብን ፋላጎት ድል ለማድረግ ካበቃ በኋላ ከቁሳዊው ዓለም በላይ ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ያውቃል ። በመሆኑም የጾም ምግቦችን መብላት ብቻ መሆን የለበትም እርሱ በሚጾምበት ጊዜ ግድ የሚለው መታቀብ ነው ። ይህም ማለት የሚመገበው ሙሉ ለሙሉ የጾም ምግብ ቢሆንም ሥጋው ሊያገኛቸው የሚናፍቃቸውን ነገሮች በሙሉ መከልከል ማለት ነው ።
ብዙ ሰዎች የሚጾሙት በልምድ ወይም በፊደል ስለሆነ ምንም የሚጠቀሙት ነገር የለም ። እነዚህ ሰዎች ጾምን መለኮታዊ ዓላማውን በመገንዘብ ስለማይጀምሩት ወደ ጾም መንፈሳዊነት ወይም ስለ ትእዛዙ መንፈሳዊነት ሊገቡ አይችሉም። በመሆኑም ሰውነታቸው ይጹም እንጂ መንፈሳቸው አይጾምም።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
+ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን +
ቅዱስ ጳውሎስ ኃጢአታችንን በደሙ ባጠበልን በእርሱ በተሰቀለው በልዑል ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን አለ ። እነርሱ የማይሰሩትን ስራ እኛ እንሰራለን ። ብዙ ታላላቅ ጦር ሜዳ ድል ያደረጉ ጀኔራሎች ( ታላላቅ የጦር ሰዎች ) ልባችንን ማሸነፍ አይችሉም ። ይኸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ታውቋል። አንዱን ወጣት የሃይማኖት ገበሬ ቅዱስ ጊዮርጊስን ሰባው ነገስታት ከነሰራዊቶቻቸው ሊያሸንፍት አልቻሉምና ። እርሱ ድል አደረጋቸው እንጂ ፤ በእርሱ ጸሎት ሁሉንም እሳት በላቸው ፣ እርሱ ግን ማንም ድል ሊያደርገው ሊያሸንፈው አልቻለም ። ብዙ መከራ ቢያጸኑበትም ፤ ስጋውን አቃጥለው አመድ አድረገው ቢበትኑበትም ቅሉ ፤ ሃይማኖቱ አስነሳው ። መድኃኔ ዓለም ተገልጦ "ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ ተነስ " አለው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ያደረገው በወደደው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ነው ። ጠላቶቹ ገደልነው ፣ አሸነፍነው ፣ ቆራረጥነው ፣ በተንነው ፣ ጠብስነው ፣ አቃጠልነው ፣ ሲሉ በወደደው በፈጣሪው በኢየሱስ ኃይል ከሙታን ብድግ ይልና ፤ ከጫጉላ ቤት እንደ ወጣ ሰው ታድሶ ፣ ለምልሞ እንደገና ሄዶ ይገጥማቸዋል ። ሶስት ጊዜ ገደሉት ሶስት ጊዜ ተነሳ ፣ በአራተኛው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነብሱ ከስጋው ተለየች ። ነገር ግን መጀመርያ አነርሱን አጥፋቶ ነው ፤ እሳት ከሰማይ ወርዶ ጠላቶቹን አጥፍቶ ሲያበቃ በሰይፍ ተሰየፈ ፤ ከአንገቱም ደም ፣ ውኃ ፣ ወተት ፈሰሰ። (ገድለ ጊዮርጊስ ) ስለዚህ በወደደን በእርሱ በኃያሉ በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን ።
ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ (በሃይማኖት የሚሰራ ታላላቅ ስራ) እንዳለ ነግሮናል ። እንግዲህ ምን እላለሁ ? ስለ ጌዴዎን ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶን ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነብያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል ። እነርሱ በእምነት መንግስታትን ድል ነሱ።" ዕብ 11:32:33 (ኦርቶዶክስያ ገጽ -94 የመ/ር ግርማ ከበደ ትምህርታዊ ስብከቶች ስብስብ )
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ቅዱስ ጳውሎስ ኃጢአታችንን በደሙ ባጠበልን በእርሱ በተሰቀለው በልዑል ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን አለ ። እነርሱ የማይሰሩትን ስራ እኛ እንሰራለን ። ብዙ ታላላቅ ጦር ሜዳ ድል ያደረጉ ጀኔራሎች ( ታላላቅ የጦር ሰዎች ) ልባችንን ማሸነፍ አይችሉም ። ይኸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ታውቋል። አንዱን ወጣት የሃይማኖት ገበሬ ቅዱስ ጊዮርጊስን ሰባው ነገስታት ከነሰራዊቶቻቸው ሊያሸንፍት አልቻሉምና ። እርሱ ድል አደረጋቸው እንጂ ፤ በእርሱ ጸሎት ሁሉንም እሳት በላቸው ፣ እርሱ ግን ማንም ድል ሊያደርገው ሊያሸንፈው አልቻለም ። ብዙ መከራ ቢያጸኑበትም ፤ ስጋውን አቃጥለው አመድ አድረገው ቢበትኑበትም ቅሉ ፤ ሃይማኖቱ አስነሳው ። መድኃኔ ዓለም ተገልጦ "ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ ተነስ " አለው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ያደረገው በወደደው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ነው ። ጠላቶቹ ገደልነው ፣ አሸነፍነው ፣ ቆራረጥነው ፣ በተንነው ፣ ጠብስነው ፣ አቃጠልነው ፣ ሲሉ በወደደው በፈጣሪው በኢየሱስ ኃይል ከሙታን ብድግ ይልና ፤ ከጫጉላ ቤት እንደ ወጣ ሰው ታድሶ ፣ ለምልሞ እንደገና ሄዶ ይገጥማቸዋል ። ሶስት ጊዜ ገደሉት ሶስት ጊዜ ተነሳ ፣ በአራተኛው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነብሱ ከስጋው ተለየች ። ነገር ግን መጀመርያ አነርሱን አጥፋቶ ነው ፤ እሳት ከሰማይ ወርዶ ጠላቶቹን አጥፍቶ ሲያበቃ በሰይፍ ተሰየፈ ፤ ከአንገቱም ደም ፣ ውኃ ፣ ወተት ፈሰሰ። (ገድለ ጊዮርጊስ ) ስለዚህ በወደደን በእርሱ በኃያሉ በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ከአሸናፈዎች እንበልጣለን ።
ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ (በሃይማኖት የሚሰራ ታላላቅ ስራ) እንዳለ ነግሮናል ። እንግዲህ ምን እላለሁ ? ስለ ጌዴዎን ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶን ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነብያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል ። እነርሱ በእምነት መንግስታትን ድል ነሱ።" ዕብ 11:32:33 (ኦርቶዶክስያ ገጽ -94 የመ/ር ግርማ ከበደ ትምህርታዊ ስብከቶች ስብስብ )
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የክርስቶስ ሰላም ይብዛልን!
