Forwarded from የረሕማን ስጦታ
❤11👍3😍1
Forwarded from Tofik Bahiru
የረጋ ወተት
ማንኛውም መስአላ ላይ አስተያየት ከመሰጠቱ በፊት አራት ሂደቶች መታለፍ አለበት:‐
⏸ ተክዪፉል መስአላ/ጥያቄውን መግለፅ
ጥያቄን ከመመለስ በፊት የጥያቄውን ሁለገብ የሚያሳይ ፍኖተ‐ካርታ ማውጣት ያስፈልጋል። ጥያቄው ከየት መጣ? ምን ዓይነት ዐውድ አለው? በየትኛው የኢስላም ክፍል ውስጥ የሚካተት ነው? የጥያቄው ዳራና ድንበሩ ምንድን ነው?… ወዘተ
ከዚህ በኋላ ምርምር፣ ጥናት፣ ክርክር ይደረጋል። የጥያቄው ካርታ ሳይወጣ የሚደረግ ጥናት፣ ውይይትና ክርክር ፋይዳ ቢስ ነው፤ ወይም ስህተት ላይ ይጥላል።
⏺ ተእሲሉል መስአላ/ከትክክለኛ የመረጃ ምንጮች ጋር ማጣመር
ይህ ሁለተኛው ሂደት ነው። በጥያቄው ላይ ወይም በተመሳሳይ ወይም በተቀራራቢ ርዕሶች ላይ የተጠቀሱ ቅዱሳን ጥቅሶችን መሰብሰብ ቀዳሚ ስራ ነው። ሁለገብ የመረጃ ሜኑ ማቅረብ ተገቢ ነው። ከዚያም መረጃዎቹ እንደየደረጃቸው ይዘረዘራሉ። ደካማ ነው ተብሎ ሳይጠቀስ የሚቀር መረጃ አይኖርም። ሁሉም ይጠቀሳል።
🈁 ተሕሊሉል መስኣላ/ትንታኔ መስጠት
የቀረቡት መረጃዎችን በማጤን የመስኣላውን ዐውድ የጠበቀ፣ ዳር ድንበሩን ያልዘነጋ ትንታኔ መስጠት። በዚህ እርከን ላይ አንድ ሺህ ዓይነት እርስ በርሳቸው የሚቃረኑ ምላሾች ሳይቀሩ ይቀርባሉ። ይደረደራሉ።
🔶 ኢስቲኽራጁ ነታኢጅ/ውጤት ወይም አቋምን ማውጣት
በዚህ እርከን መረጃዎች ከጥያቄዎቹ ዐውድ ጋር በተነፃፃሪ ይተቻሉ። በምርመራው መሰረት የወደቁና ያለፉ ሃሳቦች ወይም ምላሾች ተለይተው ይቀርባሉ። አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለሐቅ የቀረቡ ሃሳቦች በአጥኚው ግምገማ መሠረት በቅደም ተከተላቸው እንደ ጥንካሬያቸው ይፋ ይሆናሉ።
:
🔴 ሐቅን መመርመርና እውነትን ለማግኘት ይህ ሁሉ ድካም አለው። ካርታ ሳታወጡ ምላሹን ለመመለስ አትሞክሩ ለማለት ነው። ሂደቶቹን ዘሎ ብይን መስጠት ያለ ጊዜው መውለድ ነው! ያለ ጊዜ መውለድ መጨንገፍ ነው! አደጋ ነው! መክሸፍ ነው!…
ማንኛውም መስአላ ላይ አስተያየት ከመሰጠቱ በፊት አራት ሂደቶች መታለፍ አለበት:‐
⏸ ተክዪፉል መስአላ/ጥያቄውን መግለፅ
ጥያቄን ከመመለስ በፊት የጥያቄውን ሁለገብ የሚያሳይ ፍኖተ‐ካርታ ማውጣት ያስፈልጋል። ጥያቄው ከየት መጣ? ምን ዓይነት ዐውድ አለው? በየትኛው የኢስላም ክፍል ውስጥ የሚካተት ነው? የጥያቄው ዳራና ድንበሩ ምንድን ነው?… ወዘተ
ከዚህ በኋላ ምርምር፣ ጥናት፣ ክርክር ይደረጋል። የጥያቄው ካርታ ሳይወጣ የሚደረግ ጥናት፣ ውይይትና ክርክር ፋይዳ ቢስ ነው፤ ወይም ስህተት ላይ ይጥላል።
⏺ ተእሲሉል መስአላ/ከትክክለኛ የመረጃ ምንጮች ጋር ማጣመር
ይህ ሁለተኛው ሂደት ነው። በጥያቄው ላይ ወይም በተመሳሳይ ወይም በተቀራራቢ ርዕሶች ላይ የተጠቀሱ ቅዱሳን ጥቅሶችን መሰብሰብ ቀዳሚ ስራ ነው። ሁለገብ የመረጃ ሜኑ ማቅረብ ተገቢ ነው። ከዚያም መረጃዎቹ እንደየደረጃቸው ይዘረዘራሉ። ደካማ ነው ተብሎ ሳይጠቀስ የሚቀር መረጃ አይኖርም። ሁሉም ይጠቀሳል።
🈁 ተሕሊሉል መስኣላ/ትንታኔ መስጠት
የቀረቡት መረጃዎችን በማጤን የመስኣላውን ዐውድ የጠበቀ፣ ዳር ድንበሩን ያልዘነጋ ትንታኔ መስጠት። በዚህ እርከን ላይ አንድ ሺህ ዓይነት እርስ በርሳቸው የሚቃረኑ ምላሾች ሳይቀሩ ይቀርባሉ። ይደረደራሉ።
🔶 ኢስቲኽራጁ ነታኢጅ/ውጤት ወይም አቋምን ማውጣት
በዚህ እርከን መረጃዎች ከጥያቄዎቹ ዐውድ ጋር በተነፃፃሪ ይተቻሉ። በምርመራው መሰረት የወደቁና ያለፉ ሃሳቦች ወይም ምላሾች ተለይተው ይቀርባሉ። አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለሐቅ የቀረቡ ሃሳቦች በአጥኚው ግምገማ መሠረት በቅደም ተከተላቸው እንደ ጥንካሬያቸው ይፋ ይሆናሉ።
:
🔴 ሐቅን መመርመርና እውነትን ለማግኘት ይህ ሁሉ ድካም አለው። ካርታ ሳታወጡ ምላሹን ለመመለስ አትሞክሩ ለማለት ነው። ሂደቶቹን ዘሎ ብይን መስጠት ያለ ጊዜው መውለድ ነው! ያለ ጊዜ መውለድ መጨንገፍ ነው! አደጋ ነው! መክሸፍ ነው!…
❤26👍9
እለተ ረቡዕ በዙህር እና በዐስር መካከል ዱዓ ተቀባይነት አለው። በዚያ ላይ በዝናብ የሚደረግ ዱዓም ኢስቲጃባ ይከጀላል። በዱዓችሁ አስቡን!
❤61
ስለትዳር ስናስብ ለብዙ ነገሮች ትኩረት እንሰጣለን፣ ሰርጉ፣ ጥሎሹ፣ ኒካሁ፣ የቤት እቃው፣ መጋረጃው ምንጣፉ፣ ማንኪያው ሳይቀር ያሳስቡናል 😊 ያው እንደባለቤቱ የሚያስጨንቀውና የሚያሳስበው ነገር ቢለያይም!
በሰርግ ሰሞን ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ዋነኞቹን ኒካህ፣ ወሊማና የጫጉላ ምሽትን ሸሪዓዊ እይታ በዚህ ወር ውይይታችን ከኡስታዝ ቶፊቅ ባህሩ ጋር የምናደርግ ይሆናል።
የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ነሀሴ 10 እና 11 ከምሽቱ 3:30 ጀምረን እንሰየማለን 😊
እስከዛ ኮመንት ላይ በሚገኘው የቴሌግራም ሊንካችን አባል እየሆኑ ይጠብቁን 😊
https://www.tg-me.com/+X0y-TUg1v11hZDI0
በሰርግ ሰሞን ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ዋነኞቹን ኒካህ፣ ወሊማና የጫጉላ ምሽትን ሸሪዓዊ እይታ በዚህ ወር ውይይታችን ከኡስታዝ ቶፊቅ ባህሩ ጋር የምናደርግ ይሆናል።
የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ነሀሴ 10 እና 11 ከምሽቱ 3:30 ጀምረን እንሰየማለን 😊
እስከዛ ኮመንት ላይ በሚገኘው የቴሌግራም ሊንካችን አባል እየሆኑ ይጠብቁን 😊
https://www.tg-me.com/+X0y-TUg1v11hZDI0
❤40👍12
Audio
ጁሙዐ ቀን ከዐስር በኋላ
================
ኢማም አድ‐ዳረቁጥኒ፣ አልሐፊዝ አስ‐ሰኻዊ፣ ኢማም አል‐ገዛሊ እና ሌሎችም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«በጁሙዐ ቀን ሰማንያ ጊዜ በእኔ ላይ ሶለዋት ያደረገ ሰው የሰማንያ ዓመት ኃጢኣቱን አላህ ይምረዋል።»
ሰዎች «የአላህ መልክተኛ ሆይ! እንዴት ብለን ሶለዋት እናድርግቦት?» በማለት ጠየቁ።
እርሳቸውም: ‐ «እንደዚህ በል አሉ: ‐
" اللهُمَّ صَلِّ على مُحَمَّدٍ عَبْدِكَ ونَبِيِّكَ ورَسُولِكَ النَبِيِّ الأُمِّيِّ"
«አላሁም‐መ ሶሊ ዐላ ሙሐመዲን ዐብዲከ ወነቢይ‐ዪከ ወረሱሊከ አን‐ነቢይ‐ዪል ኡም‐ሚይ‐ይ»
ይህንን አንድ ብለህ ቁጠር።»
:
ሰማንያ ስትሞላ በአላህ መልክተኛ ላይ ሰላምታን በማድረግ ጨርስ። «ሶለ‐ለላሁ ዐለይሂ ወሰለም» በል።»
:
ያያያዝኩላችሁ የድምፅ ፋይል በዘመናችን ከነበሩ ታላላቅ የተሰዉፍ ሰዎች መካከል የነበሩት ሸይኽ ረጀብ ዲብ ከሙሪዶቻቸው ጋር ሶለዋት ሲያደርጉ የተቀረፀ ነው። ትንፋሻቸው ወኔያችንን ከቀሰቀሰ በማለት የተለጠፈ ነው!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/1198
================
ኢማም አድ‐ዳረቁጥኒ፣ አልሐፊዝ አስ‐ሰኻዊ፣ ኢማም አል‐ገዛሊ እና ሌሎችም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«በጁሙዐ ቀን ሰማንያ ጊዜ በእኔ ላይ ሶለዋት ያደረገ ሰው የሰማንያ ዓመት ኃጢኣቱን አላህ ይምረዋል።»
ሰዎች «የአላህ መልክተኛ ሆይ! እንዴት ብለን ሶለዋት እናድርግቦት?» በማለት ጠየቁ።
እርሳቸውም: ‐ «እንደዚህ በል አሉ: ‐
" اللهُمَّ صَلِّ على مُحَمَّدٍ عَبْدِكَ ونَبِيِّكَ ورَسُولِكَ النَبِيِّ الأُمِّيِّ"
«አላሁም‐መ ሶሊ ዐላ ሙሐመዲን ዐብዲከ ወነቢይ‐ዪከ ወረሱሊከ አን‐ነቢይ‐ዪል ኡም‐ሚይ‐ይ»
ይህንን አንድ ብለህ ቁጠር።»
:
ሰማንያ ስትሞላ በአላህ መልክተኛ ላይ ሰላምታን በማድረግ ጨርስ። «ሶለ‐ለላሁ ዐለይሂ ወሰለም» በል።»
:
ያያያዝኩላችሁ የድምፅ ፋይል በዘመናችን ከነበሩ ታላላቅ የተሰዉፍ ሰዎች መካከል የነበሩት ሸይኽ ረጀብ ዲብ ከሙሪዶቻቸው ጋር ሶለዋት ሲያደርጉ የተቀረፀ ነው። ትንፋሻቸው ወኔያችንን ከቀሰቀሰ በማለት የተለጠፈ ነው!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/1198
❤34👍10
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
«ورحمَتِي وَسِعت كُلَّ شَيء».
«ችሮታየም [እዝነቴ] ነገሩን ሁሉ ሰፋች፡፡»
:
የአላህ ረሕመት ሰይዲና ሙሐመድ [ﷺ] ናቸው። አላህ ለዓለማት እዝነት እና ችሮታ አድርጎ ልኳቸዋል!…
«ችሮታየም [እዝነቴ] ነገሩን ሁሉ ሰፋች፡፡»
:
የአላህ ረሕመት ሰይዲና ሙሐመድ [ﷺ] ናቸው። አላህ ለዓለማት እዝነት እና ችሮታ አድርጎ ልኳቸዋል!…
❤40👍1
Audio
📚አል‐አዝካር ሚን ከላሚ ሰይዲል‐አብራር
📗 ክፍል አራት:‐ የመልካም ስራን ትሩፋት የሰማ ሰው፣ በዶዒፍ ሐዲስ መስራት፣ በቀልብና በምላስ አላህን መዝከር
📆 ነሐሴ 13/ 2017 ዓ. ል.
📗 ክፍል አራት:‐ የመልካም ስራን ትሩፋት የሰማ ሰው፣ በዶዒፍ ሐዲስ መስራት፣ በቀልብና በምላስ አላህን መዝከር
📆 ነሐሴ 13/ 2017 ዓ. ል.
❤11
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
«ማንም ሰው ቢሆን በርሳቸው ደጃፍ እስካላለፈ ድረስ የተባረረ ነው። በርሳቸው ቅ ጎዳና ተጉዞ ካልሆነ በስተቀር [ደረስኩ ያለ] ሁሉ [የውሃ ሽታ] ነው።»
ሰይድ ዶ/ር ሙሐመድ አል‐ዐለዊይ [ረሒመሁላህ]
ሰይድ ዶ/ር ሙሐመድ አል‐ዐለዊይ [ረሒመሁላህ]
❤34😢6👍2
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
ወዳጅ የወደደውን አካል ብርቅታ ሲያይ፣ ከወዳጁ ሀገር ሽው የሚል ነፋስ ሲያገኘው ወይም የምናብ ውልብታው ሲጋልበው ስለሚወደው መለፈፍ ያሰኘዋል። ያለ ምርጫው ልሳኑ በቃላት ሰልፍ ይንጋጋል። ስለሐቢቡ በሚያስወራ ሱስ ይለከፋል!
ይህ ተፈጥሯዊ ነው! ለማንኛውም ተወዳጅ ይሰራል!…
:
ተወዳጁ በቀልብ ውስጥ የተንሰራፋ፣ የነፍሳችን መስፍን፣ የሩሓችን እርካታ #ሙሐመድ [ﷺ] ሲሆኑ ደግሞ ሌላ ነው!
እንኳን ሰበብ አግኝተን ንጋትና ምሽቱ፣ የቀን እና የሌሊት መፈራረቅ እንኳን እርሳቸውን ያስታውሰናል። በየሶላቱ ባለው ሶለዋት እናስባቸዋለን። ሁሌም ከኛ ጋር አሉ!
:
እነሆ አሁን ደግሞ ሌላ ሰበብ አገኘን። የውልደታቸውን ብስራት የሚዘክረን ወር ገባልን። ረቢዑን‐ነቢይ [ﷺ]!
መልካም ነገሮችን የምንከስብበት፣ ለተወዳጃችን ክብርና ፍቅር የምንጨምርበት ወር ያድርግልን!
ይህ ተፈጥሯዊ ነው! ለማንኛውም ተወዳጅ ይሰራል!…
:
ተወዳጁ በቀልብ ውስጥ የተንሰራፋ፣ የነፍሳችን መስፍን፣ የሩሓችን እርካታ #ሙሐመድ [ﷺ] ሲሆኑ ደግሞ ሌላ ነው!
እንኳን ሰበብ አግኝተን ንጋትና ምሽቱ፣ የቀን እና የሌሊት መፈራረቅ እንኳን እርሳቸውን ያስታውሰናል። በየሶላቱ ባለው ሶለዋት እናስባቸዋለን። ሁሌም ከኛ ጋር አሉ!
:
እነሆ አሁን ደግሞ ሌላ ሰበብ አገኘን። የውልደታቸውን ብስራት የሚዘክረን ወር ገባልን። ረቢዑን‐ነቢይ [ﷺ]!
መልካም ነገሮችን የምንከስብበት፣ ለተወዳጃችን ክብርና ፍቅር የምንጨምርበት ወር ያድርግልን!
❤63😍4🤔1
Forwarded from Tofik Bahiru
በውልደታቸው ወር ሰዎችን ወደ መልክተኛው [ﷺ] እልፍኝ የምናስገባ አሳላፊዎች፣ ማረፊያ አልባ ቀልቦችን በጊቢያቸው እንዲረጉ የምናደርግ አገልጋዮች እንሁን።
የተፈቃሪው ነቢይ [ﷺ] አገልጋይ እንደመሆን የተቀደሰ ስራ የለም። ልቅናቸውን እና የነጠረው ስብእናቸውን እንደማናኘት ክቡር ሙያ የለም።
ልቦችን ከተፈጥሯቸው ጋር ማስታረቅ ማለት ነው። በሙሉ ፍቅርና ታዛዥነት ወደ ሐድራቸው እንዲዞሩ ማቅናት ነው።
ለዚህ ክብር የሚታጨው በሙሐባ የታጨቀ ቀልብ ባለቤት ብቻ ነው። ፍቅር የልቡናውን ማእከል ተቆናጦ፣ ፍካሬውን የተቆጣጠረው ሰው ሙያ ነው። ሰዎች ወዳጁን እንዲወዱለት ማድረግ የመጨረሻው መሻቱ የሆነ ሰው ዓላማ ነው!
በዚህ ወር ከሌላ ጊዜ የበለጠ ስለርሳቸው እናውራ። ለልጆቻችን፣ ቤታችን ለሚዘይሩን እንግዶች፣ ለልጆቻችን፣ ላገኘነው ሁሉ ስለርሳቸው እንንገር!
:
#ረቢዑን‐ነቢይ [ﷺ]
የተፈቃሪው ነቢይ [ﷺ] አገልጋይ እንደመሆን የተቀደሰ ስራ የለም። ልቅናቸውን እና የነጠረው ስብእናቸውን እንደማናኘት ክቡር ሙያ የለም።
ልቦችን ከተፈጥሯቸው ጋር ማስታረቅ ማለት ነው። በሙሉ ፍቅርና ታዛዥነት ወደ ሐድራቸው እንዲዞሩ ማቅናት ነው።
ለዚህ ክብር የሚታጨው በሙሐባ የታጨቀ ቀልብ ባለቤት ብቻ ነው። ፍቅር የልቡናውን ማእከል ተቆናጦ፣ ፍካሬውን የተቆጣጠረው ሰው ሙያ ነው። ሰዎች ወዳጁን እንዲወዱለት ማድረግ የመጨረሻው መሻቱ የሆነ ሰው ዓላማ ነው!
በዚህ ወር ከሌላ ጊዜ የበለጠ ስለርሳቸው እናውራ። ለልጆቻችን፣ ቤታችን ለሚዘይሩን እንግዶች፣ ለልጆቻችን፣ ላገኘነው ሁሉ ስለርሳቸው እንንገር!
:
#ረቢዑን‐ነቢይ [ﷺ]
❤53😍3👍1