ሳላገኝሽ በፊት
።።።።።።።።።።።
ያኔ ...
እንድህ ነው ‘ማይባል ፣
ብዙ ነው ክፍተቴ ሞልቸው የሚጎል ፣
ባይመሽም ግብግብ በተነደለው ቀን አንዳቹ ሲታጎል ።
.
ግን አንቺ ስትመጪ ...
.
አለ አይደል ....
" ብቻነት ገምድሎ ፣
ሰው ለሰው ታድሎ ፣
አብሮነት ድልዳሉ እህል ውሃ ሲያዝል ፣
ጭርታ ጂል ክንዱ ጉልበት ከድቶት ሲዝል ፣ "
.
እንደዛ አይነት ነገር ።
.
አይነት ግን ምንድን ነው ?
.
ወይም አለ አይደለ ....
.
በዛሬው መራመድ ፣
ወደ ነገ መድረስ ተስፋ መቀጠሉ ፣
ባብሮ ፍቅር ቀንዲል ብርሀን ማንጠልጠሉ ፣
ትናንትን አራግፈው ፣
ከፉ ወቅትን ገፈው ፣
ህልም አለሙን ገርተው ነገን ሁነው መንጋት ፣
በመውደድ ማለዳ በተመስገን ልሳን በፍቅር ጧት ማውጋት፣
.
አይነት ።!
.
[ ብቻ አንቺ ስትመጪ ...
.
ህላዌ ደጃፍ ላይ ፣
ጤዛ ጋር እረግፎ ...
ያልነበር የሆነው ... የነበረው ሁሉ ፣
አንቺ ስትሄጂ ካገረሸው መሀል የርምጃዬ አመሉ፣
መንሻፈፍ ጀምሯል የግራዬ ጫማ ወደ ግራ ሶሉ ።
_
ብቻ ምን ልልሽ ነው ...
.
እንኳንስ እድሌን ደግ እጣየን መግለጥ ፣
የክፋቴን ወና ባብሮነትሽ ነድድ ሊፈስ ባንቺ መቅለጥ፣
ገላ ነፍሴን ቀርቶ ፣
አላውቅም ነበረ ያበጃጀን ጊዜ የሰራኝ ዘመንሽ ፣
በባዕዱ ጫማ ለርምጃዬ ሙላት ውሃ ልኩ እንደሆንሽ።
_
ወትሮም ...
ትናንት የጎደለው ፣
በነበር ሊተረክ በዛሬ ይሞላል ፣
( ዛሬም ትናንት ነው ! )
ዛሬ ደጉን ላይደግም ሱሉሱን አዛውሮ ነገ ላይ ይጎላል።
.
ቆይ ግን ውዴ ...
.
ትናንት ምን ይመስላል ?
.
ዛሬ ምን ያክላል ?
.
ነገስ ምን ይሆናል ?
.
.
እንጃ ።!
____
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ )

@ethiopiagna
ሀ ሁ ሂ ··· መርጌታ

ከፊደል ቤቱ ላይ አይኖቼን ተክዬ
የሀገሬን ባህል ታሪኳን ወክዬ

ከኣላዋቂዎች ፊት ማወቅን ከሚሹ ካሉበት ተስዬ
በቀጭኗ ዱላ ፊደል እየገረፍኩ ሀ ሲሉ ሀ ብዬ
ያልኩትን ሲደግሙ አሉ ከጉያዬ

ግና ይሄ አይምሮ ምንም የማያውቀው
ሀ'ን ሀ ስለው ብቻ ሀ ብሎ ላወቀው

ሀ ፐ ናት ብል ያኔ ፊደል ሳስቆጥረው
ፊደል ገበታውን በ ፐ እየጀመረ በ ሀ ነው የሚጥለው

በታዳጊ አይምሮ ሀ'ን ፐ የሚያደርገው
የሞተው እያለ ያልሞተው የሚያርገው

ድሮ ድሮ ያኔ በሀሰት መርጌታ ፊደል የቆጠረው
በ ሀ በ ፐ ፋንታ ጠጠር ያነጠረው
ዛሬ በቄስ ቤቱ
ከህፃናት ጋራ እውቀትን ሊለግስ
ሲሳሳት ይኖራል
በ ፐ' ታላቅ ክብር ሀ' ቤትን ሲያወድስ።

