በክልል ደረጃ ሲካሄድ የቆየው 5ኛው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር ተጠናቀቀ
...
ውድድሩን በበላይነት ካጠናቀቁት 14 ትምህርት ቤቶች መካከል በጽሑፍ ክርክር የላቀ ነጥብ የሚያስመዘግቡ 8 ቡድኖች በግንቦት ወር በአዲስ አባባ ከተማ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ ውድድር ተሳታፊ ይሆናሉ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለ5ኛ ጊዜ የሚያካሂደው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር የመጀመሪያው ምዕራፍ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር ተጠናቋል። ውድድሩ በ12 ክልሎች እና በ2 ከተማ አስተዳደሮች የተካሄደ ሲሆን ከ77 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 154 ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። እንዲሁም መምህራን፣ የትምህርት ቤቶች ዳይሬክተሮች፣ የትምህርት ቢሮዎች ተጠሪዎች፣ ተማሪዎች እና የተማሪዎች ወላጆች በታዳሚነት ተገኝተዋል።
የዚህ ዓመት የምስለ ችሎት ውድድር ለልማት ሲባል በግዳጅ ከመፈናቀል ጋር የተያያዙ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች (Development-based Forced Eviction and Human Rights) ላይ የሚያተኩር ነው። ውድድሩም ተማሪዎች ምናባዊ በሆነ ጉዳይ (Hypothetical Case) ላይ በመመርኮዝ የአመልካች እና የተጠሪ ወገንን ወክለው የጽሑፍ እና የቃል ክርክር የሚያደርጉበት ነው። የመደበኛ ፍርድ ቤት የክርክር ሥርዓትን የሚከተለው ይህ ውድድር በተወዳዳሪ ተማሪዎች እና በትምህርት ቤቶች ማኅበረሰብ ዘንድ የሰብአዊ መብቶች ዕውቀትንና ክህሎትን ለመገንባት ያለመ ነው
🔗 https://ehrc.org/?p=32551
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ውድድሩን በበላይነት ካጠናቀቁት 14 ትምህርት ቤቶች መካከል በጽሑፍ ክርክር የላቀ ነጥብ የሚያስመዘግቡ 8 ቡድኖች በግንቦት ወር በአዲስ አባባ ከተማ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ ውድድር ተሳታፊ ይሆናሉ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለ5ኛ ጊዜ የሚያካሂደው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር የመጀመሪያው ምዕራፍ በክልል ደረጃ በተካሄደ ውድድር ተጠናቋል። ውድድሩ በ12 ክልሎች እና በ2 ከተማ አስተዳደሮች የተካሄደ ሲሆን ከ77 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 154 ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል። እንዲሁም መምህራን፣ የትምህርት ቤቶች ዳይሬክተሮች፣ የትምህርት ቢሮዎች ተጠሪዎች፣ ተማሪዎች እና የተማሪዎች ወላጆች በታዳሚነት ተገኝተዋል።
የዚህ ዓመት የምስለ ችሎት ውድድር ለልማት ሲባል በግዳጅ ከመፈናቀል ጋር የተያያዙ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች (Development-based Forced Eviction and Human Rights) ላይ የሚያተኩር ነው። ውድድሩም ተማሪዎች ምናባዊ በሆነ ጉዳይ (Hypothetical Case) ላይ በመመርኮዝ የአመልካች እና የተጠሪ ወገንን ወክለው የጽሑፍ እና የቃል ክርክር የሚያደርጉበት ነው። የመደበኛ ፍርድ ቤት የክርክር ሥርዓትን የሚከተለው ይህ ውድድር በተወዳዳሪ ተማሪዎች እና በትምህርት ቤቶች ማኅበረሰብ ዘንድ የሰብአዊ መብቶች ዕውቀትንና ክህሎትን ለመገንባት ያለመ ነው
🔗 https://ehrc.org/?p=32551
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
በኢንዱስትሪ ፓርኮችና ፋብሪካዎች ውስጥ በሚሠሩ ሴቶች መብቶች ላይ አተኩረው በተከናወኑ ክትትሎች ላይ የተካሄደ ውይይት
...
የሴት ሠራተኞች ሰብአዊ መብቶች በተሟላ ሁኔታ መከበራቸውን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ሸገር ሲቲ እና ሃዋሳ ከተሞች በሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሴቶችን መብቶች አያያዝ በተመለከተ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። ውይይቱ ኢሰመኮ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. በአዳማ እና ሃዋሳ ከተሞች በሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሥር ባሉ 5 ፋብሪካዎች ባከናወነው ሁለተኛ ዙር የምክረ ሐሳቦች አተገባበር ክትትል እንዲሁም በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥር እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በሚገኙ 8 ፋብሪካዎች ባደረገው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች ላይ ያተኮረ ነው።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የኦሮሚያ እና የሲዳማ ክልሎች ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች፣ የጤና እና የኢንቨስትመንት ቢሮዎች፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም የሲቪል ማኅበራት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32615
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የሴት ሠራተኞች ሰብአዊ መብቶች በተሟላ ሁኔታ መከበራቸውን ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ሸገር ሲቲ እና ሃዋሳ ከተሞች በሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችና ፋብሪካዎች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሴቶችን መብቶች አያያዝ በተመለከተ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። ውይይቱ ኢሰመኮ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. በአዳማ እና ሃዋሳ ከተሞች በሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሥር ባሉ 5 ፋብሪካዎች ባከናወነው ሁለተኛ ዙር የምክረ ሐሳቦች አተገባበር ክትትል እንዲሁም በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥር እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በሚገኙ 8 ፋብሪካዎች ባደረገው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች ላይ ያተኮረ ነው።
በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የኦሮሚያ እና የሲዳማ ክልሎች ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች፣ የጤና እና የኢንቨስትመንት ቢሮዎች፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም የሲቪል ማኅበራት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32615
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የፕሬስ ነጻነት እና ሐሳብን በነጻ የመግለጽ መብት
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 29
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው።
የፕሬስ እና የሌሎች መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም የሥነ ጥበብ ፈጠራ ነጻነት ተረጋግጧል።
የፕሬስ ነጻነት በተለይ የቅድሚያ ምርመራ በማንኛውም መልኩ የተከለከለ መሆኑን እና የሕዝብን ጥቅም የሚመለከት መረጃ የማግኘት ዕድልን ያካትታል።
የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2021፣ አንቀጽ 86(1)
በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቢ ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=32623
#Ethiopia🇪🇹 #WorldPressFreedomDay #WPFD2025 #PressFreedom #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 29
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው።
የፕሬስ እና የሌሎች መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም የሥነ ጥበብ ፈጠራ ነጻነት ተረጋግጧል።
የፕሬስ ነጻነት በተለይ የቅድሚያ ምርመራ በማንኛውም መልኩ የተከለከለ መሆኑን እና የሕዝብን ጥቅም የሚመለከት መረጃ የማግኘት ዕድልን ያካትታል።
የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2021፣ አንቀጽ 86(1)
በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል በወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቢ ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=32623
#Ethiopia🇪🇹 #WorldPressFreedomDay #WPFD2025 #PressFreedom #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ብሔራዊ ኮንፈረንስ
...
ጥራቱ የተጠበቀ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት ነው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት ላይ ሚያዝያ 15 እና 16 ቀን 2017 ዓ.ም. ብሔራዊ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። የብሔራዊ ኮንፈረንሱ ዓላማ በፍትሕ ሥርዓቱ በተለይ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሂደት የሚሰጥ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት በነባራዊ ጉዳዮች እና በሚስተዋሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትብብርና በቅንጅት ለመፍታት የጋራ መወያያ መድረክ መፍጠር ነው።
በኮንፈረንሱ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የተከላካይ ጠበቆች ጽሕፈት ቤት፣ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የፍትሕ ቢሮና ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት የሚሰጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሕግ ትምህርት ቤቶች ተወካዮች እና የሲቪል ማኅበራት እና የግል የጥብቅና ተቋማት ተሳትፈዋል። እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የመድኃኒትና የወንጀል ጽሕፈት ቤት፣ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም፣ የዳኒሽ ሰብአዊ መብቶች ተቋም (DIHR) የአዲስ አበባ እና የዛምቢያ ቢሮ ተወካዮች እና የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ተሳታፊ ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32638
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ጥራቱ የተጠበቀ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት ነው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት ላይ ሚያዝያ 15 እና 16 ቀን 2017 ዓ.ም. ብሔራዊ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። የብሔራዊ ኮንፈረንሱ ዓላማ በፍትሕ ሥርዓቱ በተለይ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሂደት የሚሰጥ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት በነባራዊ ጉዳዮች እና በሚስተዋሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትብብርና በቅንጅት ለመፍታት የጋራ መወያያ መድረክ መፍጠር ነው።
በኮንፈረንሱ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የተከላካይ ጠበቆች ጽሕፈት ቤት፣ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የፍትሕ ቢሮና ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት የሚሰጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሕግ ትምህርት ቤቶች ተወካዮች እና የሲቪል ማኅበራት እና የግል የጥብቅና ተቋማት ተሳትፈዋል። እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የመድኃኒትና የወንጀል ጽሕፈት ቤት፣ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም፣ የዳኒሽ ሰብአዊ መብቶች ተቋም (DIHR) የአዲስ አበባ እና የዛምቢያ ቢሮ ተወካዮች እና የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ተሳታፊ ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32638
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የሕይወት፣ የአካል ደኅንነትና የነጻነት መብት
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 14
ማንኛውም ሰው ሰብአዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የነጻነት መብት አለው።
የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን፣ አንቀጽ 6(1) እና 7
ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር ተፈጥሯዊ መብት አለው፡፡ ይህ መብት በሕግ ሊከበር ይገባል፡፡ ማንኛውም ሰው ያለአግባብ ሕይወቱን አያጣም፡፡
ማንኛውም ሰው ለስቃይ ወይም ጭካኔ ለተሞላበት፣ ኢ-ሰብአዊ ወይም ክብርን ለሚያዋርድ አያያዝና ቅጣት ሊዳረግ አይገባም፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=32695
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 14
ማንኛውም ሰው ሰብአዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነትና የነጻነት መብት አለው።
የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን፣ አንቀጽ 6(1) እና 7
ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር ተፈጥሯዊ መብት አለው፡፡ ይህ መብት በሕግ ሊከበር ይገባል፡፡ ማንኛውም ሰው ያለአግባብ ሕይወቱን አያጣም፡፡
ማንኛውም ሰው ለስቃይ ወይም ጭካኔ ለተሞላበት፣ ኢ-ሰብአዊ ወይም ክብርን ለሚያዋርድ አያያዝና ቅጣት ሊዳረግ አይገባም፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=32695
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍4
Closing the Protection Gap: Advancing the Rights of Older Persons
...
EHRC and GANHRI Call for a Binding International Treaty at UN High-Level Meeting
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) joined global leaders and human rights advocates at the United Nations Headquarters in New York on May 8, 2025, for a High-Level Meeting convened by the President of the General Assembly on Ageing.
Held under the theme of exchanging views on the recommendations outlined in Decision 14/1 of the Open-ended Working Group on Ageing, the meeting brought together Member States, UN bodies and civil society to address the rights and well-being of older persons and define next steps toward stronger legal protections.
🔗 https://ehrc.org/?p=32721
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
EHRC and GANHRI Call for a Binding International Treaty at UN High-Level Meeting
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) joined global leaders and human rights advocates at the United Nations Headquarters in New York on May 8, 2025, for a High-Level Meeting convened by the President of the General Assembly on Ageing.
Held under the theme of exchanging views on the recommendations outlined in Decision 14/1 of the Open-ended Working Group on Ageing, the meeting brought together Member States, UN bodies and civil society to address the rights and well-being of older persons and define next steps toward stronger legal protections.
🔗 https://ehrc.org/?p=32721
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤4
Consultation: Strategy for the Participation of Victims and Vulnerable Sections of Society in the Transitional Justice Process in Ethiopia
...
The participation of victims and vulnerable sections of society must be transformative, empowering, and should drive the TJ process based on their lived experiences
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) and the Office of the High Commissioner for Human Rights—East Africa Regional Office (OHCHR-EARO) in view of their respective mandates to enhance human rights compliance, inclusion, and victim-centeredness in Ethiopia’s transitional justice (TJ) process organized a consultation on the draft Strategy for the Participation of Victims and Vulnerable Sections of Society in the Ethiopian Transitional Justice (TJ) process on April 29, 2025, in Addis Ababa.
🔗 https://ehrc.org/?p=32725
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
The participation of victims and vulnerable sections of society must be transformative, empowering, and should drive the TJ process based on their lived experiences
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) and the Office of the High Commissioner for Human Rights—East Africa Regional Office (OHCHR-EARO) in view of their respective mandates to enhance human rights compliance, inclusion, and victim-centeredness in Ethiopia’s transitional justice (TJ) process organized a consultation on the draft Strategy for the Participation of Victims and Vulnerable Sections of Society in the Ethiopian Transitional Justice (TJ) process on April 29, 2025, in Addis Ababa.
🔗 https://ehrc.org/?p=32725
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: ቤተሰብ የመመሥረት መብት
...
ሁሉ አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ፣ አንቀጽ 16 (1) እና (2)
ዕድሜያቸው ለጋብቻ የደረሰ ወንዶች እና ሴቶች በዘር፣ በዜግነት ወይም በሃይማኖት ልዩነት ሳይደረግባቸው ጋብቻ የመፈጸም እና ቤተሰብ የመመሥረት መብት አላቸው። ጋብቻው ሲፈጸም፣ በጋብቻ ወቅት እና ጋብቻው በሚፈርስበት ጊዜ እኩል መብቶች አሏቸው።
ጋብቻ በተጋቢዎች ነጻ እና ሙሉ ፈቃድ ላይ ብቻ ይመሠረታል።
የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት፣ አንቀጽ 34 (3)
ቤተሰብ የኅብረተሰብ ተፈጥሯዊ እና መሠረታዊ መነሻ ነው። ከኅብረተሰብና ከመንግሥት ጥበቃ የማግኘት መብት አለው።
🔗 https://ehrc.org/?p=32750
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ሁሉ አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ፣ አንቀጽ 16 (1) እና (2)
ዕድሜያቸው ለጋብቻ የደረሰ ወንዶች እና ሴቶች በዘር፣ በዜግነት ወይም በሃይማኖት ልዩነት ሳይደረግባቸው ጋብቻ የመፈጸም እና ቤተሰብ የመመሥረት መብት አላቸው። ጋብቻው ሲፈጸም፣ በጋብቻ ወቅት እና ጋብቻው በሚፈርስበት ጊዜ እኩል መብቶች አሏቸው።
ጋብቻ በተጋቢዎች ነጻ እና ሙሉ ፈቃድ ላይ ብቻ ይመሠረታል።
የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት፣ አንቀጽ 34 (3)
ቤተሰብ የኅብረተሰብ ተፈጥሯዊ እና መሠረታዊ መነሻ ነው። ከኅብረተሰብና ከመንግሥት ጥበቃ የማግኘት መብት አለው።
🔗 https://ehrc.org/?p=32750
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
ሰብአዊ መብቶችን ማስፋፋት፦ በ2017 ዓ.ም. በሦስተኛው ሩብ ዓመት የተሰጡ ስልጠናዎች
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 1 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ባለው ጊዜ በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ፣ በሕፃናት፣ በታራሚዎች፣ በአረጋውያን እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን በተለያዩ ከተሞች ሰጥቷል።
በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ የወጣቶችን ሚና ለማሳደግ ያለሙ ስልጠናዎች ከተለያዩ ወጣት ማኅበራት ለተውጣጡ 63 አመራሮች እና አባላት ከየካቲት 10 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. በአርባምንጭ ከተማ እና ከመጋቢት 15 እስከ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በሶዶ ከተማ ተሰጥቷል። በተመሳሳይ የማሕበረሰብ እና የሃይማኖት መሪዎችን ትኩረት ያደረጉ በድምሩ 64 ተሳታፊዎች የተሳተፉባቸው ስልጠናዎች ከየካቲት 4 እስከ 6 ቀን 2017 በጅማ እና ቢሾፍቱ ከተሞች ተከናውነዋል። በስልጠናዎቹ ስለ ሽግግር ፍትሕ ጽንሰ ሐሳብ፣ የሌሎች ሀገራት የሽግግር ፍትሕ ተሞክሮዎች እና በሂደቱ ታሳቢ ሊደረጉ የሚገቡ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች የቀረቡ ሲሆን ክህሎትን የሚያሳድጉ ተግባራዊ ልምምዶች ተካተዋል።
በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ ከአዲስ አበባ ከተማ እና ከኦሮሚያ ክልል ለተውጣጡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች በአዳማ ከተማ ከመጋቢት 1 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም. የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32785
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 1 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. ባለው ጊዜ በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ፣ በሕፃናት፣ በታራሚዎች፣ በአረጋውያን እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን በተለያዩ ከተሞች ሰጥቷል።
በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ የወጣቶችን ሚና ለማሳደግ ያለሙ ስልጠናዎች ከተለያዩ ወጣት ማኅበራት ለተውጣጡ 63 አመራሮች እና አባላት ከየካቲት 10 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. በአርባምንጭ ከተማ እና ከመጋቢት 15 እስከ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በሶዶ ከተማ ተሰጥቷል። በተመሳሳይ የማሕበረሰብ እና የሃይማኖት መሪዎችን ትኩረት ያደረጉ በድምሩ 64 ተሳታፊዎች የተሳተፉባቸው ስልጠናዎች ከየካቲት 4 እስከ 6 ቀን 2017 በጅማ እና ቢሾፍቱ ከተሞች ተከናውነዋል። በስልጠናዎቹ ስለ ሽግግር ፍትሕ ጽንሰ ሐሳብ፣ የሌሎች ሀገራት የሽግግር ፍትሕ ተሞክሮዎች እና በሂደቱ ታሳቢ ሊደረጉ የሚገቡ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች የቀረቡ ሲሆን ክህሎትን የሚያሳድጉ ተግባራዊ ልምምዶች ተካተዋል።
በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ ከአዲስ አበባ ከተማ እና ከኦሮሚያ ክልል ለተውጣጡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች በአዳማ ከተማ ከመጋቢት 1 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም. የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32785
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
83rd Ordinary Session of the African Commission on Human and Peoples’ Rights in Banjul, The Gambia
...
EHRC will closely follow the African Commission’s recommendations in response to Ethiopia’s report and monitor implementation
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) delegation, comprising of Chief Commissioner Berhanu Adello, Commissioner for Civil, Political and Socio-Economic Rights Dr. Abdi Jibril and other senior officials, participated in the 83rd Ordinary Session of the African Commission on Human and Peoples’ Rights (African Commission), in Banjul, The Gambia from May 2 to 12, 2025.
🔗 https://ehrc.org/?p=32844
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
EHRC will closely follow the African Commission’s recommendations in response to Ethiopia’s report and monitor implementation
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) delegation, comprising of Chief Commissioner Berhanu Adello, Commissioner for Civil, Political and Socio-Economic Rights Dr. Abdi Jibril and other senior officials, participated in the 83rd Ordinary Session of the African Commission on Human and Peoples’ Rights (African Commission), in Banjul, The Gambia from May 2 to 12, 2025.
🔗 https://ehrc.org/?p=32844
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
Advancing Peace, Justice and Inclusion Through Strengthened Partnerships and Collective Action
...
EHRC took part in the 2025 Sustainable Development Goal 16 (SDG 16) Conference held at UN Headquarters in New York
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) participated in the 2025 SDG 16 Conference held at UN Headquarters in New York under the theme “Advancing Peace, Justice and Institutions for Sustainable Development” on May 12, 2025. The conference convened global leaders and stakeholders from government, civil society, and multilateral organizations to assess progress and define next steps in delivering on Sustainable Development Goal 16 (SDG 16) as a foundation for broader achievement of the 2030 Agenda. The event was co-hosted by the UN Department of Economic and Social Affairs, the Permanent Mission of Italy, and the International Development Law Organization.
🔗 https://ehrc.org/?p=32848
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
EHRC took part in the 2025 Sustainable Development Goal 16 (SDG 16) Conference held at UN Headquarters in New York
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) participated in the 2025 SDG 16 Conference held at UN Headquarters in New York under the theme “Advancing Peace, Justice and Institutions for Sustainable Development” on May 12, 2025. The conference convened global leaders and stakeholders from government, civil society, and multilateral organizations to assess progress and define next steps in delivering on Sustainable Development Goal 16 (SDG 16) as a foundation for broader achievement of the 2030 Agenda. The event was co-hosted by the UN Department of Economic and Social Affairs, the Permanent Mission of Italy, and the International Development Law Organization.
🔗 https://ehrc.org/?p=32848
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1
የሴት ልጅ ግርዛትን አስመልክቶ በሚካሄድ ግልጽ የምርመራ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት
...
በሴቶች ላይ የሚፈጸም ግርዛት እና ተደጋጋሚ ግርዛትን ለማስቆም ማኀበረሰብን ማንቃት፣ ለተጎጂዎች ድጋፍ ማድረግ እና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በሴት ልጅ ግርዛት ላይ ስለሚያካሂደው ግልጽ የምርመራ መድረክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የውይይቱ ዓላማ የግልጽ ምርመራ መድረኩ ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን ማሳወቅ እና አስፈላጊ በሆኑ በትብብርና እገዛዎች ላይ መወያየት ነው።
በውይይቱ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ፍትሕ ሚኒስቴር፣ ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከአፋር እና ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ ፍትሕ ቢሮ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ጤና ቢሮ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ የሀዲያ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ፣ የፍትሕ፣ የፖሊስ እና ጤና ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም በሴት ልጅ ግርዛት ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና የኢሰመኮ የከተማ ጽሕፈት ቤቶች የሴቶች እና የሕፃናት መብቶች ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32857
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በሴቶች ላይ የሚፈጸም ግርዛት እና ተደጋጋሚ ግርዛትን ለማስቆም ማኀበረሰብን ማንቃት፣ ለተጎጂዎች ድጋፍ ማድረግ እና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ያስፈልጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በሴት ልጅ ግርዛት ላይ ስለሚያካሂደው ግልጽ የምርመራ መድረክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የውይይቱ ዓላማ የግልጽ ምርመራ መድረኩ ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን ማሳወቅ እና አስፈላጊ በሆኑ በትብብርና እገዛዎች ላይ መወያየት ነው።
በውይይቱ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ፍትሕ ሚኒስቴር፣ ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከአፋር እና ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮ፣ ፍትሕ ቢሮ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ጤና ቢሮ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ የሀዲያ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ፣ የፍትሕ፣ የፖሊስ እና ጤና ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም በሴት ልጅ ግርዛት ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና የኢሰመኮ የከተማ ጽሕፈት ቤቶች የሴቶች እና የሕፃናት መብቶች ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32857
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የሴቶች የጤና መብት
...
በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛውንም አድሎአዊ ልዩነት ለማስወገድ የተደረገ ስምምነት፣ አንቀጽ 12 (1)
አባል ሀገራት የወንዶች እና የሴቶች እኩልነትን መሠረት በማድረግ የቤተሰብ ምጣኔን ጨምሮ የጤና ጥበቃ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በጤና ጥበቃ ዘርፍ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን አድልዎ ለማስወገድ ተገቢውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳሉ።
የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል)፣ አንቀጽ 14 (2) (ሀ)
አባል ሀገራት ለሴቶች በተለይም በገጠር ለሚገኙ የመረጃ፣ የትምህርት እና የግንኙነት መርኃ ግብሮችን ጨምሮ በቂ፣ ተመጣጣኝ እና ተደራሽ የጤና አገልግሎቶችን ለመስጠት አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=33013
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛውንም አድሎአዊ ልዩነት ለማስወገድ የተደረገ ስምምነት፣ አንቀጽ 12 (1)
አባል ሀገራት የወንዶች እና የሴቶች እኩልነትን መሠረት በማድረግ የቤተሰብ ምጣኔን ጨምሮ የጤና ጥበቃ አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግ በጤና ጥበቃ ዘርፍ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን አድልዎ ለማስወገድ ተገቢውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳሉ።
የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል (ማፑቶ ፕሮቶኮል)፣ አንቀጽ 14 (2) (ሀ)
አባል ሀገራት ለሴቶች በተለይም በገጠር ለሚገኙ የመረጃ፣ የትምህርት እና የግንኙነት መርኃ ግብሮችን ጨምሮ በቂ፣ ተመጣጣኝ እና ተደራሽ የጤና አገልግሎቶችን ለመስጠት አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=33013
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
በሕክምና ተቋማት ውስጥ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን የሥራ ማቆም አድማ በተመለከተ
...
በሕክምና ተቋማት በመካሄድ ላይ ያሉ የሥራ ማቆም አድማዎች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በር እንዳይከፍቱ ትኩረት ሊሰጣቸው እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሕክምና ባለሙያዎች በሕክምና ተቋማት ውስጥ በማድረግ ላይ የሚገኙት የሥራ ማቆም አድማ እንዲሁም ይህንን ተከትሎ በመንግሥት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንዳያስከትሉ ትኩረት ሊሰጣቸው እና አፋጣኝ መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ ያሳስባል።
ኢሰመኮ አንዳንድ የሕክምና ባለሙያዎች የደመወዝ እና ከሥራ ሁኔታ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን መንግሥት እንዲመልስ ሰጥተናል ያሉት የ30 ቀናት የጊዜ ገደብ ግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም. መጠናቀቁን ተከትሎ በመንግሥት እና በሕክምና ባለሙያዎች በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃዎች በመከታተል ላይ ይገኛል። በዚህም መሠረት ኢሰመኮ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ከአጋሮ፣ ከአርባ ምንጭ፣ ከባሕር ዳር፣ ከፍቼ፣ ከጎባ፣ ከሃዋሳ እና ከጅማ ከተሞች መረጃ ማሰባሰብ ችሏል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33103
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በሕክምና ተቋማት በመካሄድ ላይ ያሉ የሥራ ማቆም አድማዎች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በር እንዳይከፍቱ ትኩረት ሊሰጣቸው እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሕክምና ባለሙያዎች በሕክምና ተቋማት ውስጥ በማድረግ ላይ የሚገኙት የሥራ ማቆም አድማ እንዲሁም ይህንን ተከትሎ በመንግሥት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንዳያስከትሉ ትኩረት ሊሰጣቸው እና አፋጣኝ መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ ያሳስባል።
ኢሰመኮ አንዳንድ የሕክምና ባለሙያዎች የደመወዝ እና ከሥራ ሁኔታ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን መንግሥት እንዲመልስ ሰጥተናል ያሉት የ30 ቀናት የጊዜ ገደብ ግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም. መጠናቀቁን ተከትሎ በመንግሥት እና በሕክምና ባለሙያዎች በመወሰድ ላይ የሚገኙትን እርምጃዎች በመከታተል ላይ ይገኛል። በዚህም መሠረት ኢሰመኮ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ከአጋሮ፣ ከአርባ ምንጭ፣ ከባሕር ዳር፣ ከፍቼ፣ ከጎባ፣ ከሃዋሳ እና ከጅማ ከተሞች መረጃ ማሰባሰብ ችሏል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33103
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት ስንል ምን ማለታችን ነው?
...
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት ማለት ከግጭት ወይም አደጋ የሚያመልጡ ሰዎች በሌላ ሀገር ከለላ የሚያገኙበት ሥነ ሥርዓት ነው። ሰዎች ለጥገኝነት ሲያመለክቱ በዘራቸው፣ በሃይማኖታቸው፣ በብሔራቸው፣ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ወይም በአንድ የተወሰነ ማኅበራዊ ቡድን ውስጥ አባል በመሆናቸው ምክንያት የሚፈጸም ጥቃት ስለሚያስፈራቸው ጥበቃ እንዲደረግላቸው ነው። ከለላ ለማግኘትም ወደ ሀገራቸው ቢመለሱ በእርግጥ ወይም በተጨባጭ ሊደርስባቸው የሚችል ማሳደድ፣ ማሠቃየት፣ መንገላታት ስለመኖሩ ማሳየት አለባቸው።
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት የሕግ መሠረቶች ምንድን ናቸው?
ዓለም አቀፍ እና ብሔራዊ የሕግ ማዕቀፎች ተጨባጭ ከሆነ ጥቃት/ጭቆና ጥበቃ ለማግኘት ጥገኝነት የመጠየቅ መብትን እና ሂደቶችን ይደነግጋሉ። ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ (Universal Declaration of Human Rights) አንቀጽ 14 ከጥቃት/ጭቆና ሸሽቶ በሌሎች ሀገሮች ጥገኝነት የመጠየቅ መብትን እውቅና ሰጥቷል። ማን እንደ ስደተኛ እንደሚቆጠር እና ሀገራት ለጥገኝነት ጠያቂዎች ከለላ ለመስጠት ያለባቸውን ግዴታዎች ከመዘርዘር አኳያ እ.ኤ.አ. በ1951 የወጣው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ስምምነት እና እ.ኤ.አ. በ1967 የስደተኞች ሁኔታን ለመደንገግ የወጣው ፕሮቶኮል ጥገኝነትን ለተመለከቱ ሕጎች መሠረት በመሆን ያገለግላሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=33120
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት ማለት ከግጭት ወይም አደጋ የሚያመልጡ ሰዎች በሌላ ሀገር ከለላ የሚያገኙበት ሥነ ሥርዓት ነው። ሰዎች ለጥገኝነት ሲያመለክቱ በዘራቸው፣ በሃይማኖታቸው፣ በብሔራቸው፣ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ወይም በአንድ የተወሰነ ማኅበራዊ ቡድን ውስጥ አባል በመሆናቸው ምክንያት የሚፈጸም ጥቃት ስለሚያስፈራቸው ጥበቃ እንዲደረግላቸው ነው። ከለላ ለማግኘትም ወደ ሀገራቸው ቢመለሱ በእርግጥ ወይም በተጨባጭ ሊደርስባቸው የሚችል ማሳደድ፣ ማሠቃየት፣ መንገላታት ስለመኖሩ ማሳየት አለባቸው።
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት የሕግ መሠረቶች ምንድን ናቸው?
ዓለም አቀፍ እና ብሔራዊ የሕግ ማዕቀፎች ተጨባጭ ከሆነ ጥቃት/ጭቆና ጥበቃ ለማግኘት ጥገኝነት የመጠየቅ መብትን እና ሂደቶችን ይደነግጋሉ። ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ (Universal Declaration of Human Rights) አንቀጽ 14 ከጥቃት/ጭቆና ሸሽቶ በሌሎች ሀገሮች ጥገኝነት የመጠየቅ መብትን እውቅና ሰጥቷል። ማን እንደ ስደተኛ እንደሚቆጠር እና ሀገራት ለጥገኝነት ጠያቂዎች ከለላ ለመስጠት ያለባቸውን ግዴታዎች ከመዘርዘር አኳያ እ.ኤ.አ. በ1951 የወጣው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ስምምነት እና እ.ኤ.አ. በ1967 የስደተኞች ሁኔታን ለመደንገግ የወጣው ፕሮቶኮል ጥገኝነትን ለተመለከቱ ሕጎች መሠረት በመሆን ያገለግላሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=33120
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍5
የትምህርት መብት፡- በአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ የተካሄደ ውይይት
...
የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የትምህርት መብት ለማረጋገጥ የትምህርት ግብአት አቅርቦት፣ ከባቢያዊ እና የመረጃ ተደራሽነት እንዲሁም የአመለካከት ክፍተቶች ላይ መሥራት ያስፈልጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በልዩ አዳሪ እና አካቶ ቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ባሕር ዳር፣ ቢሾፍቱ፣ ባኮ፣ ጋምቤላ፣ ሆሳዕና፣ መቐለ፣ ሰበታ እና ሻሸመኔ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ባከናወነው ክትትል የተለዩ ግኝቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሁለት የምክክር መድረኮች በአዲስ አበባ እና ሃዋሳ ከተሞች አካሂዷል።
በውይይት መድረኮቹ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ የጋምቤላ፣ የኦሮሚያ እና የሲዳማ ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች፣ ጽሕፈት ቤቶች እና ክትትል የተደረገባቸው ትምህርት ቤቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ኢሰመኮ በአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የአዲስ አበባ እና የባሕር ዳር ከተሞች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ተመሳሳይ የውይይት መድረክ በመጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄዱ ይታወሳል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33164
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የትምህርት መብት ለማረጋገጥ የትምህርት ግብአት አቅርቦት፣ ከባቢያዊ እና የመረጃ ተደራሽነት እንዲሁም የአመለካከት ክፍተቶች ላይ መሥራት ያስፈልጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በልዩ አዳሪ እና አካቶ ቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ባሕር ዳር፣ ቢሾፍቱ፣ ባኮ፣ ጋምቤላ፣ ሆሳዕና፣ መቐለ፣ ሰበታ እና ሻሸመኔ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ባከናወነው ክትትል የተለዩ ግኝቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሁለት የምክክር መድረኮች በአዲስ አበባ እና ሃዋሳ ከተሞች አካሂዷል።
በውይይት መድረኮቹ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ የጋምቤላ፣ የኦሮሚያ እና የሲዳማ ክልሎች ትምህርት ቢሮዎች፣ ጽሕፈት ቤቶች እና ክትትል የተደረገባቸው ትምህርት ቤቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ኢሰመኮ በአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የአዲስ አበባ እና የባሕር ዳር ከተሞች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ተመሳሳይ የውይይት መድረክ በመጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄዱ ይታወሳል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33164
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍5❤2
5ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (Human Rights Moot Court) ፍጻሜ ውድድር ተካሄደ
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 5ኛውን ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (5th National High Schools Human Rights Moot Court Competition) ፍጻሜ ውድድር ግንቦት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ከሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲካሄድ በቆየው ውድድር በ12 ክልሎች እና በ2 ከተማ አስተዳደሮች ከሚገኙ 90 ትምህርት ቤቶች 180 ተወዳዳሪ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
በዚሁ መሠረት ተማሪ ሲፈን ደረጄ እና ተማሪ ሚልኬሳ ንጋቱ ከቢሾፍቱ ከተማ የኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ የፍጻሜ ውድድሩ አሸናፊ ሆነዋል። በተጨማሪም የውድድሩ ምርጥ የቃል ተከራካሪ በመሆን ተማሪ ሲፈን ደረጄ ከኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ ያሸነፈች ሲሆን በምርጥ የጽሑፍ ክርክር ደግሞ በተመሳሳይ ከኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ የመጡት ተማሪ ሲፈን ደረጄ እና ተማሪ ሚልኬሳ ንጋቱ አሸናፊዎች ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33257
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 5ኛውን ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (5th National High Schools Human Rights Moot Court Competition) ፍጻሜ ውድድር ግንቦት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። ከሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲካሄድ በቆየው ውድድር በ12 ክልሎች እና በ2 ከተማ አስተዳደሮች ከሚገኙ 90 ትምህርት ቤቶች 180 ተወዳዳሪ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
በዚሁ መሠረት ተማሪ ሲፈን ደረጄ እና ተማሪ ሚልኬሳ ንጋቱ ከቢሾፍቱ ከተማ የኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ የፍጻሜ ውድድሩ አሸናፊ ሆነዋል። በተጨማሪም የውድድሩ ምርጥ የቃል ተከራካሪ በመሆን ተማሪ ሲፈን ደረጄ ከኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ ያሸነፈች ሲሆን በምርጥ የጽሑፍ ክርክር ደግሞ በተመሳሳይ ከኦሮሚያ ልማት ማኅበር ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ቢሾፍቱ ቅርንጫፍ የመጡት ተማሪ ሲፈን ደረጄ እና ተማሪ ሚልኬሳ ንጋቱ አሸናፊዎች ሆነዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33257
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3❤2🔥1
በማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ በሚገኙ ሕፃናት መብቶች አያያዝ ላይ የተካሄደ ውይይት
...
በማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሕፃናትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ለማሻሻል ሁሉም ባለድርሻዎች ምክረ ሐሳቦችን በቅንጅት ሊተገብሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሃዋሳ፣ ሻሸመኔ እና ወላይታ ከተሞች በሚገኙ 21 የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት ባከናወነው የምክረ ሐሳቦች አፈጻጸም ክትትል ግኝቶች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ውይይት አካሂዷል። በውይይቱ የሐረሪ፣ የኦሮሚያ፣ የሲዳማ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሴቶች፣ የሕፃናት እና የማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች ኃላፊዎች እንዲሁም የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ኢሰመኮ በማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ ከሚገኙ ሕፃናት መብቶች አያያዝ ጋር በተያያዘ ያከናወነው ክትትል ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ማዕቀፎችን መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ በተለይም የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት የቅበላ መሥፈርቶች እና መረጃ አያያዝ፣ የሕፃናት ከጥቃት የመጠበቅ መብት፣ የቅጣት (የዲሲፕሊን) እርምጃዎች፣ የጤና፣ የሥነ ልቦና፣ የትምህርት፣ የጨዋታ እና የመዝናኛ አገልግሎቶች፣ የእምነት ነጻነት እና የተሳትፎ መብቶችን በተመለከተ የተለዩ ግኝቶች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎች እና የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33299
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሕፃናትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ለማሻሻል ሁሉም ባለድርሻዎች ምክረ ሐሳቦችን በቅንጅት ሊተገብሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ ሃዋሳ፣ ሻሸመኔ እና ወላይታ ከተሞች በሚገኙ 21 የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት ባከናወነው የምክረ ሐሳቦች አፈጻጸም ክትትል ግኝቶች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ውይይት አካሂዷል። በውይይቱ የሐረሪ፣ የኦሮሚያ፣ የሲዳማ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሴቶች፣ የሕፃናት እና የማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች ኃላፊዎች እንዲሁም የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ኢሰመኮ በማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ ከሚገኙ ሕፃናት መብቶች አያያዝ ጋር በተያያዘ ያከናወነው ክትትል ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ማዕቀፎችን መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ በተለይም የሕፃናት ማሳደጊያ ተቋማት የቅበላ መሥፈርቶች እና መረጃ አያያዝ፣ የሕፃናት ከጥቃት የመጠበቅ መብት፣ የቅጣት (የዲሲፕሊን) እርምጃዎች፣ የጤና፣ የሥነ ልቦና፣ የትምህርት፣ የጨዋታ እና የመዝናኛ አገልግሎቶች፣ የእምነት ነጻነት እና የተሳትፎ መብቶችን በተመለከተ የተለዩ ግኝቶች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎች እና የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33299
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: በሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች የተጎዱ ሕፃናት
...
የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 39
ተዋዋይ ሀገራት የማናቸውም ዐይነት የእንክብካቤ እጦት፣ ብዝበዛ፣ ያልተገባ አያያዝ፣ ማሰቃየት ወይም ሌላ ማናቸውም ዐይነት ጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብአዊ የሆነ ወይም ክብርን የሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት ወይም የትጥቅ ግጭት ሰለባ የሆነን ሕፃን በአካልና በሥነ ልቦና ከደረሰበት ጉዳት እንዲያገግምና ከኅብረተሰቡ ጋር እንዲቀላቀል ለማድረግ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ።
ይህ ዐይነቱ ሕፃኑን ከጉዳቱ እንዲያገግም እና ወደ ኅብረተሰቡ እንዲቀላቀል የማድረግ ተግባር የሕፃኑን ጤንነት፣ ለራስ ዋጋ የመስጠት ስሜት እና ክብር ለማዳበር በሚያመች ሁኔታ ውስጥ መከናወን አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=33355
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 39
ተዋዋይ ሀገራት የማናቸውም ዐይነት የእንክብካቤ እጦት፣ ብዝበዛ፣ ያልተገባ አያያዝ፣ ማሰቃየት ወይም ሌላ ማናቸውም ዐይነት ጭካኔ የተሞላበት፣ ኢ-ሰብአዊ የሆነ ወይም ክብርን የሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት ወይም የትጥቅ ግጭት ሰለባ የሆነን ሕፃን በአካልና በሥነ ልቦና ከደረሰበት ጉዳት እንዲያገግምና ከኅብረተሰቡ ጋር እንዲቀላቀል ለማድረግ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ።
ይህ ዐይነቱ ሕፃኑን ከጉዳቱ እንዲያገግም እና ወደ ኅብረተሰቡ እንዲቀላቀል የማድረግ ተግባር የሕፃኑን ጤንነት፣ ለራስ ዋጋ የመስጠት ስሜት እና ክብር ለማዳበር በሚያመች ሁኔታ ውስጥ መከናወን አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=33355
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1
ሀገር አቀፍ ውይይት፦ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከፕሮጀክት ኤክስፔዳይት ጀስቲስ (Project Expedite Justice, PEJ) ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ላይ ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል።
በኢሰመኮ፣ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች ባለድርሻዎች መካከል ያለውን ትብብርና ቅንጅት ማጠናከርን ዓላማ ባደረገው ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሲዳማ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እና ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ሰጪ አካላት ተሳትፈዋል።
በውይይት መድረኩ ኢሰመኮን ጨምሮ የሦስት ተቋማት የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳን የተመለከቱ ገለጻዎች፣ መልካም ተሞክሮዎች እና ተግዳሮቶች ቀርበዋል። በኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ፅንሰ ሐሳባዊ ማብራሪያ፣ የሰብአዊ መብቶች ስነዳ ዐይነቶች፣ የስነዳ አስፈላጊነት፣ በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ እና ማስፋፋት ላይ ኢሰመኮ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የሚጋሯቸው ጉዳዮች፣ በሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ መካከል ያለው ልዩነት እና አንድነት እንዲሁም ተግባራዊ ሊሆኑ የሚገቡ የሰብአዊ መብቶች መርሖች፣ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ወሰን (scope) እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ገለጻ ተድርጓል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33387
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከፕሮጀክት ኤክስፔዳይት ጀስቲስ (Project Expedite Justice, PEJ) ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ላይ ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል።
በኢሰመኮ፣ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች ባለድርሻዎች መካከል ያለውን ትብብርና ቅንጅት ማጠናከርን ዓላማ ባደረገው ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሲዳማ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሰብአዊ መብቶች ላይ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት እና ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ሰጪ አካላት ተሳትፈዋል።
በውይይት መድረኩ ኢሰመኮን ጨምሮ የሦስት ተቋማት የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳን የተመለከቱ ገለጻዎች፣ መልካም ተሞክሮዎች እና ተግዳሮቶች ቀርበዋል። በኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ፅንሰ ሐሳባዊ ማብራሪያ፣ የሰብአዊ መብቶች ስነዳ ዐይነቶች፣ የስነዳ አስፈላጊነት፣ በሰብአዊ መብቶች ጥበቃ እና ማስፋፋት ላይ ኢሰመኮ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የሚጋሯቸው ጉዳዮች፣ በሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ መካከል ያለው ልዩነት እና አንድነት እንዲሁም ተግባራዊ ሊሆኑ የሚገቡ የሰብአዊ መብቶች መርሖች፣ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ ምርመራ እና ስነዳ ወሰን (scope) እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ገለጻ ተድርጓል።
🔗 https://ehrc.org/?p=33387
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1👍1
