ክህደት ክፍል 07 - Destination unknown
የሆሄያት ህብር| @gGetem
ክህደት ክፍል 08 - Destination unknown
የሆሄያት ህብር| @gGetem
ክህደት ክፍል 09 - Destination unknown
የሆሄያት ህብር| @gGetem
[በሠላሳ ክረምት]
.
.
ከቦኛል ፍርሀት ከቦኛል እርጅና
የጉብዝናው ወራት
በወጉ በወጉ አላለፈምና።
ያወዛውዘኛል የአዝማናት ነፋስ
መደገፊያ ምርኩዝ ከማን ብርቱ ልዋስ?
እነሳ የነበርኩ ተስፈንጥሬ እንዳነር
እራመድ የነበርኩ በግሮቼ ጀግኜ
ክንፌን ቆርጬ ጣልኩ ከፍርሀት ወግኜ።
ሳዘግም
እግሮቼ ሲርዱ
ስተኛ ጭኖቼ ሲበርዱ
የገላዬ ሙቀት ሲሸሽ ቀን ጠብቆ
ቆፈን ሲዳበለኝ እንደስም ተጣብቆ
እትቱ ዘፈኔ
ፀደይ እንዳልወጣ በጋን እንዳልገፋ
ግንባሩ ላይ ይዟል የማለፍ ወረፋ።
በሰላሳ ክረምት በሰላሳ በጋ
ገሚሱ የርግማን ጥቂቱ የፀጋ
ተብዬ ብጠየቅ “ምን አደረክበት?”
መልሴ
እንደሞላለት ሰው ዝም ብዬ ኖርኩበት።
@gGetem
@gGetem
.
.
ከቦኛል ፍርሀት ከቦኛል እርጅና
የጉብዝናው ወራት
በወጉ በወጉ አላለፈምና።
ያወዛውዘኛል የአዝማናት ነፋስ
መደገፊያ ምርኩዝ ከማን ብርቱ ልዋስ?
እነሳ የነበርኩ ተስፈንጥሬ እንዳነር
እራመድ የነበርኩ በግሮቼ ጀግኜ
ክንፌን ቆርጬ ጣልኩ ከፍርሀት ወግኜ።
ሳዘግም
እግሮቼ ሲርዱ
ስተኛ ጭኖቼ ሲበርዱ
የገላዬ ሙቀት ሲሸሽ ቀን ጠብቆ
ቆፈን ሲዳበለኝ እንደስም ተጣብቆ
እትቱ ዘፈኔ
ፀደይ እንዳልወጣ በጋን እንዳልገፋ
ግንባሩ ላይ ይዟል የማለፍ ወረፋ።
በሰላሳ ክረምት በሰላሳ በጋ
ገሚሱ የርግማን ጥቂቱ የፀጋ
ተብዬ ብጠየቅ “ምን አደረክበት?”
መልሴ
እንደሞላለት ሰው ዝም ብዬ ኖርኩበት።
@gGetem
@gGetem
.......
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኘናቸው
ስመን ጠቆምናቸው
በተዘጋ ጎጆ
በእንባ እየተራጨን
ከመገፋት ጽዋ
በቀል ተጎነጨን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ነን ብለን አመንን
ውበትን ለመንን
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኛናቸው
በእናባ ጸለይናቸው
ፍቅርን ተሳልን
በበቀል ቆሰልን
ሳሚ ያጣ ከንፈር
አቃፊ ያጣ ገላ
የወደድነው ሁላ
ጸጸት አስጎነጨን
ስቆ ለእንባ እያጨን
አሸሸ መዳፋን
ነፈገን እቅፋን
ጸደቁብን በቃል
ውበት ልብ ይበቃል
ብለው ልብን ሸሹ
ገፍተው አቆሸሹ
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራምም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ጉለት ሆንን ያምላካቸው
ያምላካችን
በመልካችን
ለወደድነው አነስን
ለአፈቀርነው እረከስን
ተጎነጨን መገፋትን
መተፋትን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኘናቸው
ስመን ጠቆምናቸው
በተዘጋ ጎጆ
በእንባ እየተራጨን
ከመገፋት ጽዋ
በቀል ተጎነጨን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ነን ብለን አመንን
ውበትን ለመንን
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኛናቸው
በእናባ ጸለይናቸው
ፍቅርን ተሳልን
በበቀል ቆሰልን
ሳሚ ያጣ ከንፈር
አቃፊ ያጣ ገላ
የወደድነው ሁላ
ጸጸት አስጎነጨን
ስቆ ለእንባ እያጨን
አሸሸ መዳፋን
ነፈገን እቅፋን
ጸደቁብን በቃል
ውበት ልብ ይበቃል
ብለው ልብን ሸሹ
ገፍተው አቆሸሹ
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራምም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ጉለት ሆንን ያምላካቸው
ያምላካችን
በመልካችን
ለወደድነው አነስን
ለአፈቀርነው እረከስን
ተጎነጨን መገፋትን
መተፋትን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ክህደት ክፍል 10 - Destination unknown
የሆሄያት ህብር| @gGetem
ከዳመናው መሀል ይፈልቃል ኃያል ጢስ
ድል ለሀገሬ ሊሰጥ
በፈረሱ ይነጉዳል የአራዳው ጊዮርጊስ
ይዘምታል በሰማይ አማኝ ህዝቡን ከልሎ
የአምላክ ውብ ምድር
ቅድስት ኢትዮጵያ አትደፈር ብሎ
ይጎርፋል ሰው
ጦር ጋሻውን በእጁ አንጠልጥሎ
ምንሽር አልቤኑን በጀርባው ላይ አዝሎ
በባዶ እግሩ ጋሬጣውን ረቶ
እንዴትስ ይቀራል
ከንጉሱ ከንፈር የማርያም ስም ወጥቶ
ልክ እንደ ጦር እቃ ታቦት ተሸክሞ
ልክ እንደ አዘቦት ቀን በጾም ተሸልሞ
ቅንጣት እህል ሳይጎርስ በእምነቱ ቁሞ
ቅዳሴውን ሳይሽር በሰዓቱ ተገኝቶ
‹‹አሀዱ›› ሲል በህብረት አንድነት ገንብቶ
የዋለ ገበሬ የዋለ ሰራዊት
ድል አፍሶ ቢመለስ ይደንቃል ወይ ጥቂት?
(አይደንቅም)
አቡነ ማቲዎስ እምነትን አግዝፈው
ለሰራዊት ሲባል
‹‹ጾም ይሻር›› የሚል ትእዛዝ ተላልፈው
ከንጉስ ተሟግተው
በመስቀል አሳልመው
ባርከው ተዋጊውን ቢልኩ ወደ ውጊያ
ሰው በእህል ሳይሆን
በእምነት እንደሚረታ
ምስክር ትሆን ዘንድ አሸነፈች ጦቢያ
እኔ ግን
የድል ታሪክ ይዤ
ቆሚያለሁ ፈዝዤ
ተኝቻለሁ ደንዝዤ
አልስራ ጀብድ አልፈጽም ገድል
እንዴት ያቅተኛል
መዘከር እንኳን የአባቶቼን ድል?
ቢገባኝ ኖሮ የነጻነት ክብር
የካቲት ጊዮርጊስ
ስዕለት ባስገባሁ ለመቆሜ ተአምር
በባዶ እግር ሄዶ ጫማ ያለበሰኝ
ከአራቱም አቅጣጫ
ለአንድ አላማ ዘምቶ ሀገር ያወረሰኝ
በዘር ጎጠኝነት
ተከፋፍዬ ቢያይ በእንባው በወቀሰኝ
‹‹ ከአንድነት እርካብ ቁልቁል ተፈጥፍጠህ
በቁንጽል ማንነት ራስክን ለውጠህ
የምትኖር ሁላ አድዋን አስታውሰህ
ሁን እንደ ጥንቱ ፍቅርን ተንተርሰህ
አሻፈረኝ ካልክ ግን
‹‹ማርያምን!›› እፋረድኃለው በሰማይ
በሀገሬ ጀርባ ላይ ፈልተኃል እንደ ተባይ ››
ብሎ ባወጀብኝ
ሽልብታዬን አይቶ
እብደቴን ታዝቦ ከሞቴ ባነቃኝ
ጾም ጸሎትን ትቼ
አርብ ሮብን ረስቼ
ቅዳሴ ሰዓታት
ማህሌት ኪዳንን እኒህን ዘንግቼ
ለሆዴ አድሬ ስኖር እንደ አሳማ
ይደንቃል ወይ እውነት
ተረግጬ ብቀር ልክ እንደ ቄጤማ?
ተንኜ ብቀር ልክ እንደ ጤዛ?
ተሸንፌ ብታይ ወድቄ እንደ ዋዛ?
(አይደንቅም)
ዋ ለእኔ!
ዋ እኔ!
ርግብ ጋር ዘምቼ
ለቀረሁኝ ሞቼ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
ድል ለሀገሬ ሊሰጥ
በፈረሱ ይነጉዳል የአራዳው ጊዮርጊስ
ይዘምታል በሰማይ አማኝ ህዝቡን ከልሎ
የአምላክ ውብ ምድር
ቅድስት ኢትዮጵያ አትደፈር ብሎ
ይጎርፋል ሰው
ጦር ጋሻውን በእጁ አንጠልጥሎ
ምንሽር አልቤኑን በጀርባው ላይ አዝሎ
በባዶ እግሩ ጋሬጣውን ረቶ
እንዴትስ ይቀራል
ከንጉሱ ከንፈር የማርያም ስም ወጥቶ
ልክ እንደ ጦር እቃ ታቦት ተሸክሞ
ልክ እንደ አዘቦት ቀን በጾም ተሸልሞ
ቅንጣት እህል ሳይጎርስ በእምነቱ ቁሞ
ቅዳሴውን ሳይሽር በሰዓቱ ተገኝቶ
‹‹አሀዱ›› ሲል በህብረት አንድነት ገንብቶ
የዋለ ገበሬ የዋለ ሰራዊት
ድል አፍሶ ቢመለስ ይደንቃል ወይ ጥቂት?
(አይደንቅም)
አቡነ ማቲዎስ እምነትን አግዝፈው
ለሰራዊት ሲባል
‹‹ጾም ይሻር›› የሚል ትእዛዝ ተላልፈው
ከንጉስ ተሟግተው
በመስቀል አሳልመው
ባርከው ተዋጊውን ቢልኩ ወደ ውጊያ
ሰው በእህል ሳይሆን
በእምነት እንደሚረታ
ምስክር ትሆን ዘንድ አሸነፈች ጦቢያ
እኔ ግን
የድል ታሪክ ይዤ
ቆሚያለሁ ፈዝዤ
ተኝቻለሁ ደንዝዤ
አልስራ ጀብድ አልፈጽም ገድል
እንዴት ያቅተኛል
መዘከር እንኳን የአባቶቼን ድል?
ቢገባኝ ኖሮ የነጻነት ክብር
የካቲት ጊዮርጊስ
ስዕለት ባስገባሁ ለመቆሜ ተአምር
በባዶ እግር ሄዶ ጫማ ያለበሰኝ
ከአራቱም አቅጣጫ
ለአንድ አላማ ዘምቶ ሀገር ያወረሰኝ
በዘር ጎጠኝነት
ተከፋፍዬ ቢያይ በእንባው በወቀሰኝ
‹‹ ከአንድነት እርካብ ቁልቁል ተፈጥፍጠህ
በቁንጽል ማንነት ራስክን ለውጠህ
የምትኖር ሁላ አድዋን አስታውሰህ
ሁን እንደ ጥንቱ ፍቅርን ተንተርሰህ
አሻፈረኝ ካልክ ግን
‹‹ማርያምን!›› እፋረድኃለው በሰማይ
በሀገሬ ጀርባ ላይ ፈልተኃል እንደ ተባይ ››
ብሎ ባወጀብኝ
ሽልብታዬን አይቶ
እብደቴን ታዝቦ ከሞቴ ባነቃኝ
ጾም ጸሎትን ትቼ
አርብ ሮብን ረስቼ
ቅዳሴ ሰዓታት
ማህሌት ኪዳንን እኒህን ዘንግቼ
ለሆዴ አድሬ ስኖር እንደ አሳማ
ይደንቃል ወይ እውነት
ተረግጬ ብቀር ልክ እንደ ቄጤማ?
ተንኜ ብቀር ልክ እንደ ጤዛ?
ተሸንፌ ብታይ ወድቄ እንደ ዋዛ?
(አይደንቅም)
ዋ ለእኔ!
ዋ እኔ!
ርግብ ጋር ዘምቼ
ለቀረሁኝ ሞቼ
@gGetem
@gGetem
@gGetem
..........
አላቅም
አታቅም
የልቧን ተናግራ
ዝምታ ሰብራ
ጭምት ነበረች
እኔን ስታገኝ
ቃላት ፈጠረች
የፊደል አይደል
የቋንቋ በደል
ውሸት ነው የሚሉት
ነገ ላይ ደርሰው
ክደው
አፍርሰው
የቋንቋ አይደለም
በፍቅር ቀለም
ከገጽ ከአካሏ
ምልክት ስላ
ከሩቅ ነበረ ያናገረቺኝ
ደምቃ የታየቺኝ
አታቅም
አላቅም
ሴት አሽኮርምሜ
ከንፈር ተስሜ
ገላን በጠረን
ናፍቆት በዘፈን
አላባበልኩም
አላጫወትኩም
ጭምት ነበርኩኝ
ሰው የሚሞቀኝ
ወሬ የሚርቀኝ
ጥርሶቼ ስቀው
እግሬ ቦርቀው
ቀን ያላለፉ
አንቺ ጋር ደርሰው
ተኮላተፉ
መሳም አማረኝ
ያማረ ጉንጯን
አገጭ.....አገጯን
እየደጋገሙ
እየደጋገሙ
መኖር እየሳሙ
ከእቅፏ
ከአፏ
ህይወት ታዘንባለች
መኖር ታስርባለች
እየደጋገሙ
እየደጋገሙ
ክፉዋን ሳይሰሙ
አምላክ እንደው ጨካኝ
ክፉ
ዐዕላፍ ሳይረግፋ
የሰው መንጋ
ሞት ከደጇ ላይጠጋ
ገዝቼላት ሞትን
መለየትን
ከዘር እዳ ልነጥላት
እኔው ሞቷን ልሙትላት
ዕድሜ አውሼ
ተውሼ
ከእባብ ከሚዳቆ
ከዛፍ ከሸንበቆ
ትንሽ ዕለት
ትንሽ አመት
ተመጽውቼ
ልሙትላት
ሞቷን ትቼ
አላቅም
አታቅም
ብቻ በሰው አቅም
አኛን አንደገባን
መፋቀር ነው ብለን
አንድ ጎጆ ገባን
የጭምቶች ፍቅር
የአይናፈሮች ሀገር
ማገር
ሆነልኝ አለማወቋ
አታቅም እንጂ
ያሰግራል ሳቋ
ሀቋ
ከፊቷ ላይ ቅራኔ የለም
የኔ አለም
ባታቅም
ባላቅም
በሰው አቅም
እኔና እሷን እንደገባን
መፋቀር ነው ብለን
አንድ ጎጆ ገባን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
አላቅም
አታቅም
የልቧን ተናግራ
ዝምታ ሰብራ
ጭምት ነበረች
እኔን ስታገኝ
ቃላት ፈጠረች
የፊደል አይደል
የቋንቋ በደል
ውሸት ነው የሚሉት
ነገ ላይ ደርሰው
ክደው
አፍርሰው
የቋንቋ አይደለም
በፍቅር ቀለም
ከገጽ ከአካሏ
ምልክት ስላ
ከሩቅ ነበረ ያናገረቺኝ
ደምቃ የታየቺኝ
አታቅም
አላቅም
ሴት አሽኮርምሜ
ከንፈር ተስሜ
ገላን በጠረን
ናፍቆት በዘፈን
አላባበልኩም
አላጫወትኩም
ጭምት ነበርኩኝ
ሰው የሚሞቀኝ
ወሬ የሚርቀኝ
ጥርሶቼ ስቀው
እግሬ ቦርቀው
ቀን ያላለፉ
አንቺ ጋር ደርሰው
ተኮላተፉ
መሳም አማረኝ
ያማረ ጉንጯን
አገጭ.....አገጯን
እየደጋገሙ
እየደጋገሙ
መኖር እየሳሙ
ከእቅፏ
ከአፏ
ህይወት ታዘንባለች
መኖር ታስርባለች
እየደጋገሙ
እየደጋገሙ
ክፉዋን ሳይሰሙ
አምላክ እንደው ጨካኝ
ክፉ
ዐዕላፍ ሳይረግፋ
የሰው መንጋ
ሞት ከደጇ ላይጠጋ
ገዝቼላት ሞትን
መለየትን
ከዘር እዳ ልነጥላት
እኔው ሞቷን ልሙትላት
ዕድሜ አውሼ
ተውሼ
ከእባብ ከሚዳቆ
ከዛፍ ከሸንበቆ
ትንሽ ዕለት
ትንሽ አመት
ተመጽውቼ
ልሙትላት
ሞቷን ትቼ
አላቅም
አታቅም
ብቻ በሰው አቅም
አኛን አንደገባን
መፋቀር ነው ብለን
አንድ ጎጆ ገባን
የጭምቶች ፍቅር
የአይናፈሮች ሀገር
ማገር
ሆነልኝ አለማወቋ
አታቅም እንጂ
ያሰግራል ሳቋ
ሀቋ
ከፊቷ ላይ ቅራኔ የለም
የኔ አለም
ባታቅም
ባላቅም
በሰው አቅም
እኔና እሷን እንደገባን
መፋቀር ነው ብለን
አንድ ጎጆ ገባን
@gGetem
@gGetem
@gGetem
መለያየት ማለት
እየው ትላንትና ከትላንትም በስቲያ
ያዩሽ ሰዎች ሁሉ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ ዓለም ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው
ለእኔ እና ለአንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
ያለመተያየት መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ሕይወት
ዘወትር ዘወትር ምናልባት
ምናልባት እያለች የምትኖር ሕይወት
በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት
በተስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው
ልቤና ልቡናው ተጣብቋል በያቸው
እንጂ በእኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት
By Efrem seyoum
@gGetem
@gGetem
እየው ትላንትና ከትላንትም በስቲያ
ያዩሽ ሰዎች ሁሉ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ ዓለም ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው
ለእኔ እና ለአንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
ያለመተያየት መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ሕይወት
ዘወትር ዘወትር ምናልባት
ምናልባት እያለች የምትኖር ሕይወት
በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት
በተስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው
ልቤና ልቡናው ተጣብቋል በያቸው
እንጂ በእኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት
By Efrem seyoum
@gGetem
@gGetem
እሙ...አንቺን እያሰብኩኝ
ግጥም ልፅፍ ተነሳሁኝ
ግና ደግሞ አንዴት ብዬ...
........እንዴት ብዬ እንደምገልፅሽ ግራ ገባኝ
ቃሉ ሁሉ አነሰብኝ
ትናንትና ስለ ፍቅር ብዙ ፅፌ
እልፍን ስንኝ አሰልፌ
ነፍስን ከስጋ ስነጥል
ከጨረቃ ግድም ሳውል
ፍጡሩን ሰው ከፀሃይ ጋር ሳስተካከል
በባዶነት ለታሰረው የተስፋን ጠል ሳወርድለት
ሀዘን ሰብሮት ለሚያለቅሰው መፅናናትን ስሆንለት....እንዳልነበር
ዛሬ ግና.....ላንቺ የሚሆን ፈልጌ አጣው
እንዴት ብዬ አሙን በቃል
እንዴት ሊሆን....?እንዴት አንቺን በቃል
የለም እኮ የሚገልፅሽ ከስነ-ቃል
የለም እኮ......የለም
ገጣሚ ጆሲ(Joy see)
※※※※※ ሼር ያድርጉ!! ※※※※※
አዘጋጅ፦ண @gGetem
ண @gGetem
═══════ ♢.✰.♢ ════
ግጥም ልፅፍ ተነሳሁኝ
ግና ደግሞ አንዴት ብዬ...
........እንዴት ብዬ እንደምገልፅሽ ግራ ገባኝ
ቃሉ ሁሉ አነሰብኝ
ትናንትና ስለ ፍቅር ብዙ ፅፌ
እልፍን ስንኝ አሰልፌ
ነፍስን ከስጋ ስነጥል
ከጨረቃ ግድም ሳውል
ፍጡሩን ሰው ከፀሃይ ጋር ሳስተካከል
በባዶነት ለታሰረው የተስፋን ጠል ሳወርድለት
ሀዘን ሰብሮት ለሚያለቅሰው መፅናናትን ስሆንለት....እንዳልነበር
ዛሬ ግና.....ላንቺ የሚሆን ፈልጌ አጣው
እንዴት ብዬ አሙን በቃል
እንዴት ሊሆን....?እንዴት አንቺን በቃል
የለም እኮ የሚገልፅሽ ከስነ-ቃል
የለም እኮ......የለም
ገጣሚ ጆሲ(Joy see)
※※※※※ ሼር ያድርጉ!! ※※※※※
አዘጋጅ፦ண @gGetem
ண @gGetem
═══════ ♢.✰.♢ ════