ከዚኽ በፊት “ነቢያት ስለራሳቸው ምን አሉ?” ብለን ከተናገሯቸው ቃላት በጣም በጥቂቱ አይተናል፤ በዚኽኛው [እና ምናልባት ከረዘመ በቀጣዩም] ጽሑፍ የምንዳስሰው ደግሞ እግዚአብሔር ለነቢያቱ የሰጣቸውን ምላሽ፥ በትኅትናቸውና እግዚአብሔርን ‛እሺ’ በማለታቸው ያደረገላቸውን ነገር በጥቂቱ እንመለከታለን።
ከነቢዩ ሙሴ እንጀምር፤ በፈርዖን ቤት ኹሉ ተመቻችቶለት ሲኖር ቆይቶ ‛ጎበዝ በኾነ ጊዜ’ ወንድሞቹ (ዕብራውያን) የሚሠሩትን ተመለከተ። ግብጻዊ የኾነውም ዕብራውያንን ሲመታ ተመለከተው፤ ማንም እንደሌለ አይቶ ‛ገደለው፤ በአሸዋም ውስጥ ሸሸገው።’ በቀጣዩም ቀን ኹለት ዕብራውያን ሲጣሉ አይቶ ‛በዳዩን፦ ለምን ባልንጀራኽን ትመታዋለኽ? አለው። ያም፦ በእኛ ላይ አንተን #አለቃ ወይስ #ዳኛ ማን አደረገኽ? ወይስ ግብፃዊውን እንደ ገደልኸው ልትገድለኝ ትሻለህን? አለው። ሙሴም፦ በእውነት ይህ ነገር ታውቋል ብሎ ፈራ። ፈርዖንም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ሙሴን ሊገድለው ፈለገ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ፊት ኰበለለ፥ በምድያምም ምድር ተቀመጠ።’ ሙሉ ታሪኩን ኦሪት ዘጸአት 2፥11-15 ላይ ታገኙታላችኹ። አኹን እኛ የምንፈልገው ክፍል ላይ እናተኩር። ዕብራዊው ወንድሙን የሚደበድበው ሙሴ ለጠየቀው ጥያቄ ሲመልስ ‛በእኛ ላይ አንተን አለቃ ወይስ ዳኛ ማን አደረገኽ?’ ብሎት ነበር።
እንድናስተውል የፈለግኹት ነገር ምንድን ነው? እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ከኾንን [እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሊኾን የታመነ ነውና] ማንም ሊያሸንፈን አይችልም። ከዚኽ ቀጥሎ የማስቀምጠው ጥቅስ ይኽን ሐሳብ ግልጽ የሚያደርግላችኹ ይመስለኛል፤ “ሙሴ በሕዝቡ #ሊፈርድ ተቀመጠ።” (ዘጸ. 18፥13) ‛ማን ፈራጅ አደረገኽ?’ የተባለው ሙሴ ‛በሕዝቡ ሊፈርድ ተቀመጠ።’
ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር በመኾኑ በሕዝቡ ላይ የመፍረድን ሥልጣን አግኝቷል። ከእግዚአብሔር ጋር ከኾንን ምንም እንኳን ከርሱ ጋር ባልነበርንበት ወራት የሚገዙን የነበሩ ከእግዚአብሔር የሚለዩን ሥራዎች የሚሰለጥኑብን ብንኾንም በሥጋችን ላይ ጨክነን ወደእግዚአብሔር ከቀረብን ግን ምንም አይነት ሥጋዊ ምኞት የማያሸንፈን እንደምንኾን ከሙሴ ታሪክ እንማራለን። ቅዱስ እስጢፋኖስም “ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው? ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።” (ሐዋ. 7፥35) በማለት ይናገራል።
“እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ እይ፥ እኔ ለፈርዖን አምላክ #አድርጌኻለሁ።” (ዘጸ. 7፥1) እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ስንኾን ሥጋዊ ምኞታችንን መግታት ቀላል ይኾናል፤ ከዚኽም አልፈን ርኩሳን መናፍስትንም ማዘዝ መቆጣጠር እንችላለን።
ሙሴ በፈርዖን ቤት አድጎ ኋላ በሱ ላይ የተሾመው (የጸጋ አምላክነትን/ገዥነትን የተቀበለው) እግዚአብሔር ከርሱ ጋር በመኾኑ ነው። እኛም በቀደመ ሕይወታችን የርኩሳን አጋንንትን ምክር ሰምተን ለፈቃደ ሥጋችን አድልተን ከእግዚአብሔር ብንለይም እግዚአብሔር ከዚኽ ሕይወት እንደሚያወጣን አምነን፥ ለፍቅረ እግዚአብሔር ቀንተን፥ የተከፈለልንን ዋጋ አስበን ከኃጢአት ብንርቅ ነፍሳችንን ከማትረፋችንም በተጨማሪ በርኩሳን አጋንንት ላይም ሥልጣን ይኖረናል። ጌታችን በወንጌል “በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚኽም #የሚበልጥ ያደርጋል” (ዮሐ. 14፥12) እንዳለው።
አላብዛባችኹ፤ ሐሳቤን ልጠቅልል። እግዚአብሔር ኹላችንንም ወደርሱ እንድንመለስ ጠርቶናል። ወደርሱ እስከሚጠራን ቀን ድረስም በትዕግሥት የንስሐ ዕድሜን እየጨመረ ይጠብቀናል። ጥሪውን ተቀብለን ከመጣን የሠራነውን ከርሱ ያራቀንን ኃጢአት ምንም #ያልሠራን እስክመስል ድረስ በንስሐ ያጥበናል።
“ሁላችን በብዙ ነገር #እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው።” (ያዕ. 3፥2) እንዳለ ሐዋርያው ኹለመናችንን ለርሱ አስገዝተን ወደርሱ ተመልሰን ከርሱ ጋር እንድንኖር እግዚአብሔር ይርዳን።
ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ከዚኽ በፊት “ነቢያት ስለራሳቸው ምን አሉ?” ብለን ከተናገሯቸው ቃላት በጣም በጥቂቱ አይተናል፤ በዚኽኛው [እና ምናልባት ከረዘመ በቀጣዩም] ጽሑፍ የምንዳስሰው ደግሞ እግዚአብሔር ለነቢያቱ የሰጣቸውን ምላሽ፥ በትኅትናቸውና እግዚአብሔርን ‛እሺ’ በማለታቸው ያደረገላቸውን ነገር በጥቂቱ እንመለከታለን።
ከነቢዩ ሙሴ እንጀምር፤ በፈርዖን ቤት ኹሉ ተመቻችቶለት ሲኖር ቆይቶ ‛ጎበዝ በኾነ ጊዜ’ ወንድሞቹ (ዕብራውያን) የሚሠሩትን ተመለከተ። ግብጻዊ የኾነውም ዕብራውያንን ሲመታ ተመለከተው፤ ማንም እንደሌለ አይቶ ‛ገደለው፤ በአሸዋም ውስጥ ሸሸገው።’ በቀጣዩም ቀን ኹለት ዕብራውያን ሲጣሉ አይቶ ‛በዳዩን፦ ለምን ባልንጀራኽን ትመታዋለኽ? አለው። ያም፦ በእኛ ላይ አንተን #አለቃ ወይስ #ዳኛ ማን አደረገኽ? ወይስ ግብፃዊውን እንደ ገደልኸው ልትገድለኝ ትሻለህን? አለው። ሙሴም፦ በእውነት ይህ ነገር ታውቋል ብሎ ፈራ። ፈርዖንም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ሙሴን ሊገድለው ፈለገ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ፊት ኰበለለ፥ በምድያምም ምድር ተቀመጠ።’ ሙሉ ታሪኩን ኦሪት ዘጸአት 2፥11-15 ላይ ታገኙታላችኹ። አኹን እኛ የምንፈልገው ክፍል ላይ እናተኩር። ዕብራዊው ወንድሙን የሚደበድበው ሙሴ ለጠየቀው ጥያቄ ሲመልስ ‛በእኛ ላይ አንተን አለቃ ወይስ ዳኛ ማን አደረገኽ?’ ብሎት ነበር።
እንድናስተውል የፈለግኹት ነገር ምንድን ነው? እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ከኾንን [እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሊኾን የታመነ ነውና] ማንም ሊያሸንፈን አይችልም። ከዚኽ ቀጥሎ የማስቀምጠው ጥቅስ ይኽን ሐሳብ ግልጽ የሚያደርግላችኹ ይመስለኛል፤ “ሙሴ በሕዝቡ #ሊፈርድ ተቀመጠ።” (ዘጸ. 18፥13) ‛ማን ፈራጅ አደረገኽ?’ የተባለው ሙሴ ‛በሕዝቡ ሊፈርድ ተቀመጠ።’
ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር በመኾኑ በሕዝቡ ላይ የመፍረድን ሥልጣን አግኝቷል። ከእግዚአብሔር ጋር ከኾንን ምንም እንኳን ከርሱ ጋር ባልነበርንበት ወራት የሚገዙን የነበሩ ከእግዚአብሔር የሚለዩን ሥራዎች የሚሰለጥኑብን ብንኾንም በሥጋችን ላይ ጨክነን ወደእግዚአብሔር ከቀረብን ግን ምንም አይነት ሥጋዊ ምኞት የማያሸንፈን እንደምንኾን ከሙሴ ታሪክ እንማራለን። ቅዱስ እስጢፋኖስም “ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው? ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።” (ሐዋ. 7፥35) በማለት ይናገራል።
“እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ እይ፥ እኔ ለፈርዖን አምላክ #አድርጌኻለሁ።” (ዘጸ. 7፥1) እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ስንኾን ሥጋዊ ምኞታችንን መግታት ቀላል ይኾናል፤ ከዚኽም አልፈን ርኩሳን መናፍስትንም ማዘዝ መቆጣጠር እንችላለን።
ሙሴ በፈርዖን ቤት አድጎ ኋላ በሱ ላይ የተሾመው (የጸጋ አምላክነትን/ገዥነትን የተቀበለው) እግዚአብሔር ከርሱ ጋር በመኾኑ ነው። እኛም በቀደመ ሕይወታችን የርኩሳን አጋንንትን ምክር ሰምተን ለፈቃደ ሥጋችን አድልተን ከእግዚአብሔር ብንለይም እግዚአብሔር ከዚኽ ሕይወት እንደሚያወጣን አምነን፥ ለፍቅረ እግዚአብሔር ቀንተን፥ የተከፈለልንን ዋጋ አስበን ከኃጢአት ብንርቅ ነፍሳችንን ከማትረፋችንም በተጨማሪ በርኩሳን አጋንንት ላይም ሥልጣን ይኖረናል። ጌታችን በወንጌል “በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚኽም #የሚበልጥ ያደርጋል” (ዮሐ. 14፥12) እንዳለው።
