ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ አሳፋሪ ልማዶች አንዱ የሆነውን የመንገድ ላይ መፀዳዳትን እስከመጨረሻው ለማስቀረት በሺዎች የሚቆጠሩ የህዝብ ዘመናዊ መፀዳጃ ቤት ቤቶችን ለመገንባት በጠ/ሚ አብይ አህመድ የ“ጽዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” ንቅናቄን ይፋ አድርገዋል ።

ጽዱ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚውለውን በጀት ለማሰባሰብ የጠ/ሚ ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት ዲጂታል ቴሌቶን አስጀምሯል። ይህን ተከትሎ ብዙዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው ሂሳብ ቁጥር 1000623230248 የድርሻቸውን በማበርከት ላይ ይገኛሉ።
     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
🔖 ስራ እናስጀምርዎ - በነፃ

ከቤትዎ ሆነው በኦንላይን ከኛ ጋር ይስሩ!!!

ምንም ክፍያ አይጠይቅም፣ አሰራሩን በነፃ እናስተምራለን።

እቃዎችን በተለያዩ የኦንላይን አማራጮች
በመሸጥ ተጨማሪ ገቢ ያግኙ፣ ገንዘብ ይስሩ!

👉100 ሪሴለሮችን እንፈልጋለን።

በቴሌግራም፣ በፌስቡክ፣ በማርኬትፕሌስ፣ በቲክቶክ፣
በኢንስታግራም፣ በራስዎ በማስተዋወቅ እቃዎችን ይሽጡ!

https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (ይቀላቀሉ)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)

Contact 👉 @Habeshastorechat

በተለይ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ጎን ለጎን የምትሰሩት!

በስማርት ስልክዎ አሁኑኑ ካሉበት ስራ ይጀምሩ!
አሜሪካ ለዓለም ፍጻሜ መሸሸጊያ የሚውል አውሮፕላን እንዲሰራ አዘዘች፡፡

የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር አሜሪካ እንደ ኑክሌር አይነት ጦርነት ቢነሳ ከአደጋ መጠበቅ የሚቻልበት አውሮፕላን እንዲሰራ ማዘዟ ተገልጿል፡፡

እንደ ሮይተርስ ዘገባ አሜሪካ በ1970ዎቹ የተሰራ የክፉ ቀን መጠለያ አውሮፕላን የሰራች ሲሆን ይህ አውሮፕላን አርጅቷል በሚል አዲስ ልዩ አውሮፕላን እንዲሰራ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ ለክፉ ቀን ማምለጫ ይሆናል የተባለው ይህ አውሮፕላንም 13 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይፈጃል የተባለ ሲሆን ሴራ ኔቫዳ ኮርፖሬሽን የተሰኘው ኩባንያ አዲሱን አውሮፕላን እንደሚሰራው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

ኢ-4ቢ የተሰኘ ስያሜ ያለው ይህ አዲስ አውሮፕላን አውሮፕላን በፈረንጆቹ 2036 እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል፡፡የአሜሪካ አየር ሀይል ንብረት የሆነው ይህ ልዩ የክፉ ቀን መሸሸጊያ አውሮፕላን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንትን ጨምሮ ሌሎች ቁልፍ አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና ሌሎች እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች እና ቴክኖሎጂዎችን ይዟል ተብሏል፡፡

እንዲሁም አውሮፕላኑ እንደ ኑክሌር ጦርነት፣ አውዳሚ አደጋዎች እና ሌሎች አስጊ ክስተቶች ቢከሰቱ መሪዎች በዚህ አውሮፕላን ላይ በመሆን ትዕዛዝ እና ውሳኔዎችን እንዲያካሂዱ ያገለግላልም ተብሏል፡፡ የመሰብሰቢያ ቢሮዎች፣ የነዳጅ መሙያዎች እና የተግባቦት መሳሪያዎችም ያሉት ሲሆን አሁን በስራ ላይ ያለው የክፉ ቀን መሸሸጊያ አውሮፕላን ከ2030 በኋላ ከአገልግሎት ውጪ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡

     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
🔖 ስራ እናስጀምርዎ - በነፃ

👉ተጨማሪ 150 ሪሴለሮችን እንፈልጋለን።

ከቤትዎ ሆነው በኦንላይን ከኛ ጋር ይስሩ!!!