የዘመኑን አንዳንድ አስተማሪዎች ይመለከታል

የጊዜ ልጅ
@ethiopiagna
ስኬታማና ስኬት አልባ ሰዎች

>>ስኬት አልባ ሰዎች የችግሩ አካል ሲሆኑ ስኬታማዎቹ ደግሞ የመፍትሄው አካል ናቸው።

>>ስኬታማዎቹ እቅድ ሲኖራቸው ስኬት አልባዎቹ ደግሞ ምክንያት አላቸው፤

>>ስኬታማዎቹ ይህንን ላድርግ ሲሉ ስኬት አልባዎቹ ደግሞ ይህ የእኔ ስራ አይደለም ይላሉ፤

>>ስኬታማዎቹ ለእያንዳንዱ ችግር መፍትሄ ሲፈልጉ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ለእያንድአንዱ መፍትሄ ችግሩን ይፈልጋሉ፤

>>ስኬታማዎቹ አስቸጋሪ ቢሆንም እንኳን ማድረግ እንደሚቻል ሲገልጹ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ቢቻልም አስቸጋሪ መሆኑን ይገልጻሉ፤

>>ስኬታማዎቹ ስህተት ሰርተው ለስህተታቸው ሙሉ ሀላፊነት ሲወስዱ ሌሎቹ ደግሞ ጥፋቱ የእኔ አይደለም በማለት በህተታተቸው ላይ ሌላ ስህተት ይደርባሉ።

>>ስኬታማዎቹ መስዋእት ሲከፍሉ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ቃል ብቻ ይገባሉ፤

>>ስኬታማዎቹ የሆነ ነገር ማድረግ ይገባኛል ሲሉ ተቃራኒዎቹ ደግሞ የሆነ ነገር ሊደረግ ይገባል ይላሉ፡፡

>>ስኬታማዎቹ የቅንጅቱ አካል ሲሆኑ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ከቅንጅቱ ይርቃሉ
>>ስኬታማዎቹ አማራጮችን ሲፈልጉ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ችግሮችን ይፈልጋሉ፤

>>ስኬታማዎቹ ስኬታማ መሆን የሚቻለው በጥረት መሆኑን ሲያምኑ ተቃራኒዎቹ ደግሞ ስኬታማ የሚሆነው በሌሎች ማጣት ላይ ተመስርቶ መሆኑን ያምናሉ፤

>>ስኬታማዎቹ መጻኢውን ሲመለከቱ እነዚያዎቹ ደግሞ ያለፈውን ይናፍቃሉ፤

>>ስኬታማዎቹ ሙቀት ፈጣሪዎች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ የሙቀቱ መለኪያዎቹ ይሆናሉ፤

>>ስኬታማዎቹ የሚሉትን በጥንቃቄ አስቀድመው ሲመርጡ ተቃራኒዎቹ ደግሞ የሚሉት የመጣላቸውን ነው፤

>>ስኬታማዎቹ ጠንካራ ክርክር ቀለል ባለ አገላለጽ ሲጠቀሙ ስኬት አልባዎቹ ደግሞ ቀላል ክርክር ነገር ግን በከባድ አገላለጽ ይጠቀማሉ፡

>>ስኬታማዎቹ በጥቅም ላይ ጠንካራ ሆነው ነገር ግን በሌሎች ቀላል ነገሮች ለመስማማት ዝግጁ ሲሆኑ እነዚያዎቹ ደግሞ በተራ ነገሮች ላይ ጠንካሮች ሆነው በጥቅም ላይ ግን ለመደራደር ዝግጅዎች ናቸው።

>>ስኬታማዎቹ ሌሎች በአንተ ላይ ሊያደርጉብህን የማትፈልገውን ነገር በሌሎች ላይ አታድርግ የሚለውን ፍልስፍና ሲከተሉ ደካማዎቹ ደግሞ የሚያምኑት ሌሎች በአንተ ላይ ከማድረጋቸው በፊት ቀድመህ አድርግባቸው የሚለውን ይከተላሉ።

>>ከየትኛው ወገን ናችሁ???

ሠናይ ቀን!

🇪🇹 @Ethiopiagna 🇪🇹
ቅደም ተከተልን የማወቅ ጥበብ

“የሚያጣድፍ ነገር ሁሉ አስፈላጊ ነገር አይደለም” - Stephen Covey

አንድ ቀን አንድ የማኔጅመንት ሳይንስ ሊቅ ለተማሪዎቹ ንግግር በማድረግ ላይ ነበር፡፡ ይህ ሰው ለእነዚህ በጣም ለተነሳሱና ብሩህ አእምሮ ላላቸው ተማሪዎች በመናገር ላይ እያለ አንድን ነገር አደረገ፡፡ አንድ ባሊ አመጣና ጠረጴዛው ላይ ካስቀመጠ በኋላ ድንጋዮችን በማምጣት ባሊውን አፉ ድረስ ጢም አድርጎ በድንጋይ ሞላው፡፡ ይህንን ካደረገ በኋላ፣ “ይህ ባሊ ሙሉ ነው የሚል እጁን ያውጣ” አለ፡፡

በክፍሉ ያሉ ተማሪዎች በሙሉ እጃቸውን አወጡ፡፡ “እርግጠኛ ናችሁ?” አላቸው፡፡ “አዎን” በማለት እርግጠኝነታቸውን አረጋገጡለት፡፡ ከዚያም ከጠረጴዛው ስር አስቀምጦት ወደነበረው ሌላ ባሊ አጁን ዘርግቶ አነሳውና በውስጡ ያለውን ጠጠር ወደዚያ ድንጋይ ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰው፡፡ ጠጠሮቹ ሹልክልክ እያሉ ባገኙት ቀዳዳ ሁሉ ገቡ፡፡

“አሁንስ ባሊው ሙሉ ነው የምትሉ ስንት ናችሁ?” አለ መልሶ፡፡ አሁን አሰልጣኙ ምን ሊል እንደፈለገ በመጠኑ እየገባቸው ስለመጣ በማንገራገር የተደባለቀ ምላሽ ሰጡት፡፡ አንዳንዶቹ፣ “አሁን ሙሉ ነው” ሲሉ፤ ሌሎቹ ደግሞ፣ “አሁንም አልሞላም” አሉ፡፡ አሁንም በመቀጠል እጁን ወደ ጠረጴዛው ስር ሰደድ በማድረግ ሌላ ባሊ አነሳ፡፡
ይህኛው ባሊ በአሸዋ የተሞላ ነው፡፡ ወዲያውኑ አሸዋውን ወደዚያ ድንጋይና ጠጠር ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰው፡፡ አሸዋዎቹ ሹልክልክ እያሉ ባገኙት ቀዳዳ ሁሉ ገቡ፡፡ ለሶስተኛ ጊዜ፣ “አሁንስ ባሊው ሙሉ ነው የምትሉ ስንት ናችሁ?” አሁን ተማሪዎቹ በሙሉ በአንድ ቃል፣ “ባሊው አሁንም አልሞላም” ብለው መለሱለት፣ አካሄዱ ገብቷቸው፡፡ አሰልጣኙ እንደገና ሌላ ውኃ የሞላበት ባሊ ከጠረጴዛው ስር በማንሳት ድንጋይ፣ ጠጠርና አሸዋ ሞልቶበት ወደነበረው ባሊ አፈሰሰውና በባሊው ውስጥ ሌላ ምንም ነገር መጨመር እስከማይቻል ድረስ ሞላው፡፡

የመጨረሻው ትምህርታዊ ጥያቄ እንዲህ የሚል ነበር፡፡ “ከዚህ ምሳሌ የምናገኘው ዋና ቁምነገር ምንድን ነው?” አላቸው፡፡ አንዱ ሰልጣኝ አጁን አውጥቶ፣ “ምንም እንኳ ጊዜህ በብዙ ነገር ቢጨናነቅ፣ አሁንም ሌላ ነገርን አጨናንቀህ ማድረግ እንደምትች ነው” አለው፡፡

አሰልጣኙም፣ “ተሳስተሃል! የዚህ ምሳሌ ዋነኛ ትምህርት በመጀመሪያ ትልልቆቹን ድንጋዮች ባሊው ውስጥ ባትጨምር ኖሮ ትንንሾቹን ጠጠሮች፣ አሸዋውንና ውሃውን መጨመር አትችልም ነበር፡፡ ትልልቆቹ ድንጋዮች የሚወክሉት በሕይወትህ ያሉትን ዋና ዋና የሕይወት አላማዎችና ግቦች ነው፡፡

ቤተሰብህ፣ ጤንነትህ፣ የትምህርትህ አቅጣጫ፣ ዋነኛ ሕልሞችህና የመሳሰሉት … ዋና ዋና ከሚባሉት “ድንጋዮች” መካከል ይገኛሉ፡፡ በመጀመሪያ በእነዚህ ነገር ካልተደላደልክና የሕይወትህን አቅጣጫ ካልሞላኸው፣ በጥቃቅን ነገሮች ተጨናንቀህ ሕይወትህን ታባክናለህ፡፡

አንዳንድ ሰዎች ጊዜን በአግባቡ የመጠቀምን ጥበብ ማዳበር በራሱ እጅግ አድካሚ ስራ ነው ብለው ያስባሉ፡፡ ነገር ግን ሁኔታው የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ ዛሬ የሕይወቴን ዋና ዓላማ በመለየትና ቅድሚያን ለእርሱ በመስጠት መልክ የያዘ ሕይወት ለመኖር ማቀድ ካልቻልኩ ነገ በዚህና በዚያ የባከነውን ጊዜዬን መለስ ብዬ ከማየትና ከመቆጨት ውጪ ምንም ነገር ለማድረግ ያስቸግረኛል፡፡

ሠናይ ቀን!

🇪🇹 @Ethiopiagna 🇪🇹
በጊዜያዊ ስሜቶች (“ሙዶችህ”) አትታለል

ሰው በተፈጥሮው መልካም ገጠመኝ ሲደርስለትና በጣም በጋለና ግሩም በሆነ ስሜት (“ሙድ”) ውስጥ ሲሆን ከዚያ ቀን ጀምሮ ልብህን የሚያሳዝን ምንም ነገር እንማይገጥመው የማሰብ ዝንባሌ አለው፡፡ በተቃራኒውም በአንዳንድ ክፉ ገጠመኞች ምክንያት በጣም በወደቀ “ሙድ” ስሜት ውስጥ ራሳችንን ስናገኘው ከዚያ ሁኔታ የመውጫ ጭላንጭሉ አይታየንም፡፡ ይህ ከጊዜው “ሙድ” የተነሳ የሚመጣ “የቋሚነት” ስሜት በውሳኔአችን ላይ ጣልቃ ይገባና የኋላ ኋላ የምንጸጸትባቸውን ውሳኔዎች እንድንወስን ይገፋፉናል፡፡

ለምሳሌ፣ ይከፈለትልኛል ብለህ የጠበከው የእድል በር ባልጠበከው መንገድ ቢዘጋና የወደቀ “ሙድ” ውስጥ ብትሆን፣ ኑሮ ሊያስጠላህና የተለያዩ ውሳኔዎችን እንድትወስን ሊገፋፋህ ይችላል፡፡ “ሙዱን” ግን ማሳለፍ የግድ ነው፡፡ አየህ፣ በክፉም ሆነ በጥሩ የጠለቀ ስሜት ውስጥ ስትሆን አእምሮህ ለሕይወትህ የሚጠቅምህንና የማይጠቅምህን ነገር የማመዛዘኑ ሁኔታ ይወርዳል፡፡ እነዚህ የ“ሙድ” ውጣውረዶች ግን እየመጡ የሚሄዱ እንደሆኑና፣ እውነታ ብቻ ዘላቂ እንደሆነ በማሰብ አይኖችህን እውነታው ላይ ጣል - የማያልፍ ነገር የለምና።

ሠናይ ቀን!

🇪🇹 @Ethiopiagna 🇪🇹
እኛም ባለጠጎች ነን!

በአለም ላይ ብዙ ሰዎች ባለጠጋ ሆነው ሳለ ራሳቸውን ድኃ እንደሆኑ በማሳመን ከእምቅ ብቃታቸው በታች ኖረው ያልፋሉ፡፡ ይህ የሚሆንበት ምክንያት ባለጠጋ የሚለውን ቃልና ሃሳብ በሚገባ ስለማይገነዘቡት ነው፡፡ አንዳንዱ የሕብረተሰብ ክፍል “ብልጽግና” ለሚለው ቃል የሰጠንን ትርጉም ተቀብለው ያንን ሲጠባበቁ በእጃቸውና በውስጣቸው ያላቸውን ሃብት ሳይጠቀሙ ያልፋሉ፡፡

ብልጽግና ሁለንተናዊ ነው፡፡ ብልጽግና ገንዘብን ብቻ ሳይሆን ማንነትና ራእይን ያካተተ ነው፡፡ አየህ፣ ሰው ብዙ ገንዘብ ኖሮት ስግብግብ ከሆነ ብልጽግናው ምኑ ላይ ነው? ሰው ባለስልጣን ሆኖ ጨካን ከሆነ ብልጽግናው የቱ ጋር ነው? ሰው አዋቂ ሆኖ ትእቢተኛ ከሆነ የበለጸገው በምንድነው? ሰው ባለሞያ ሆኖ በዝባዥና ሌባ ከሆነ በለጸገ የሚባለው እንዴት ነው? እነዚህ ሁሉ የድህነት እንጂ የብልጽግና ምልክቶች አይደሉም፡፡

ሃብትና ብልጽግና አንጻራዊ ነው፤ እንዲሁም ሁለንተናዊ ነው፡፡ ስለዚህም፣ የሕይወትህን ዓላማ ካወቀክና ይህ ዓላማህ ለህብረተሰቡ አንድን መፍትሄ የሚያመጣ ከሆነ አንተም ባለጠጋ ነህ! ለለየኸው ዓላማህ የሚመጥን ፈቃደኝነትና ትጋት ካለህና ያንን ለማዳበር በመንቀሳቀስ ላይ ከሆንክ አንተም ባለጸጋ ነህ!

ዓላማህን በመከታተል ጉዞህ ደስተኛ ከሆንክና በዙሪያህ ለሚገኙ ሰዎች የደስታና የመነሳሳት ምንጭ ከሆነክ አንተም ባለጠጋ ነህ!
ዶ/ር እዮብ ማሞ

ሰናይ ቀን!

🇪🇹 @Ethiopiagna 🇪🇹
"ቀንህን በጎ ሀሳቦችን በማሰብ ጀምር"

ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነቃ ምስጋና በማቅረብና ስለ ቀኑ መልካምነት ለራስህ በመንገር ፋንታ "ኤጭ ዛሬ ቀኑ እንዴት ይቀፋል?አሁን እንዴት ብዬ ነው ወደ ጉዳዬ የምሔደው?!" ብትል ወይ ከስራህ አልያም ከትምህርትህ ወይም በአጠቃላይ ከምትሔድበት ትቀራለህ ወይ ታረፍዳለህ።ከሔድክም በፍላጎት አትሔድም። በማርፈድህ ወይ አለቃህ ወይም መምህርህ ሊናደድብህና ሊቆጣህ ይችላል።

ለጉዳዩ የሚኖርህን ፍላጎት በጠዋት የምትይዘው መጥፎ ስሜት ይሰርቀዋል። ይህን ስሜት የሚወልደው ደግሞ የገዛ ሀሳብህ ነው። መሳሳብ ማለትም ይኸው ነው። ሀሳብህ አቻ ስሜታዊ ይዞታን ሲያስከትልብህ ስሜትህ ደግሞ በተራው እውነታህን ይፈጥራል።

በእርግጥ ስሜታዊ ይዞታህ ሙሉ በሙሉ በጥዋቱ ሀሳብህ ላይ የሚመረኮዝ አይደለም። በተወሰነ መልኩም ቢሆን ማታ ወደ መኝታህ ስታመራ ይዘህ የነበረው ሀሳብ ላይም ጥገኛ ሊሆን ይችላል። የማታው ሀሳብህ የቀኑ ውሎህን ሲመስል፤ የቀኑ ውሎህ ደግሞ በበፊተኛው ጠዋት ደጋግመህ ያሰብከው ሀሳብህ ማለት ነው።

መልካም ቀን!

🇪🇹 @Ethiopiagna 🇪🇹
የሰው ልጅ ትክክለኛ ባህሪ ሲገለጥ!!

. አሪፍ ፀባይ አለዉ የምትለዉ ሰዉ ለብቻዉ ሲሆን ትክክለኛ ነገር ይሰራል?

• የካፌ አስተናጋጅ፣ ፅዳት የሚሰሩ ሰዎችን፣ ነዳጅ የሚቀዱ ሰዎችን እንዴት ነዉ የሚያነጋግራቸዉ?

