Forwarded from የረሕማን ስጦታ
የተወዳጁን ነቢይ [ﷺ] ታላቅነት ከሚያስረዱ የአላህ ስጦታዎች መካከል መሬት ውስጥ የርሳቸው ዝክር ያልተወሳበት ምንም ዘመን አለመኖሩ ተጠቃሽ ነው። ምድር ከተፈጠረች ጀምሮ እስከ ፍፃሜዋ ድረስ ያልተቋረጠ መታወስ ተከትቦላቸዋል። ምክንያቱም ከዘመን በቀደመው የሩሕ ዓለም ውስጥ ነቢያት ከሰይዲና አደም [ﷺ] ጀምሮ እስከ ቂያማ ያሉትን ሰብስቦ አላህ [ሱብሐነሁ] ቃልኪዳን አስገብቷቸዋል።
ነቢይ ሙሐመድ [ﷺ] በእነርሱ ዘመን ከመጡ ሊያምኑባቸው፣ ሊያግዟቸው እና ሊከተሏቸው፣ ለህዝባቸውም የርሳቸውን መምጣት እንዲያበስሩ አደራ ተጥሎባቸዋል። አላህ እንዲህ ብሏል: ‐
«አላህ የነቢያትን ቃል ኪዳን ከመጽሐፍና ከጥበብ ሰጥቻችሁ ከዚያም «ከእናንተ ጋር ላለው (መጽሐፍ) የሚያረጋግጥ መልክተኛ ቢመጣላችሁ በርሱ በእርግጥ እንደምታምኑበት በእርግጥም እንድትረዱት ሲል በያዘ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ አረጋገጣችሁን በዚህም ላይ ኪዳኔን ያዛችሁምን» አላቸው፡፡ «አረጋገጥን» አሉ፡፡ «እንግዲያስ መስክሩ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከመስካሪዎቹ ነኝ» አላቸው፡፡»
:
አንጀት አረስርሱ ኢማም አል‐ቡሶይሪይ [ረዲየላሁ ዐንሁ] የሀምዚያ መድብላቸው ላይ አሳምረው ገልፀውታል: ‐
ما مضت فترةٌ من الرُّسْلِ إِلّا
بَشَّرَت قومَها بك الأنبياءُ
تتباهَى بك العصورُ وتَسمو
بِك علياءٌ بعدها علياءُ
«ከቶ አላለፈም የነቢያት ዘመን
አንቱ ሳያወሳ ሳያውጅ ጀብድሁን
መልክተኛው ነግሯል አለቅነትሁን
የሁሉ መላቂያው አንቱ መሆንሁን።
የቀን መፎከሪያ ከፍ ብሎ የሚታይ
ደምቆ የሚያፈካው አልቆ እንደ ሰማይ
የዘመናት ዝክር የዝንቱ ዳንኪራ
ተሰቅሎ የሚኖር የማይወርድ ባንዲራ
አንቱ መሆንሁን ይኖራል ሲያወራ
ሁሉም በየተራ!…
ነቢይ ሙሐመድ [ﷺ] በእነርሱ ዘመን ከመጡ ሊያምኑባቸው፣ ሊያግዟቸው እና ሊከተሏቸው፣ ለህዝባቸውም የርሳቸውን መምጣት እንዲያበስሩ አደራ ተጥሎባቸዋል። አላህ እንዲህ ብሏል: ‐
«አላህ የነቢያትን ቃል ኪዳን ከመጽሐፍና ከጥበብ ሰጥቻችሁ ከዚያም «ከእናንተ ጋር ላለው (መጽሐፍ) የሚያረጋግጥ መልክተኛ ቢመጣላችሁ በርሱ በእርግጥ እንደምታምኑበት በእርግጥም እንድትረዱት ሲል በያዘ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ አረጋገጣችሁን በዚህም ላይ ኪዳኔን ያዛችሁምን» አላቸው፡፡ «አረጋገጥን» አሉ፡፡ «እንግዲያስ መስክሩ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከመስካሪዎቹ ነኝ» አላቸው፡፡»
:
አንጀት አረስርሱ ኢማም አል‐ቡሶይሪይ [ረዲየላሁ ዐንሁ] የሀምዚያ መድብላቸው ላይ አሳምረው ገልፀውታል: ‐
ما مضت فترةٌ من الرُّسْلِ إِلّا
بَشَّرَت قومَها بك الأنبياءُ
تتباهَى بك العصورُ وتَسمو
بِك علياءٌ بعدها علياءُ
«ከቶ አላለፈም የነቢያት ዘመን
አንቱ ሳያወሳ ሳያውጅ ጀብድሁን
መልክተኛው ነግሯል አለቅነትሁን
የሁሉ መላቂያው አንቱ መሆንሁን።
የቀን መፎከሪያ ከፍ ብሎ የሚታይ
ደምቆ የሚያፈካው አልቆ እንደ ሰማይ
የዘመናት ዝክር የዝንቱ ዳንኪራ
ተሰቅሎ የሚኖር የማይወርድ ባንዲራ
አንቱ መሆንሁን ይኖራል ሲያወራ
ሁሉም በየተራ!…
❤52👍8😍1
የሙቀዲመቱ ባፈድል ኪታቡል‐ሐጅ እዚህ ድረስ ነበር። አላህ ካለ በሐጅ እና በዐስሩ የዙል‐ሒጃ ቀናት ዙርያ ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማከታተል እሞክራለሁ። እየተከታተላችሁ፣ ለሌሎችም እያጋራችሁ ቆዩኝ። ቻናሉ አሁን ካለው ተከታይ በላይ በሰፊው እንዲሰራጭና እንዲያድግ እንድታግዙኝም እጠይቃለሁ!
👍16❤9
ከረጅም ገፍላችን ስንመለስ ዐስሩ የምድር ልዩ እና ድንቅ ቀናት (ዐሽሩ ዚልሒጃ) እየቀረቡ ነው። በሚቀጥሉት ቀናት በተለያየ መልኩ ስለነርሱ አንስተን እንተዋወሳለን። እስከዚያው ይህንን ቻናል ለዘመድ ለጓደኛችሁ በማጋራት ያስተዋውቁልን። ተከታዩን ሊንክን በመጫን ቤተሰብ መሆን ይቻላል።
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤51👍4
በእጃችን የሚገኙ የሙቀዲመቱ ባፈድል ህትመቶች እዚህ ድረስ ናቸው። ስለዚህ በ48ኛው ክፍል ኪታባችንን አኽትመናል። አልሀምዱሊላህ!
❤9
المقدمة الحضرمية.pdf
2.9 MB
እኛ በእጃችን በስፋት በሚገኙት ህትመቶች መሰረት ኪታባችንን ብናኸትምም ደራሲው ሸይኽ ዐብዱላህ ባፈድል አል‐ሐድረሚይ [ረሒመሁላህ] ግን ከዚህ በኋላም ቀጥለውበታል። ባያያዝኩላችሁ ፒዲኤፍ ላይ እንደምታዩት ኪታቡል‐ቡዩዕን እስከ ባቡል‐ሂባ ድረስ አስሂደውታል። የማይቀረው ሞት መጥቶ ጠፊውን ዓለም ተሰናበቱ እንጂ!
ከርሳቸው በኋላም አል‐ሚንሃጁል ቀዊም ብለው ለዚህ ኪታብ ሸርሕ የሰሩት ታላቁ የሻፊዒያ ልሂቅ ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ [ረዲየላሁ ዐንሁ] በዋናው ደራሲ አጣጣልና እቅድ መሰረት እርሳቸው ካቆሙበት የቀጠሉ ቢሆንም እስከ ፈራኢድ ድረስ ከፃፉ በኋላ የሰማዩን ጥሪ እሺ ብለው ነጎዱ። እርሳቸውንም አላህ ይማራቸው። እኛንም በደጋጎቹ ዒልም እና በረካ ይጥቀመን!
አሚን!
ለሁለቱም ፋቲሓ እንቅራላቸው!
ከርሳቸው በኋላም አል‐ሚንሃጁል ቀዊም ብለው ለዚህ ኪታብ ሸርሕ የሰሩት ታላቁ የሻፊዒያ ልሂቅ ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ [ረዲየላሁ ዐንሁ] በዋናው ደራሲ አጣጣልና እቅድ መሰረት እርሳቸው ካቆሙበት የቀጠሉ ቢሆንም እስከ ፈራኢድ ድረስ ከፃፉ በኋላ የሰማዩን ጥሪ እሺ ብለው ነጎዱ። እርሳቸውንም አላህ ይማራቸው። እኛንም በደጋጎቹ ዒልም እና በረካ ይጥቀመን!
አሚን!
ለሁለቱም ፋቲሓ እንቅራላቸው!
👍24❤4
ከረዥም አመታት ጀምሮ በሀገራችን ከተለመደው በተለየ ሁኔታ ለተማሪዎቼ ሙቀዲመቱ ባፈድልን ከአቡሹጃዕ አስቀድሜ አስተምራለሁ። በ እርግጥ ከጊዜያት በኋላ ሰዎች እንደነገሩኝ ከሆነ ይህንኑ ሃሳብ በዓለም ላይ ታዋቂ የሆኑ ሻፊዒዮች ያሉባቸው የዒልም ስፍራዎችም እየሰሩበት ይገኛል። የነርሱን ምክንያት ባላውቅም የእኔ ምክንያት በዋናነት አንድ ነው። እርሱም አቡሹጃዕ ከዒባዳ በዘለል ሌሎች የፊቅህ ክፍሎችን የግብይት ህጎችን፣ የኒካሕ እና ተያያዥ ህጎችን፣ ውርስ፣ የወንጀለኛ መቅጫ ህግጋትን [ጂናያት] እና ሌሎችንም በሰፋፊ መፅሐፍት ላይ የሚሰፍሩ ትምህርቶችን በመያዟ ነው። በተጨማሪም አቀራረቧ ከመብራራት የራቀ በጣም አጭር በመሆኗ ሃሳቧ አይያዝም። ስትተነተን ትንቦረቀቃለች፣ ለአብዝሃኛው ሙስሊም የነፍስ ወከፍ እውቀቶች ያልሆኑ ነጥቦችንም አካታለች ብዬ ስለማስብ ነው።
በአንጻሩ ባፈድል መጠኗ ሚዛናዊ ከመሆኑ ጋር ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የነፍስ ወከፍ እውቀቶችን ብቻ የያዘች በመሆኗ አንገብጋቢና ለሁሉም ሙስሊም አማካይ ናት ብዬ አስባለሁ። ባፈድል አርካኑል‐ኢስላምን ብቻ በበቂ ስፋት የምትዳስስ መጽሐፍ ናት።
እግረመንገዴን ኢስላማዊ እውቀት ሚሹ ታናናሾቼ እውቀትን ካሪኩለም ተከትለው ቀደምቶቻችን ባስቀመጡት መልኩ፣ ሸይኽ ስር፣ እርከናቸውን ጠብቀው እንዲጓዙ እመክራለሁ። ጉራማይሌ የሆነ የእውቀት ፍለጋ የጊዜ ብክነት ከማስከተሉ ጋር የማይጨበጥ ጉም ውስጥ ይከታል። አዋቂ የሚመስሉ ጥራዝ ነጠቆችን እንጂ የእውነት የእውቀት ባለቤቶችን አያፈራም።
በመጨረሻም የአዝካር ነወዊ ደርሳችንን በመጪው ሳምንት በሳምንት ሁለት ቀን መለቀቅ እንደሚቀጥል ከመግለፅ ጋር በርካቶቻችሁ ስትወተውቱ የነበረው የአቡሹጃዕ ደርስን በቀጥታ [ላይቭ] ለማስተማር ከራሴ ጋር እየተማከርኩ መሆኑን አሳውቃለሁ። ኢንሻአላህ!
ሙኽተሶር አቡ ሹጃዕ [አል‐ጛየቱ ወት‐ተቅሪብ] እኔ ዘንድ እጅግ በጣም ተወዳጅ ከሆኑ ልቤ ውስጥ ልዩ ስፍራ ያላት መጽሐፍ ናት! ትርጉምና ማብራሪያዋንም ከዚህ ቀደም ''ሰፊናን'' በሰራሁበት መንገድ ማዘጋጀቴንና በቅርቡ በመጽሐፍ ጥራዝ በእጃችሁ እንደምትገባ አበስራለሁ!
በዱዓችሁ!
በአንጻሩ ባፈድል መጠኗ ሚዛናዊ ከመሆኑ ጋር ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የነፍስ ወከፍ እውቀቶችን ብቻ የያዘች በመሆኗ አንገብጋቢና ለሁሉም ሙስሊም አማካይ ናት ብዬ አስባለሁ። ባፈድል አርካኑል‐ኢስላምን ብቻ በበቂ ስፋት የምትዳስስ መጽሐፍ ናት።
እግረመንገዴን ኢስላማዊ እውቀት ሚሹ ታናናሾቼ እውቀትን ካሪኩለም ተከትለው ቀደምቶቻችን ባስቀመጡት መልኩ፣ ሸይኽ ስር፣ እርከናቸውን ጠብቀው እንዲጓዙ እመክራለሁ። ጉራማይሌ የሆነ የእውቀት ፍለጋ የጊዜ ብክነት ከማስከተሉ ጋር የማይጨበጥ ጉም ውስጥ ይከታል። አዋቂ የሚመስሉ ጥራዝ ነጠቆችን እንጂ የእውነት የእውቀት ባለቤቶችን አያፈራም።
በመጨረሻም የአዝካር ነወዊ ደርሳችንን በመጪው ሳምንት በሳምንት ሁለት ቀን መለቀቅ እንደሚቀጥል ከመግለፅ ጋር በርካቶቻችሁ ስትወተውቱ የነበረው የአቡሹጃዕ ደርስን በቀጥታ [ላይቭ] ለማስተማር ከራሴ ጋር እየተማከርኩ መሆኑን አሳውቃለሁ። ኢንሻአላህ!
ሙኽተሶር አቡ ሹጃዕ [አል‐ጛየቱ ወት‐ተቅሪብ] እኔ ዘንድ እጅግ በጣም ተወዳጅ ከሆኑ ልቤ ውስጥ ልዩ ስፍራ ያላት መጽሐፍ ናት! ትርጉምና ማብራሪያዋንም ከዚህ ቀደም ''ሰፊናን'' በሰራሁበት መንገድ ማዘጋጀቴንና በቅርቡ በመጽሐፍ ጥራዝ በእጃችሁ እንደምትገባ አበስራለሁ!
በዱዓችሁ!
👍40❤24
================
የዐስሩ የዙል‐ሒጅ‐ጃ ቀናት
ትሩፋት
================
⚀ አላህ የማለባቸው ቀናት: ‐
አላህ የማለባቸው ነገሮች ልቅና ያላቸው ነገሮች ናቸው። ምክንያቱም የልቅና ባለቤት ልቅና ባለው ነገር እንጂ በሌላ አይምልም። አላህ እንዲህ አለ: ‐
«በጎህ እምላለሁ፡፡ በዐሥር ሌሊቶችም፡፡»
በርካታ የተፍሲር ልሂቃን እንደሚሉት ዐስር ሌሊቶች በማለት የተጠቀሱት ዐስሩ የዙልሒጃ የመጀመሪያ ቀናት ናቸው።
ኢብኑ ከሲር «ይህ ትክክለኛው ተፍሲር ነው።» ብለውታል።
:
⚁ ዚክር ማብዛት የታዘዘባቸው "የታወቁ ቀናት": ‐
አላህ እንዲህ ብሏል: ‐
[لِّيَشْهَدُوا۟ مَنَٰفِعَ لَهُمْ وَيَذْكُرُوا۟ ٱسْمَ ٱللَّهِ فِىٓ أَيَّامٍ مَّعْلُومَٰتٍ عَلَىٰ مَا رَزَقَهُم مِّنۢ بَهِيمَةِ ٱلْأَنْعَٰمِ فَكُلُوا۟ مِنْهَا وَأَطْعِمُوا۟ ٱلْبَآئِسَ ٱلْفَقِيرَ]
«ለእነሱ የሆኑ ጥቅሞችን ይጣዱ ዘንድ በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከለማዳ እንስሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ (ይመጡሃል)፡፡»
:
⚂ ምርጦቹ የአላህ ቀናት: ‐
ከጃቢር [ረዐ] እንደተዘገበው ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ምርጦቹ የዱንያ ቀናት ዐስሩ የወርሀ ዙልሒጃ ቀናት ናቸው።
ሰዎችም «በሌሎች ወራት በጂሃድ ላይ ከማሳለፍም ይበልጣሉ?» በማለት ጠየቁ።
የአላህ መልክተኛም [ﷺ] «አዎን! በሌሎች ወራት በአላህ መንገድ ላይ (ጂሃድ) ላይ ከመሆንም ይበልጣሉ። ፊቱን በአፈር ላይ ያደረገ (ሰማእት የሆነ) ሰው ሲቀር!» በማለት መለሱ።» በዝ‐ዛር እና ኢብኑ ሒባን ዘግበውታል።
:
⚃ የዐረፋ ቀንን የያዙ ቀናት: ‐
የዐረፋ ቀን ዘጠነኛው የዙልሒጃ ቀን ነው። ታላቁ የሐጅ ስራ የሚከናወንበት ቀን ነው። ኃጢኣት የሚማርበት ቀን ነው። ሰዎች ከእሳት ነፃ የሚሆኑበት ቀን ነው። በዐስሩ የዙል‐ሒጃ ቀናት ውስጥ ከዐረፋ ቀን በቀር ምንም ባይኖር እንኳን የዐስሩን ቀናት ትሩፋት የገዘፈ ያደርገዋል።
:
⚄ የእርዱ ቀንን (የዒዱል‐አድሓ ቀን) በውስጣቸው የያዙ ቀናት: ‐
አንዳንድ ዐሊሞች ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ቀን ይህ ቀን ነው። ታላቁ የሐጅ ቀን (የውሙል‐ሐጂል‐አክበር) ይኸው ቀን ነው። ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «አላህ ዘንድ ታላቅ የሆነው ቀን የእርዱ ቀን ነው።» አቡ ዳዉድ እና ነሳኢይ ዘግበውታል።
:
⚅ ዋናዎቹ የዒባዳ ዘርፎችን ያካተቱ ቀናት: ‐
አል‐ሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር "ፈትሑል‐ባሪ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐ «የዙል‐ሒጃ ዐስሩ ቀናት ከሌሎች ቀናት የተለዩት ዋናዎቹ የዒባዳ ዘርፎችን አካተው በመያዛቸው ነው። እነሱም ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ ናቸው። በሌሎች ጊዜያት ይህ ሊሳካ የሚችል አይደለም።»
:
❦ ዛሬ እነዚህ የተከበሩ ቀናት አንድ ብለው ጀምረዋል። ራሳችንን እና ቤተሰቦቻችንን ቀስቅሰን በዒባዳ እንበርታ!
አላህ ተውፊቁን ይለግሰን!
http://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
የዐስሩ የዙል‐ሒጅ‐ጃ ቀናት
ትሩፋት
================
⚀ አላህ የማለባቸው ቀናት: ‐
አላህ የማለባቸው ነገሮች ልቅና ያላቸው ነገሮች ናቸው። ምክንያቱም የልቅና ባለቤት ልቅና ባለው ነገር እንጂ በሌላ አይምልም። አላህ እንዲህ አለ: ‐
«በጎህ እምላለሁ፡፡ በዐሥር ሌሊቶችም፡፡»
በርካታ የተፍሲር ልሂቃን እንደሚሉት ዐስር ሌሊቶች በማለት የተጠቀሱት ዐስሩ የዙልሒጃ የመጀመሪያ ቀናት ናቸው።
ኢብኑ ከሲር «ይህ ትክክለኛው ተፍሲር ነው።» ብለውታል።
:
⚁ ዚክር ማብዛት የታዘዘባቸው "የታወቁ ቀናት": ‐
አላህ እንዲህ ብሏል: ‐
[لِّيَشْهَدُوا۟ مَنَٰفِعَ لَهُمْ وَيَذْكُرُوا۟ ٱسْمَ ٱللَّهِ فِىٓ أَيَّامٍ مَّعْلُومَٰتٍ عَلَىٰ مَا رَزَقَهُم مِّنۢ بَهِيمَةِ ٱلْأَنْعَٰمِ فَكُلُوا۟ مِنْهَا وَأَطْعِمُوا۟ ٱلْبَآئِسَ ٱلْفَقِيرَ]
«ለእነሱ የሆኑ ጥቅሞችን ይጣዱ ዘንድ በታወቁ ቀኖችም ውስጥ ከለማዳ እንስሳዎች በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ያወሱ ዘንድ (ይመጡሃል)፡፡»
:
⚂ ምርጦቹ የአላህ ቀናት: ‐
ከጃቢር [ረዐ] እንደተዘገበው ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ምርጦቹ የዱንያ ቀናት ዐስሩ የወርሀ ዙልሒጃ ቀናት ናቸው።
ሰዎችም «በሌሎች ወራት በጂሃድ ላይ ከማሳለፍም ይበልጣሉ?» በማለት ጠየቁ።
የአላህ መልክተኛም [ﷺ] «አዎን! በሌሎች ወራት በአላህ መንገድ ላይ (ጂሃድ) ላይ ከመሆንም ይበልጣሉ። ፊቱን በአፈር ላይ ያደረገ (ሰማእት የሆነ) ሰው ሲቀር!» በማለት መለሱ።» በዝ‐ዛር እና ኢብኑ ሒባን ዘግበውታል።
:
⚃ የዐረፋ ቀንን የያዙ ቀናት: ‐
የዐረፋ ቀን ዘጠነኛው የዙልሒጃ ቀን ነው። ታላቁ የሐጅ ስራ የሚከናወንበት ቀን ነው። ኃጢኣት የሚማርበት ቀን ነው። ሰዎች ከእሳት ነፃ የሚሆኑበት ቀን ነው። በዐስሩ የዙል‐ሒጃ ቀናት ውስጥ ከዐረፋ ቀን በቀር ምንም ባይኖር እንኳን የዐስሩን ቀናት ትሩፋት የገዘፈ ያደርገዋል።
:
⚄ የእርዱ ቀንን (የዒዱል‐አድሓ ቀን) በውስጣቸው የያዙ ቀናት: ‐
አንዳንድ ዐሊሞች ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ቀን ይህ ቀን ነው። ታላቁ የሐጅ ቀን (የውሙል‐ሐጂል‐አክበር) ይኸው ቀን ነው። ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «አላህ ዘንድ ታላቅ የሆነው ቀን የእርዱ ቀን ነው።» አቡ ዳዉድ እና ነሳኢይ ዘግበውታል።
:
⚅ ዋናዎቹ የዒባዳ ዘርፎችን ያካተቱ ቀናት: ‐
አል‐ሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር "ፈትሑል‐ባሪ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐ «የዙል‐ሒጃ ዐስሩ ቀናት ከሌሎች ቀናት የተለዩት ዋናዎቹ የዒባዳ ዘርፎችን አካተው በመያዛቸው ነው። እነሱም ሶላት፣ ጾም፣ ሶደቃ እና ሐጅ ናቸው። በሌሎች ጊዜያት ይህ ሊሳካ የሚችል አይደለም።»
:
❦ ዛሬ እነዚህ የተከበሩ ቀናት አንድ ብለው ጀምረዋል። ራሳችንን እና ቤተሰቦቻችንን ቀስቅሰን በዒባዳ እንበርታ!
አላህ ተውፊቁን ይለግሰን!
http://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤21👍14
