Telegram Web Link
ሰሙነ ሕማማት
ሐሙስ
የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ
አረንጓዴ ሐሙስ
ምሴተ ሐሙስ
የትህትና ሐሙስ
ዕጽበተ ሐሙስ

ጌታ በትህትና እግር ያጠበበት
ዕለተ_ሐሙስ
#ዕጽበተ_ሐሙስ
ይህ ቀን የጌታ ትህትና በአባቶች ካህናት የሚታይበት ውብ ዕለት


" እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 13:14)
ሰሙነ ሕማማት
#መልካም_አርብ
ስቅለት
የሐዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራኒዮ በእንጨት መስቀል ላይ
ራሱን ስለ እኛ መስዋዕት አድርጎ ያቀረበበት እለት

ዮሐንስ 19:16
ስለዚህ በዚያን ጊዜ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጣቸው።
17: ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
18: በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
19: ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም፦ “የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ፡” የሚል ነበረ።
- ሉቃስ 22:42:
“አባት ሆይ፥ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ፡” እያለ ይጸልይ ነበር።
43: ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።
Live stream started
ማቴዎስ 27:45
ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
46: በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ?” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።
ይህም፦ “አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ?” ማለት ነው።
47: በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው፦ “ይህስ ኤልያስን ይጠራል፡” አሉ።
48: ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ቀዳም ሹር
በብሉይ ኪዳን በዚህች ቀን ከስራዎች ያረፈው አምላክ ያው እግዚአብሔር በዚህች እለት በጥልቅ ዝምታ ነፍስ በተለየው መለኮት በተዋሃደው ስጋ በመቃብር ዋለ። ለዚህም በዓመቱ ሰንበትነቷ ተሽሮ ሲጾምባት ይዋላል።
ማቴዎስ 27:57
በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤
59: ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥
60: ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።
ገብረ ሰላም በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ
ቆላስይስ1:19-20
እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአልና።

@eotchntc
በአንድ ሰው ምክንያት ሞት ወደ ዓለም ገብቶ ነበር ። ከአዳም ጀምሮ ለ 5 እልፍ አመታት ሞት ነገሦ ነበር።

ነገር ግን ክርስቶስ በሥጋ በመጣ ጊዜ እንደ ሞቱ ያይደለ ሕይወት በብዙ እጥፍ በዛች።

ትንሣኤውም ለእኛ ትንሣኤ መሰረት ሆነልን ። ቅሉ ክርስቶስ ትንሣኤም ሕይወትም እኔ ነኝ ብሎ ተናግሮ ነበር።

ቀጥቅጥ መዝራዕቶ እንዳለ ዛሬ የእልፍ ዘመን ጠላት ተቀጠቀጠ።

ከዛሬ ጀምሮ ሞት አቅም የለውም አቅሙንም  አጥቷል።

ስለዚህም እኛ በክርስቶስ ያመንን ክርስቲያኖች ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ ድል መንሣትህስ የት አለ እያልን እንሳለቅበታለን።

በዚህም ትንሣኤ ክርስቶስ የሃይማኖታችን ማዕከል ሆነ ። ክርስቶስ ካልተነሣማ እምነታችን ከንቱ ነዋ!

ስለዚህም በብርሃኑ ብርሃንን አየን እያልን መላ ዘመናችንን እንዘምራለን።

በብርሃኑ ተመላለሱ!

ሰዱቃዊ ሁሉ ባያምን ብርሃኑን ፤
ያመነው እኛ ግን እንመሰክራለን።

እንኳን አደረሰን !

ትንሣኤ ፳፻፲፯ ዓ.ም

ባሕር ዳር

@Pauli0111
Live stream finished (1 day)
Live stream started
- 1ኛ ቆሮንቶስ 15:20
አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
21: ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።
22: ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
23: ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ ክርስቶስ እንደ በኩራት ነው፥ በኋላም በመምጣቱ ለክርስቶስ የሆኑት ናቸው፤
24: በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።
"ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤
አሰሮ ለሰይጣን፤
አግዐዞ ለአዳም፤
ሰላም
እምይዕዜሰ፤
ኮነ፤
ፍስሐ ወሰላም።"

"ክርስቶስ መሥዋዕቱን ስለ ሁላችንም ኾኖ አቀረበ፡፡ ከመጀመሪያው ጥፋት ተጠያቂነት ሁላችንም ነጻ ያደርገን ዘንድ መቅደስ ሰውነቱን ስለ ሁላችን ሲል ለሞት አሳልፎ ሰጠ ፡፡"
    ቅዱስ አትናቴዎስ

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሰን፣ አደረሳችሁ

    መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንልን !!!
ማዕዶት(መሻገር)
#ሰኞ
ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ከሞት
ወደ ህይወት መሻገራችን የሚነገርባት እለት።
@eotchntc
ቶማስ
#ማክሰኞ
በዚህች ቀን ቶማስ ጌታችንን አይቶ ብቻ ባለማመኑ መንካት አለብኝ ብሎ ጎኑን በመንካት የጌታን ጌትነት አምላክነት የመሰከረበት ዕለት ነው።

ዮሐንስ 20:27: ከዚያም በኋላ ቶማስን፦ “ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን፡” አለው።
28: ቶማስም፦ “ጌታዬ አምላኬም፡” ብሎ መለሰለት።
29: ኢየሱስም፦ “ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው፡” አለው።

@eotchntc
አልአዛር
#ረቡዕ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደውን አልአዛርን ከመቃብር ያስነሳበት
እርሱ ትንሳኤና ህይወት መሆኑን ያረጋገጠበት ዕለት ይታሰባል።

ዮሐንስ 11:43
ይህንም ብሎ፡ በታላቅ ድምፅ፦ “አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና፡” ብሎ ጮኸ።
44: የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፊቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም፦ “ፍቱትና ይሂድ ተዉት፡” አላቸው።

@eotchntc
#ብጹዕ_አባታችን_አቡነ_ገብርኤል
ከሰሞኑ አባታችን ስለ #ቤዛነት ባስተማሩት ከቤተክርስቲያን በወጣ(ባፈነገጠ) ትምህርት ምክንያት ብዙ ውዝግብ መነሳቱ ይታወቃል።
ቤተክርስቲያንም ለአርብ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርታለች።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ጉባኤው የፍቅር እና የበረከት ሆኖ ብጹዕነታቸው ወደ ቀናው ትምህርት የሚመለሱበት አባቶቻችን አበው እንደተለመደው ጥበብና ማስተዋላቸውን የሚያሳዩበት
አድርግልን።እመቤታችን ሆይ በሐዋርያት መካከል እንደተገኘሽ በአባቶቻችን ጉባኤ ላይ ተገኚ።
መንፈስ ቅዱስ ሆይ ሁሉን ላንተ እንሰጣለን።

በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሁን አሜን🤲🤲🤲🤲

@eotchntc
አዳም ሐሙስ
#ሐሙስ
ይህቺ ዕለት አዳም ሐሙስ ትባላለች
ለአዳምና ለልጆቹ የተገባላቸው ኪዳን መፈጸሙን የሚታሰብበት ዕለት
@eotchntc
2025/06/30 06:03:03
Back to Top
HTML Embed Code: