የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ ምስጋኑ አረጋ የአውሮፓ ኅብረት ካውንስል ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ ያሳለፈው የቪዛ ገደብ ውሳኔ "የማይጠቅም ውሳኔ" ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

ሚንስትር ደዔታው በ"ኤክስ" ገጻቸው ባሠፈሩት መልዕክት፣ ጉዳዩ በኢትዮጵያና አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት ውስጥ "አዋኪ ጉዳይ መኾን ሊኾን አይገባውም" ብለዋል። አውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ ጠንካራ አጋር መኾኑን የጠቀሱት ምስጋኑ፣ ችግሩ ባስቸኳይ ሊፈታ እንደሚገባው ገልጸዋል።

ኅብረቱ በአውሮፓ አገራት ውስጥ የመቆየት ፍቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያዊያን ላይ ከጣለው የቪዛ ገደብ በተጨማሪ፣ የዲፕሎማቲክና አገልግሎት ፓስፖርት ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ያለ ክፍያ ቪዛ እንዳይሰጣቸው አግዷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግሥት ያቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ ትናንት ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በአስቸጋሪ ኹኔታ ላይ የነበሩ 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን መልሷል።

ትናንት ከተመለሱት ፍልሰተኞች መካከል፣ 1 ሺህ 98ቱ ወንዶች፣ 79ኙ ሴቶች እንዲኹም ሦስቱ ጨቅላ ሕጻናት እንደኾኑ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።

228ቱ ተመላሾች ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች ዕድሜ ያላቸው ናቸው ተብሏል።

ኮሚቴው ከሚያዝያ 4 ጀምሮ እስከ ትናንት በጠቅላላው 13 ሺህ 900 ፍልሰተኞችን ከሳዑዲ ዓረቢያ መልሷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#ሰበር
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል።

የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል።

በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም።

ምንጭ፦ የማህበረ ቅዱሳን የፌስቡክ ገፅ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ያሳዝናል‼️

ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል።

በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው።

ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ተጨማሪ‼️

ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድን ጨምሮ ሁለት የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ታሠሩ

በቅርቡ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ ለጥያቄ ይፈለጋሉ በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው ለሚዲያችን ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜና በኢትዮጵያ ኦርትዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ተፈታች‼️

አርቲስት አዲስአለም ጌታነህ ከ21 ቀናት እስር በኋላ ዛሬ ተፈታለች።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
They predicted yesterday the DUMP of Bitcoin
Already in the channel published the dates of the next BTC PUMP!

Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈
Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈
Click 👉 CHECK NEXT PUMP DATES 👈

JOIN FAST! Only the first 1000 people will be accepted! 🔥
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ማስተር ካርድ ለአምስት ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያ ቤት በተደረገው በዚሁ ስምምነት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን የካርድ ባንክ አገልግሎት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት እንደሚያግዘው ተነግሯል።

በተጨማሪም አዳዲስ የካርድ አገልግሎቶችን ለማስጀመር እንደሚረዳም ተጠቁሟል።በዚህ የአምስት አመት ሰምምነት መሰረት የባንኩን ደንበኞች ፍላጎት በማሟላት ላይ የሚያተኩሩ እና አለም የደረሰበትን አዳዲስ አገልግሎቶችን በሀገር ውሰጥ በማስተዋወቅ ጥሬ ገንዘብ አልባ ማህበረሰብን ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንደሚያደርግ ይገመታል።

ማስተር ካርድ ከ210 ሀገሮች በላይ የሚሰራ አለማቀፍ የክፍያ አቀላጠፊ ድርጅት ሲሆን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር መስራት ከጀመረ እረጅም አመታት እንደሆነ ይታወቃል።
በአቃቂ የገበያ ማዕከል ትናንት ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች ወደሙ

ሚያዚያ 24 ቀን2016  ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 የንግድ ሱቆች ሙሉ በሙሉና በከፊል መውደማቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፎቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷል።

በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ነው።

በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ መቆየቱንም አቶ ንጋቱ ጨምረው ነግረውናል።ኮሚሽኑ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ
ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ከዚህ ቀደም ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ እርምጃዎች አልተወሰዱም።

በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ኮሚሽኑ አሳስቧል።

ዳጉ_ጆርናል
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"አንዱ ሰለ ሁሉ ሞተ።" (2ኛ ቆሮ ም. 5:14)

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳቹ። አደረሰን።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ ይሁንልን።
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ሁለት ጭንቅላት ያለው ህጻን ተወለደ።