አላብዛባችኹ፤ ሐሳቤን ልጠቅልል። እግዚአብሔር ኹላችንንም ወደርሱ እንድንመለስ ጠርቶናል። ወደርሱ እስከሚጠራን ቀን ድረስም በትዕግሥት የንስሐ ዕድሜን እየጨመረ ይጠብቀናል። ጥሪውን ተቀብለን ከመጣን የሠራነውን ከርሱ ያራቀንን ኃጢአት ምንም #ያልሠራን እስክመስል ድረስ በንስሐ ያጥበናል።
“ሁላችን በብዙ ነገር #እንሰናከላለንና፤ በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ሥጋውን ሁሉ ደግሞ ሊገታ የሚችል ፍጹም ሰው ነው።” (ያዕ. 3፥2) እንዳለ ሐዋርያው ኹለመናችንን ለርሱ አስገዝተን ወደርሱ ተመልሰን ከርሱ ጋር እንድንኖር እግዚአብሔር ይርዳን።
ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ኅዳር ፳፩
ጽዮን ማርያም
ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው።
“ታቦተ ጽዮን” የሚለውንም ስያሜ ያገኘችው ጽዮን ተብላ በምትጠራው የእስራኤል ከተማ ስም ነው፡፡ ጽዮን ማለት ተፀወነ፡ ተጠጋ፣ ተማጠነ ማለት ነው፡፡ ክቡረ ዳዊትም ጽዮንን አምባ፣ መጠጊያ አድርጎ ብዙ ጠላቶቹን ተዋግቶ አሸንፎ ድልን ተጎናጽፏል።
ጽዮን የተባለችው የታላቁ የዳዊት ከተማ የተገፉና የተበደሉ ሕዝቦች ሁሉ እውነተኛ ፍርድ ለማግኘት፣ ተሰብስበው የሚሰነብቱባት ከተማ ስለነበረች፣ ጽላተ ሙሴም በዚያ ስለነበረች በርሷ ተማጽነውም ችግራቸው ሰለሚቃለል ታቦቷ “ታቦተ ጽዮን” ተብላለች፡፡
ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።
"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)
የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በቃል ኪዳን ታቦት ትመሰላለች ይኽቺም ፦
✿ የእግዚአብሔር የጌትነቱ መግለጫ የኾነችው፤
✿ በፍልስጥኤም ይመለክ የነበረ ጣዖትን ቀጥቅጣ ያጠፋች፤
✿ በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሰፈች፤
✿ በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት ፤
✿ ልጁ ሰሎሞንም ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ናት፡፡
ጌታ የታቦቷን አሠራር ሲነግረው "ሽምሽር ስጢን ከሚባል ከማይነቅዝ እንጨት ቀርጸኽ አብጅ ከታች እንደ ዙፋን አራት እግር አውጣለት ሞላልነቱን ኹለት ክንድ ከስንዝር ቁመቱ ክንድ ከስንዝር ወርዱን ክንድ ከስንዝር ኹለት ክንድ ከስንዝር ምስሃል ለዚኽ ቁመት የለውም አራት ቀለበት ኹለት ሙሎጊያ አበጅለት አፍአውን ውስጡን በንጹሕ ወርቅ ለብጠው በምስማኩና በምስማኩ ኹለቱን ኪሩቤል እንደሚናተፉ አውራ ዶሮዎች አንገታቸውን ደፋ አድርገኽ በላይ ሣልበት ዙሪያውን ፈለግ አውጣለት ብጽብጽ ወርቅ አፍስበት ጽላቶቹን በውስጡ አኑር" ብሎታል፡፡
ይኸውም ምሳሌ
✅ታቦት ፡- የእመቤታችን
✅ወርቅ፡- የንጽሕናዋ የቅድስናዋ
✅ታቹ መቀመጫው ፡- የንጽሓት እንስት
✅ላዩ መግጠሚያው ፡- የንጹሓን አበው
✅ግራ ቀኙ ፡- የሐና የኢያቄም
✅ወደ ውስጥ የገባችው:-የድንግል ማርያም ያቺ በመኻከላቸወም እንደኾነች እመቤታችንም ከሐና ከኤያቂም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው።
✅ኹለት ክንድ ከስንዝር:- ከአዳም እስከ ኖኅ ባለው ዘመን 2260 ዘመን ይመስላል ይኸውም በኖኅ ዘመን አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ ለመገኘቷ ምሳሌ፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ቁመቱ :- ከኖኅ እስከ ሙሴ ባለው ዘመን ይመስላል ይኸውም 1600 ዘመን ነው። በዚህ ዘመን አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ወርዱ:- ከሙሴ እስከ እመቤታችን ባለው ዘመን ይመስላል ይኽውም 1640 ዘመን ይኾናል ይኽ በኾነ አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ምሳሌዎቿ የሚሆኑ አማናዊት ድንግል ማርያም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አራቱ ቀለበት:- የአራት ወገን ንጽሕናዋ ምሳሌ ይኸውም ክርእይ /ኃጢአትን ከማየት/፤ ከሰሚዕ/ኃጢአትን ከመስማት/ ፤ ከገሲስ/በእጅ ዳሰሶ ኃጢአትን ከመሥራት እና ከአጼንዎ /የኃጢአት መዐዛን ከማሽተት/ እመቤታችን ከነዚኽ ኹሉ ተጠብቃለችና
✅ኹለቱ ቀለበት:- የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌ
✅ኹለቱ ሥዕለ ኪሩቤል:- የጠባቂ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልና የአብሳሪ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ምሳሌ ናቸው ይኽውም የብሉይ ሊቀ ካህናት በዓመት አንድ ቀን ገብቶ ከኹለቱ ኪሩቤል መካከል ቃል ሰምቶ ይወጣ ነበር ቅድስት ድንግል ማርያም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ተጠብቃ ከቅዱስ ገብርኤል ቃል ሰምታ አካላዊ ቃልን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ያለ ዘር ያለ ሩካቤ ፀንሳ ተገኝታለችና።
ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ይኽንን መንፈሳዊ ምስጢር በጥልቅት በመመርመር ድንግል ማርያምን ፡-
👉በምስጢር የተመላች ታቦት
👉 እሳትን የተመላች ታቦት
👉የቅዱስ ቃል ታቦት
👉የቃል ኪዳን ታቦት በማለት ገልጿታል፡፡
ኅዳር 21 ቀን የሚከበረውም የእመቤታችን ምሳሌዎች የተገለጡበት እና የተለያዩ ሥራዎች የተሰሩበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህም፡-
1. ነቢዩ ዘካርያስ ሁለንተናው ወርቅ የሆነ፣ የዘይት ማሰሮ በራሱ ላይ የነበረበትንና ሰባት መብራቶች ያሉትን መቅረዝ ሲያበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡ ዘካ. 4፤1-2። ዘካርያስ ያየው ብርሃን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ. 8፤12፡፡ ይህ ብርሃን የታየባትና የተገለጠባት መቅረዝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡ ብርሃን መቅረዝ እንዲያዝና እንዲገለጥ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ተገልጦልናል፡፡ ጨለማ ዓለምን አብርቷል፡፡ ብርሃን ክርስቶስን ወልዳለችና እርሷም እመ ብርሃን / የብርሃን እናት/ ትባላለች፡፡
2. ታቦተ ጽዮን ዳጎንን ገልብጣ በመጣል ኃይሏን የገለጠችበት ዕለት ነው፡፡ በፍልስጥኤማውያን ተማርካ ቤተ ጣዖት ወስደው ከጣዖታቸው ከዳጎን በታች አስቀምጠዋት ነበር፡፡ ታቦተ ጽዮን ግን በላይዋ ያለውን ዳጎንን ገልብጣ ጥላ እርሷ ከላይ ተቀመጠች፡፡ በታቦት የሚገለጠው የእግዚአብሔር ኃይል ነው፡፡ ምክንያቱም በታቦቱ ላይ ያለው ሕገ እግዚአብሔርና ስመ እግዚአብሔር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስም የጸና ክንድ ነውና ሁሉን ያሸንፋል። ስለዚህ ምንም እንኳ ለጊዜው ስትማረክ ደካማ ብትመስልም መማረኳ ግን ኃይሏን ለመግለጥ፣ ለአሕዛብ የጣዖትን ከንቱነት የታቦትን ክቡርነት ለመግለጥ ነበር፡፡
3. ቀዳማዊ ምኒልክ ታቦቱን ይዞ አክሱም የገባበት፣ ንግሥት ሳባ ታላቅ በዓል አድርጋ የተቀበለችበት፣
4. አብረሃ ወአጽብሐ በአክሱም ከተማ 12 ቤተ መቅደስ ያለው ቤተ ክርስቲያን በአስደናቂ ሁኔታ ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ቅዳሴ ቤቱን ያከበሩበት፣ እንዲሁም
5. በ9ኛው መ/ክ/ዘመን ዮዲት ክርስትና ለማጥፋት በተነሳች ጊዜ በእርሷ ምክንያት ታቦተ ጽዮን ወደ ዝዋይ ሐይቅ የተሰደደችበት፡፡ በኋላም የሰላሙ ዘመን ሲመጣ ተመልሳ አክሱም የገባችበት በዚሁ በኅዳር 21 ስለሆነ በእነዚህ በተደራራቢ ታሪኮች ምክንያት በየዓመቱ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል “ኅዳር ጽዮን በአክሱም ጽዮን” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
የእመቤታችን ልመናዋ ክብሯ አማላጅነቷም ከእኛ ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘለዓለም ጸንቶ ይኑር! አሜን!
ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ጽዮን ማርያም
ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው።
“ታቦተ ጽዮን” የሚለውንም ስያሜ ያገኘችው ጽዮን ተብላ በምትጠራው የእስራኤል ከተማ ስም ነው፡፡ ጽዮን ማለት ተፀወነ፡ ተጠጋ፣ ተማጠነ ማለት ነው፡፡ ክቡረ ዳዊትም ጽዮንን አምባ፣ መጠጊያ አድርጎ ብዙ ጠላቶቹን ተዋግቶ አሸንፎ ድልን ተጎናጽፏል።
ጽዮን የተባለችው የታላቁ የዳዊት ከተማ የተገፉና የተበደሉ ሕዝቦች ሁሉ እውነተኛ ፍርድ ለማግኘት፣ ተሰብስበው የሚሰነብቱባት ከተማ ስለነበረች፣ ጽላተ ሙሴም በዚያ ስለነበረች በርሷ ተማጽነውም ችግራቸው ሰለሚቃለል ታቦቷ “ታቦተ ጽዮን” ተብላለች፡፡
ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።
"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)
የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በቃል ኪዳን ታቦት ትመሰላለች ይኽቺም ፦
✿ የእግዚአብሔር የጌትነቱ መግለጫ የኾነችው፤
✿ በፍልስጥኤም ይመለክ የነበረ ጣዖትን ቀጥቅጣ ያጠፋች፤
✿ በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሰፈች፤
✿ በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት ፤
✿ ልጁ ሰሎሞንም ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት ናት፡፡
ጌታ የታቦቷን አሠራር ሲነግረው "ሽምሽር ስጢን ከሚባል ከማይነቅዝ እንጨት ቀርጸኽ አብጅ ከታች እንደ ዙፋን አራት እግር አውጣለት ሞላልነቱን ኹለት ክንድ ከስንዝር ቁመቱ ክንድ ከስንዝር ወርዱን ክንድ ከስንዝር ኹለት ክንድ ከስንዝር ምስሃል ለዚኽ ቁመት የለውም አራት ቀለበት ኹለት ሙሎጊያ አበጅለት አፍአውን ውስጡን በንጹሕ ወርቅ ለብጠው በምስማኩና በምስማኩ ኹለቱን ኪሩቤል እንደሚናተፉ አውራ ዶሮዎች አንገታቸውን ደፋ አድርገኽ በላይ ሣልበት ዙሪያውን ፈለግ አውጣለት ብጽብጽ ወርቅ አፍስበት ጽላቶቹን በውስጡ አኑር" ብሎታል፡፡
ይኸውም ምሳሌ
✅ታቦት ፡- የእመቤታችን
✅ወርቅ፡- የንጽሕናዋ የቅድስናዋ
✅ታቹ መቀመጫው ፡- የንጽሓት እንስት
✅ላዩ መግጠሚያው ፡- የንጹሓን አበው
✅ግራ ቀኙ ፡- የሐና የኢያቄም
✅ወደ ውስጥ የገባችው:-የድንግል ማርያም ያቺ በመኻከላቸወም እንደኾነች እመቤታችንም ከሐና ከኤያቂም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው።
✅ኹለት ክንድ ከስንዝር:- ከአዳም እስከ ኖኅ ባለው ዘመን 2260 ዘመን ይመስላል ይኸውም በኖኅ ዘመን አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ ለመገኘቷ ምሳሌ፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ቁመቱ :- ከኖኅ እስከ ሙሴ ባለው ዘመን ይመስላል ይኸውም 1600 ዘመን ነው። በዚህ ዘመን አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አንድ ክንድ ከስንዝር ወርዱ:- ከሙሴ እስከ እመቤታችን ባለው ዘመን ይመስላል ይኽውም 1640 ዘመን ይኾናል ይኽ በኾነ አርአያ ድንግል ታቦተ ኖኅ አርአያ ድንግል ጽላተ ሙሴ ምሳሌዎቿ የሚሆኑ አማናዊት ድንግል ማርያም ለመገኘቷ ምሳሌ ነው፡፡
✅አራቱ ቀለበት:- የአራት ወገን ንጽሕናዋ ምሳሌ ይኸውም ክርእይ /ኃጢአትን ከማየት/፤ ከሰሚዕ/ኃጢአትን ከመስማት/ ፤ ከገሲስ/በእጅ ዳሰሶ ኃጢአትን ከመሥራት እና ከአጼንዎ /የኃጢአት መዐዛን ከማሽተት/ እመቤታችን ከነዚኽ ኹሉ ተጠብቃለችና
✅ኹለቱ ቀለበት:- የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌ
✅ኹለቱ ሥዕለ ኪሩቤል:- የጠባቂ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልና የአብሳሪ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ምሳሌ ናቸው ይኽውም የብሉይ ሊቀ ካህናት በዓመት አንድ ቀን ገብቶ ከኹለቱ ኪሩቤል መካከል ቃል ሰምቶ ይወጣ ነበር ቅድስት ድንግል ማርያም በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ተጠብቃ ከቅዱስ ገብርኤል ቃል ሰምታ አካላዊ ቃልን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ያለ ዘር ያለ ሩካቤ ፀንሳ ተገኝታለችና።
ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ይኽንን መንፈሳዊ ምስጢር በጥልቅት በመመርመር ድንግል ማርያምን ፡-
👉በምስጢር የተመላች ታቦት
👉 እሳትን የተመላች ታቦት
👉የቅዱስ ቃል ታቦት
👉የቃል ኪዳን ታቦት በማለት ገልጿታል፡፡
ኅዳር 21 ቀን የሚከበረውም የእመቤታችን ምሳሌዎች የተገለጡበት እና የተለያዩ ሥራዎች የተሰሩበት ዕለት ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህም፡-
1. ነቢዩ ዘካርያስ ሁለንተናው ወርቅ የሆነ፣ የዘይት ማሰሮ በራሱ ላይ የነበረበትንና ሰባት መብራቶች ያሉትን መቅረዝ ሲያበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡ ዘካ. 4፤1-2። ዘካርያስ ያየው ብርሃን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ዮሐ. 8፤12፡፡ ይህ ብርሃን የታየባትና የተገለጠባት መቅረዝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡ ብርሃን መቅረዝ እንዲያዝና እንዲገለጥ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ተገልጦልናል፡፡ ጨለማ ዓለምን አብርቷል፡፡ ብርሃን ክርስቶስን ወልዳለችና እርሷም እመ ብርሃን / የብርሃን እናት/ ትባላለች፡፡
2. ታቦተ ጽዮን ዳጎንን ገልብጣ በመጣል ኃይሏን የገለጠችበት ዕለት ነው፡፡ በፍልስጥኤማውያን ተማርካ ቤተ ጣዖት ወስደው ከጣዖታቸው ከዳጎን በታች አስቀምጠዋት ነበር፡፡ ታቦተ ጽዮን ግን በላይዋ ያለውን ዳጎንን ገልብጣ ጥላ እርሷ ከላይ ተቀመጠች፡፡ በታቦት የሚገለጠው የእግዚአብሔር ኃይል ነው፡፡ ምክንያቱም በታቦቱ ላይ ያለው ሕገ እግዚአብሔርና ስመ እግዚአብሔር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ስም የጸና ክንድ ነውና ሁሉን ያሸንፋል። ስለዚህ ምንም እንኳ ለጊዜው ስትማረክ ደካማ ብትመስልም መማረኳ ግን ኃይሏን ለመግለጥ፣ ለአሕዛብ የጣዖትን ከንቱነት የታቦትን ክቡርነት ለመግለጥ ነበር፡፡
3. ቀዳማዊ ምኒልክ ታቦቱን ይዞ አክሱም የገባበት፣ ንግሥት ሳባ ታላቅ በዓል አድርጋ የተቀበለችበት፣
4. አብረሃ ወአጽብሐ በአክሱም ከተማ 12 ቤተ መቅደስ ያለው ቤተ ክርስቲያን በአስደናቂ ሁኔታ ሠርተው ከጨረሱ በኋላ ቅዳሴ ቤቱን ያከበሩበት፣ እንዲሁም
5. በ9ኛው መ/ክ/ዘመን ዮዲት ክርስትና ለማጥፋት በተነሳች ጊዜ በእርሷ ምክንያት ታቦተ ጽዮን ወደ ዝዋይ ሐይቅ የተሰደደችበት፡፡ በኋላም የሰላሙ ዘመን ሲመጣ ተመልሳ አክሱም የገባችበት በዚሁ በኅዳር 21 ስለሆነ በእነዚህ በተደራራቢ ታሪኮች ምክንያት በየዓመቱ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል “ኅዳር ጽዮን በአክሱም ጽዮን” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
የእመቤታችን ልመናዋ ክብሯ አማላጅነቷም ከእኛ ከህዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘለዓለም ጸንቶ ይኑር! አሜን!
ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ለነፍሳችን ኹለተኛዋ ነፍስ
ወዳጄ ሆይ! እምነት ለነፍስህ ኹለተኛዋ ነፍስ እንደሆነች መርምርና እወቅ፡፡ ሥጋ በነፍስ እንድትቆም የነፍስም በሕይወት መኖር በእምነትህ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ እምነትህን ብትክድ ወይም ከራስህ ብታርቃት ነፍስህ ምውት ትሆናለች፡፡
በዚህም መሠረት የሚሞት ሥጋችን በነፍስ ላይ ጥገኛ እንደሆነች ነፍሳችንም በእምነት ላይ ጥገኛ ናት፡፡ እምነትም በእግዚአብሔር አብና በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ባደረገን በእውነተኛ ልጁ ላይ ጥገኛ ናት፡፡
በዚህም እውነት ሰው ነፍሱን በሰማያት ካሉት ጋር ያገናኛታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰው በነፍሱ በሕይወት ይኖራል፡፡ በሥጋ ሰውነቱም ያያል ይመለከታል። እንዲሁ እኛም በእምነት በፍቅርና በጥበብ የእግዚአብሔር መልክ ገንዘባችን አድርገን ከመለኮቱ ተካፋይ እንሆናለህ። ስለዚህም በነፍሳችን የሞትን እንዳንሆን ይህን ድንቅ የሆነ ማሰሪያ እንዳንበጥስ ወይም ነፍሳችን ከእምነት ባዶ እንዳናደርጋት እንጠቀቅ፡፡ ጌታችን ይህን አስመልከቶ እንዲህ ብሎ አስተምሮናልና “ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው።” (ማቴ.8፥22) ይህ አየር በእኛ ላይ በንፍሐት እፍ ሳይባልብን ሥጋችንን በሕይወት የሚያቆያት ነው፡፡ የምንተነፍሰው አየር የተቋረጠበት ሰው ሕይወቱ ትቆማለች፤ በሥጋው የሞተ ይሆናል፡፡ እንዲሁ ራሱን ከእውነተኛ ልጁ ከእግዚአብሔር ቃል የለየ ሰውም በነፍሱ የሞተ ይሆናል፡፡ እኔ ሕይወትን የሚሰጠው የእውነተኛ ልጁን ምስክርነት ሳያገኝ ለሞተ ሰው አዝናለሁ፡፡ ልክ እንደ ውቅያኖስ እርሱ የሕይወት ምንጭ ነውና፡፡
እርሱ ሰው በመሆን ፈቃዱን እንድናውቀው አደረገን፡፡ ሞትን ድል ለመንሳት ሲል እጅግ መጠማቱ ለእኛ ያለውን ፍቅር አረጋገጠልን። መጽሐፍ ቅዱስ በእምነት ጻድቅ የሆነ እርሱ በሕይወት እንዲኖር አትሞልናል፡፡ እውነት የተባለው እርሱ ራሱን ዋናው ሥር በማድረግ በጎ ምግባራትን ደግሞ በእርሱ ላይ ባለን እምነት ላይ የተንጠለጠሉ ፍሬዎች አደረጋቸው፡፡
እነሆ መልካም ምግባሮቻችን በእውነትኛው ግንድ በእርሱ ቅርንጫፎች ሆነው በዝተው ፍሬን ይሠጣሉ፡፡ እነሆ በሚታይ ምሳሌ የተሰወሩ ምሥጢራት በዓይን እንደሚታዩ ሆነው ተገለጡ። ሥጋ ልክ ትርፉን ለማግኘት እንደጓጓ ነጋዴ ነው እንዲሁ ሕሊናም ከእርሱ ጋር በእምነትን በሕይወት መርከብ ትርፍን እንደሚሰብስብ መርከበኛ ነው፡፡
ሥጋ በነፍስ እንዲቆም ነፍስም ምንም እንኳ ሕያዊት ብትሆን ያለ በጎ ሥራ ሕይወት እንደሌላት፤ ነፍስ በእምነት በሚሠራ የጽድቅ ሥራ በሕይወት እንደምትኖር መጽሐፍ ቅዱስ መስክሮልናል፡፡ በክርስቶስ አምኖ የነበረው አልዓዛር ለዚህ ለምንለው እውነተኛ ምስክር ይሆን ዘንድ ሕያው ሆኖ ተነሣ፡፡
እርሱ ከመቃብር በጠራው በጌታችን ቃል ሕይወቱ ጣፍጣ ሕያው ሆነ፡፡ እንዲሁ በአልዓዛር ምሳሌ አህዛብ በሕቡዕ በሚኖረው ሕይወት ሕያዋን ሆኑ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በአይሁድ ሥራ ምሳሌ ወንበዴው ራሱን ሰቀለ እንደ ውርስ አድርጎ ሞቱን ለጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተወላቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእርሱ ላይ ባለን እምነት በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ሆነን እምነታችንን ጠብቀን እንድንኖር ይርዳን፡፡
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ወዳጄ ሆይ! እምነት ለነፍስህ ኹለተኛዋ ነፍስ እንደሆነች መርምርና እወቅ፡፡ ሥጋ በነፍስ እንድትቆም የነፍስም በሕይወት መኖር በእምነትህ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ እምነትህን ብትክድ ወይም ከራስህ ብታርቃት ነፍስህ ምውት ትሆናለች፡፡
በዚህም መሠረት የሚሞት ሥጋችን በነፍስ ላይ ጥገኛ እንደሆነች ነፍሳችንም በእምነት ላይ ጥገኛ ናት፡፡ እምነትም በእግዚአብሔር አብና በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ባደረገን በእውነተኛ ልጁ ላይ ጥገኛ ናት፡፡
በዚህም እውነት ሰው ነፍሱን በሰማያት ካሉት ጋር ያገናኛታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰው በነፍሱ በሕይወት ይኖራል፡፡ በሥጋ ሰውነቱም ያያል ይመለከታል። እንዲሁ እኛም በእምነት በፍቅርና በጥበብ የእግዚአብሔር መልክ ገንዘባችን አድርገን ከመለኮቱ ተካፋይ እንሆናለህ። ስለዚህም በነፍሳችን የሞትን እንዳንሆን ይህን ድንቅ የሆነ ማሰሪያ እንዳንበጥስ ወይም ነፍሳችን ከእምነት ባዶ እንዳናደርጋት እንጠቀቅ፡፡ ጌታችን ይህን አስመልከቶ እንዲህ ብሎ አስተምሮናልና “ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው።” (ማቴ.8፥22) ይህ አየር በእኛ ላይ በንፍሐት እፍ ሳይባልብን ሥጋችንን በሕይወት የሚያቆያት ነው፡፡ የምንተነፍሰው አየር የተቋረጠበት ሰው ሕይወቱ ትቆማለች፤ በሥጋው የሞተ ይሆናል፡፡ እንዲሁ ራሱን ከእውነተኛ ልጁ ከእግዚአብሔር ቃል የለየ ሰውም በነፍሱ የሞተ ይሆናል፡፡ እኔ ሕይወትን የሚሰጠው የእውነተኛ ልጁን ምስክርነት ሳያገኝ ለሞተ ሰው አዝናለሁ፡፡ ልክ እንደ ውቅያኖስ እርሱ የሕይወት ምንጭ ነውና፡፡
እርሱ ሰው በመሆን ፈቃዱን እንድናውቀው አደረገን፡፡ ሞትን ድል ለመንሳት ሲል እጅግ መጠማቱ ለእኛ ያለውን ፍቅር አረጋገጠልን። መጽሐፍ ቅዱስ በእምነት ጻድቅ የሆነ እርሱ በሕይወት እንዲኖር አትሞልናል፡፡ እውነት የተባለው እርሱ ራሱን ዋናው ሥር በማድረግ በጎ ምግባራትን ደግሞ በእርሱ ላይ ባለን እምነት ላይ የተንጠለጠሉ ፍሬዎች አደረጋቸው፡፡
እነሆ መልካም ምግባሮቻችን በእውነትኛው ግንድ በእርሱ ቅርንጫፎች ሆነው በዝተው ፍሬን ይሠጣሉ፡፡ እነሆ በሚታይ ምሳሌ የተሰወሩ ምሥጢራት በዓይን እንደሚታዩ ሆነው ተገለጡ። ሥጋ ልክ ትርፉን ለማግኘት እንደጓጓ ነጋዴ ነው እንዲሁ ሕሊናም ከእርሱ ጋር በእምነትን በሕይወት መርከብ ትርፍን እንደሚሰብስብ መርከበኛ ነው፡፡
ሥጋ በነፍስ እንዲቆም ነፍስም ምንም እንኳ ሕያዊት ብትሆን ያለ በጎ ሥራ ሕይወት እንደሌላት፤ ነፍስ በእምነት በሚሠራ የጽድቅ ሥራ በሕይወት እንደምትኖር መጽሐፍ ቅዱስ መስክሮልናል፡፡ በክርስቶስ አምኖ የነበረው አልዓዛር ለዚህ ለምንለው እውነተኛ ምስክር ይሆን ዘንድ ሕያው ሆኖ ተነሣ፡፡
እርሱ ከመቃብር በጠራው በጌታችን ቃል ሕይወቱ ጣፍጣ ሕያው ሆነ፡፡ እንዲሁ በአልዓዛር ምሳሌ አህዛብ በሕቡዕ በሚኖረው ሕይወት ሕያዋን ሆኑ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በአይሁድ ሥራ ምሳሌ ወንበዴው ራሱን ሰቀለ እንደ ውርስ አድርጎ ሞቱን ለጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተወላቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእርሱ ላይ ባለን እምነት በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ሆነን እምነታችንን ጠብቀን እንድንኖር ይርዳን፡፡
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
አጋንንት
ርኩሳንና ረቂቅ መናፍስት የሚጠሩበት መጠሪያ ሲሆን በብዙ ቁጥር አጋንንት ሲባሉ ጋኔን የተናጠል ስያሜያቸው ነው:: የአለቃቸው መጠሪያ ሰይጣን ሲሆን እርሱን የሚከተሉ ሠራዊቱ አጋንንት ተብለው ይጠራሉ፡፡
አጋንንት እነማን ናቸው?
በዕለተ እሁድ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ ሲፈጥራቸውም በብሩህ አእምሮ በረቂቅ ተፈጥሮ ፈጥሯቸው ነበርና በእምነት ይፈልጉኝ በአምልኮ ያቅርቡኝ በምስጋና ያክብሩኝ ተመራምረው ያግኙኝ እገለጽላቸዋለሁ ብሎ ተሰወረ፡፡ በዚህን ጊዜ ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚል ጥያቄ በመላእክት መካከል ተነስቶ ዓለመ መላእክት ተሸበረ፡፡
በመጀመሪያ ማዕረግ /በከፍታ ስፍራ/ ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ በላይ የተቀመጠው ሳጥናኤል የተባለው አለቃ ከነሰራዊቱ ነበር ወደ እርሱ የሚደርሰውን ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚለውን ከታች ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ የሚነሳውን ድምጽ በሰማ ጊዜ ከእርሱ በላይ በማዕረግ የተቀመጠ እንደሌለ አይቶ እኔ ፈጠርኋችሁ ልበላቸው ብሎ እሰበ አሰቦም አልቀረ እኔ ፈጠ ርኋችሁ አላቸው ኃጢአትን አደረገ ሐሰትንም ወለደ። /2ጴጥ2÷4/ ዮሐን 8፥44/ በዚህን ጊዜ የእርሱ ነገድ ሰራዊቱ ከሦስት ተከፋፈሉ፡፡
1ኛው - ከሰራዊቱ አንዱ እጅ አዎ ፈጠርከን ብሎ ተቀበለ ወድቆ ሰገደ
2ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ፈጥሮን ይሆን ሲለ ተጠራጠረ
3ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ምን አንተ ትፈጥረናለህ ስለምንበዛ እኛ ብንፈጥርህ እንጂ አሉ።
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ጨርሶ ሳያስክዳቸው ልገለጽላቸው አለ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የተባለውም አለቃ «ንቁም በበህላዊነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ» /የፈጠረንን እስክናውቅ ባለንበት እንጽና/ ብሎ በማወጅ የመላእክትን ዓለም አረጋጋ እግዚአብሔርም ከወደ ምስራቅ ብርሃን ገለፀላቸው /በብርሃን ጐርፍ ተገለፀላቸው/ ያን ጊዜ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአበሔር እያሉ ጮኹ ከድምጽም የተነሳ መድረኩ ተንቀጠቀጠ የክብሩንም መቅደስ የጣኑ ጢስ ሞላው /ት.ኢሳ 6፥3/ የመላእክትም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያመፀውን መልአክ ከነሰራዊቱ ሊዋጋ ለሰልፍ ወጣ በሰማይ ሰልፍ ሆነ / ራእ ዮሐ 12፥7/ የካዱትን መላእክት ተዋጋቸው ዲያብሎስም ድልን ተነስቶ ከነሰራዊቱ ወደ ምድር ተጣለ /ራእ ዮሐ 12፥9/
መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው የቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮት ግን አጋንንት በብዙ ልዩ ልዩ መጠሪያ የሚጠሩ የወደቀው መልአክና ሠራዊቶቹ መሆናቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ /ራእ 12፥9፣ ሕዝ. 28፥14፣ ኢሳ. 14፥12/ መልአካዊ ክብራቸውንና ሥልጣናቸውን ተገፈው የወደቁት መላእክት ስለመሆናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናገኛቸው ብዙ ማስረጃዎች በስፋት የሚገልጹት ሁለቱን
1.አጋንንት በኃጢአት ምክንያት የወደቁት መላአክት ስስመሆናቸው
«እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉት መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው. . .» /2ጴጥ. 2፥4/ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይመሰክራል :: /ሉቃ 10÷8 ማቴ 13:29/
2.አጋንንት በትዕቢት ምክንያት የወደቁት መሳአክት ስስመሆናቸው
«አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብን ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥህ፡፡ አንተም በልብህ ወደ ሰማይ አርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፡፡ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ ከደመ ናዎች ከፍታ በላይ አርጋለሁ:: በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጉድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ፡፡» /ኢሳ. 14፥12/ ይላል::
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ርኩሳንና ረቂቅ መናፍስት የሚጠሩበት መጠሪያ ሲሆን በብዙ ቁጥር አጋንንት ሲባሉ ጋኔን የተናጠል ስያሜያቸው ነው:: የአለቃቸው መጠሪያ ሰይጣን ሲሆን እርሱን የሚከተሉ ሠራዊቱ አጋንንት ተብለው ይጠራሉ፡፡
አጋንንት እነማን ናቸው?
በዕለተ እሁድ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ ሲፈጥራቸውም በብሩህ አእምሮ በረቂቅ ተፈጥሮ ፈጥሯቸው ነበርና በእምነት ይፈልጉኝ በአምልኮ ያቅርቡኝ በምስጋና ያክብሩኝ ተመራምረው ያግኙኝ እገለጽላቸዋለሁ ብሎ ተሰወረ፡፡ በዚህን ጊዜ ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚል ጥያቄ በመላእክት መካከል ተነስቶ ዓለመ መላእክት ተሸበረ፡፡
በመጀመሪያ ማዕረግ /በከፍታ ስፍራ/ ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ በላይ የተቀመጠው ሳጥናኤል የተባለው አለቃ ከነሰራዊቱ ነበር ወደ እርሱ የሚደርሰውን ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚለውን ከታች ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ የሚነሳውን ድምጽ በሰማ ጊዜ ከእርሱ በላይ በማዕረግ የተቀመጠ እንደሌለ አይቶ እኔ ፈጠርኋችሁ ልበላቸው ብሎ እሰበ አሰቦም አልቀረ እኔ ፈጠ ርኋችሁ አላቸው ኃጢአትን አደረገ ሐሰትንም ወለደ። /2ጴጥ2÷4/ ዮሐን 8፥44/ በዚህን ጊዜ የእርሱ ነገድ ሰራዊቱ ከሦስት ተከፋፈሉ፡፡
1ኛው - ከሰራዊቱ አንዱ እጅ አዎ ፈጠርከን ብሎ ተቀበለ ወድቆ ሰገደ
2ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ፈጥሮን ይሆን ሲለ ተጠራጠረ
3ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ምን አንተ ትፈጥረናለህ ስለምንበዛ እኛ ብንፈጥርህ እንጂ አሉ።
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ጨርሶ ሳያስክዳቸው ልገለጽላቸው አለ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የተባለውም አለቃ «ንቁም በበህላዊነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ» /የፈጠረንን እስክናውቅ ባለንበት እንጽና/ ብሎ በማወጅ የመላእክትን ዓለም አረጋጋ እግዚአብሔርም ከወደ ምስራቅ ብርሃን ገለፀላቸው /በብርሃን ጐርፍ ተገለፀላቸው/ ያን ጊዜ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአበሔር እያሉ ጮኹ ከድምጽም የተነሳ መድረኩ ተንቀጠቀጠ የክብሩንም መቅደስ የጣኑ ጢስ ሞላው /ት.ኢሳ 6፥3/ የመላእክትም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያመፀውን መልአክ ከነሰራዊቱ ሊዋጋ ለሰልፍ ወጣ በሰማይ ሰልፍ ሆነ / ራእ ዮሐ 12፥7/ የካዱትን መላእክት ተዋጋቸው ዲያብሎስም ድልን ተነስቶ ከነሰራዊቱ ወደ ምድር ተጣለ /ራእ ዮሐ 12፥9/
መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው የቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮት ግን አጋንንት በብዙ ልዩ ልዩ መጠሪያ የሚጠሩ የወደቀው መልአክና ሠራዊቶቹ መሆናቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ /ራእ 12፥9፣ ሕዝ. 28፥14፣ ኢሳ. 14፥12/ መልአካዊ ክብራቸውንና ሥልጣናቸውን ተገፈው የወደቁት መላእክት ስለመሆናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናገኛቸው ብዙ ማስረጃዎች በስፋት የሚገልጹት ሁለቱን
1.አጋንንት በኃጢአት ምክንያት የወደቁት መላአክት ስስመሆናቸው
«እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉት መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው. . .» /2ጴጥ. 2፥4/ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይመሰክራል :: /ሉቃ 10÷8 ማቴ 13:29/
2.አጋንንት በትዕቢት ምክንያት የወደቁት መሳአክት ስስመሆናቸው
«አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብን ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥህ፡፡ አንተም በልብህ ወደ ሰማይ አርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፡፡ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ ከደመ ናዎች ከፍታ በላይ አርጋለሁ:: በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጉድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ፡፡» /ኢሳ. 14፥12/ ይላል::
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"ከሁለቱ የጽድቅ እንቅፋቶች እናስተውል"!
፩.ጸድቄአለሁና
፪. አልጸድቅም
ጸላኤ ሠናያት ሰውን የሚጎዳበት ሁለት ወጥመዶች አሉት። አንዱ ጸድቂያለሁ ማሰኘት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አልጸድቅም ማሰኘት ነው። በሁለቱም ምክንያቶች ጽድቅ መሥራት አይቻልም። ጸድቄያለሁ የሚያሰኛቸው መናፍቃንን ነው። ለምን ሲባሉ ጌታን እወደዋለሁና ይላሉ። አምናለሁና ይላሉ።
ጌታን ስለምወደው ጸድቄያለሁና ጽድቅ አልሠራም የምትል ከሆነ የምትድን አይምሰልህ። ለምን ትለኝ እንደሆነ ጌታ ራሱ በመውደድ ብቻ አላዳነንምና። እወዳችሁአለሁና ዳኑ ብሎ በዙፋኑ ተቀምጦ ትእዛዝ ሰጥቶ አልቀረም።
ወዶ ምን አደረገ ትለኝ እንደሆነ፦
ምሉዕ ስፉሕ ጌታ በጠባብ ደረት በአጭር ተወሰነ። ሰማይን በደመና የሚሸፍነው በጨርቅ ተጠቀለለ።
ከነደ እሳትነቱ የተነሳ ኪሩቤል የሚንቀጠቀጡለት በብላቴናዋ በድንግል ማኅፀን ተወሰነ። ምድርና ሰማይን የሚያቀልጣቸው የክብር መብረቅ በክንደቿ ታቀፈችው። በፊቱ የእሳት ጎርፍ የሚንቆረቆርለትን በከንፈሮቿ ሳመችው። አገልጋዮቹን የእሳት ነበልባል የሚያደርገውን እንዳይበርደው እንስሶች አሟሟቁት። አዳራሹን በመብረቅ የሠራው በበረት ተኛ። ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን የተሠወረው ቅጠል ለበሰ። የስደተኞች ተስፋ ተሰደደ። የሰማይና የምድር አባት በየጥቂቱ አደገ። ምድርን በደሙ የሚያነጻት ማይን ያነጻት ዘንድ ተጠመቀ። የዓለማት ዓለም ማደሪያ አጥቶ ቀን በምኩራብ ሌሊት በተራራ ተንከራተተ። የመምህራን አምላክ ለማይሰማ ሕዝብ በሰው ቃል ዝቅ ብሎ አስተማረ። ለመምህራን በሞገስ መከበርን የሰጠ እየተሰደበ አስተማረ። መላእክት እያመሠገኑ ለማመስገን የሚሳሡለት የአይሁድን ጽርፈት ሰማ። ለተበደሉት የሚፈርድላቸው በፍርድ አደባባይ ቆመ። ከፍርድ የሚያድነው ተፈረደበት። እስረኞችን የሚፈታ ታሰረ። ሰውን ወደ ሰማይ በልዕልና ስቦ የሚያሳርገውን ጎተቱት። መንሥኤ
ሙታኑን ጣሉት። ቁስለኞችን የሚፈውሰውን ቸንክረው አቆሰሉት። ራሱን ሊያለብስ የመጣውን አራቆቱት። ርኩሳኑን በደሙ ያጠበውን ርኩስ ምራቅ ተፉበት።የኃጢአትን እሾህ የሚነቅለውን የእሾህ አክሊል ደፉበት። የሕይወትን ውኃ መራራ አጡጡት። ዲያብሎስን በመስቀሉ የቸነከረውንበጦር ወጉት። ሕይዎት እርሱን ሰቅለው ገደሉት። የምድር መሠረት የሰማይን ጽንዓት በምድር ውስጥ ተቀበረ። ትንሣኤና ሕይወት ነውና ሞትን በሞቱ ደምስሶ ተነሣ!
ወደጄ ሆይ ጌታን ስለምወደው ስለማምነው ጸድቄያለሁ የምትል ከሆነ እንዲህ ብሎ ሲጠይቅህ ምን ትመልስለታለህ? ልጄ ሆይ እኔ አንተን ወድጄ ተሰቀልኩልህ።አንተ እኔን ወደህ ምን ሆንህልኝ?በዚህ ጊዜ ስለምወድህ ትጋት ትቼ ሰነፍሁልህ ልትለው ነው? ሁሉን የሚችል አምላክ በቃሉ ብቻ ማዳን እየቻለ ነገር ግን ፍቅሩን በመከራ ገልጦ ካዳነ ሰው ለአምላኩ ቃል ብቻ እንዴት ይበቃዋል?
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወረቅ እንዲህ ሲለን እንስማ!
"ኢትበል እፈቅድ ባሕቲቱ=ወዳጄ እወዳለሁ ብቻ አትበል"ዋናተኛ ዋና እወዳለሁ በማለት ወንዝ ይሻገራልን?ሐናጺ መሆን የሚሻ ቤት መስራት በመፈለግ ብቻ ሙያውን ሳይለምድ ቤት መስራት ይችላልን? መርከበኛ መሆን የሚሻ መርከብ መቅዘፍን ሳይለምድ ሊቀ ሐመር መሆን ይችላልን?ጸሐፊስ መጻፍ በመፈለግ ብቻ ፊደል ሳያውቅ መጻፍ ይችላልን? መንጻት የሚፈልግስ ሳይታጠብ በመፈለግ ብቻ ይነጻልን? የተራበስ ስለ ምግብ በማሰብ ብቻ ይጠግባልን? ጽድቅንስ በመሥራት እንጅ በመውደድ ብቻ መዳን ይቻላልን?
ሁለተኛው ደግሞ አልጸድቅም ማለት ነው።
እንደዚህ የሚያሰኛቸው ደግሞ ምእመናንን ነው። መጀመሪያ ጥቂት ጥቂት እያለ ከጽድቅ ስራ ያወጣቸዋል። ከዚያ እግዚአብሔር መሐሪ ነው እያሰኘ ኃጢአት እንዲጨምሩ ያደርጋቸዋል። ከዚያ ወዲያ ፍጹም ኃጢአተኛ ሲሆኑ በኋላ እንዳይመለሱ መቼም አልጸድቅ ያስብላቸዋል።
የእመቤ ታችን ልጆች ንቁበት። ላልጸድቅ ሲያሰኛችሁ ክርስቶስ የውበት ባሕር ነው ብላችሁ መልሱለት። በአንዲት ውኃ ብዙ ሰዎች ቢታጠቡ ትደፈርሳለች። ክርስቶስ ግን የጎሰቆሉ ሁሉ ወደ እርሱ ገብትው ሲነጹ የእነርሱ ጉስቁልና እርሱን የማይለውጠው የምሕረት ባሕር ነውና እየገባን እንንጻ! በጭቃ የተለወሰውን ወርቅ ወልውለው አጥርተው ለአክሊልነት ያበቁታል። በእግር ከሚረገጥ ጭቃ በታች የነበረውን አጥርተው ከራስ በላይ ያውሉታል። ከምእመንነት በታች ወርዶ ጌታውን የካደውን ቅዱስ ጴጥሮስን በንስሐ ጠርቶ ርእሰ ሐዋርያት እንዳደረገው አትዘንጋ! እግዚአብሔር ቸር ነው ብሎ ኃጢአት መስራት ነው እንጅ ክፉ
እግዚአብሔር ቸር ነው እያሉ መመለስ ያድናል።
አሁንም ተስፋ ቆርጠን አንዘግይ! ለመመለስ ያብቃን!ደግሞ ማንንም የማትጸየፍ እናት አለችን። ምን ብንገዳገድ እርሷን እየተመረኮዝን እንነሳ!( በትረ ሃይማኖት ድንግል ማርያም)
ርዕሰ_ሊቃውንት_አባ_ገብረ_ኪዳን
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
፩.ጸድቄአለሁና
፪. አልጸድቅም
ጸላኤ ሠናያት ሰውን የሚጎዳበት ሁለት ወጥመዶች አሉት። አንዱ ጸድቂያለሁ ማሰኘት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አልጸድቅም ማሰኘት ነው። በሁለቱም ምክንያቶች ጽድቅ መሥራት አይቻልም። ጸድቄያለሁ የሚያሰኛቸው መናፍቃንን ነው። ለምን ሲባሉ ጌታን እወደዋለሁና ይላሉ። አምናለሁና ይላሉ።
ጌታን ስለምወደው ጸድቄያለሁና ጽድቅ አልሠራም የምትል ከሆነ የምትድን አይምሰልህ። ለምን ትለኝ እንደሆነ ጌታ ራሱ በመውደድ ብቻ አላዳነንምና። እወዳችሁአለሁና ዳኑ ብሎ በዙፋኑ ተቀምጦ ትእዛዝ ሰጥቶ አልቀረም።
ወዶ ምን አደረገ ትለኝ እንደሆነ፦
ምሉዕ ስፉሕ ጌታ በጠባብ ደረት በአጭር ተወሰነ። ሰማይን በደመና የሚሸፍነው በጨርቅ ተጠቀለለ።
ከነደ እሳትነቱ የተነሳ ኪሩቤል የሚንቀጠቀጡለት በብላቴናዋ በድንግል ማኅፀን ተወሰነ። ምድርና ሰማይን የሚያቀልጣቸው የክብር መብረቅ በክንደቿ ታቀፈችው። በፊቱ የእሳት ጎርፍ የሚንቆረቆርለትን በከንፈሮቿ ሳመችው። አገልጋዮቹን የእሳት ነበልባል የሚያደርገውን እንዳይበርደው እንስሶች አሟሟቁት። አዳራሹን በመብረቅ የሠራው በበረት ተኛ። ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን የተሠወረው ቅጠል ለበሰ። የስደተኞች ተስፋ ተሰደደ። የሰማይና የምድር አባት በየጥቂቱ አደገ። ምድርን በደሙ የሚያነጻት ማይን ያነጻት ዘንድ ተጠመቀ። የዓለማት ዓለም ማደሪያ አጥቶ ቀን በምኩራብ ሌሊት በተራራ ተንከራተተ። የመምህራን አምላክ ለማይሰማ ሕዝብ በሰው ቃል ዝቅ ብሎ አስተማረ። ለመምህራን በሞገስ መከበርን የሰጠ እየተሰደበ አስተማረ። መላእክት እያመሠገኑ ለማመስገን የሚሳሡለት የአይሁድን ጽርፈት ሰማ። ለተበደሉት የሚፈርድላቸው በፍርድ አደባባይ ቆመ። ከፍርድ የሚያድነው ተፈረደበት። እስረኞችን የሚፈታ ታሰረ። ሰውን ወደ ሰማይ በልዕልና ስቦ የሚያሳርገውን ጎተቱት። መንሥኤ
ሙታኑን ጣሉት። ቁስለኞችን የሚፈውሰውን ቸንክረው አቆሰሉት። ራሱን ሊያለብስ የመጣውን አራቆቱት። ርኩሳኑን በደሙ ያጠበውን ርኩስ ምራቅ ተፉበት።የኃጢአትን እሾህ የሚነቅለውን የእሾህ አክሊል ደፉበት። የሕይወትን ውኃ መራራ አጡጡት። ዲያብሎስን በመስቀሉ የቸነከረውንበጦር ወጉት። ሕይዎት እርሱን ሰቅለው ገደሉት። የምድር መሠረት የሰማይን ጽንዓት በምድር ውስጥ ተቀበረ። ትንሣኤና ሕይወት ነውና ሞትን በሞቱ ደምስሶ ተነሣ!
ወደጄ ሆይ ጌታን ስለምወደው ስለማምነው ጸድቄያለሁ የምትል ከሆነ እንዲህ ብሎ ሲጠይቅህ ምን ትመልስለታለህ? ልጄ ሆይ እኔ አንተን ወድጄ ተሰቀልኩልህ።አንተ እኔን ወደህ ምን ሆንህልኝ?በዚህ ጊዜ ስለምወድህ ትጋት ትቼ ሰነፍሁልህ ልትለው ነው? ሁሉን የሚችል አምላክ በቃሉ ብቻ ማዳን እየቻለ ነገር ግን ፍቅሩን በመከራ ገልጦ ካዳነ ሰው ለአምላኩ ቃል ብቻ እንዴት ይበቃዋል?
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወረቅ እንዲህ ሲለን እንስማ!
"ኢትበል እፈቅድ ባሕቲቱ=ወዳጄ እወዳለሁ ብቻ አትበል"ዋናተኛ ዋና እወዳለሁ በማለት ወንዝ ይሻገራልን?ሐናጺ መሆን የሚሻ ቤት መስራት በመፈለግ ብቻ ሙያውን ሳይለምድ ቤት መስራት ይችላልን? መርከበኛ መሆን የሚሻ መርከብ መቅዘፍን ሳይለምድ ሊቀ ሐመር መሆን ይችላልን?ጸሐፊስ መጻፍ በመፈለግ ብቻ ፊደል ሳያውቅ መጻፍ ይችላልን? መንጻት የሚፈልግስ ሳይታጠብ በመፈለግ ብቻ ይነጻልን? የተራበስ ስለ ምግብ በማሰብ ብቻ ይጠግባልን? ጽድቅንስ በመሥራት እንጅ በመውደድ ብቻ መዳን ይቻላልን?
ሁለተኛው ደግሞ አልጸድቅም ማለት ነው።
እንደዚህ የሚያሰኛቸው ደግሞ ምእመናንን ነው። መጀመሪያ ጥቂት ጥቂት እያለ ከጽድቅ ስራ ያወጣቸዋል። ከዚያ እግዚአብሔር መሐሪ ነው እያሰኘ ኃጢአት እንዲጨምሩ ያደርጋቸዋል። ከዚያ ወዲያ ፍጹም ኃጢአተኛ ሲሆኑ በኋላ እንዳይመለሱ መቼም አልጸድቅ ያስብላቸዋል።
የእመቤ ታችን ልጆች ንቁበት። ላልጸድቅ ሲያሰኛችሁ ክርስቶስ የውበት ባሕር ነው ብላችሁ መልሱለት። በአንዲት ውኃ ብዙ ሰዎች ቢታጠቡ ትደፈርሳለች። ክርስቶስ ግን የጎሰቆሉ ሁሉ ወደ እርሱ ገብትው ሲነጹ የእነርሱ ጉስቁልና እርሱን የማይለውጠው የምሕረት ባሕር ነውና እየገባን እንንጻ! በጭቃ የተለወሰውን ወርቅ ወልውለው አጥርተው ለአክሊልነት ያበቁታል። በእግር ከሚረገጥ ጭቃ በታች የነበረውን አጥርተው ከራስ በላይ ያውሉታል። ከምእመንነት በታች ወርዶ ጌታውን የካደውን ቅዱስ ጴጥሮስን በንስሐ ጠርቶ ርእሰ ሐዋርያት እንዳደረገው አትዘንጋ! እግዚአብሔር ቸር ነው ብሎ ኃጢአት መስራት ነው እንጅ ክፉ
እግዚአብሔር ቸር ነው እያሉ መመለስ ያድናል።
አሁንም ተስፋ ቆርጠን አንዘግይ! ለመመለስ ያብቃን!ደግሞ ማንንም የማትጸየፍ እናት አለችን። ምን ብንገዳገድ እርሷን እየተመረኮዝን እንነሳ!( በትረ ሃይማኖት ድንግል ማርያም)
ርዕሰ_ሊቃውንት_አባ_ገብረ_ኪዳን
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"ከእናንተ እያንዳንዱ በመጾሙ ያገኘውን ጥቅም ውስጡን (ሕሊናውን) ይጠይቅ ዘንድ እማልዳችኋለሁ፤ እማፀናችሁማለሁ! ብዙ ጥቅም እንዳገኘ ከተረዳ ይህን ያገኘው በመበርታቱ ምክንያት እንደ ኾነ ይቍጠር፡፡ ምንም ነገር ያላገኘ እንደ ኾነ ግን ቀሪውን ጊዜ ተግቶ በመጾም የንግድ ዕቃዎችን (መንፈሳዊ በቁዔትን) ለማግኘት ይጠቀምበት፡፡
ወርሐ ጾሙ እስከሚፈጸም ድረስ ባዶ እጃችንን እንዳንቀርና ታላቅ የኾነ ትርፍን እናግኝ ዘንድ ራሳችንን ልል ዘሊላን አናድርግ፡፡ በዚህ መንገድ የጾምን ዋጋ ልናጣ አይገባምና፡፡ እስከ አሁን ድረስ የጾሙን ድካም ታግሠናልና፡፡ የጾምን ድካም ታግሠው እያለ የጾምን ፍሬ ጻማ አለማግኘት አለና፡፡
ከምግበ ሥጋ ርቀን እያለ ከምግበ ኃጢአት ካልራቅን፣ ሥጋ የማንበላ ኾነን እያለ የድኾችን ቤት ተስገብግበን የምንበላ (የማንመጸውት) ከኾነ፣ ወይን ጠጥተን የማንሰክር ኾነን እያለ በክፉ መሻት የምንሰክር ከኾነ፣ ቀኑን ሙሉ በአፋችን እንጀራ የማያልፍ ኾኖ እያለ በምኞት ዓይን የምንቅበዘበዝ ከኾነ የጾምን ፍሬ አናገኝምና፡፡ የጾምን ድካም እየደከምን እያለ የዓመፀኞችን ተውኔት የምንመለከት ከኾነ የጾምን ዋጋ እንደማናገኝ ዕወቅ፤ ተረዳም፡፡"
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ወርሐ ጾሙ እስከሚፈጸም ድረስ ባዶ እጃችንን እንዳንቀርና ታላቅ የኾነ ትርፍን እናግኝ ዘንድ ራሳችንን ልል ዘሊላን አናድርግ፡፡ በዚህ መንገድ የጾምን ዋጋ ልናጣ አይገባምና፡፡ እስከ አሁን ድረስ የጾሙን ድካም ታግሠናልና፡፡ የጾምን ድካም ታግሠው እያለ የጾምን ፍሬ ጻማ አለማግኘት አለና፡፡
ከምግበ ሥጋ ርቀን እያለ ከምግበ ኃጢአት ካልራቅን፣ ሥጋ የማንበላ ኾነን እያለ የድኾችን ቤት ተስገብግበን የምንበላ (የማንመጸውት) ከኾነ፣ ወይን ጠጥተን የማንሰክር ኾነን እያለ በክፉ መሻት የምንሰክር ከኾነ፣ ቀኑን ሙሉ በአፋችን እንጀራ የማያልፍ ኾኖ እያለ በምኞት ዓይን የምንቅበዘበዝ ከኾነ የጾምን ፍሬ አናገኝምና፡፡ የጾምን ድካም እየደከምን እያለ የዓመፀኞችን ተውኔት የምንመለከት ከኾነ የጾምን ዋጋ እንደማናገኝ ዕወቅ፤ ተረዳም፡፡"
ለተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09