ምንም ክፍያ አይጠይቅም፣ አሰራሩን በነፃ እናስተምራለን።

እቃዎችን በተለያዩ የኦንላይን አማራጮች
በመሸጥ ተጨማሪ ገቢ ያግኙ፣ ገንዘብ ይስሩ!

በቴሌግራም፣ በፌስቡክ፣ በማርኬትፕሌስ፣ በቲክቶክ፣
በኢንስታግራም፣ በራስዎ በማስተዋወቅ እቃዎችን ይሽጡ!

https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (ይቀላቀሉ)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)

Contact 👉 @Habeshastorechat

በተለይ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ጎን ለጎን የምትሰሩት!

በስማርት ስልክዎ አሁኑኑ ካሉበት ስራ ይጀምሩ!
ብሊንከን ከአረብ ሀገራት አቻዎቻቸው ጋር ለመምከር ሪያድ ገቡ!

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በጋዛ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ሰባተኛ የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸውን እያደረጉ ነው። ሚኒስትሩ ከአምስት የኣአረብ ሀገራት አቻዎቻቸው ጋር ለመምከር ዛሬ ሳኡዲ አረቢያ ገብተዋል።

ብሊንከን ከአረብ ኤምሬትስ፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር በሪያድ የሚያደርጉት ምክክር በጋዛ ከጦርነቱ በኋላ ምን አይነት አስተዳደር ይዋቀር በሚለው ዙሪያ ያተኩራል ተብሏል።

አሜሪካ ሃማስ ሙሉ በሙሉ መደምሰስ አለበት የሚለውን የእስራኤል አቋም ብትደግፍም እስራኤል ጋዛ ሰርጥን ዳግም እንድትቆጣጠር ግን እንደማትፈልግ ስትገልጽ ቆይታለች። አለማቀፍ እውቅና ያለውን የፍልስጤም አስተዳደር ያካተተ እና የአረብ ሀገራት ድጋፍ ያለው አስተዳደር እንዲመሰረትም ትፈልጋለች። የሰብአዊ ድጋፍ የሚገባበት መንገድን ማስፋት እና የፈራረሰችውን ጋዛን መልሶ ለማቋቋም ከአውሮፓ ሀገራት ጋር በትብብር ሊሰራ የታሰበውን ስራ በተመለከተም ውይይት ይደረጋል ብሏል ሬውተርስ በዘገባው።

ሳኡዲ አረቢያ እና ሌሎች የአረብ ሀገራት ከእስራኤል ጋር ግንኙነታቸውን ለማደስ የጀመሩት ጥረትን በተመለከተም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ እንደሚመክሩ ነው የተገለጸው።የአረብ ሀገራት ከእስራኤል ጋር ግንኙነታቸውን ሲያድሱ እስራኤል ለፍልስጤም ነጻ ሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ ዋሽንግተንም ጫና እንደምታደርግ ስምምነት ቢኖርም ኔታንያሁ በተደጋጋሚ ውድቅ አድርገውታል።

በመካከለኛው ምስራቅ ሰባት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሰባተኛ ጉብኝታቸውን እያደረጉ የሚገኙት ብሊንከን የጋዛውን ጦርነት የሚያስቆምና ታጋቾችን የሚያስለቅቅ መፍትሄ አላገኙም።
የጥንቃቄ መልዕክት
***
መጪው የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ የበዓል ግብይቱ ከወትሮው ከፍተኛ ነው፡፡ ይህንን አጋጣሚ አጭበርባሪዎች ሀሰተኛ የብር ኖቶችን እና የውጭ አገር ገንዘቦችን ለማዘዋወር ይጠቀሙበታል፡፡