በኦሮሚያ ምሥራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ ትላንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አንዲት እናት በተደረገላት የቀዶ ህክምና ከአንገት በላይ ሁለት ጭንቅላት (Dicephalic parapagus) ያለው ወንድ ልጅ፤ ክብደቱ 4.2 ኪ.ግ የሚመዝን በሰላም ተገላግላለች።

ልጁ የተወለደው በሲሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ ሲሆን በሆስፒታሉ የህጻናት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ቶኩማ ባይሳ የልጁን ቀጣይ ህይወት ለመወሰን ወደ ከፍተኛ ሆስፒታል ሪፈር እንዲደረግ መወሰኑን ገልጸዋል።

ዶ/ር ቶኩማ አክለውም፥ እናትየው የመጀመሪያ ልጇ እንደሆነ ጠቅሰው አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንዳለች ገልጸዋል።

ዘገባው የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
ጌታቸው ረዳ‼️

“ በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት “ - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር።

በዚህም ፤ “ የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም “ ብለዋል።

“ የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን “ ያሉት አቶ ጌታቸው “ ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው “ ሲሉ አክለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ “ ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል “ ሲሉም ገልጸዋል።

“ ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል “ ሲሉም አስገንዝበዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ “ በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን “ ብለዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ የባንኩን ስም እየጠሩ የሚሰሩ የሀይማኖት ሰባኪዎችን ተጠያቂ ለማድረግ የሚሞክርበት የህግ አግባብ ካለ እንደሚያጣራ አስታወቀ

👉🏼 የባንኩ ፕሬዚዳንት " በጸሎት ገንዘብ እንዲበረክት እንጂ የሚጨመር ገንዘብ የለም" ብለዋል


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ የባንኩን ሂሳብ ደብተር ረግጠዉ ፣ አላስፈላጊ እና አዋራጅ ሊባል የሚችል ድርጊት የሚፈጽሙ የሀይማኖት ሰባኪዎችን ተጠያቂ ለማድረግ የሚሞክርበት አግባብ ካለ እንደሚያጣራ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ለመንግስታዊዉ አዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ ተናግረዋል‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ፤ በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ቪዲዮዎችን መመልከታቸዉን ተናግረዉ በ 21ኛዉ ክፍለዘመን እንደዚ የሚያስብ ሰዉ ስለመኖሩ መገረማቸውን ተናግረዋል። በቅድሚያ ሀሰተኛ ቪዲዮ እንደመሰላቸዉ የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ይህ ከሃይማኖታዊ ተግባር ያፈነገጠ እና የማይወክል መሆኑን አመላክተዋል።

"ሰርተህ ለፍተህ ያገኘኸዉ ገንዘብ እንዲበረክት መጸለይ እንጂ በጸሎት ሂሳብ ላይ የሚጨመር ገንዘብ እንደሌለ ህዝቡ መገንዘብ አለበት" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። ጉዳዩ ህግ ካለዉ እና ሊፈታ ከቻለ ባንኩ ጉዳዩን እንደሚመለከተዉ በቃለምልልሳቸው ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ህዝቡ አይሳሳት ሲሉም አሳስበዋል።
የDV አሸናዎች ዛሬ ይታወቃሉ‼️

ከአጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ

የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2025 አሸናፊዎች ዛሬ ቅዳሜ  ይፋ ይደረጋሉ።

ለዲቪ (Diversity Visa) 2025 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov/ESC/ ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።

ማስታወሻ:— የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል።

ውጤቱ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዛሬ ቅዳሜ ሚያዚያ 26/2016 ከምሽት 1:00 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ይሆናል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

አንድ አመልካች ዲቪ 2025 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ  ይሄ dvprogram.state.gov/ESC/ ድረገጽ መሆኑን አስገንዝቧል።

አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።
 
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ተፈታ‼️

ልጅ ያሬድ ተፈቷል💇‍♂

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ክብር የሚነካ ቃላት ተናገሮ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረው ልጅ ያሬድ በዛሬው ዕለት ተፈቷል።

@sheger_press
@sheger_press
ለመላው የኢትዮ መረጃ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ   እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ  ይሆን ዘንድ እየተመኘን

በዓሉን ስናከብር ዓቅመ ደካሞችን በመርዳት ይሆን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን።

መልካም በዓል

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/05/05 06:32:37
Back to Top
HTML Embed Code: