Tofik Bahiru pinned «ጁሙዐ እና ዒድ ዒድ በጁሙዓ ቀን ከዋለ ጁሙዓዎች መደበኛውን ቀጠሮ ተከትለው በየመስጂዱ ይሰገዳሉ። ስለዚህ ማንኛውም ሙስሊም ዒዱን በጀመዐ ከሰገደ በኋላ ጁሙዓውንም እንደተለመደው ቢያስከትል እጅግ የተመረጠ ነው። ነገርግን ሁለቱንም ሶላቶች ማስገኘት የማያስችል ምክንያት ካለው ጁሙዓን ማስበለጥ አለበት። ምክንያቱም ጁሙዐ የነፍስ ወከፍ ግዴታ ነው። ጁሙዓን ግዴታ የሚያደርጉ መስፈርቶች ተሟልተው እስከተገኙ ድረስ…»
በዒድ አል‐አድሓ ቀን መስራት ያለብንን ❿ ነገሮች እናስታውስ: ‐
❶ የቀኑን ትልቅነት ማሰብ፤ የውሙል‐ሐጂል‐አክበር ነው።
❷ ድምፅን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማድረግ፤
❸ ገላ መታጠብ፤ አዲስ ወይም ምርጥ ልብሳችንን መልበስ፤ ሽቶ መቀባት፤ ጥርስን መፋቅ፤
❹ ሶላት እስከሚጠናቀቅ ድረስ ምንም ሳንቀምስ እንደጾመኛ "ኢምሳክ" ማድረግ።
❺ ወደ ዒድ ሶላት ሜዳ ተሰብስበን በህብረት ተክቢራ ደምቀን መሄድ፤
❻ ሶላታችንን መስገድ፤ ኹጥባ ማዳመጥ፤
❼ በዜማ እና በሌላ ጨዋታ ዒዱን ማድመቅ፤
❽ የሄዱበትን መንገድ ቀይሮ መመለስ፤
❾ በዒዱ ቀን ዓቅመ ደካማዎችን መዘየር፤ በደስታ እንዲያሳልፉት ማገዝ፤
❿ በነዚህ የደስታ ሰዓት እንኳን በግፍ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንን በተለይም ፊሊስጢኖችን በዱዓ ማሰብ።
:
በድል ጨረቃ ታጅበን፣ በኢስላም ልዕልና ደምቀን፣ በሀገራችን ሰላም ተውበን፣ በአንድነት እና በፍቅር ከአመት አመት ያድርሰን!
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም!
http://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❶ የቀኑን ትልቅነት ማሰብ፤ የውሙል‐ሐጂል‐አክበር ነው።
❷ ድምፅን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማድረግ፤
❸ ገላ መታጠብ፤ አዲስ ወይም ምርጥ ልብሳችንን መልበስ፤ ሽቶ መቀባት፤ ጥርስን መፋቅ፤
❹ ሶላት እስከሚጠናቀቅ ድረስ ምንም ሳንቀምስ እንደጾመኛ "ኢምሳክ" ማድረግ።
❺ ወደ ዒድ ሶላት ሜዳ ተሰብስበን በህብረት ተክቢራ ደምቀን መሄድ፤
❻ ሶላታችንን መስገድ፤ ኹጥባ ማዳመጥ፤
❼ በዜማ እና በሌላ ጨዋታ ዒዱን ማድመቅ፤
❽ የሄዱበትን መንገድ ቀይሮ መመለስ፤
❾ በዒዱ ቀን ዓቅመ ደካማዎችን መዘየር፤ በደስታ እንዲያሳልፉት ማገዝ፤
❿ በነዚህ የደስታ ሰዓት እንኳን በግፍ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንን በተለይም ፊሊስጢኖችን በዱዓ ማሰብ።
:
በድል ጨረቃ ታጅበን፣ በኢስላም ልዕልና ደምቀን፣ በሀገራችን ሰላም ተውበን፣ በአንድነት እና በፍቅር ከአመት አመት ያድርሰን!
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም!
http://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤45
ተክቢራ በአይ‐ያም አት‐ተሽሪቅ
===================
«በአይ‐ያም አት‐ተሽሪቅ ቀናት (ከዒዱል‐አድሓ እለት ቀጥለው ባሉት ሦስት ቀናት) የሚደረገው ተክቢራ የግድ ከፈርድ ሶላት በኋላ መሆን አይጠበቅበትም። [በመርሳት ወይም በሌላ ምክንያት] ቢተወውም በተመቸው ጊዜ ሊያደርገው ይችላል።»
ኢማም ነወዊይ "ሚንሃጅ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «በአይ‐ያም አት‐ተሽሪቅ ቀናት ሶላት ቀዷእ ሲያወጣ፣ መደበኛ ሱና ሶላቶችን ሲጨርስ፣ ማንኛውም ዓይነት ሱና ሲሰግድ አስከትሎ ተክቢራ ማድረግ ይወደዳል የሚለው [የኢማም ሻፊዒይ] ሀሳብ እጅግ የተሻለ (አዝሀር) የሆነው ሃሳብ ነው።»
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይሰሚይ "ቱሕፋ" በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዳሰፈሩት: ‐ «ለምሳሌ: ‐ ከዱሓ ሶላት፣ ከዒድ ሶላት እና ከመሳሰሉት ሶላቶች በኋላ፣ ልቅ ከሆኑ ሱና ሶላቶች በኋላ፣ እንደውም ከጀናዛ ሶላት በኋላ ሳይቀር ተክቢራ ይደረጋል። ምክንያቱም ተክቢራ የጊዜው ዓርማ ነው።»
"ሙኽተሶሩ ባፈድል" በበኩሏ እንዲህ ትላለች: ‐
«ከሐጀኛ ውጪ ያለ ሰው ሁሉ ከፈርድም ሆነ ከሱና ሶላት በኋላ ተክቢራ ያደርጋል። ሶላቱ ትኩስም ይሁን ቀዷእ ወይም የጀናዛ ሶላት ምንም ልዩነት የለም። ተክቢራውን ከረሳ ሲያስታውስ ያድርገው።»
የዒድ ተክቢራ በህብረት ብቻ የሚደረግ የሚመስላቸውም ሰዎች ይኖራሉ። ነገርግን ስህተት ነው። ተክቢራው በግልም በጀመዓም እንደሚደረግ ይታወስ።
:
ዒድ ይደጋግመን። በጤናና በሰላም አመት ከአመት ያድርሰን ያድርሳችሁ።
ዒድ ሙባረክ!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
===================
«በአይ‐ያም አት‐ተሽሪቅ ቀናት (ከዒዱል‐አድሓ እለት ቀጥለው ባሉት ሦስት ቀናት) የሚደረገው ተክቢራ የግድ ከፈርድ ሶላት በኋላ መሆን አይጠበቅበትም። [በመርሳት ወይም በሌላ ምክንያት] ቢተወውም በተመቸው ጊዜ ሊያደርገው ይችላል።»
ኢማም ነወዊይ "ሚንሃጅ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «በአይ‐ያም አት‐ተሽሪቅ ቀናት ሶላት ቀዷእ ሲያወጣ፣ መደበኛ ሱና ሶላቶችን ሲጨርስ፣ ማንኛውም ዓይነት ሱና ሲሰግድ አስከትሎ ተክቢራ ማድረግ ይወደዳል የሚለው [የኢማም ሻፊዒይ] ሀሳብ እጅግ የተሻለ (አዝሀር) የሆነው ሃሳብ ነው።»
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይሰሚይ "ቱሕፋ" በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዳሰፈሩት: ‐ «ለምሳሌ: ‐ ከዱሓ ሶላት፣ ከዒድ ሶላት እና ከመሳሰሉት ሶላቶች በኋላ፣ ልቅ ከሆኑ ሱና ሶላቶች በኋላ፣ እንደውም ከጀናዛ ሶላት በኋላ ሳይቀር ተክቢራ ይደረጋል። ምክንያቱም ተክቢራ የጊዜው ዓርማ ነው።»
"ሙኽተሶሩ ባፈድል" በበኩሏ እንዲህ ትላለች: ‐
«ከሐጀኛ ውጪ ያለ ሰው ሁሉ ከፈርድም ሆነ ከሱና ሶላት በኋላ ተክቢራ ያደርጋል። ሶላቱ ትኩስም ይሁን ቀዷእ ወይም የጀናዛ ሶላት ምንም ልዩነት የለም። ተክቢራውን ከረሳ ሲያስታውስ ያድርገው።»
የዒድ ተክቢራ በህብረት ብቻ የሚደረግ የሚመስላቸውም ሰዎች ይኖራሉ። ነገርግን ስህተት ነው። ተክቢራው በግልም በጀመዓም እንደሚደረግ ይታወስ።
:
ዒድ ይደጋግመን። በጤናና በሰላም አመት ከአመት ያድርሰን ያድርሳችሁ።
ዒድ ሙባረክ!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤32👍6
ኡድሒያ ማረድ አንዳንድ ዐሊሞች ዘንድ ዋጂብ ቢሆንም አብዝሃኞቹ ዘንድ ጥብቅ ሱና ነው። ጎረቤትን በከብት ፈርስ፣ በተጣሉ የከብት ቆሻሻዎች ማስቸገር እና በማንኛውም መልኩ አዛ ማድረግ ደግሞ ሐራም ነው።
እባካችሁ ወዳጆች የእርዳችን ፋና የሆኑ የደም፣ የፈርስ ተረፈ ቆሻሻ እያስወገድን የዲናችንን ግዴታ እንወጣ። መልካም ስራችንን አናበላሽ!
እባካችሁ ወዳጆች የእርዳችን ፋና የሆኑ የደም፣ የፈርስ ተረፈ ቆሻሻ እያስወገድን የዲናችንን ግዴታ እንወጣ። መልካም ስራችንን አናበላሽ!
👍45❤9
ዛሬ አያም ተሽሪቅ ሦስተኛ ቀን ነው። እርዳችንን ያልፈፀምን እስከ መጪው መግሪብ ድረስ እድሉ አለን። ኡድሒያ አስቤዛ አይደለም። ዒባዳ ነው። ስጋውን ለመብላት ሳይሆን መስዋዒት በማድረግ ወደ አላህ ለመቅረብ እንነይት።
:
«ሱና ዐለል ዐይን» — የነፍስ ወከፍ ሱና ነው የሚሉ ዐሊሞች አሉ። በአንድ ቤት ውስጥ ከአንድ በላይ ዓቅም ያላቸው ሰዎች ካሉ እያንዳንዳቸው በተናጠል ማረድ አለባቸው ማለታቸው ነው። ስለዚህ ድሆችን ማገዝ ያስችለን ዘንድ በርከት አድርገን እንረድ። «ኡድሒያ ደሙ መሬት ከመውደቁ በፊት አላህ ዘንድ ነው የሚያርፈው።»…
:
በዒድ መደሰት የዲን ዓርማ ነው። ተደሰቱ! በመንዙማው ተፅናኑ። በነሺዳው ድምፅ ተዛናኑ። ልጆቻችሁን አጫውቱ። ቤታችሁን በልዩ ድባብ አድምቁት።…
:
ከማንኛውም ሶላት በኋላ ተክቢራ ይቀጥላል። እስከ ነገ ዐስር ድረስ። ከነገው ዐስር በኋላም ተክቢራው ተደርጎ ይጠናቀቃል።…
ዒዱኩም ሙባረክ!
:
«ሱና ዐለል ዐይን» — የነፍስ ወከፍ ሱና ነው የሚሉ ዐሊሞች አሉ። በአንድ ቤት ውስጥ ከአንድ በላይ ዓቅም ያላቸው ሰዎች ካሉ እያንዳንዳቸው በተናጠል ማረድ አለባቸው ማለታቸው ነው። ስለዚህ ድሆችን ማገዝ ያስችለን ዘንድ በርከት አድርገን እንረድ። «ኡድሒያ ደሙ መሬት ከመውደቁ በፊት አላህ ዘንድ ነው የሚያርፈው።»…
:
በዒድ መደሰት የዲን ዓርማ ነው። ተደሰቱ! በመንዙማው ተፅናኑ። በነሺዳው ድምፅ ተዛናኑ። ልጆቻችሁን አጫውቱ። ቤታችሁን በልዩ ድባብ አድምቁት።…
:
ከማንኛውም ሶላት በኋላ ተክቢራ ይቀጥላል። እስከ ነገ ዐስር ድረስ። ከነገው ዐስር በኋላም ተክቢራው ተደርጎ ይጠናቀቃል።…
ዒዱኩም ሙባረክ!
❤64👍10
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
«ጀግንነት እና ተገንነት ምርጥ ጠባይ ነው። ጀግንነት ማለት የቁጣ አቅምን ለአዕምሮ ፍርድ ተገዥ እንዲሆን ማድረግ ነው። ተገንነት ማለት ለመልካም ነገር ስኬት ሲባል ነፍስን ያለ ፍርሃት ሞት ወዳለበት ስፍራ መላክ ነው።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በጀግንነትና በተገንነት ይታወቁ ነበር። እጅግ የከበዱ አደገኛ ሁኔታዎች ላይ ተገኝተው ተፈትነዋል። በርካታ ጀግኖችና ጀብደኞች በተደጋጋሚ ከዙርያቸው ሸሽተዋል። እርሳቸው ግን ቦታቸው ላይ ፀንተው ተጋፍጠዋል። ሳያፈገፍጉ ፊትለፊት ፍልሚያቸውን ቀጥለዋል። አልተርበተበቱም።
ማንኛውም ጀግና ጥቂትም ቢሆን የሽሽት አጋጣሚም ይኖረዋል። ያፈገፈገበት ቀንም አያጣውም። ይህ ግን እርሳቸውን አይጨምርም!»
📚 አሽ‐ሺፋእ ቢተዕሪፊ ሑቁቂል‐ሙስጦፋ፥ ኢማም ቃዲ ዒያድ
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በጀግንነትና በተገንነት ይታወቁ ነበር። እጅግ የከበዱ አደገኛ ሁኔታዎች ላይ ተገኝተው ተፈትነዋል። በርካታ ጀግኖችና ጀብደኞች በተደጋጋሚ ከዙርያቸው ሸሽተዋል። እርሳቸው ግን ቦታቸው ላይ ፀንተው ተጋፍጠዋል። ሳያፈገፍጉ ፊትለፊት ፍልሚያቸውን ቀጥለዋል። አልተርበተበቱም።
ማንኛውም ጀግና ጥቂትም ቢሆን የሽሽት አጋጣሚም ይኖረዋል። ያፈገፈገበት ቀንም አያጣውም። ይህ ግን እርሳቸውን አይጨምርም!»
📚 አሽ‐ሺፋእ ቢተዕሪፊ ሑቁቂል‐ሙስጦፋ፥ ኢማም ቃዲ ዒያድ
❤43
ከዚክር ማህደር
ኑሮ የተወሳሰበ ሰው ምን ይበል?
ከሰይዲና ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር እንደተዘገበው የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«አንዳችሁ የኑሮው ጉዳይ ከተወሳሰበበት ከቤቱ ሲወጣ እንዲህ ከማለት ምን ያግደዋል?!: ‐
«በአላህ ስም ነፍሴን፣ ገንዘቤን እና ዲኔን [በማስተካከል ላይ እታገዛለሁ]።
አላህ ሆይ! በፍርድህ አስደስተኝ። ያዘገየኸውን ማስቸኮል፣ ያስቀደምከውን ማዘግየት እስከማልወድ ድረስ በተወሰነልኝ ነገር ላይ በረከት አድርግልኝ።»
ኢብኑ ሱኒይ ዘግበውታል። አዝካር ላይ ኢማም ነወዊይ ጠቅሰውታል።
ኑሮ የተወሳሰበ ሰው ምን ይበል?
ከሰይዲና ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር እንደተዘገበው የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«አንዳችሁ የኑሮው ጉዳይ ከተወሳሰበበት ከቤቱ ሲወጣ እንዲህ ከማለት ምን ያግደዋል?!: ‐
«በአላህ ስም ነፍሴን፣ ገንዘቤን እና ዲኔን [በማስተካከል ላይ እታገዛለሁ]።
አላህ ሆይ! በፍርድህ አስደስተኝ። ያዘገየኸውን ማስቸኮል፣ ያስቀደምከውን ማዘግየት እስከማልወድ ድረስ በተወሰነልኝ ነገር ላይ በረከት አድርግልኝ።»
ኢብኑ ሱኒይ ዘግበውታል። አዝካር ላይ ኢማም ነወዊይ ጠቅሰውታል።
❤54👍9
ከተፈቃሪያችን [ﷺ] ጋር የተሰጠን ትልቁ የአላህ ፀጋ ከርሳቸው ጋር የተፈቀደልን ቅርበት ነው። ሶለዋት እና ሰላምታ ስናቀርብላቸው ይደርሳቸዋል። እርሳቸው ናፍቀናቸው አንብተዋል። እኛ የርሳቸው እጣ እርሳቸውም የኛ እድል እንደሆኑ ነግረውናል። የህይወት ውሏቸው፣ የአካል ገፅታቸው እና የቤተሰብ ግንኙነታቸው ሳይቀር ተሰንዶ ተዘግቦልናል። ከህይወታቸው ገፅታ እኛ ዘንድ ሳይደርስ ተዳፍኖ የቀረ የለም!
ስለዚህ ፍቅር ያለው ወዳጃቸው ከእቅፋቸው ሳይወጣ፣ ተዝካራቸው ከህይወት ማእዱ ሳይርቅ ይመላለስበታል። እነሆ ዛሬ ዝክረ ሂጅራቸው ድምቀታችን ይሆን ዘንድ አላህ አድርሶናል!
አልሐምዱሊላህ!
እናም አደራ የምላችሁ!…
ስለ ሂጅራቸው ለልጆቻቸን እንንገር። እለቱን ከታሪክ ዐውዱ ጋር አቆራኝተን ደማቅ ወጋችን እናድርገው። የመድረሳ ባለቤቶች፣ የመስጂድ አስተዳዳሪዎች፣ ዳዒዎች፣ የረሱልን ፍቅር በትውልድ ልብ ውስጥ መዝራት የሚሻ ሁሉ ዓመቱን ሁሉ ከህይወታቸው ክስተት እየቀዳ ይጠጣ። ለሌላውም ያጋራ። ከህይወት ቅኝታቸው የሚገኘውን አስተምህሮና ለዛ ይቋደስ!
እንኳን ለ1447 ኛው ዓመተ ሂጅራ አደረሳችሁ! የከርሞ ሰው ይበለን!
ስለዚህ ፍቅር ያለው ወዳጃቸው ከእቅፋቸው ሳይወጣ፣ ተዝካራቸው ከህይወት ማእዱ ሳይርቅ ይመላለስበታል። እነሆ ዛሬ ዝክረ ሂጅራቸው ድምቀታችን ይሆን ዘንድ አላህ አድርሶናል!
አልሐምዱሊላህ!
እናም አደራ የምላችሁ!…
ስለ ሂጅራቸው ለልጆቻቸን እንንገር። እለቱን ከታሪክ ዐውዱ ጋር አቆራኝተን ደማቅ ወጋችን እናድርገው። የመድረሳ ባለቤቶች፣ የመስጂድ አስተዳዳሪዎች፣ ዳዒዎች፣ የረሱልን ፍቅር በትውልድ ልብ ውስጥ መዝራት የሚሻ ሁሉ ዓመቱን ሁሉ ከህይወታቸው ክስተት እየቀዳ ይጠጣ። ለሌላውም ያጋራ። ከህይወት ቅኝታቸው የሚገኘውን አስተምህሮና ለዛ ይቋደስ!
እንኳን ለ1447 ኛው ዓመተ ሂጅራ አደረሳችሁ! የከርሞ ሰው ይበለን!
❤62👍8😍2
ከዓሹራእ ጾም ጋር የተያያዙ ዐስር ህግጋት: ‐
❶ የዓሹራ ጾም ያለፈውን ዓመት ኃጢኣት ያስምራል። ይህ ሲባል ተውበት የሚያሻቸውን ከባባድ ኃጢኣት ሳይሆን ቀላል (ሶጛኢር) ኃጢኣቶችን ነው።
❷ ዓሹራን መጾም የተወደደበት ምክንያት አላህ ነቢዩ ሙሳን (ዐለይሂስ‐ሰላም) እና ህዝባቸውን ከፊርዐውን ያዳነበት ቀን መሆኑን በማሰብ አላህን ማመስገን ነው።
❸ የዓሹራ ጾም ደረጃዎች ሦስት ናቸው። በላጩ አስቀድሞ አንድ ቀን ከበስተኋላውም አንድ ቀን በድምሩ ሦስት ቀን መጾም ነው።
ሁለተኛው ከበስተፊቱ ወይም አንድ ቀን ከበስተኋላው መጾም ነው። በድምሩ ሁለት ቀን መጾም።
ሦስተኛው ሁኔታ እራሱን የዓሹራን ቀን (ሙሐረም 10ን) መጾም ናቸው።
❹ ከበስተፊቱ ወይም/እና ከበስተኋላው አንድ ቀን መጾም የተወደደበት ምክንያት ከአይሁዶች ለመለየት ነው። እነርሱ የዓሹራን ቀን ብቻ ነው የሚጾሙት።
❺ በዓሹራ ቀን ከጾም ውጪ ከሌሎች የዓመቱ ቀናት በተለየ ሁኔታ የተደነገገ ምንም ዓይነት ዒባዳ የለም። ነገርግን ቤተሰብን በሚበላና በሚጠጣ ነገር ማስፋፋት (ማንበሻበሽ) እንደሚወደድ የሚገልፅ ሐዲስ ተዘግቧል። አብዝሃኞቹ ልሂቃንም በሐዲሱ ሠርተዋል። ከዚያ ውጪ ለእለቱ መታጠብ፣ ሽቶ መቀባባት፣ መኳል… ተወዳጅ ነው የሚሉ የቅጥፈት (መውዱዕ) ሐዲሶች ተዘግበዋል። መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
❻ ከረመዳን ወር በኋላ ለጾም የተወደዱ ወራት አሽሁሩል‐ሑሩም (የተከበሩት ወራት) ናቸው። ከነርሱ ደግሞ በላጩ ሙሐረም ነው። ከዚያም ረጀብ፣ ዙል‐ሒጃ፣ ዙል‐ቀዕዳ በተከታታይ ለጾም የተመረጡ ወራት ናቸው። ከአሽሁሩል‐ሑሩም ቀጥሎ ሸዕባን ምርጥ የጾም ወር ነው።
❼ በዓሹራ ቀን ለረመዳን ቀዷ ነይቶ የጾመ ሰው የሁለቱንም ጾሞች ምንዳ ያገኛል። ፈርዱ ከጫንቃው ላይ ይነሳል፤ ሱና የሆነውን የዓሹራን ምንዳ ያገኛል።
❽ የዓሹራን ቀን ከእለቱ የዙህር ወቅት በፊት ባለው ጊዜ ነይቶ መጾም ይቻላል። ይኸውም እንደማንኛውም ሱና ጾም ማለት ነው። በሌሊት ነይቶ ማደር ግዴታ አይደለም። እንደሚታወቀው ፈርድ ጾሞች ግን ለነገ ጾም ከመግሪብ እስከ ፈጅር ባለው ካልተነየተ አይሆንም።
❾ የዓሹራ ጾም ያመለጠው ሰው ቀዷ ቢያወጣው ይወደዳል። የሻፊዒያ መዝሀብ ዐሊሞች መደበኛ ጾሞችን ቀዷ ማውጣት እንደሚወደድ በግልፅ ፅፈዋል።
❿ በመሰረቱ ሴት ባሏ በሀገር እያለ ያለፍቃዱ መጾም አትችልም። ነገርግን በተለይ እንደ ዓሹራ በዓመት አንዴ የሚዘዋወሩ ቀናትን ለመጾም አለመከልከሉ ብቻ ይበቃታል። ስለዚህ በግልፅ መፍቀዱ ወይም ማስፈቀድ አያስፈልጋትም።
አላሁ አዕለም!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❶ የዓሹራ ጾም ያለፈውን ዓመት ኃጢኣት ያስምራል። ይህ ሲባል ተውበት የሚያሻቸውን ከባባድ ኃጢኣት ሳይሆን ቀላል (ሶጛኢር) ኃጢኣቶችን ነው።
❷ ዓሹራን መጾም የተወደደበት ምክንያት አላህ ነቢዩ ሙሳን (ዐለይሂስ‐ሰላም) እና ህዝባቸውን ከፊርዐውን ያዳነበት ቀን መሆኑን በማሰብ አላህን ማመስገን ነው።
❸ የዓሹራ ጾም ደረጃዎች ሦስት ናቸው። በላጩ አስቀድሞ አንድ ቀን ከበስተኋላውም አንድ ቀን በድምሩ ሦስት ቀን መጾም ነው።
ሁለተኛው ከበስተፊቱ ወይም አንድ ቀን ከበስተኋላው መጾም ነው። በድምሩ ሁለት ቀን መጾም።
ሦስተኛው ሁኔታ እራሱን የዓሹራን ቀን (ሙሐረም 10ን) መጾም ናቸው።
❹ ከበስተፊቱ ወይም/እና ከበስተኋላው አንድ ቀን መጾም የተወደደበት ምክንያት ከአይሁዶች ለመለየት ነው። እነርሱ የዓሹራን ቀን ብቻ ነው የሚጾሙት።
❺ በዓሹራ ቀን ከጾም ውጪ ከሌሎች የዓመቱ ቀናት በተለየ ሁኔታ የተደነገገ ምንም ዓይነት ዒባዳ የለም። ነገርግን ቤተሰብን በሚበላና በሚጠጣ ነገር ማስፋፋት (ማንበሻበሽ) እንደሚወደድ የሚገልፅ ሐዲስ ተዘግቧል። አብዝሃኞቹ ልሂቃንም በሐዲሱ ሠርተዋል። ከዚያ ውጪ ለእለቱ መታጠብ፣ ሽቶ መቀባባት፣ መኳል… ተወዳጅ ነው የሚሉ የቅጥፈት (መውዱዕ) ሐዲሶች ተዘግበዋል። መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
❻ ከረመዳን ወር በኋላ ለጾም የተወደዱ ወራት አሽሁሩል‐ሑሩም (የተከበሩት ወራት) ናቸው። ከነርሱ ደግሞ በላጩ ሙሐረም ነው። ከዚያም ረጀብ፣ ዙል‐ሒጃ፣ ዙል‐ቀዕዳ በተከታታይ ለጾም የተመረጡ ወራት ናቸው። ከአሽሁሩል‐ሑሩም ቀጥሎ ሸዕባን ምርጥ የጾም ወር ነው።
❼ በዓሹራ ቀን ለረመዳን ቀዷ ነይቶ የጾመ ሰው የሁለቱንም ጾሞች ምንዳ ያገኛል። ፈርዱ ከጫንቃው ላይ ይነሳል፤ ሱና የሆነውን የዓሹራን ምንዳ ያገኛል።
❽ የዓሹራን ቀን ከእለቱ የዙህር ወቅት በፊት ባለው ጊዜ ነይቶ መጾም ይቻላል። ይኸውም እንደማንኛውም ሱና ጾም ማለት ነው። በሌሊት ነይቶ ማደር ግዴታ አይደለም። እንደሚታወቀው ፈርድ ጾሞች ግን ለነገ ጾም ከመግሪብ እስከ ፈጅር ባለው ካልተነየተ አይሆንም።
❾ የዓሹራ ጾም ያመለጠው ሰው ቀዷ ቢያወጣው ይወደዳል። የሻፊዒያ መዝሀብ ዐሊሞች መደበኛ ጾሞችን ቀዷ ማውጣት እንደሚወደድ በግልፅ ፅፈዋል።
❿ በመሰረቱ ሴት ባሏ በሀገር እያለ ያለፍቃዱ መጾም አትችልም። ነገርግን በተለይ እንደ ዓሹራ በዓመት አንዴ የሚዘዋወሩ ቀናትን ለመጾም አለመከልከሉ ብቻ ይበቃታል። ስለዚህ በግልፅ መፍቀዱ ወይም ማስፈቀድ አያስፈልጋትም።
አላሁ አዕለም!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤40👍5
ቀናችንን በኢስቲግፋር ድምቀት እንጀምረው!…
ከአቡ ሙሳ አል‐አሽዓሪይ እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል: ‐
«ምን ጊዜም ንጋት ላይ በጠዋት መቶ ጊዜ ኢስቲግፋር ሳላደርግ ቀርቼ አላውቅም።»
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
ከአቡ ሙሳ አል‐አሽዓሪይ እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል: ‐
«ምን ጊዜም ንጋት ላይ በጠዋት መቶ ጊዜ ኢስቲግፋር ሳላደርግ ቀርቼ አላውቅም።»
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤35👍7
Tofik Bahiru
ASHURA 1447.pdf
ዐሹራ ነገ ነው። የቻልን ነገን እና ከነገ ወዲያን ጨምረን እንፁም። ስለ ዐሹራ ለልጆቻችን እንንገር። እንተዋወስ!
በዱዓ እንበርታ። ከአላህ በቀር ምንም ያልነበራቸውን ሰይዲና ሙሳ [ዐለይሂ ሰላም] ከዘመናቸው አምባገነን ጉልበተኛ ያዳነና ድል የሰጠ ጌታ ከርሱ በቀር ምንም የሌላቸውን የዘመናችን ድኩማንን ከጨቋኞቻቸው አድኖ ድሉን ይስጣቸው እያልን እንለምን።
በዱዓ እንበርታ። ከአላህ በቀር ምንም ያልነበራቸውን ሰይዲና ሙሳ [ዐለይሂ ሰላም] ከዘመናቸው አምባገነን ጉልበተኛ ያዳነና ድል የሰጠ ጌታ ከርሱ በቀር ምንም የሌላቸውን የዘመናችን ድኩማንን ከጨቋኞቻቸው አድኖ ድሉን ይስጣቸው እያልን እንለምን።
❤78👍2
ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ሐቅ እንዳላቸው ሁሉ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ የተጣለ መብት አላቸው።
ልጅ የተሰጣችሁ ወዳጆች!
አባቶች፣ እናቶች!
የልጆቻችሁን አካላዊ ፍላጎት ማሟላት ብቻ በቂ አይደለም። መብልና መጠጥ መድኅናቸውን አይጠብቅም። ስኬታቸውን አያረጋግጥም።
አካላዊ ፍላጎታቸውን ከማሟላት የላቀ ሌላ አሳሳቢ ግዴታ አለባችሁ። የሩሕ ቀለባቸውን የማቅረብ፣ የአኺራ ስንቃቸውን መስጠት አለባችሁ። ዲን እና ስነምግባር እንዲኖራቸው መርዳት ግዴታችሁ ነው!
ልጆቻችሁን ለእሳት ትታችሁ የምትድኑት እሳት አይኖርም!
:
«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡ በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ኀይለኞች የኾኑ መላእክት አልሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምጹም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፡፡»
ሱረቱ ተሕሪም፥ አንቀጽ 06
ልጅ የተሰጣችሁ ወዳጆች!
አባቶች፣ እናቶች!
የልጆቻችሁን አካላዊ ፍላጎት ማሟላት ብቻ በቂ አይደለም። መብልና መጠጥ መድኅናቸውን አይጠብቅም። ስኬታቸውን አያረጋግጥም።
አካላዊ ፍላጎታቸውን ከማሟላት የላቀ ሌላ አሳሳቢ ግዴታ አለባችሁ። የሩሕ ቀለባቸውን የማቅረብ፣ የአኺራ ስንቃቸውን መስጠት አለባችሁ። ዲን እና ስነምግባር እንዲኖራቸው መርዳት ግዴታችሁ ነው!
ልጆቻችሁን ለእሳት ትታችሁ የምትድኑት እሳት አይኖርም!
:
«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡ በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ኀይለኞች የኾኑ መላእክት አልሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምጹም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፡፡»
ሱረቱ ተሕሪም፥ አንቀጽ 06
❤42😢4