Forwarded from የረሕማን ስጦታ
«[ዐረቦች ዘንድ] በተከበሩት ሌሎች ወራት ሳይሆን በወርሀ ረቢዐል‐አወል መወለዳቸው እርሳቸው በዘመናት ክብር የሚከበሩ ሳይሆኑ ዘመን በእርሳቸው እንደሚከበር ያመለክታል።»
ኢማም ኢብኑ ሐጀር [ረሒመሁላህ]
ኢማም ኢብኑ ሐጀር [ረሒመሁላህ]
❤39👍5
https://www.tg-me.com/mercy_to_the_worlds
👆ከላይ ያለው ሊንክ ስለ የዓለማቱ እዝነት ብቻ እያወራን ፍቅርና ናፍቆትን የምናብሰለስልበት ቻናል ነው። ተቀላቀሉን። ለሌሎችም ሼር አድርጉልን። ባረከላሁ ፊኩም!
👆ከላይ ያለው ሊንክ ስለ የዓለማቱ እዝነት ብቻ እያወራን ፍቅርና ናፍቆትን የምናብሰለስልበት ቻናል ነው። ተቀላቀሉን። ለሌሎችም ሼር አድርጉልን። ባረከላሁ ፊኩም!
Telegram
የረሕማን ስጦታ
{ وَما أَرسَلناكَ إِلّا رَحمَةً لِلعالَمينَ }[ الأنبياء: ١٠٧ ]
«(ሙሐመድ ሆይ!) ለዓለማትም እዝነት አድርገን እንጅ አልላክንህም፡፡»
«(ሙሐመድ ሆይ!) ለዓለማትም እዝነት አድርገን እንጅ አልላክንህም፡፡»
👍9
የተወዳጁ ነቢይ [ﷺ] ወሬ ሲነሳ የሙእሚኖች ልብ፣ የተቂዮች መንፈስ፣ የሙሒቦች ስሜት ይነቃል።
ሲራቸውን ሲሰሙ እዝነ ህሊናቸው በናፍቆት ይፈነድቃል። ስለ ግሩም ጠባያቸው ለማድመጥ ሁለመናቸው ይንጠራራል። የላቀው ስብእናቸውን ለማድነቅ ነፍሳቸው ይንገበገባል። የተከበረው አደባቸውን ለማሰብ አይምሯቸው ይተጋል። ሁሌም በየአመቱ የውልደታቸውን በረከት ለመዝከር ወዳጅ ሁሉ ይሰበሰባል!
ይህ መልካም ልማዳቸው ነው። የዝንተ ዓለም ደስታቸውን በተለየ ሁኔታ በውልደት ወራቸው ያስታውሳሉ። ወደ ምድር መምጣታቸውን እንደ አዲስ ያስቡና እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም እንደ አዲስ በድጋሚ ይፈነድቃሉ። በየሀገሩ ዚክራ ነቢይ [ﷺ] ይደራል። ህፃን አዋቂው ሁላ በስማቸውና በግብራቸው ትውስታ ይነቃነቃል። ይህ ዘመን ጠገብ የመልካሞቹ ውርስ ነው!
ከወርሀ ረቢዕ ሁሉም ድርሻውን ይወስዳል። በየፈርጁ እንደሚሰራው ስራ ይለያያል። ቀጥ ያለውን የመልካሞቹን ጎዳና ይዞ የሚሄድ አለ። ከጠፊዎች ጋር የሚጠፋ ሸህዋ አምላኩም ሞልቷል። በመካከልም ልብንና አዕምሮን ጠቅልሎ በሚወስደው የውልደታቸው ክስተት ሰሞን እንኳን ልቡን በሌላ ነገር፣ በሃሳብ ጅምናስቲክ እና በቡድን ግብግብ የሚጠመድም አለ። እኛ ግን መልካም እንነይት። ስለሳቸው ሲራ አብዝተን ለማጥናት፣ ስብዕናቸውን በተለየ ሁኔታ ለመሰልጠን፣ የሶለዋት ክምችታችንን ለማድለብና መልእክታቸውን ለሌላ ለማድረስ።…
{ قُل كُلٌّ يَعمَلُ عَلى شاكِلَتِهِ فَرَبُّكُم أَعلَمُ بِمَن هُوَ أَهدى سَبيلًا }[ الإسراء: ٨٤ ]
«ሁሉም በሚመስለው መንገዱ ላይ ይሠራል፡፡ ጌታችሁም እርሱ መንገዱ ቀጥተኛ የኾነውን ሰው ዐዋቂ ነው በላቸው፡፡»
ዛሬ ረቢዑል‐አወል ሰባት ብሏል!
እንኳን ለደማቁ ወር ለረቢዑን‐ነቢይ አደረሳችሁ!
ሲራቸውን ሲሰሙ እዝነ ህሊናቸው በናፍቆት ይፈነድቃል። ስለ ግሩም ጠባያቸው ለማድመጥ ሁለመናቸው ይንጠራራል። የላቀው ስብእናቸውን ለማድነቅ ነፍሳቸው ይንገበገባል። የተከበረው አደባቸውን ለማሰብ አይምሯቸው ይተጋል። ሁሌም በየአመቱ የውልደታቸውን በረከት ለመዝከር ወዳጅ ሁሉ ይሰበሰባል!
ይህ መልካም ልማዳቸው ነው። የዝንተ ዓለም ደስታቸውን በተለየ ሁኔታ በውልደት ወራቸው ያስታውሳሉ። ወደ ምድር መምጣታቸውን እንደ አዲስ ያስቡና እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም እንደ አዲስ በድጋሚ ይፈነድቃሉ። በየሀገሩ ዚክራ ነቢይ [ﷺ] ይደራል። ህፃን አዋቂው ሁላ በስማቸውና በግብራቸው ትውስታ ይነቃነቃል። ይህ ዘመን ጠገብ የመልካሞቹ ውርስ ነው!
ከወርሀ ረቢዕ ሁሉም ድርሻውን ይወስዳል። በየፈርጁ እንደሚሰራው ስራ ይለያያል። ቀጥ ያለውን የመልካሞቹን ጎዳና ይዞ የሚሄድ አለ። ከጠፊዎች ጋር የሚጠፋ ሸህዋ አምላኩም ሞልቷል። በመካከልም ልብንና አዕምሮን ጠቅልሎ በሚወስደው የውልደታቸው ክስተት ሰሞን እንኳን ልቡን በሌላ ነገር፣ በሃሳብ ጅምናስቲክ እና በቡድን ግብግብ የሚጠመድም አለ። እኛ ግን መልካም እንነይት። ስለሳቸው ሲራ አብዝተን ለማጥናት፣ ስብዕናቸውን በተለየ ሁኔታ ለመሰልጠን፣ የሶለዋት ክምችታችንን ለማድለብና መልእክታቸውን ለሌላ ለማድረስ።…
{ قُل كُلٌّ يَعمَلُ عَلى شاكِلَتِهِ فَرَبُّكُم أَعلَمُ بِمَن هُوَ أَهدى سَبيلًا }[ الإسراء: ٨٤ ]
«ሁሉም በሚመስለው መንገዱ ላይ ይሠራል፡፡ ጌታችሁም እርሱ መንገዱ ቀጥተኛ የኾነውን ሰው ዐዋቂ ነው በላቸው፡፡»
ዛሬ ረቢዑል‐አወል ሰባት ብሏል!
እንኳን ለደማቁ ወር ለረቢዑን‐ነቢይ አደረሳችሁ!
❤31
Audio
📚አል‐አዝካር ሚን ከላሚ ሰይዲል‐አብራር
📗 ክፍል አምስት:‐ በፈዷኢሉል አዕማል መስራት፣ ሒለቁ ዚክር፣ የቀልብና የልሳን ዚክር፣ የዚክር ፈዳኢል፣ የዛኪር ሁኔታው
📆 ነሐሴ 24/ 2017 ዓ. ል.
📗 ክፍል አምስት:‐ በፈዷኢሉል አዕማል መስራት፣ ሒለቁ ዚክር፣ የቀልብና የልሳን ዚክር፣ የዚክር ፈዳኢል፣ የዛኪር ሁኔታው
📆 ነሐሴ 24/ 2017 ዓ. ል.
❤15
{ لَقَد مَنَّ اللَّهُ عَلَى المُؤمِنينَ إِذ بَعَثَ فيهِم رَسولًا مِن أَنفُسِهِم يَتلو عَلَيهِم آياتِهِ وَيُزَكّيهِم وَيُعَلِّمُهُمُ الكِتابَ وَالحِكمَةَ وَإِن كانوا مِن قَبلُ لَفي ضَلالٍ مُبينٍ }[ آل عمران: ١٦٤ ]
«አላህ በምእምናን ላይ ከጎሳቸው የኾነን፤ በእነርሱ ላይ አንቀጾቹን የሚያነብ፣ የሚጠራቸውም፣ መጽሐፍንና ጥበብን የሚያስተምራቸውም የኾነን መልእክተኛ በውስጣቸው በላከ ጊዜ፤ በእርግጥ ለገሰላቸው፡፡ እነርሱም ከዚያ በፊት በግልጽ ስህተት ውስጥ ነበሩ፡፡»
:
«የሚያጠራቸው» ሲል…
ማጥራት የርሳቸው ስልጣንና ስራ መስሎ ቀርቧል። በእርግጥ ቀጥተኛ ስራቸው ሰዎች የሚጠሩበትን እውቀት በማስተማር ሰዎች እንዲጠሩ ማገዝ ነው። በዚሁ አያ ላይ «መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራቸውን» ሲል ይህንኑ ያንፀባርቃል። የማጥራት ሂደቱ ሙእሚኖችን የሚለውጡት፣ ከሺርክ እና ከኃጢኣት ጠርተው በኢማን ከፍታ ላይ እንዲያርፉ የሚያደርጓቸው መጽሐፉን እና ጥበብን በመጠቀም ነው።…
ይህ አንድ አካሄድ ነው!…
በእርግጥ "ማጥራት" የርሳቸው ስራ ሆኖ የቀረበበት ሌላም መንገድ ይኖራል።…
ወጣቱ ልጅ ዝሙት እንዲፈቀድለት ፈልጎ እርሳቸው ዘንድ መጣና በተከበረው እጃቸው ዳብሰው ዱዓ አደረጉለት። ወዲያው በልቡ ውስጥ ተጎዝጉዞ የነበረው ቆሻሻ ቡንን አለ። ወስዋሱም ጠፋ። ቀልቡ ተረጋጋ።
ከሱማማ ኢብኑ ኡሳል ጋር የነበራቸው ረዥም ውይይት፣ ምርኮኛ ሆኖ በእጃቸው ገብቶ ሳለ በተደጋጋሚ የነበራቸው ግንኙነት ቀልቡን አጠራለት። በኢማን ላይ እንዲቆምም ብርታት ሆነው።
በርካታ ሰዎችን በእጃቸው ደረታቸውን በመዳበስ ብቻ በነፍሶቻቸው ውስጥ የነበረን ቆሻሻ ያፀዱላቸዋል። ለከፍታና ለፅናት ያበቋቸውም ነበር።
ከዚህ ውጪ እጅግ የታወቁ በርካታ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት በእጃቸው በመዳበስ ብቻ በሶሓቦቻቸው ላይ የሚከሰቱ አካላዊ በሽታዎችን ያክሙ እንደነበር ተዘግቧል።
እናም ከመጽሐፍ [ቁርኣን] መምህርነታቸው ባሻገር ሁለመናቸው ቀልብን የሚያፀዳ ምትሀት ባለቤትም ነበር። ስለዚህም "ማጥራት" የርሳቸው ቀጥተኛ ተግባር ተደርጎ በቁርኣን ተጠቅሷል ማለትም እንችላለን። አላሁ አዕለም!
:
وصلى الله وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه.
#ረቢዑን‐ነቢይ
«አላህ በምእምናን ላይ ከጎሳቸው የኾነን፤ በእነርሱ ላይ አንቀጾቹን የሚያነብ፣ የሚጠራቸውም፣ መጽሐፍንና ጥበብን የሚያስተምራቸውም የኾነን መልእክተኛ በውስጣቸው በላከ ጊዜ፤ በእርግጥ ለገሰላቸው፡፡ እነርሱም ከዚያ በፊት በግልጽ ስህተት ውስጥ ነበሩ፡፡»
:
«የሚያጠራቸው» ሲል…
ማጥራት የርሳቸው ስልጣንና ስራ መስሎ ቀርቧል። በእርግጥ ቀጥተኛ ስራቸው ሰዎች የሚጠሩበትን እውቀት በማስተማር ሰዎች እንዲጠሩ ማገዝ ነው። በዚሁ አያ ላይ «መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራቸውን» ሲል ይህንኑ ያንፀባርቃል። የማጥራት ሂደቱ ሙእሚኖችን የሚለውጡት፣ ከሺርክ እና ከኃጢኣት ጠርተው በኢማን ከፍታ ላይ እንዲያርፉ የሚያደርጓቸው መጽሐፉን እና ጥበብን በመጠቀም ነው።…
ይህ አንድ አካሄድ ነው!…
በእርግጥ "ማጥራት" የርሳቸው ስራ ሆኖ የቀረበበት ሌላም መንገድ ይኖራል።…
ወጣቱ ልጅ ዝሙት እንዲፈቀድለት ፈልጎ እርሳቸው ዘንድ መጣና በተከበረው እጃቸው ዳብሰው ዱዓ አደረጉለት። ወዲያው በልቡ ውስጥ ተጎዝጉዞ የነበረው ቆሻሻ ቡንን አለ። ወስዋሱም ጠፋ። ቀልቡ ተረጋጋ።
ከሱማማ ኢብኑ ኡሳል ጋር የነበራቸው ረዥም ውይይት፣ ምርኮኛ ሆኖ በእጃቸው ገብቶ ሳለ በተደጋጋሚ የነበራቸው ግንኙነት ቀልቡን አጠራለት። በኢማን ላይ እንዲቆምም ብርታት ሆነው።
በርካታ ሰዎችን በእጃቸው ደረታቸውን በመዳበስ ብቻ በነፍሶቻቸው ውስጥ የነበረን ቆሻሻ ያፀዱላቸዋል። ለከፍታና ለፅናት ያበቋቸውም ነበር።
ከዚህ ውጪ እጅግ የታወቁ በርካታ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት በእጃቸው በመዳበስ ብቻ በሶሓቦቻቸው ላይ የሚከሰቱ አካላዊ በሽታዎችን ያክሙ እንደነበር ተዘግቧል።
እናም ከመጽሐፍ [ቁርኣን] መምህርነታቸው ባሻገር ሁለመናቸው ቀልብን የሚያፀዳ ምትሀት ባለቤትም ነበር። ስለዚህም "ማጥራት" የርሳቸው ቀጥተኛ ተግባር ተደርጎ በቁርኣን ተጠቅሷል ማለትም እንችላለን። አላሁ አዕለም!
:
وصلى الله وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه.
#ረቢዑን‐ነቢይ
❤20👍1😍1
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
❤50😍7
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
ለመውሊድ ቀን የሚሆን መልካም ሃሳብ ልንገራችሁ!
ቤተሰቦቻችንን ሰብስበን የላቀውን የውልደት ትርክታቸውን መንገር። በሰይዳችን [ﷺ] መምጣት የሰው ልጆች ያገኙትን ፀጋ ማብራራት። የተወሰኑ መድሖችን በጋራ ማንጎራጎር። የተለየና የሚወዱትን ምግብ ማብላት።…
ይህ በልጆቻችን ልብ ውስጥ የፍቅር ስሜት ያነብራል። ለታላቁ ነቢይ [ﷺ] ያላቸውን ክብር ይጨምራል። የአላህን ፀጋዎች አስታውሶ የማመስገን ዝንባሌ ያድጋል። እድሜ ልካቸውን በነቢይ [ﷺ] ፍቅር ላይ እንዲፀኑ ንቅናቄ ይፈጥራል!
እኛ በሙረቢ ሸይኾቻችን በዚህ መልኩ ታንፀን ጠቅሞናል። እናንተ ደግሞ ለልጆቻችሁ ሞክሩት!
እንኳን አደረሳችሁ!
ቤተሰቦቻችንን ሰብስበን የላቀውን የውልደት ትርክታቸውን መንገር። በሰይዳችን [ﷺ] መምጣት የሰው ልጆች ያገኙትን ፀጋ ማብራራት። የተወሰኑ መድሖችን በጋራ ማንጎራጎር። የተለየና የሚወዱትን ምግብ ማብላት።…
ይህ በልጆቻችን ልብ ውስጥ የፍቅር ስሜት ያነብራል። ለታላቁ ነቢይ [ﷺ] ያላቸውን ክብር ይጨምራል። የአላህን ፀጋዎች አስታውሶ የማመስገን ዝንባሌ ያድጋል። እድሜ ልካቸውን በነቢይ [ﷺ] ፍቅር ላይ እንዲፀኑ ንቅናቄ ይፈጥራል!
እኛ በሙረቢ ሸይኾቻችን በዚህ መልኩ ታንፀን ጠቅሞናል። እናንተ ደግሞ ለልጆቻችሁ ሞክሩት!
እንኳን አደረሳችሁ!
❤133👍2
Forwarded from Tofik Bahiru
አቡ ሰዒድ አል‐ኹድሪይ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንዲህ ይላሉ: ‐
«የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ክብ ሰርተው የተቀመጡ ባልደረቦቻቸው ዘንድ ወጡና «ለምን ተቀመጣችሁ?» አሏቸው።
የተከበሩት ሶሐቦችም: ‐ «አላህን ልንዘክር፣ ለኢስላም ስለመራንና በርሱም ችሮታውን ስላኖረልን ልናመሰግነው ተቀምጠናል።» በማለት መለሱ።
እርሳቸውም: ‐ «በአላህ ማሉ! የተቀመጣችሁት ከዚህ ውጪ ሌላ ምክንያት አይደለም?» አሉ።
ሶሐቦቹም «ወላሂ! ከርሱ ውጪ በሌላ ምክንያት አልተቀመጥንም።» በማለት መለሱ።
የአላህ መልክተኛም [ﷺ] እንዲህ አሉ: ‐ «እኔም ተጠራጥሬያችሁ አላስማልኳችሁም። ነገርግን ጂብሪል እኔ ዘንድ መጣና አላህ እናንተን [በማወደስ] መላኢካዎች ላይ እየፎከረ እንደሆነ ነግሮኝ ነው!»
ሙስሊም ዘግበውታል።
:
ለመላው ወዳጆቼና ተከታታዮቼ እንኳን ለታላቁ የነቢዩ [ﷺ] ዝክረ መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ!
«የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ክብ ሰርተው የተቀመጡ ባልደረቦቻቸው ዘንድ ወጡና «ለምን ተቀመጣችሁ?» አሏቸው።
የተከበሩት ሶሐቦችም: ‐ «አላህን ልንዘክር፣ ለኢስላም ስለመራንና በርሱም ችሮታውን ስላኖረልን ልናመሰግነው ተቀምጠናል።» በማለት መለሱ።
እርሳቸውም: ‐ «በአላህ ማሉ! የተቀመጣችሁት ከዚህ ውጪ ሌላ ምክንያት አይደለም?» አሉ።
ሶሐቦቹም «ወላሂ! ከርሱ ውጪ በሌላ ምክንያት አልተቀመጥንም።» በማለት መለሱ።
የአላህ መልክተኛም [ﷺ] እንዲህ አሉ: ‐ «እኔም ተጠራጥሬያችሁ አላስማልኳችሁም። ነገርግን ጂብሪል እኔ ዘንድ መጣና አላህ እናንተን [በማወደስ] መላኢካዎች ላይ እየፎከረ እንደሆነ ነግሮኝ ነው!»
ሙስሊም ዘግበውታል።
:
ለመላው ወዳጆቼና ተከታታዮቼ እንኳን ለታላቁ የነቢዩ [ﷺ] ዝክረ መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ!
❤73
Audio
ጁሙዐ ቀን ከዐስር በኋላ
================
ኢማም አድ‐ዳረቁጥኒ፣ አልሐፊዝ አስ‐ሰኻዊ፣ ኢማም አል‐ገዛሊ እና ሌሎችም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«በጁሙዐ ቀን ሰማንያ ጊዜ በእኔ ላይ ሶለዋት ያደረገ ሰው የሰማንያ ዓመት ኃጢኣቱን አላህ ይምረዋል።»
ሰዎች «የአላህ መልክተኛ ሆይ! እንዴት ብለን ሶለዋት እናድርግቦት?» በማለት ጠየቁ።
እርሳቸውም: ‐ «እንደዚህ በል አሉ: ‐
" اللهُمَّ صَلِّ على مُحَمَّدٍ عَبْدِكَ ونَبِيِّكَ ورَسُولِكَ النَبِيِّ الأُمِّيِّ"
«አላሁም‐መ ሶሊ ዐላ ሙሐመዲን ዐብዲከ ወነቢይ‐ዪከ ወረሱሊከ አን‐ነቢይ‐ዪል ኡም‐ሚይ‐ይ»
ይህንን አንድ ብለህ ቁጠር።»
:
ሰማንያ ስትሞላ በአላህ መልክተኛ ላይ ሰላምታን በማድረግ ጨርስ። «ሶለ‐ለላሁ ዐለይሂ ወሰለም» በል።»
:
ያያያዝኩላችሁ የድምፅ ፋይል በዘመናችን ከነበሩ ታላላቅ የተሰዉፍ ሰዎች መካከል የነበሩት ሸይኽ ረጀብ ዲብ ከሙሪዶቻቸው ጋር ሶለዋት ሲያደርጉ የተቀረፀ ነው። ትንፋሻቸው ወኔያችንን ከቀሰቀሰ በማለት የተለጠፈ ነው!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/1198
================
ኢማም አድ‐ዳረቁጥኒ፣ አልሐፊዝ አስ‐ሰኻዊ፣ ኢማም አል‐ገዛሊ እና ሌሎችም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«በጁሙዐ ቀን ሰማንያ ጊዜ በእኔ ላይ ሶለዋት ያደረገ ሰው የሰማንያ ዓመት ኃጢኣቱን አላህ ይምረዋል።»
ሰዎች «የአላህ መልክተኛ ሆይ! እንዴት ብለን ሶለዋት እናድርግቦት?» በማለት ጠየቁ።
እርሳቸውም: ‐ «እንደዚህ በል አሉ: ‐
" اللهُمَّ صَلِّ على مُحَمَّدٍ عَبْدِكَ ونَبِيِّكَ ورَسُولِكَ النَبِيِّ الأُمِّيِّ"
«አላሁም‐መ ሶሊ ዐላ ሙሐመዲን ዐብዲከ ወነቢይ‐ዪከ ወረሱሊከ አን‐ነቢይ‐ዪል ኡም‐ሚይ‐ይ»
ይህንን አንድ ብለህ ቁጠር።»
:
ሰማንያ ስትሞላ በአላህ መልክተኛ ላይ ሰላምታን በማድረግ ጨርስ። «ሶለ‐ለላሁ ዐለይሂ ወሰለም» በል።»
:
ያያያዝኩላችሁ የድምፅ ፋይል በዘመናችን ከነበሩ ታላላቅ የተሰዉፍ ሰዎች መካከል የነበሩት ሸይኽ ረጀብ ዲብ ከሙሪዶቻቸው ጋር ሶለዋት ሲያደርጉ የተቀረፀ ነው። ትንፋሻቸው ወኔያችንን ከቀሰቀሰ በማለት የተለጠፈ ነው!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/1198
❤14
Al_Majdooja_tul_hasana_fil_istighasa_be_Asma_Allah_al_Husna_by_imam.pdf
234.7 KB
ከሶለዋታችን በኋላ የጁሙዐ ዱዓችንን በሰይዲ አል‐ኢማም ዩሱፍ አን‐ነብሃኒ ታዋቂ የአላህ ስሞች ዱዓ መድብል "አል‐ሙዝደወጀቱል‐ሐስናእ" ለፊለስጢን (ጋዛ) ወንድሞቻችን ነስር እንዲያገኙ እና በጉዳያቸው ላይ የአላህ እገዛ እንዲገባበት ዱዓ እናድርግ!
❤18😍6👍2
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
ኑሩ ሙሐመድ
[ክፍል ስድስት]
ንጹሁ/አጥ‐ጧሂር [ﷺ]
አካላቸው፣ ልብሳቸው፣ ቤታቸው እና ማረፊያቸው ሁሉ ንፁህ ነበር። አካላቸው ንፁህና የፀዳ ነበር። የሂንድን ገለፃ ከዚህ ቀደም አሳልፈነዋል:‐
"الأنور المتجرد"
«[ከፀጉር] የተራቆተው የአካል ክፍላቸው እጅግ አንፀባራቂ ነው።» በማለት ገልፀዋቸዋል።
ይህ የንፅህናቸው ምልክት ነው።
በቲርሚዚይ ዘገባ ከአቡ ጡፈይል እንደተገኘው:‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ቀይ የቀላቀለ ነጭ፣ ውብ፣ አንፀባራቂ እና ባለመካከለኛ ቁመት ናቸው።»
አሁንም ቲርሚዚይ ከኢብኑ አቢ ጁሕፋ አባታቸውን በመጥቀስ እንደዘገቡት እንዲህ ብለዋል:‐ «የአላህ መልክተኛን [ﷺ] ቀይ ሙሉ ልብስ ለብሰው አይቻቸዋለሁ። የባታቸውን ንጣት አሁን ድረስ የማየው ይመስለኛል።»
ልብሳቸው ከጉልበታቸው በታች የባታቸው አጋማሽ ድረስ ስለነበረ የተከበረ ባታቸውን አይተውታል።
የጠረናቸው ማራኪነት የአካላቸውን ንፅህና ይመሰክራል።
ከሰይዲና አነስ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ «ቀጭንም ሆነ ወፍራም ሐርን ነክቻለሁ፤ እንደ ነቢዩ [ﷺ] መዳፍ የለሰለሰ ግን አላገኘሁም። ሁሉንም ዓይነት ሽቶ አሽትቻለሁ እንደ ነቢዩ [ﷺ] ጠረን ማራኪ ግን አላገኘሁም።» ቡኻሪ ዘግበውታል።
አቡ ቂርሷፋ እንዲህ ይላሉ:‐
«እኔ፣ እናቴ እና አክስቴ የአላህ መልክተኛን [ﷺ] ቃል ተጋብተናቸው ተመለስን። ከዚያም እናቴና አክስቴ እንዲህ አሉ:‐ «ልጄ ሆይ! እንደዚህ አይነት ሰው አይተን አናውቅም። መልኩ የሚያምር፣ ልብሱ የፀዳ፣ ንግግሩ የለዘበ እንደርሱ አይነት ሰው አላየንም። ብርሃን ከአፉ የሚወጣ ይመስላል።»
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አካላቸው ጽዱ ነበር። ልብሳቸውም የጠራ ነበሩ። ከቤት ሲወጡም ሆነ ወደ ቤት ሲመለሱ ጥርሳቸውን ይፍቁ ነበር።
ለንፅሕና ያላቸውን ቦታ በትእዛዞቻቸውና በአስተምህሯቸው ፋና መገምገም እንችላለን!…
[ይቀጥላል]
[ክፍል ስድስት]
ንጹሁ/አጥ‐ጧሂር [ﷺ]
አካላቸው፣ ልብሳቸው፣ ቤታቸው እና ማረፊያቸው ሁሉ ንፁህ ነበር። አካላቸው ንፁህና የፀዳ ነበር። የሂንድን ገለፃ ከዚህ ቀደም አሳልፈነዋል:‐
"الأنور المتجرد"
«[ከፀጉር] የተራቆተው የአካል ክፍላቸው እጅግ አንፀባራቂ ነው።» በማለት ገልፀዋቸዋል።
ይህ የንፅህናቸው ምልክት ነው።
በቲርሚዚይ ዘገባ ከአቡ ጡፈይል እንደተገኘው:‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ቀይ የቀላቀለ ነጭ፣ ውብ፣ አንፀባራቂ እና ባለመካከለኛ ቁመት ናቸው።»
አሁንም ቲርሚዚይ ከኢብኑ አቢ ጁሕፋ አባታቸውን በመጥቀስ እንደዘገቡት እንዲህ ብለዋል:‐ «የአላህ መልክተኛን [ﷺ] ቀይ ሙሉ ልብስ ለብሰው አይቻቸዋለሁ። የባታቸውን ንጣት አሁን ድረስ የማየው ይመስለኛል።»
ልብሳቸው ከጉልበታቸው በታች የባታቸው አጋማሽ ድረስ ስለነበረ የተከበረ ባታቸውን አይተውታል።
የጠረናቸው ማራኪነት የአካላቸውን ንፅህና ይመሰክራል።
ከሰይዲና አነስ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ «ቀጭንም ሆነ ወፍራም ሐርን ነክቻለሁ፤ እንደ ነቢዩ [ﷺ] መዳፍ የለሰለሰ ግን አላገኘሁም። ሁሉንም ዓይነት ሽቶ አሽትቻለሁ እንደ ነቢዩ [ﷺ] ጠረን ማራኪ ግን አላገኘሁም።» ቡኻሪ ዘግበውታል።
አቡ ቂርሷፋ እንዲህ ይላሉ:‐
«እኔ፣ እናቴ እና አክስቴ የአላህ መልክተኛን [ﷺ] ቃል ተጋብተናቸው ተመለስን። ከዚያም እናቴና አክስቴ እንዲህ አሉ:‐ «ልጄ ሆይ! እንደዚህ አይነት ሰው አይተን አናውቅም። መልኩ የሚያምር፣ ልብሱ የፀዳ፣ ንግግሩ የለዘበ እንደርሱ አይነት ሰው አላየንም። ብርሃን ከአፉ የሚወጣ ይመስላል።»
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አካላቸው ጽዱ ነበር። ልብሳቸውም የጠራ ነበሩ። ከቤት ሲወጡም ሆነ ወደ ቤት ሲመለሱ ጥርሳቸውን ይፍቁ ነበር።
ለንፅሕና ያላቸውን ቦታ በትእዛዞቻቸውና በአስተምህሯቸው ፋና መገምገም እንችላለን!…
[ይቀጥላል]
❤20