• ሰዉ ገንዘቡንና ሰአቱን የሚጠቀምበት መንገድ የሰዉየዉን ስብእና በትክክል ይናገራል፡፡

አባቴ ሳምንቱን ሙሉ በስራ ተወጥሮ ነዉ የሚያሳልፈዉ፡፡ እቤት ሲመጣ እንኳን አመሻሽቶ፣ ከስራ ደክሞት ነበር፡፡

ማታ የቀረዉን ትንሽ ሰአት ለኛ 'እንደአባት' ለእናታችን ደግሞ 'እንደባል' የሚገባዉን ሁሉ ይረዳን፣ ያግዘን ነበር፡፡

በሱ እድሜ ያሉ ብዙ ሰዎች ልክ እቤት ሲገቡ ቲቪ ላይ ተጥደዉ እንደሚያመሹት ሳይሆን እኛን የቤት ስራ በማገዝ፣ እናቴን ደግሞ ከጎኗ ሆኖ ጅርባዋን ሲያሽ፣ እግሬን ቆረጠመኝ ስትለዉ እግሯን ቁጭ ብሎ በቫዝሊን ሲያስታምም ነበር ልጅነቴን የማስታዉሰዉ፡፡

እንደአባቴ አይነት 'የገባበትን ሃላፊነት በትክክል አዉቆ' ቤተሰቡን ብር ከመወርወር ባለፈ ተንከባክቦና ደግፎ አሳድጎናል፡፡

ለዚህ ነዉ መልካም የሆኑትን እንቁላሎች ከተበላሹት ለመለየት ዉሃ ዉስጥ የሚከተተዉ፡፡

የችግርና የመከራ ወቅት ሲጀመር የምትወደዉ ሰዉ ማንነት በትክክል እየጠራ፣ እየታየና እየተገለጠ ይመጣል፡፡

🇪🇹 ሰናይ ቀን! 🇪🇹

@Ethiopiagna
ሚስጥራዊ መልስ
.......................
ምን ነበር ካንገትሽ
ከደረትሽ ስቦ ውስጥሽ የሚከተኝ
ምንድን ነው ጠረንሽ
ሳልጠጋሽ ገና የሚያንከተክተኝ
ምን ናቸው እጣቶችሽ
በዳሰሳ ብቻ አለም የሚያስረሱ
ምን ናቸው እግሮችሽ
ገና ከሩቅ ሲያዩኝ ኖር ብለው እሚነሱ
ከናፍርሽሳ ምንድን ነው ጣዕሙ
ምንድን ነው ስሬቱ
አይን ሁሉ ነገርሽ ምን ይሆን ውበቱ
ምንድን ነው ሚስጥርሽ ፍቺሽ ከየት አለ
መልስ አገኝሽ ዘንዳ ባገባሽ ምንአለ...
#anita
Forwarded from መርጌታ መንግስቱ የባህል ህክምናና መዳሀኒት ቀማሚ (...እናት ጊዜ...)
የተበላሹ ንቅሳቶችን እንዲ ለማሳምር 0923880303 ይደውሉ
ዛሬ ነገ ነው?
"አባዬ ዛሬ ነገ ነው?" አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ። አባት እየተበሳጨ "ምንድን ነው የምትለኝ?" አለ። ልጅም "ዛሬ ነገ ነው ወይ?" አባት እንቅልፉ ስላለቀቀው "ሂድና እናትህን ጠየቃት በቃ ልተኛበት" አለና እየተበሳጨ ፊቱን ቨፈነ።

ልጅ ወደ እናቱ ሄዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት " እማዬ ዛሬ ነገ ነው?" እናት ፈገግ አለች "ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?" አለች የልጇን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች "ትናንት አስተማሪያችን 'ነገ ትምህርት የለም' ብላን ነበር፣ ዛሬ ነገ ነው?" አላት። እናት "እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው" አለች እየሳቀች።

ይህ ለሕፃኑ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም። ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው። ለነገ እንማራለን፣ ለነገ እንሰራለን፣ ለነገ እንገነባለን። የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ። ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን። ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን። እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን። መጽሐፍ" ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ ተመልከቱ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና" "ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ!" ይላል። ያዕ 4:15 / ማቴ 6:34

ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሳሪያም አንዱ "ነገ" በሚል ቃል ማዘናጋት ነው። ነገ እማራለሁ፣ ነገ እሔዳለሁ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ፣ ነገ ንስሐ እገባለሁ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሰራለሁ ነገ ነገ ነገ። ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉስ በመቅሰፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር። በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ:- ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው። ፈርኦንም :- ነገ አለ።

እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው። ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን አይነት ክፉ አመል አለብህ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ፣ አልተስተካከል ያለህ ድክመት፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? "አቤቱ አሁን አድን" ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ።

ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ፣ ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ፣ ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም። ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግስቱም መልሳችን ነገ ነው። "ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው" እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሰራ የማንፈልገውን እየሰራን እንኖራለን። ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም "የተወደደ ሰዓት አሁን ነው" መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትስጥ። ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው። ማንም ሊሰራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት።

አሁኑኑ ተነስ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመስራት፣ ክፉውን ነገር ለመተው ነገ አደርገዋለሁ አትበል ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅ "ነገ አደርገዋለሁ" ብለህ ነበር፣ ዛሬም "ነገ" አትበል ምክንያቱም ሕፃኑ እንዳለው "ዛሬ ነገ ነው!"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 8 ቀን 2012 ዓ.ም
ቪክቶሪያ አውስትራሊ
https://vm.tiktok.com/ZMdbFstN5/


ስለ ሀገራችን በወጣቶች ብቻ የተሰራ የ2ደቂቃ ቪድዮ ነው::

ስለ ስደተኛ ወገኖቼ ይመለከተኛል እምንል ከሆነ ከላይ ያለውን ሊንክ በመጫን ቪድዮውን ላይክ እና ኮሜንት እንስጠው::

ደት ይብቃን!
"ከብረው ይቆዩን ከብረው
በአመት ወንድ ልጅ ወልደው
ሰላሳ ጥጆች አስረው
ከብረው ይቆዩን ከብረው"
ከሚል ምርቃት ላይ ፣ ጥያቄ ነጎደ
መክበር አይችልም ወይ ፣ ሴትን የወለደ ?
"የመበልፀግ ዘመን" ...
የሚል ጥቅሷን ይዛ ፣ በተነሳች ሀገር
አይቻላትም ወይ
ከሰላሳ በላይ ፣ እልፍ ጥጃ ማሰር?
።፣፣፣፣።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣
ሁልጊዜ ወንድ ልጅ ፣ እየተከበረ
ሁል ጊዜ ሰላሳ ፣ ጥጃ ከታሰረ
ድግግሞሽ እንጂ ፣ ይህን ምን ይሉታል
አዲስ ዓመት መጣ፣ አዲስ ነገር የታል?

መልካም አዲስ ዓመት

የኔ ብዬ ስዬሽ
ሙሉ እድሜን ልኖር ካንቺ ጋር ስዳራ
ላይሰሙኝ ጆሮዎችሽ
ስምሽን ደጋግሜ በልቤ ስጣራ
መስማት አትችል ይሆን
እያልኩኝ ቀን ተሌት ስፋጠጥ ስፈራ

ንግግሬ ታክቶሽ ሰማው ስታወሪ
ያላንዳች ምስክር ያላንዳች አባሪ

አንቺ ስታወሪ
ስውር ነው ድምጸትሽ
ረቂቅ ነው ቃልሽ
አንቺ ስታወሪ
አይኖቼ ይሰማሉ
የልቤ ምቶቿ አንቺን አምጣ ይላሉ

ግና
ምን ዋጋ አለው ታድያ
አንቺን ለማናገር ብሞክር በመላ
ሆነሽ ከተገኘሽ
ሳናግርሽ የኔ ስታወሪ የሌላ..
ምን ዋጋ አለው
እናት?
ምን ትርፍ አለው ማየት ጣትሽ ተሽቆጥቁጦ
የማውቀው ቀለበት ከጣትሽ አምልጦ
ምንስ ትርጉም አለው
ልብሽ ላያስበኝ ስሜን ሺ ቢጣራ
አይንሽ ቢፈልገኝ ቀን ሌት በጠራራ
ምኑ ሊገባኝ ነው ቅኔ ሆኖ ተግባርሽ
ስትፈልጊ ብቻ ሁል ጊዜ እማገኝሽ
ባል ልሁን ወንድምሽ??
አኒታ
Forwarded from z z
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
ቢታኒያ ኮሌጅ ከዚህ በታች ለተዘረዘሩ ክፍት የስራ መደቦች መስፈርቱን የሚያሟሉ ብቁ ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
Forwarded from z z
2024/04/29 01:52:30
Back to Top
HTML Embed Code: