Forwarded from የረሕማን ስጦታ
«በአላህ መልክተኛ [ﷺ] ማመንን ምሉእ ከሚያደርጉት ነገሮች መካከል:‐ በሰው ልጅ ገፅታ ላይ እንደርሳቸው ያለ ውበት የተሰበሰበበት ማንም አካል አለመኖሩን ማመን ይጠቀሳል። ምክንያቱም ውጫዊ ገፅታ የውስጥ ውበት እና የመልካም ጠባይም ምልክቶች ናቸው። በዚህ ረገድ ከርሳቸው በላይ ምልኣት ላይ የደረሰ፣ እንደውም የሚወዳደራቸው ሰው የለም። ስለዚህ የዚህ ምልኣት ምልክት የሆነው [ውብ ገጽታ] ላይም የሚደርስባቸው የለም።
ከዚህ በመነሳት ኢማም አል‐ቁርጡቢይ [ረሒመሁላህ] አንዳቸውን ዋቢ በማድረግ እንዲህ ብለዋል:‐ «ውበታቸው ሙሉ ለሙሉ አልተገለጠም። ውበታቸው ሙሉ በሙሉ ቢገለጥ ኖሮ ሶሐቦቹ እርሳቸውን መመልከት በተሳናቸው ነበር።»
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ [ረሒመሁላህ]
ከዚህ በመነሳት ኢማም አል‐ቁርጡቢይ [ረሒመሁላህ] አንዳቸውን ዋቢ በማድረግ እንዲህ ብለዋል:‐ «ውበታቸው ሙሉ ለሙሉ አልተገለጠም። ውበታቸው ሙሉ በሙሉ ቢገለጥ ኖሮ ሶሐቦቹ እርሳቸውን መመልከት በተሳናቸው ነበር።»
ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ [ረሒመሁላህ]
❤18😍2
ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ.) ዘውታሪው ብርሃን.pdf
1.7 MB
2004 በኢትዮጲያ አካባቢ የተከተበች ድርሰቴ ናት። ከ13 ዓመት በኋላ በዛሬው ተውፊቅ ባትታረምም አንብቡልኝ ብዬ ጀባ ብያለሁ። በብዛት አሳትማችሁ መሶደቅ የምትሹ ካላችሁ 0911473590 በመደወል አለቃዬን አናግሩ😊
❤31
የጨረቃ ግርዶች ይኖራል እየተባለ ነው። ከዚህ ቀደም የጻፍነውን አንብቡ። ይጠቅማችኋል!
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/20
https://www.tg-me.com/fiqshafiyamh/20
❤8
የሶላቱል-ኩሱፍ ህግጋት
===============
❶ ትርጓሜ
በዐረብኛ ቋንቋ ኩሱፍ ወይም ኹሱፍ ተመሳሳይ ቃላቶች ናቸው፡፡ የፊቅህ ልሂቃን ዘንድ ‹‹ኩሱፍ››ን ለፀሀይ ‹‹ኹሱፍን›› ደግሞ ለጨረቃ ግርዶሽ መጠቀም የተለመደ ነው፡፡
:
❷ ድንጉግነት
ሻፊዒይ (ረሒ) ከአቡ መስዑድ አል-በድሪይ እንደዘገቡት ‹‹የነቢዩ (ﷺ) ልጅ የሆኑት ኢብራሂም ሲያርፉ ሰዎች ‹‹እርሱ በመሞቱ ምክንያት ፀሀይ ተጋረደች፡፡›› ተባባሉ፡፡ ነቢዩ (ﷺ) ግን እንዲህ አሉ፡- ‹‹ፀሀይ እና ጨረቃ ሁለት የአላህ ተዓምራቶች ናቸው፡፡ ማንም ስለሞተ ወይም ስለተወለደ አይጋረዱም፡፡ ይህ መከሰቱን ስትመለከቱ አላህን ለማውሳት እና ለሶላት ተጣደፉ፡፡››
:
ሰዎች ተሰብስበው ቢሰግዱት መልካም ነው፡፡ ከሶላቱ በኋላ ኹጥባ ማድረግም ይወደዳል፡፡ ስለዚህ መሰብሰብ እንደተደነገገባቸው ሶላቶች ገላ መታጠብ ይወደዳል፡:፡
አዛን አይደረግም፡፡ ነገርግን ‹‹አስ-ሶላተ ጃሚዓህ›› የሚል ጥሪ ይደረጋል፡፡
ሶላቱል-ኩሱፍን በህብረትም ሆነ በግል መስገድ ይፈቀዳል፡፡ መንገደኛም ሆነ በሀገሩ ተቀማጭ የሆነ ሰው መስገድ ይችላል፡፡
❸ አፈጻጸም
አብዝሃኞቹ ዑለሞች ዘንድ ሶላቱል-ኩሱፍ ሁለት ረከዓ ነው፡፡: በእያንዳንዱ ረከዓ ላይ ደግሞ ሁለት ጊዜ መቆም አለ፡፡ ሁለት ጊዜ ቂርኣት አለ፡፡ ሁለት ጊዜ ሩኩዕ አለ፡፡ ሁለት ሱጁድም አለ፡፡
:
የተሟላ ነው የሚባለው አፈጻጸም ሰውየው መጀመሪያ በሚቆምበት ሰዓት ከፋቲሓ በኋላ ሱረቱል-በቀራን ወይም ከርሱ ጋር የሚቀራረብ ርዝመት ያለውን ምዕራፍ ያነባል፡፡ በሁለተኛው ቂያም ላይ ከፋቲሓ በኋላ ሱረቱል-ዒምራንን የሚያህል ርዝመት ያለውን ሱራ ያነባል፡፡ በሶስተኛው ቂያም ላይ መጠኑ ከዚህ ያነሰ ምዕራፍ ያነባል፤ ለምሳሌ ሱረቱ ኒሳእን፡፡ በኣራተኛው ቂያም ላይ አሁንም ከፋቲሓ በኋላ ከሱረቱ ኒሳእ ያነሰ ምዕራፍ ያነባል፤ ለምሳሌ፡- ሱረቱል-ማኢዳን፡፡
መጀመሪያ ይቆማል፡፡ የጠቀስነውን ያህል ቁርኣንን ያነባል፡፡ ከዚያም ይነሳል፡፡ በድጋሚ የጠቀስነውን ያህል ቁርአን ያነባል፡፡ ከዚያም ይነሳል፤ ወደ ሱጁድ ይወርዳል፤ ሁለቱን ሱጁዶች በተለመደው መልኩ ያሟላል፡፡ ከዚያም ይነሳል፡፡ ቁርኣንን ባሳለፍነው መልኩ ለሦስተኛ ጊዜ ያነባል፡፡ ከዚያም ሩኩዕ ይወርዳል፡፡ ተመልሶ ይቆማል፡፡ ቁርኣንን ለአራተኛ ጊዜ ያነባል፡፡ ከዚያም ተመልሶ ሩኩዕ ያደርጋል፡፡ ከዚያም ወደ ሱጁድ ይወርዳል፡፡ ከዚህ በኋላ በተለመደው መልኩ ሶላቱን ይቀጥላል፡፡
የመጀመሪያው ሩኩዕ ላይ ከሱረቱል-በቀራ መቶ አንቀጾችን ለሚያህል ጊዜ ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ሰማንያ የሱረቱል-በቀራ አንቀጾችን ሊያስነብብ ለሚችል ለሚችል ጊዜ ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ በሦስተኛው ሩኩዕ ላይ ሰባ፣ በአራተኛው ላይ ሃምሳ የሱረቱል-በቀራ አንቀጾችን የሚያህል ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ የሱጁዶቹ ርዝመት ከሩኩዑ ርዝመት ጋር የሚጣጣም መሆኑ የተወደደ መሆኑ በመረጃ የተደገፈ ነው፡፡
በሶላቱል-ኩሱፍ ላይ የፈለገውን ሱራ ማንበብ ይችላል፡፡ በፋቲሓ ብቻ መብቃቃትም ይችላል። ቂርኣቱን ረዥም ማድረግም ሆነ ማሳጠር ይፈቀዳል፡፡
:
❹ ድምጽን ከፍ ወይም ዝቅ ማድረግ
ጨረቃ ሲጋረድ የሚሰገደው ሶላት ላይ ድምጽን ከፍ ማድረግ ይወደዳል፡፡ ፀሀይ ሲጋረድ የሚሰገደው ሶላት ላይ ግን በቀን እንደሚሰገዱት ፈርድ ሶላቶች ድምጹን ዝቅ አድርጎ ይሰግዳል፡፡
:
❺ የሚሰገድበት ወቅት
ሶላቱል-ኩሱፍ እና ሶላቱል-ኹሱፍ የፀሀይ ወይም የጨረቃ ግርዶሽ በሚፈጠርበት ወቅት የሚሰገዱ ሶላቶች ናቸው፡፡
ሶላት ከመጀመሩ በፊት ፀሀይ ግርዶዋ ተገፍፎ ከተገለጠች ወይም እንደተጋረደች የምትጠልቅበት ወቅት ደርሶ ከጠለቀች የፀሀይ ግርዶሽ ሶላት (ሶላቱል-ኩሱፍ) ያመልጣል፡፡
የጨረቃ ግርዶሽ ሶላት (ሶላቱል-ኹሱፍ) ደግሞ ሶላት ከመጀመሩ በፊት ግርዶሹ ተገፍፎ በመገለጧ ወይም ነግቶ ፀሀይ በመውጣቷ ያመልጣል፡፡
ሶላት ከጀመረ በኋላ መግገለጥ ከተከሰተ ግን ሶላቱን አቅልሎ በመደበኛው መልኩ ያገባድደዋል፡፡
:
❻ ኢማምን በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ማግኘት
ተከትሎ የሚሰግድ ሰው ኢማሙን በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ካገኘው ምን ያደርጋል?
ኢማም ሻፊዒይ እንዲህ ይላሉ፡- ‹‹በዚህ ሁኔታ የደረሰበትን ረከዓ አላገኘውም፡፡ ምክንያቱም የረከዓውን አብላጫ ክፍል አላገኘም፡፡››… ‹‹በዚህ መሰረት ተከታዩ የቀረውን የረከዓውን ክፍል ኢማሙን ለመከተል በሚል ይሰግደዋል፡፡ ከዚያም ኢማሙ ሶላቱን ሲያገባድድ ተከታዩ ይነሳል፡፡ ግርዶሹ አሁንም ካለ ሁለተኛውን ረከዓ በመደበኛው አፈጻጸሙ ያከናውነዋል፡፡ ግርዶሹ ገተገለጠ ደግሞ ሶላቱን በመደበኛው አፈጻጸም ነገርግን አሳጥሮ ይሰግደዋል፡፡››
:
❼ የሶላቱል-ኩሱፍ ኹጥባ
ሶላቱን ሲያገባድድ ሁለተ ኹጥባ ማድረግ ሱና ነው፡፡ ሁለቱን ኹጥባዎቸ በመካከል በመቀመጥ ይለያቸዋል፡፡ ‹‹ሐምድ›› የሚለው ስርወ-ቃል እና ከርሱ የተፈለቀቁ ቃላቶችን በመጠቀም አላህን ያመሰግናል፡፡ በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለዋት ያወርዳል፡፡ አላህን በመታዘዝና እርሱን በመፍራት ላይ ምክር ያደርጋል፡፡ ቢያንስ አንድ አንቀጽ ያነባል፡፡ በአጭሩ ልክ እንደ ጁሙዓ ዓይነት ኹጥባ ያደርጋል፡፡
ኢማም ሻፊዒይ እንዲህ ይላሉ፡- ‹‹ምጽዋት እንዲሰጡ ይምከራቸው፡፡ ተውበት እንዲያደርጉ ይዘዛቸው፡፡ አላህን ምህረት እንዲለምኑና ከኃጢኣት እንዲርቁ አደራ ይበላቸው፡፡››
:
❽ ዱዓና ዚክር
በግርዶሽ ወቅት ዚክር፣ ኢስቲግፋር፣ ዱዓ እና ሌሎች ወደ አላህ የሚያቃርቡ መልካም ተግባራትን ማብዛት ይወደዳል፡፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ግርዶሽን ስትመለከቱ ዱዓ፣ ተክቢራ እና ሶደቃ አድርጉ፡፡››
በሌላ ዘገባ፡- ‹‹አላህን ወደ መዝከር፣ ወደ ዱዓ እና ወደ ኢስቲግፋር ፍጠኑ፡፡››
ግርዶሽ ሳይንሳዊ ትንታኔው ምንም ይሁን ምን የአላህ ማስፈራሪያ መሆኑ ይታመናል፡፡ ስለዚህ አላህ በመልካም እንዲያሳልፈው መለመን እና ደንግጦ ወደ አምልኮ መጣደፍ ይገባል፡፡ ከሶላት በኋላ ወደ ቂብላ አቅጣጫ ዞሮ በፍርሃት ስሜት ዱዓ ማድረግ የተወደደ ተግባር ነው፡፡
አላህ የተሻለ ያውቃል!!
www.tg-me.com/fiqshafiyamh
===============
❶ ትርጓሜ
በዐረብኛ ቋንቋ ኩሱፍ ወይም ኹሱፍ ተመሳሳይ ቃላቶች ናቸው፡፡ የፊቅህ ልሂቃን ዘንድ ‹‹ኩሱፍ››ን ለፀሀይ ‹‹ኹሱፍን›› ደግሞ ለጨረቃ ግርዶሽ መጠቀም የተለመደ ነው፡፡
:
❷ ድንጉግነት
ሻፊዒይ (ረሒ) ከአቡ መስዑድ አል-በድሪይ እንደዘገቡት ‹‹የነቢዩ (ﷺ) ልጅ የሆኑት ኢብራሂም ሲያርፉ ሰዎች ‹‹እርሱ በመሞቱ ምክንያት ፀሀይ ተጋረደች፡፡›› ተባባሉ፡፡ ነቢዩ (ﷺ) ግን እንዲህ አሉ፡- ‹‹ፀሀይ እና ጨረቃ ሁለት የአላህ ተዓምራቶች ናቸው፡፡ ማንም ስለሞተ ወይም ስለተወለደ አይጋረዱም፡፡ ይህ መከሰቱን ስትመለከቱ አላህን ለማውሳት እና ለሶላት ተጣደፉ፡፡››
:
ሰዎች ተሰብስበው ቢሰግዱት መልካም ነው፡፡ ከሶላቱ በኋላ ኹጥባ ማድረግም ይወደዳል፡፡ ስለዚህ መሰብሰብ እንደተደነገገባቸው ሶላቶች ገላ መታጠብ ይወደዳል፡:፡
አዛን አይደረግም፡፡ ነገርግን ‹‹አስ-ሶላተ ጃሚዓህ›› የሚል ጥሪ ይደረጋል፡፡
ሶላቱል-ኩሱፍን በህብረትም ሆነ በግል መስገድ ይፈቀዳል፡፡ መንገደኛም ሆነ በሀገሩ ተቀማጭ የሆነ ሰው መስገድ ይችላል፡፡
❸ አፈጻጸም
አብዝሃኞቹ ዑለሞች ዘንድ ሶላቱል-ኩሱፍ ሁለት ረከዓ ነው፡፡: በእያንዳንዱ ረከዓ ላይ ደግሞ ሁለት ጊዜ መቆም አለ፡፡ ሁለት ጊዜ ቂርኣት አለ፡፡ ሁለት ጊዜ ሩኩዕ አለ፡፡ ሁለት ሱጁድም አለ፡፡
:
የተሟላ ነው የሚባለው አፈጻጸም ሰውየው መጀመሪያ በሚቆምበት ሰዓት ከፋቲሓ በኋላ ሱረቱል-በቀራን ወይም ከርሱ ጋር የሚቀራረብ ርዝመት ያለውን ምዕራፍ ያነባል፡፡ በሁለተኛው ቂያም ላይ ከፋቲሓ በኋላ ሱረቱል-ዒምራንን የሚያህል ርዝመት ያለውን ሱራ ያነባል፡፡ በሶስተኛው ቂያም ላይ መጠኑ ከዚህ ያነሰ ምዕራፍ ያነባል፤ ለምሳሌ ሱረቱ ኒሳእን፡፡ በኣራተኛው ቂያም ላይ አሁንም ከፋቲሓ በኋላ ከሱረቱ ኒሳእ ያነሰ ምዕራፍ ያነባል፤ ለምሳሌ፡- ሱረቱል-ማኢዳን፡፡
መጀመሪያ ይቆማል፡፡ የጠቀስነውን ያህል ቁርኣንን ያነባል፡፡ ከዚያም ይነሳል፡፡ በድጋሚ የጠቀስነውን ያህል ቁርአን ያነባል፡፡ ከዚያም ይነሳል፤ ወደ ሱጁድ ይወርዳል፤ ሁለቱን ሱጁዶች በተለመደው መልኩ ያሟላል፡፡ ከዚያም ይነሳል፡፡ ቁርኣንን ባሳለፍነው መልኩ ለሦስተኛ ጊዜ ያነባል፡፡ ከዚያም ሩኩዕ ይወርዳል፡፡ ተመልሶ ይቆማል፡፡ ቁርኣንን ለአራተኛ ጊዜ ያነባል፡፡ ከዚያም ተመልሶ ሩኩዕ ያደርጋል፡፡ ከዚያም ወደ ሱጁድ ይወርዳል፡፡ ከዚህ በኋላ በተለመደው መልኩ ሶላቱን ይቀጥላል፡፡
የመጀመሪያው ሩኩዕ ላይ ከሱረቱል-በቀራ መቶ አንቀጾችን ለሚያህል ጊዜ ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ሰማንያ የሱረቱል-በቀራ አንቀጾችን ሊያስነብብ ለሚችል ለሚችል ጊዜ ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ በሦስተኛው ሩኩዕ ላይ ሰባ፣ በአራተኛው ላይ ሃምሳ የሱረቱል-በቀራ አንቀጾችን የሚያህል ተስቢሕ ያደርጋል፡፡ የሱጁዶቹ ርዝመት ከሩኩዑ ርዝመት ጋር የሚጣጣም መሆኑ የተወደደ መሆኑ በመረጃ የተደገፈ ነው፡፡
በሶላቱል-ኩሱፍ ላይ የፈለገውን ሱራ ማንበብ ይችላል፡፡ በፋቲሓ ብቻ መብቃቃትም ይችላል። ቂርኣቱን ረዥም ማድረግም ሆነ ማሳጠር ይፈቀዳል፡፡
:
❹ ድምጽን ከፍ ወይም ዝቅ ማድረግ
ጨረቃ ሲጋረድ የሚሰገደው ሶላት ላይ ድምጽን ከፍ ማድረግ ይወደዳል፡፡ ፀሀይ ሲጋረድ የሚሰገደው ሶላት ላይ ግን በቀን እንደሚሰገዱት ፈርድ ሶላቶች ድምጹን ዝቅ አድርጎ ይሰግዳል፡፡
:
❺ የሚሰገድበት ወቅት
ሶላቱል-ኩሱፍ እና ሶላቱል-ኹሱፍ የፀሀይ ወይም የጨረቃ ግርዶሽ በሚፈጠርበት ወቅት የሚሰገዱ ሶላቶች ናቸው፡፡
ሶላት ከመጀመሩ በፊት ፀሀይ ግርዶዋ ተገፍፎ ከተገለጠች ወይም እንደተጋረደች የምትጠልቅበት ወቅት ደርሶ ከጠለቀች የፀሀይ ግርዶሽ ሶላት (ሶላቱል-ኩሱፍ) ያመልጣል፡፡
የጨረቃ ግርዶሽ ሶላት (ሶላቱል-ኹሱፍ) ደግሞ ሶላት ከመጀመሩ በፊት ግርዶሹ ተገፍፎ በመገለጧ ወይም ነግቶ ፀሀይ በመውጣቷ ያመልጣል፡፡
ሶላት ከጀመረ በኋላ መግገለጥ ከተከሰተ ግን ሶላቱን አቅልሎ በመደበኛው መልኩ ያገባድደዋል፡፡
:
❻ ኢማምን በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ማግኘት
ተከትሎ የሚሰግድ ሰው ኢማሙን በሁለተኛው ሩኩዕ ላይ ካገኘው ምን ያደርጋል?
ኢማም ሻፊዒይ እንዲህ ይላሉ፡- ‹‹በዚህ ሁኔታ የደረሰበትን ረከዓ አላገኘውም፡፡ ምክንያቱም የረከዓውን አብላጫ ክፍል አላገኘም፡፡››… ‹‹በዚህ መሰረት ተከታዩ የቀረውን የረከዓውን ክፍል ኢማሙን ለመከተል በሚል ይሰግደዋል፡፡ ከዚያም ኢማሙ ሶላቱን ሲያገባድድ ተከታዩ ይነሳል፡፡ ግርዶሹ አሁንም ካለ ሁለተኛውን ረከዓ በመደበኛው አፈጻጸሙ ያከናውነዋል፡፡ ግርዶሹ ገተገለጠ ደግሞ ሶላቱን በመደበኛው አፈጻጸም ነገርግን አሳጥሮ ይሰግደዋል፡፡››
:
❼ የሶላቱል-ኩሱፍ ኹጥባ
ሶላቱን ሲያገባድድ ሁለተ ኹጥባ ማድረግ ሱና ነው፡፡ ሁለቱን ኹጥባዎቸ በመካከል በመቀመጥ ይለያቸዋል፡፡ ‹‹ሐምድ›› የሚለው ስርወ-ቃል እና ከርሱ የተፈለቀቁ ቃላቶችን በመጠቀም አላህን ያመሰግናል፡፡ በነቢዩ (ﷺ) ላይ ሶለዋት ያወርዳል፡፡ አላህን በመታዘዝና እርሱን በመፍራት ላይ ምክር ያደርጋል፡፡ ቢያንስ አንድ አንቀጽ ያነባል፡፡ በአጭሩ ልክ እንደ ጁሙዓ ዓይነት ኹጥባ ያደርጋል፡፡
ኢማም ሻፊዒይ እንዲህ ይላሉ፡- ‹‹ምጽዋት እንዲሰጡ ይምከራቸው፡፡ ተውበት እንዲያደርጉ ይዘዛቸው፡፡ አላህን ምህረት እንዲለምኑና ከኃጢኣት እንዲርቁ አደራ ይበላቸው፡፡››
:
❽ ዱዓና ዚክር
በግርዶሽ ወቅት ዚክር፣ ኢስቲግፋር፣ ዱዓ እና ሌሎች ወደ አላህ የሚያቃርቡ መልካም ተግባራትን ማብዛት ይወደዳል፡፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ግርዶሽን ስትመለከቱ ዱዓ፣ ተክቢራ እና ሶደቃ አድርጉ፡፡››
በሌላ ዘገባ፡- ‹‹አላህን ወደ መዝከር፣ ወደ ዱዓ እና ወደ ኢስቲግፋር ፍጠኑ፡፡››
ግርዶሽ ሳይንሳዊ ትንታኔው ምንም ይሁን ምን የአላህ ማስፈራሪያ መሆኑ ይታመናል፡፡ ስለዚህ አላህ በመልካም እንዲያሳልፈው መለመን እና ደንግጦ ወደ አምልኮ መጣደፍ ይገባል፡፡ ከሶላት በኋላ ወደ ቂብላ አቅጣጫ ዞሮ በፍርሃት ስሜት ዱዓ ማድረግ የተወደደ ተግባር ነው፡፡
አላህ የተሻለ ያውቃል!!
www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤10👍6
Tofik Bahiru
የሶላቱል-ኩሱፍ ህግጋት =============== ❶ ትርጓሜ በዐረብኛ ቋንቋ ኩሱፍ ወይም ኹሱፍ ተመሳሳይ ቃላቶች ናቸው፡፡ የፊቅህ ልሂቃን ዘንድ ‹‹ኩሱፍ››ን ለፀሀይ ‹‹ኹሱፍን›› ደግሞ ለጨረቃ ግርዶሽ መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ : ❷ ድንጉግነት ሻፊዒይ (ረሒ) ከአቡ መስዑድ አል-በድሪይ እንደዘገቡት ‹‹የነቢዩ (ﷺ) ልጅ የሆኑት ኢብራሂም ሲያርፉ ሰዎች ‹‹እርሱ በመሞቱ ምክንያት ፀሀይ ተጋረደች፡፡››…
አንድ ወንድማችን ደርሱን እንዲህ አሳጥሮታል። ጀዛሁላሁ ኸይራ!
Forwarded from Tofik Bahiru
እግረ መንገድ
=========
በነቢዩ [ﷺ] ዘመን ፀሀይ ተጋረደች። ሰዎች ይህ የሆነው የርሳቸው ጨቅላ ህፃን ልጅ ኢብራሂም [ዐሰ] በመሞቱ እንደሆነ አወሩ።
:
ይህንን ያደረጉት የአላህን መልክት ቀን ከሌት የሚያስተላልፈው ነቢይ ቀላል ሰው አለመሆኑን ከማመናቸው የተነሳ ነው። ተፈጥሮን ያስገኘው ፈጣሪ መልክተኛነት ልዩ ደረጃን ስላገኙ ተፈጥሮ የርሳቸውን የህይወት አፅናፎች እየተከተለች እንድታዝንና እንድትደሰት ያደርግላቸዋል የሚል እምነት አድሮባቸው ነው። ለነቢያቸው የነበራቸው ክብር ከዚህም በላይ ቢባል እንዲቀበሉ የሚያደርግ ነበር። ደግሞም ሰዪዳችን በርካታ መለዮዎች አሏቸው፤ ይህ ከዚያ ውስጥ ቢካተት አይገርምም።…
:
ወሬው ከየት እንደመጣ አልታወቀም። እርሳቸው ልጄ ስለሞተ ፀሀይ ተጋረደ አላሉም። እንደማንኛውም ወፍ ዘራሽ ወሬ በቅጥፈት ጀመረ። አማኞች ለነቢያቸው ﷺ ባላቸው ፍቅር ተነሳስተው ሳያጣሩ አናፈሱት።
:
ነገርግን የአላህ ነቢይ ﷺ ምን አደረጉ?
የወሬውን እውነተኝነት የሚያጠናክር ፍንጭ ሰጡ?
እኔ ባልልም ሰዎች ይህንን ክብር ከሰጡኝ ዝም ልበላቸው እንዳሻቸው ያውሩ አሉ?…
በፍፁም!
ህዝቡን ሰበሰቡ። አላህን አመሰገኑ። አወደሱት። ከዚያም «ፀሀይና ጨረቃ የአላህ ተዐምራት ናቸው። ማንም ስለሞተም ሆነ ስለተወለደ አይጋረዱም።…» አሉ።
:
የሰዎች አዕምሮና ልብ የአማና እቃቸው ነው። በውስጣቸው እውነትን ብቻ የመሙላት ግዳጅ አለባቸው። ከጌታቸው በሆነው መልክት በሉ የተባሉትን ብቻ ይላሉ። ክብርና ዝናን፣ የሰዎችን አድናቆትና ፍቅር ለተሸከሙት እውነት ይሰዋሉ። ስለዚህ ከሰው መሀል ቆመው አእምሮን ይገርዛሉ! እምነትን ያፀዳሉ! ሀሰትን ይዋጋሉ!
ኃላፊነታቸው ይህ ነው!…
:
ታዲያ ሰዪዲ ሙሐመድ ﷺ ነቢይ ነኝ ሲሉ ዱንያዊ መሻት እንደሌላቸው ጥብቅ መረጃ አላገኘንም!?
አሽሀዱ አንነ ሙሐመደን ረሱሉላህ!
www.tg-me.com/fiqshafiyamh
=========
በነቢዩ [ﷺ] ዘመን ፀሀይ ተጋረደች። ሰዎች ይህ የሆነው የርሳቸው ጨቅላ ህፃን ልጅ ኢብራሂም [ዐሰ] በመሞቱ እንደሆነ አወሩ።
:
ይህንን ያደረጉት የአላህን መልክት ቀን ከሌት የሚያስተላልፈው ነቢይ ቀላል ሰው አለመሆኑን ከማመናቸው የተነሳ ነው። ተፈጥሮን ያስገኘው ፈጣሪ መልክተኛነት ልዩ ደረጃን ስላገኙ ተፈጥሮ የርሳቸውን የህይወት አፅናፎች እየተከተለች እንድታዝንና እንድትደሰት ያደርግላቸዋል የሚል እምነት አድሮባቸው ነው። ለነቢያቸው የነበራቸው ክብር ከዚህም በላይ ቢባል እንዲቀበሉ የሚያደርግ ነበር። ደግሞም ሰዪዳችን በርካታ መለዮዎች አሏቸው፤ ይህ ከዚያ ውስጥ ቢካተት አይገርምም።…
:
ወሬው ከየት እንደመጣ አልታወቀም። እርሳቸው ልጄ ስለሞተ ፀሀይ ተጋረደ አላሉም። እንደማንኛውም ወፍ ዘራሽ ወሬ በቅጥፈት ጀመረ። አማኞች ለነቢያቸው ﷺ ባላቸው ፍቅር ተነሳስተው ሳያጣሩ አናፈሱት።
:
ነገርግን የአላህ ነቢይ ﷺ ምን አደረጉ?
የወሬውን እውነተኝነት የሚያጠናክር ፍንጭ ሰጡ?
እኔ ባልልም ሰዎች ይህንን ክብር ከሰጡኝ ዝም ልበላቸው እንዳሻቸው ያውሩ አሉ?…
በፍፁም!
ህዝቡን ሰበሰቡ። አላህን አመሰገኑ። አወደሱት። ከዚያም «ፀሀይና ጨረቃ የአላህ ተዐምራት ናቸው። ማንም ስለሞተም ሆነ ስለተወለደ አይጋረዱም።…» አሉ።
:
የሰዎች አዕምሮና ልብ የአማና እቃቸው ነው። በውስጣቸው እውነትን ብቻ የመሙላት ግዳጅ አለባቸው። ከጌታቸው በሆነው መልክት በሉ የተባሉትን ብቻ ይላሉ። ክብርና ዝናን፣ የሰዎችን አድናቆትና ፍቅር ለተሸከሙት እውነት ይሰዋሉ። ስለዚህ ከሰው መሀል ቆመው አእምሮን ይገርዛሉ! እምነትን ያፀዳሉ! ሀሰትን ይዋጋሉ!
ኃላፊነታቸው ይህ ነው!…
:
ታዲያ ሰዪዲ ሙሐመድ ﷺ ነቢይ ነኝ ሲሉ ዱንያዊ መሻት እንደሌላቸው ጥብቅ መረጃ አላገኘንም!?
አሽሀዱ አንነ ሙሐመደን ረሱሉላህ!
www.tg-me.com/fiqshafiyamh
❤18
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
ኢብኑ ኹዘይማ እና ሌሎችም እንደዘገቡት:‐
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] የግርዶሽ ሶላት ሰገዱ።…
«ከዚያም ሱጁድ አደረጉ። ራሳቸውን ከመሬት ላይ ሳያነሱ ረዥም ጊዜ ቆዩ። [በጭንቀት] «ኡፍ! ኡፍ!» በማለት [እየተነፈሱ] እንዲህ ዱዓ አደረጉ:‐
«ጌታዬ ሆይ! እኔ በመካከላቸው እስካለሁ ድረስ እንደማትቀጣቸው ቃል ገብተህልኝ አልነበር?!… ጌታዬ ሆይ! እኛ ምህረት እስከለመንህ ድረስ እንደማትቀጣን ቃል ገብተህልኝ አልነበር?!…»
:
እዚህ ጋር ቁምና በቃላቶቻቸው መካከል ያለውን የአባት ጭንቀት፣ ለኡመታቸው ያላቸውን ርሕራሔ ተመልከት!
ለአላህ ያላቸውን ፍርሐት እና በማንኛውም ጊዜ የአላህ ቅጣት እንዳይመጣ ምን ያህል ይሳቀቁ እንደነበርም በጥልቀት ታዘብ!…
ይህ ሁሉ ፍርሃት ከታላቅ ማንነታቸው እና አላህ ከሰጣቸው በርካታ ስጦታዎች ጋር መሆኑን ስታይ ደግሞ "ከማናችሁም በላይ አላህን ፈሪው እኔ ነኝ።" ማለታቸው ለምን እንደሆነ ይገለጥልሃል።
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] የግርዶሽ ሶላት ሰገዱ።…
«ከዚያም ሱጁድ አደረጉ። ራሳቸውን ከመሬት ላይ ሳያነሱ ረዥም ጊዜ ቆዩ። [በጭንቀት] «ኡፍ! ኡፍ!» በማለት [እየተነፈሱ] እንዲህ ዱዓ አደረጉ:‐
«ጌታዬ ሆይ! እኔ በመካከላቸው እስካለሁ ድረስ እንደማትቀጣቸው ቃል ገብተህልኝ አልነበር?!… ጌታዬ ሆይ! እኛ ምህረት እስከለመንህ ድረስ እንደማትቀጣን ቃል ገብተህልኝ አልነበር?!…»
:
እዚህ ጋር ቁምና በቃላቶቻቸው መካከል ያለውን የአባት ጭንቀት፣ ለኡመታቸው ያላቸውን ርሕራሔ ተመልከት!
ለአላህ ያላቸውን ፍርሐት እና በማንኛውም ጊዜ የአላህ ቅጣት እንዳይመጣ ምን ያህል ይሳቀቁ እንደነበርም በጥልቀት ታዘብ!…
ይህ ሁሉ ፍርሃት ከታላቅ ማንነታቸው እና አላህ ከሰጣቸው በርካታ ስጦታዎች ጋር መሆኑን ስታይ ደግሞ "ከማናችሁም በላይ አላህን ፈሪው እኔ ነኝ።" ማለታቸው ለምን እንደሆነ ይገለጥልሃል።
❤20😢1😍1
Forwarded from የረሕማን ስጦታ
ኑሩ ሙሐመድ
[ክፍል ሰባት]
የንጽሕና መንገድ
ንጽሕና ፅኑ ትእዛዛቸው ነው። ንጽሕና መጠበቅ ያለውን መልካም ውጤት እያስረዱ ሰዎችን ይቀሰቅሱም ነበር። ቆሻሻነትን ይዋጉ ነበር። ይህንን በተለያየ ረገድ እንመልከተው:‐
❶ ንጽሕና ከኢስላም መሰረታዊያን እንደሆነ አብራርተዋል:‐
ቲርሚዚይ ከሰዕድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «አላህ መልካም ነው። መልካምን ይወዳል። ንጹሕ ነው። ንጽሕናን ይወዳል። ቸር ነው። ቸርነትን ይወዳል። ለጋስ ነው። ልግስናን ይወዳል። ቀዬዎቻችሁን አጽዱ። ከአይሁዶች ጋር አትመሳሰሉ።»
ከሱለይማን ኢብኑ ሱረድ እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ጥርሳችሁን ፋቁ። ራሳችሁን አጽዱ። ዊትርም [ነጠላ ሶላት] ስገዱ። አላህ ነጠላ (ዊትር/አንድ) ነው። ዊትር [ነጠላን] ይወዳል።»
አል‐ኸጢብ እና ሌሎችም ከሰይዳ ዓኢሻ እንደዘገቡት የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ኢስላም ጽዱ ነው። ራሳችሁን አጽዱ። ንጹሕ እንጂ ጀነት አይገባም።»
አቡሁረይራ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «በምትችሉት ነገር ሁሉ ራሳችሁን አጽዱ። አላህ ኢስላምን የገነባው በንጽሕና ነው። ንጹሕ እንጂ ጀነት አይገባም።»
❷ ቅስቀሳዎቻቸው:‐
በበርካታ ሐዲሶች ሰዎች እንዲታጠቡ ቀስቅሰዋል። ካለመታጠብ አስጠንቅቀዋል። ከዚህ ውስጥ ጥቂቱን እናንሳ:‐
ኢማም አሕመድ ከጃቢር [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
«በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ በየሰባት ቀኑ አንዴ መታጠብ አለበት። እርሱም የጁሙዐ ቀን ነው።»
አንዳንድ የአካላት ጫፎችን ስለማጽዳት በተናጠል አብራርተው ተናግረዋል። ቆሻሻ የሚያጠራቅሙ እነዚህ አካላትን ማጽዳት ተፈጥሮኣዊ የኃይማኖት ድንጋጌ መሆኑን ገልጸዋል። የሁሉም የነቢያት መልክት ውስጥ የሰረጸ የአላህ ትእዛዝ እንደሆነም ተናግረዋል:‐
ሙስሊም ከዓኢሻ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
ዐስር ነገሮች ተፈጥሮኣዊ የኃይማኖት ድንጋጌዎች (ሱነን አል‐ፊጥራ) ናቸው:‐
⚀ ቀድሞ‐ቀመስን (የላይኛውን የከንፈር ጺም) ማሳጠር፤
⚁ የአገጭን ጺም ማጎፈር፤
⚂ ጥርስን መፋቅ፤
⚃ በአፍንጫ ውሃን መሳብ (ኢስቲንሻቅ)፤
⚄ ጥፍርን መቁረጥ፤
⚅ የጣት መገጣጠሚያዎችን ማጠብ፤
⚆ የብብትን ጸጉር መንጨት፤
⚇ የብልት ጸጉርን መላጨት፤
⚈ ኢስቲንጃእ ማድረግ።»
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እነዚህን የአካል ክፍሎች ለረዥም ጊዜ ችላ ማለት እንደማይገባ አሳስበዋል።
ሱነኑ አቢ ዳዉድ ላይ ከሐሰን [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ቀድሞ‐ቀመስን ለማሳጠር፣ ጥፍርን መመቁረጥ፣ የብብት ጸጉርን ለመንጨት እና የብልት ፀጉርን ለመላጨት የጊዜ ገደብ አድርገውልን ነበር። ከአርባ ቀን በላይ ቸላ ብለን እንዳንተው መድበዋል።»
ማለትም ችላ ብሎ መተው የግድ የሚሆንበት በየሳምንቱ ማጽዳት የማይመችበት ሁኔታ ቢፈጠር እንኳን ከዐርባ ቀን በላይ ማሳለፍ ግን ክልክል ነው። የክልክልነት ደረጃው ላይ ልሂቃን የተለያዩ አስተያየቶችን ቢሰጡም፣ መከልከሉ ግን ያስማማል።
❸ የምግብና የመጠጥ ተረፎችን ማጽዳት:‐
ሐኪም እና ቲርሚዚይ ከዐብዱላህ ኢብኑ ቡስር እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
«ጥፍሮቻችሁን ቁረጡ። የተቆረጡ ጥፍሮቻችሁን ቅበሩ። የጣቶቻችሁን መተጣጠፊያ አጽዱ። ላንቃዎቻችሁን ከምግብ ፋና አጽዱ። ጥርሳችሁን ፋቁ። ጥርሳችሁን ቢጫ አድርጋችሁ አፋችሁ እየገማ እኔ ዘንድ አትግቡ።»
ቲርሚዚይ ከሰልማን [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «የምግብ በረከቱ ከበስተፊቱ እና ከበስተኋላው እጅን መታጠብ ነው።»
❹ ልብስን ስለማጽዳት:‐
ጦበራኒይ እና አቡኑዐይም ከዑመር ኢብኑል‐ኸጧብ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ሙእሚንን አላህ ዘንድ ክብር (ከራማ) ከሚያሰጡት ነገሮች መካከል የልብስ ጽዳት እና [ከዱንያ ነገሮች] በትንሽ ነገር መብቃቃት ይገኙበታል።»
አቡኑዐይም ከጃቢር እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አንድ ሰውዬን ልብሱ ቆሽሾ አዩት። ከዚያም እንዲህ በማለት ተቆጡ:‐ «ይህ ሰውዬ ልብሱን የሚያጸዳበት ነገር አላገኘምና ነው [እንዲህ የቆሸሸው]?!»
እርሳቸው ዘንድ ቆሻሻ ልብስ ያስወቅሳል። በእርግጥ ሰውየውን በቀጥታ አልተናገሩትም። ቀልቡን ለመጠበቅ ለሌላ ሰው ነው መልክት ያደረሱት። በዚያውም ሌሎች ሰዎች ሰምተው ይጠነቀቃሉ። በዚያውም ልብሳቸውን በንፅህና ለማይለብሱ ሁሉ ወቀሳቸውን ያደርሳሉ።
ነቢዩ [ﷺ] ልብስን ለቆሻሻ መዳረግንም ይቃወሙ ነበር። ከአሽዐስ ኢብኑ ሱለይም እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ አክስቴ አጎቷን ጠቅሳ እንደምትናገረው እንዲህ ብለዋል:‐
«በመዲና መንገድ ላይ እየሄድኩኝ ከጀርባዬ አንድ ሰው እንዲህ ሲል አገኘሁት:‐ «ሽርጥህን ከፍ አድርግ። ይህ ጽዱ፣ ፈሪሐ አላህ ያለበት እና ልብስህንም የሚበረክት እንዲሆን ያደርግልሃል።» ከዚያም [ዘወር ስል] የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ሆነው አገኘኋቸው። የአላህ መልክተኛ ሆይ! የአዘቦት [የስራ] ልብስ ነውኮ።» አልኳቸው።
እርሳቸውም:‐ «እና የእኔን ፈለግ አትከተልም!» አሉኝ። አተኩሬ ሳያቸው ሽርጣቸው የባታቸው አጋማሽ ላይ ነው።»
ቲርሚዚይ "ሸማኢል" በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ዘግበውታል።
[ይቀጥላል]…
[ክፍል ሰባት]
የንጽሕና መንገድ
ንጽሕና ፅኑ ትእዛዛቸው ነው። ንጽሕና መጠበቅ ያለውን መልካም ውጤት እያስረዱ ሰዎችን ይቀሰቅሱም ነበር። ቆሻሻነትን ይዋጉ ነበር። ይህንን በተለያየ ረገድ እንመልከተው:‐
❶ ንጽሕና ከኢስላም መሰረታዊያን እንደሆነ አብራርተዋል:‐
ቲርሚዚይ ከሰዕድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «አላህ መልካም ነው። መልካምን ይወዳል። ንጹሕ ነው። ንጽሕናን ይወዳል። ቸር ነው። ቸርነትን ይወዳል። ለጋስ ነው። ልግስናን ይወዳል። ቀዬዎቻችሁን አጽዱ። ከአይሁዶች ጋር አትመሳሰሉ።»
ከሱለይማን ኢብኑ ሱረድ እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ጥርሳችሁን ፋቁ። ራሳችሁን አጽዱ። ዊትርም [ነጠላ ሶላት] ስገዱ። አላህ ነጠላ (ዊትር/አንድ) ነው። ዊትር [ነጠላን] ይወዳል።»
አል‐ኸጢብ እና ሌሎችም ከሰይዳ ዓኢሻ እንደዘገቡት የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ኢስላም ጽዱ ነው። ራሳችሁን አጽዱ። ንጹሕ እንጂ ጀነት አይገባም።»
አቡሁረይራ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «በምትችሉት ነገር ሁሉ ራሳችሁን አጽዱ። አላህ ኢስላምን የገነባው በንጽሕና ነው። ንጹሕ እንጂ ጀነት አይገባም።»
❷ ቅስቀሳዎቻቸው:‐
በበርካታ ሐዲሶች ሰዎች እንዲታጠቡ ቀስቅሰዋል። ካለመታጠብ አስጠንቅቀዋል። ከዚህ ውስጥ ጥቂቱን እናንሳ:‐
ኢማም አሕመድ ከጃቢር [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
«በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ በየሰባት ቀኑ አንዴ መታጠብ አለበት። እርሱም የጁሙዐ ቀን ነው።»
አንዳንድ የአካላት ጫፎችን ስለማጽዳት በተናጠል አብራርተው ተናግረዋል። ቆሻሻ የሚያጠራቅሙ እነዚህ አካላትን ማጽዳት ተፈጥሮኣዊ የኃይማኖት ድንጋጌ መሆኑን ገልጸዋል። የሁሉም የነቢያት መልክት ውስጥ የሰረጸ የአላህ ትእዛዝ እንደሆነም ተናግረዋል:‐
ሙስሊም ከዓኢሻ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
ዐስር ነገሮች ተፈጥሮኣዊ የኃይማኖት ድንጋጌዎች (ሱነን አል‐ፊጥራ) ናቸው:‐
⚀ ቀድሞ‐ቀመስን (የላይኛውን የከንፈር ጺም) ማሳጠር፤
⚁ የአገጭን ጺም ማጎፈር፤
⚂ ጥርስን መፋቅ፤
⚃ በአፍንጫ ውሃን መሳብ (ኢስቲንሻቅ)፤
⚄ ጥፍርን መቁረጥ፤
⚅ የጣት መገጣጠሚያዎችን ማጠብ፤
⚆ የብብትን ጸጉር መንጨት፤
⚇ የብልት ጸጉርን መላጨት፤
⚈ ኢስቲንጃእ ማድረግ።»
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እነዚህን የአካል ክፍሎች ለረዥም ጊዜ ችላ ማለት እንደማይገባ አሳስበዋል።
ሱነኑ አቢ ዳዉድ ላይ ከሐሰን [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ቀድሞ‐ቀመስን ለማሳጠር፣ ጥፍርን መመቁረጥ፣ የብብት ጸጉርን ለመንጨት እና የብልት ፀጉርን ለመላጨት የጊዜ ገደብ አድርገውልን ነበር። ከአርባ ቀን በላይ ቸላ ብለን እንዳንተው መድበዋል።»
ማለትም ችላ ብሎ መተው የግድ የሚሆንበት በየሳምንቱ ማጽዳት የማይመችበት ሁኔታ ቢፈጠር እንኳን ከዐርባ ቀን በላይ ማሳለፍ ግን ክልክል ነው። የክልክልነት ደረጃው ላይ ልሂቃን የተለያዩ አስተያየቶችን ቢሰጡም፣ መከልከሉ ግን ያስማማል።
❸ የምግብና የመጠጥ ተረፎችን ማጽዳት:‐
ሐኪም እና ቲርሚዚይ ከዐብዱላህ ኢብኑ ቡስር እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
«ጥፍሮቻችሁን ቁረጡ። የተቆረጡ ጥፍሮቻችሁን ቅበሩ። የጣቶቻችሁን መተጣጠፊያ አጽዱ። ላንቃዎቻችሁን ከምግብ ፋና አጽዱ። ጥርሳችሁን ፋቁ። ጥርሳችሁን ቢጫ አድርጋችሁ አፋችሁ እየገማ እኔ ዘንድ አትግቡ።»
ቲርሚዚይ ከሰልማን [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «የምግብ በረከቱ ከበስተፊቱ እና ከበስተኋላው እጅን መታጠብ ነው።»
❹ ልብስን ስለማጽዳት:‐
ጦበራኒይ እና አቡኑዐይም ከዑመር ኢብኑል‐ኸጧብ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐ «ሙእሚንን አላህ ዘንድ ክብር (ከራማ) ከሚያሰጡት ነገሮች መካከል የልብስ ጽዳት እና [ከዱንያ ነገሮች] በትንሽ ነገር መብቃቃት ይገኙበታል።»
አቡኑዐይም ከጃቢር እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አንድ ሰውዬን ልብሱ ቆሽሾ አዩት። ከዚያም እንዲህ በማለት ተቆጡ:‐ «ይህ ሰውዬ ልብሱን የሚያጸዳበት ነገር አላገኘምና ነው [እንዲህ የቆሸሸው]?!»
እርሳቸው ዘንድ ቆሻሻ ልብስ ያስወቅሳል። በእርግጥ ሰውየውን በቀጥታ አልተናገሩትም። ቀልቡን ለመጠበቅ ለሌላ ሰው ነው መልክት ያደረሱት። በዚያውም ሌሎች ሰዎች ሰምተው ይጠነቀቃሉ። በዚያውም ልብሳቸውን በንፅህና ለማይለብሱ ሁሉ ወቀሳቸውን ያደርሳሉ።
ነቢዩ [ﷺ] ልብስን ለቆሻሻ መዳረግንም ይቃወሙ ነበር። ከአሽዐስ ኢብኑ ሱለይም እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል:‐ አክስቴ አጎቷን ጠቅሳ እንደምትናገረው እንዲህ ብለዋል:‐
«በመዲና መንገድ ላይ እየሄድኩኝ ከጀርባዬ አንድ ሰው እንዲህ ሲል አገኘሁት:‐ «ሽርጥህን ከፍ አድርግ። ይህ ጽዱ፣ ፈሪሐ አላህ ያለበት እና ልብስህንም የሚበረክት እንዲሆን ያደርግልሃል።» ከዚያም [ዘወር ስል] የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ሆነው አገኘኋቸው። የአላህ መልክተኛ ሆይ! የአዘቦት [የስራ] ልብስ ነውኮ።» አልኳቸው።
እርሳቸውም:‐ «እና የእኔን ፈለግ አትከተልም!» አሉኝ። አተኩሬ ሳያቸው ሽርጣቸው የባታቸው አጋማሽ ላይ ነው።»
ቲርሚዚይ "ሸማኢል" በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ዘግበውታል።
[ይቀጥላል]…
❤27
Audio
📚አል‐አዝካር ሚን ከላሚ ሰይዲል‐አብራር
📗 ክፍል 7:‐ ዚክርን ያስለመደ ሰው ‐ ዚክር አስመልክቶ የተፃፉ መጽሐፍት
📆 መስከረም 17/ 2018 ዓ. ል.
📗 ክፍል 7:‐ ዚክርን ያስለመደ ሰው ‐ ዚክር አስመልክቶ የተፃፉ መጽሐፍት
📆 መስከረም 17/ 2018 ዓ. ል.
❤11
ሰር‐ሪይ አስ‐ሰቀጢይ [ቀደሰላሁ ሲረሁ] እንዲህ ይላሉ:‐
«ከምንም በላይ ምርጦቹ ነገሮች አምስት ናቸው:‐
⚀ ስለ ኃጢኣት ማልቀስ፤
⚁ የራስን ነውር ማረም፤
⚂ ሩቅ አዋቂ የሆነውን ጌታ መፍራት፤
⚃ ከቀልብ ላይ ጥላሸትን ማስወገድ፤
⚄ ለነፍስ ዝንባሌ አለማዘንበል።»
📔 ሒልየቱል‐አውሊያእ፥ ኢማም አቡ ኑዐይም [ረሒመሁላህ]
«ከምንም በላይ ምርጦቹ ነገሮች አምስት ናቸው:‐
⚀ ስለ ኃጢኣት ማልቀስ፤
⚁ የራስን ነውር ማረም፤
⚂ ሩቅ አዋቂ የሆነውን ጌታ መፍራት፤
⚃ ከቀልብ ላይ ጥላሸትን ማስወገድ፤
⚄ ለነፍስ ዝንባሌ አለማዘንበል።»
📔 ሒልየቱል‐አውሊያእ፥ ኢማም አቡ ኑዐይም [ረሒመሁላህ]
❤36👍5
«ሰውየው «ሰዎችን አይመክርም። «የማልሰራበትን አልናገርም።» እያለም ይከራከራል።» በማለት ኢማም ሐሰን አልበስሪይ [ረሒመሁላህ] ተጠየቁ።
እርሳቸውም:‐ «ከኛ መካከል የሚናገረውን የሚሰራ ማን አለ?! ሸይጧን በዚህ በኩል ተሳክለቶለት በመልካም ባያዝ እና ከመጥፎ ባይከለክል ይወድ ነበር!» በማለት መለሱ
📖 ለጧኢፉል‐መዓሪፍ
እርሳቸውም:‐ «ከኛ መካከል የሚናገረውን የሚሰራ ማን አለ?! ሸይጧን በዚህ በኩል ተሳክለቶለት በመልካም ባያዝ እና ከመጥፎ ባይከለክል ይወድ ነበር!» በማለት መለሱ
📖 ለጧኢፉል‐መዓሪፍ
❤34👍3