በመሆኑም የበዓል ግብይቶዎን በተለያዩ የዲጂታል ባንኪንግ የክፍያ አማራጮች በመጠቀም ራስዎን በሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶች ከመጭበርበር ይጠብቁ፡፡

ሆኖም በጥሬ ገንዘብ መገበያየት ግዴታ በሚሆንባቸው ሁኔታዎች ሁሉ ከፍተኛ ማጣራት እና ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ሲሆን፣ ከዚህ መልእክት ጋር ያያዝነውን ከብሄራዊ ባንክ የተገኘ ትክክለኛ የብር ኖቶችን የደህንንነት መጠበቂያ ምልክቶች እና ምስሎች የሚያሳይ መረጃ በትኩረት እንድታዩ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
🌺የበአል ቅናሽ ፓኬጅ🌺

1. Feenik Vacuum ፔርሙስ (1.5 Litre!)
2. ቡናና ቅመም መፍጫ
3. ሽቶ መቀነሻ

🌺ዋጋ ፣ 3100birr / ቅናሹን ይጠቀሙ!

ሱቅ ሲመጡ ከአንዳንድ እቃዎች ላይ አስተያየት እናደርጋለን

  ☎️ 0901882392
    ☎️ 0931448106

አድራሻ፣ ከ4ኪሎ መገናኛ መንገድ ላይ ቤሊየር መብራቱ ጋር ከአቤኔዘር ህንፃ ፊትለፊት አዲሱ፣ አል-ዘይን ህንፃ 207ቁ፣

💬  በTelegram ለማዘዝ ⤵️ ይጠቀሙ
👉 @Antenehg1
Foldable High Capacity Travel Bags 
        💯 High Quality

🥰እንዳያመልጣችሁ / ምርጥ ቦርሳ ነው።
ጠንካራ እና ተጣጣፊ ፣ በጣም የሚያምር!

⚡️Lightweight Travel Carry Bag
⚡️24” High Capacity
⚡️Water-resistant multiple pockets
⚡️Multifunctional Sports Travel Bags

👉It is portable with multiple ways to carry, handheld, shoulder-on, or put on luggage.

💦 ዋጋ፦ 1,400ብር

        ☎️ 0901882392
        ☎️ 0931448106
ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለአብን ከፍተኛ አመራር ሹመት ሰጡ!

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር ለሆኑት ለአቶ መልካሙ ፀጋዬ ሹመት ሰጥተዋል። ርእሰ መሥተዳድሩ አቶ መልካሙ ጸጋዬን የክልሉ ባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አድርገው መሾማቸውን በብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።

     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
🔖 ስራ እናስጀምርዎ - በነፃ

👉ተጨማሪ 300 ሪሴለሮችን እንፈልጋለን።

ከቤትዎ ሆነው በኦንላይን ከኛ ጋር ይስሩ!!!

ምንም ክፍያ አይጠይቅም፣ አሰራሩን በነፃ እናስተምራለን።

እቃዎችን በተለያዩ የኦንላይን አማራጮች
በመሸጥ ተጨማሪ ገቢ ያግኙ፣ ገንዘብ ይስሩ!

በቴሌግራም፣ በፌስቡክ፣ በማርኬትፕሌስ፣ በቲክቶክ፣
በኢንስታግራም፣ በራስዎ በማስተዋወቅ እቃዎችን ይሽጡ!

https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (ይቀላቀሉ)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)
https://www.tg-me.com/AddisEkaResellers (join-us)

Contact 👉 @Habeshastorechat

በተለይ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ጎን ለጎን የምትሰሩት!

በስማርት ስልክዎ አሁኑኑ ካሉበት ስራ ይጀምሩ!
በአማራ ክልል ከ4 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች በትምህር ገበታቸው ላይ አለመሆናቸውን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በበኩሉ አንጻራዊ ሰላም በሰፈነባቸው አከባቢዎች ት/ት እያስጀመርኩ ነው ብሏል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአወዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ እንዳስታወቀው በአማራ ክልል አራት ነጥብ 1 ሚሊየን ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ አይደለም።

በክልል ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አራት ሺ 178 ትምህርት ቤቶች በክልሉ በመካሄድ ላይ ባለው ግጭት እና ከዚህ ቀደም በነበረው ጦርነት ሳቢያ ተዘግተዋል፤ ከነዚህ ት/ት ቤቶች ውስጥ 300 የሚሆኑት መጎዳታቸውን እና 350 የሚሆኑት ሌሎቹ ደግሞ አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ቢሮው ጠቁሟል።

ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን በላይ የሚሆኑ የክልሉ ተማሪዎች በትምህርት ምገባ እንደሚያሻቸው የማስተባበሪያ ቢሮው የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ በይፋዊ የኤክስ ገጹ ባጋራው መረጃ አመላክቷል።

በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል አንጻራዊ የሰላም መሻሻል በታየባቸው የክልሉ አካባቢዎች የሚገኙ ከ360 በላይ ትምህርት ቤቶች ተቋርጦ የነበረው የመማር ማስተማር ስራ መጀመራቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደግሰው መለሰ አስታውቀዋል።

ቢሮው የባከነውን ጊዜ ለማካካስ እንዲቻል የይዘት ማጣጣም ፕሮግራም በማውጣት ለትምህርት ተቋማት መላኩን ያመላከተቱት ሃላፊው መማር ማስተማር የጀመሩ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች የማካካሻ ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ብለዋል።በድርቅና ተያያዥ ስራዎች በተጎዱ አካባቢዎች በሚገኙ 442 ት/ት ቤቶች የሚማሩ ከ221 ሽህ በላይ ተማሪዎች በመንግስት፣ በአለም ምግብ ድርጅትና በሌሎች አጋር ድርጅቶች አማካኝነት የትምህርት ቤት ምገባ እየተሰጠ መሆኑን አቶ ደግሰው መለሰ ተናግረዋል፡

     T.me/ethio_mereja
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ ለአምስት ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ዛሬ ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት በተደረገው በዚሁ ስምምነት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን የካርድ ባንክ አገልግሎት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት እንደሚያግዘው ተነግሯል።

በተጨማሪም አዳዲስ የካርድ አገልግሎቶችን ለማስጀመር እንደሚረዳም ተጠቁሟል።በዚህ የአምስት አመት ሰምምነት መሰረት የባንኩን ደንበኞች ፍላጎት በማሟላት ላይ የሚያተኩሩ እና አለም የደረሰበትን አዳዲስ አገልግሎቶችን በሀገር ውሰጥ በማስተዋወቅ ጥሬ ገንዘብ አልባ ማህበረሰብን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንደሚያደርግ ይገመታል።

ማስተር ካርድ ከ210 ሀገሮች በላይ የሚሰራ አለማቀፍ የክፍያ አቀላጠፊ ድርጅት ሲሆን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር መስራት ከጀመረ እረጅም አመታት እንደሆነ ይታወቃል።

     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
ኢትዮጵያ በአውሮፓ ህብረት ውሳኔ ማዘኗን ገለጸች፡፡

የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ዕለት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ የመስጠት ሂደት ላይ ጊዜያዊ ገደቦች ማስቀመጡን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ህብረቱ ውሳነውን ያሳለፈው የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ ህጋዊ መኖሪያ ያላገኙ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተባባሪ አልሆነም በሚል የቪዛ ገደብ ጥያለሁ ብሏል፡፡በህብረቱ አዲስ ውሳኔ መሰረትም ኢትዮጵያዊያን ከዚህ በፊት በአውሮፓ ሀገራት በ15 ቀናት ውስጥ ለቪዛ ጥያቄቸው ምላሽ ያገኙ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ውሳኔ መሰረት ይህንን ወደ 45 ቀናት ከፍ አድርጓል፡፡

ውሳኔው የአገልግሎት እና ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት የያዙ የቪዛ አመልካች ኢትዮጵያዊያንንም እንደሚጨምር በወቅቱ ተገልጾ ነበር፡፡ በአውሮፓ ህብረት ዋና ከተማ ብራስልስ ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የአውሮፓ ህብረት ውሳኔ የሚያበሳጭ ነው ብሏል፡፡ኢምባሲው የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያዊያን ላይ ያስተላለፈው የቪዛ ገደብ ወቅቱን ያላገናዘበ ነው ያለ ሲሆን ኢትዮጵያ በአውሮፓ ሀገራት የመኖሪያ ፈቃድ ያላገኙ ኢትዮጵያዊያንን ለመመለስ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገች ባለበት ወቅት ውሳኔው መተላለፉ ቅር እንዳሰኘውም አስታውቋል፡፡

በአውሮፓ ያለ መኖሪያ ፈቃድ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ዜግነትና ተያያዥ መረጃዎች እየተጣሩ ነበር ያለው ኢምባሲው እነዚህን ዜጎች ክብራቸውን በጠበቀ መልኩ እንዴት መመለስ እንደሚቻል ዝግጅት እያደረግን ነበር እንጂ ተባባሪ አልነበርም ሲል ኢምባሲው በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡የአውሮፓ ም/ቤት ውሳኔ ኢትዮጵያ በአውሮፓ ሀገራት የመኖሪያ ፈቃድ ያላገኙ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እያደረገችው ያለውን ጥረት ሊያስተጓጉል እንደሚችልም ኢምባሲው በሰጠው ምላሽ ላይ አስታውቋል፡፡
       @ethio_mereja
ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር የተቋቋሙ አስተዳደሮች እስከ ሰኔ 30 መፍትሔ እንደሚያገኙ ጄነራል ታደሰ ተናገሩ


የትግራይን ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ስር ተጠቅለው የተቋቋሙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች እስከ ሰኔ 30/ 2016 ዓ.ም መፍትሔ እንደሚያገኙ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል።

ጄነራል ታደሰ ባለፉት ሁለት ቀናት የፕሪቶሪያ ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት አተገባበር በተመለከተ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመከላከያ እና ከፌደራል መንግሥት ባለስልጣናት ጋር ያደረጉትን ውይይት መሰረት በማድረግ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው ይህንን የተናገሩት።

የአማራ ክልል ይገባኛል በሚላቸው እና የትግራይን ጦርነት ተከትሎ ክልሉ ጠቅልሎ እንደ አዲስ ያዋቀራቸው የደቡብ ትግራይ እና ጸለምቲ ወረዳዎች መፍትሄ ለማበጀት እስከ ግንቦት 30/2016 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ ስምምነት ላይ መደረሱን ጄነራል ታደሰ ገልጸዋል።

በተጨማሪም በአማራ ክልል በኩል ወልቃይት ተብሎ በሚጠራው ምዕራብ ትግራይ እንደ አዲስ የተቋቋመው አስተዳደር እስከ ሰኔ 30 ባለው ጊዜ መፍትሔ ይበጅለታል ብለዋል።

በዚህም ውይይት ላይ ትጥቅ መፍታትን አስመልክቶ የትኞቹ አስተዳዳራዊ መዋቅሮች መፍረስ እንዳለባቸው እና የተፈናቀሉ ዜጎች እንደሚመለሱ ዝርዝር እቅድ የወጣ ሲሆን ይህንንም የሚቆጣጠረው እና የሚያረጋግጠው የአፍሪካ ኅብረት የስምምነት ክትትል አረጋጋጭ እና አስከባሪ ኮሚቴ እንደሚሆን ተገልጿል። ኮሚቴው መቀለ ላይ ቢሮ እንዳለው ከዚህ ቀደም ጄነራል ታደሰ መናገራቸው ይታወሳል።

     T.me/ethio_mereja
       @ethio_mereja
2024/05/03 03:20:34
Back to Top
HTML Embed Code: