😲
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ፈረስ ናቹ አሉን
ባዶ ስም ተረፈን
ያለምልክቱ ያለማዕረጉ
በአህዮች ጫንቃ ላይ ፥ ኮርቻ እያረጉ።
ገፍትረው ሲጥሉን ፥ አውቀን የተደፋን
ጎትተው ሲጥሉን ፥ ወድቀን የተደፋን
ወድቆ መነሳትን...
ቢያዩት ብለን እንጂ
እንቅፋት መሆኑ ፥ እኛስ መቼ ጠፋን ?
ዝቅ ዝቅ ፥ እያደሩ ማነስ
ሌት ያነጠፉትን ፥ ቀን መልሶ መልበስ።
ግር ብለው ሄደው ፥ ግር ብለው መጡ
እውነት ስትገለጥ ፥ በየተራ ወጡ
ወትሮስ በሐሰት ችሎት ፥ ማንን ነው ሚቀጡ?
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🎬 ፍራሽ አዳሽ
ተስፋሁን ከበደ
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
አስተያየት 👉🏽 @leoyri
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ፈረስ ናቹ አሉን
ባዶ ስም ተረፈን
ያለምልክቱ ያለማዕረጉ
በአህዮች ጫንቃ ላይ ፥ ኮርቻ እያረጉ።
ገፍትረው ሲጥሉን ፥ አውቀን የተደፋን
ጎትተው ሲጥሉን ፥ ወድቀን የተደፋን
ወድቆ መነሳትን...
ቢያዩት ብለን እንጂ
እንቅፋት መሆኑ ፥ እኛስ መቼ ጠፋን ?
ዝቅ ዝቅ ፥ እያደሩ ማነስ
ሌት ያነጠፉትን ፥ ቀን መልሶ መልበስ።
ግር ብለው ሄደው ፥ ግር ብለው መጡ
እውነት ስትገለጥ ፥ በየተራ ወጡ
ወትሮስ በሐሰት ችሎት ፥ ማንን ነው ሚቀጡ?
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
🎬 ፍራሽ አዳሽ
ተስፋሁን ከበደ
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
አስተያየት 👉🏽 @leoyri
┏─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─┓
❘ ❝ ሰው፡ከሆኑ፡በቂያችን፡ነው። ❞ ᴀ ❘
┗─━─━─━─━≪♡≫━─━─━─━─
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo Leጅ)
#ይህች የአሁን ጠሀይ
(ሚካኤል .አ)
ቦግ እልም... ቦግ እልም
ቦግ እልም.. .ቦግ እልም
ወዳጄ ሆይ ቆዝም!
መኖሪያን ማበጀት
በንዋይ መደርጀት
ከእንስት ጭኖች ስር መቅጠፍ አንዲት በለስ
በትዝታ ቅኝት ቅኔ ወጉን መድረስ
ማጣጣም ሙዚቃ
መንገስ እንደ አለቃ
የማለዳ ፀሀይ
የደረጀ ንዋይ
የአንገት ሀብል ማሰር.. .
በውድ ወይን መስከር
መኪና ማሽከርከር
መደነስ መጨፈር.. .
አይንን በአይን ማየት
ስንዴን ከእንክርዳድ ለይቶ ማበርየት
ከቤተሰብ ጋራ ጨዋታን መጋራት
ከምቹ አልጋ ላይ ያለ ሀሳብ መተኛት
ደማቅ ታሪክ መፃፍ
የእውቅና በራፍ ...
ሁሉም ደስታ ናቸው
ቦግ እልም... ቦግ እልም
ቦግ እልም.. .ቦግ እልም
ከዚህ ሀሴት ማዶ ወዳጄ ሆይ ቆዝም
ሁሉም ይላል እልም!
ትጠልቃለች ፀሀይ... መድረሻህ ነው አፈር
አሁን ብርሀን ሳለ
ለእግዜር ቀብድ ስጠው ... ከሱ እልፍኝ ለማደር።
@gGetem
@gGetem
@leoyri
(ሚካኤል .አ)
ቦግ እልም... ቦግ እልም
ቦግ እልም.. .ቦግ እልም
ወዳጄ ሆይ ቆዝም!
መኖሪያን ማበጀት
በንዋይ መደርጀት
ከእንስት ጭኖች ስር መቅጠፍ አንዲት በለስ
በትዝታ ቅኝት ቅኔ ወጉን መድረስ
ማጣጣም ሙዚቃ
መንገስ እንደ አለቃ
የማለዳ ፀሀይ
የደረጀ ንዋይ
የአንገት ሀብል ማሰር.. .
በውድ ወይን መስከር
መኪና ማሽከርከር
መደነስ መጨፈር.. .
አይንን በአይን ማየት
ስንዴን ከእንክርዳድ ለይቶ ማበርየት
ከቤተሰብ ጋራ ጨዋታን መጋራት
ከምቹ አልጋ ላይ ያለ ሀሳብ መተኛት
ደማቅ ታሪክ መፃፍ
የእውቅና በራፍ ...
ሁሉም ደስታ ናቸው
ቦግ እልም... ቦግ እልም
ቦግ እልም.. .ቦግ እልም
ከዚህ ሀሴት ማዶ ወዳጄ ሆይ ቆዝም
ሁሉም ይላል እልም!
ትጠልቃለች ፀሀይ... መድረሻህ ነው አፈር
አሁን ብርሀን ሳለ
ለእግዜር ቀብድ ስጠው ... ከሱ እልፍኝ ለማደር።
@gGetem
@gGetem
@leoyri
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
🤐👱♀እህህ👱♀😴
#ገጣሚ_ረድኤት_አሰፋ
#አንባቢ_መክሊት_Z
የሆሄያት ህብር🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@gGetem
@gGetem
💥አዲስ አቅራቢያችን ስለሆነች እንደተለመደው ሀሳብ አስተያየታችሁን አድርሱን።
#ገጣሚ_ረድኤት_አሰፋ
#አንባቢ_መክሊት_Z
የሆሄያት ህብር🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@gGetem
@gGetem
💥አዲስ አቅራቢያችን ስለሆነች እንደተለመደው ሀሳብ አስተያየታችሁን አድርሱን።
በላይ በቀለ ወያ
.
ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል።
።።።
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢመስል...
ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ....
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ.
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
።።።።።
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
።።።።
ነግሬሽ ነበረ
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
።።።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
።።።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
@gGetem
.
.
.
.
.
.
@www.tg-me.com/leoyri
.
ገላሽ ገላ አይመርጥም ፣ ከሁሉ ይጋደማል
ከንፈርሽ አየር ነው ፣ በሁሉም ይሳማል
ከሴት ክብርሽ ይልቅ ፣ ስሜትሽ ይቀድማል።
።።።
ነግሬሽ ነበረ፡፡
ጭን ከሰማይ ቢገዝፍ ፣ ከጭንቅላት ያንሳል
ምን ተራራ ቢመስል...
ጡትም አቅመ ቢስ ነው ፣ ሲነኩት ይፈርሳል፡፡
ነግሬሽ ነበረ....
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯ የአምላክ ነው ፣ እንደ እናት ስታስብ!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ክብረቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ ፣ እናቶች አይደሉም
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ.
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
።።።።።
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።
ሴት ክብሯን ስታጣ ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
።።።።
ነግሬሽ ነበረ
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ስሜት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።
።።።
ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።
።።።
ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይተኛታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!
@gGetem
.
.
.
.
.
.
@www.tg-me.com/leoyri
Telegram
Sirake Péterøs👦☞Ye Yerijo Leጅ
ሰኔ 16😘 kidanua🥰
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
ምሽት በረንዳ ላይ
(በእውቀቱ ስዩም)
አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ
በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤
“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”
እያልሁ አስባለሁ፥
ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ
በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤
በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::
@gGetem
@gGetem
@sirak6
(በእውቀቱ ስዩም)
አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ
በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤
“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”
እያልሁ አስባለሁ፥
ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ
በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤
በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::
@gGetem
@gGetem
@sirak6
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#በአንቀልባ_ያዘለው
────────────
"ረገጥኩት!" ይላል ፥ ሰይጣንን በእግሬ
"ጨፈለኩት!" ይላል ፥ ያንን ክፉ አውሬ
መሬት እየደቃ ፥ ዘራፍ ይላል ጃሎ
"እዩት ጣልኩት!" ይላል ፥ የሞተውን ገ'ሎ
ጄነራሉን ሰይጣን ፥ በጀርባው ላይ አዝሎ ።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ሰሎሞን ሞገስ
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ምንጭ ➸ ብዕር ያለው ያውጋ
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
አስተያየት 👉🏽 @Leoyri
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨ #ዛሬን_ያነበበ ፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨ #ነገን_ይማራል❗️፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#በአንቀልባ_ያዘለው
────────────
"ረገጥኩት!" ይላል ፥ ሰይጣንን በእግሬ
"ጨፈለኩት!" ይላል ፥ ያንን ክፉ አውሬ
መሬት እየደቃ ፥ ዘራፍ ይላል ጃሎ
"እዩት ጣልኩት!" ይላል ፥ የሞተውን ገ'ሎ
ጄነራሉን ሰይጣን ፥ በጀርባው ላይ አዝሎ ።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ሰሎሞን ሞገስ
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ምንጭ ➸ ብዕር ያለው ያውጋ
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
አስተያየት 👉🏽 @Leoyri
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨ #ዛሬን_ያነበበ ፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨ #ነገን_ይማራል❗️፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
▨▨▨▨▨▨▨▨▨▨▨
#እንስተ_ፀሎት
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ ©
የሆሄያት ህብር™🦋🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
www.tg-me.com/leoyri
www.tg-me.com/gGetem
Mole Enter_🍁
Plc share&Join
🎤🎬 #ሳሮን_ተክለ_ወልድ©
ተፃፈ፦04-09-2015ዓ.ም
የሳምንቱ_ ለ
▦▦▦▦▦▦▦▦▦▦▥▦▦▦
በትዕግስት ለጠበቃችሁን ከልብ እናመሰግናለን ።❤️🙏
#እንስተ_ፀሎት
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ ©
የሆሄያት ህብር™🦋🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
www.tg-me.com/leoyri
www.tg-me.com/gGetem
Mole Enter_🍁
Plc share&Join
🎤🎬 #ሳሮን_ተክለ_ወልድ©
ተፃፈ፦04-09-2015ዓ.ም
የሳምንቱ_ ለ
▦▦▦▦▦▦▦▦▦▦▥▦▦▦
በትዕግስት ለጠበቃችሁን ከልብ እናመሰግናለን ።❤️🙏
🇪🇹እሮብ ሚያዝያ ፳፰ ፳፻፲፪ ዓ.ም
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ሰው_ብቻ
───────
አሁንማ ጀንበር ገባች
አይናችን ስር ተስፋ ሞተ
የመጀገን ቀን አበቃ
የስንፋናህ ዘመን ባተ
አልልህም ምን ብደክም
ርቃን እውነት አስገርፎኝ
በበደልህ ብታሸንፍ
ሀቄ በቁም ህይወት ገፎኝ
መኖርና መሞት መሀል
ያለን ጣዕም አስክረሳ
ባሳልፍም ብዙ ዘመን
እርጥብ ቁስል እልፍ አበሳ
ሙት አለሜ ደስ ብሎኛል!
ዋንዛ ልብህ እንደሙጃ
ሲልፈሰፈስ ተሸንፎ
ጥቅጥቅ ነፍስ ሲገላለጥ
ወና ሲሆን እንደቀፎ
ኧረ አሜን ነው
አሜን አሜን
ደግሞ አሜን አሜን ብዙ
"ይቅርታ" ሲል ይገለጣል
ትሁት ሲሆን የሰው ወዙ
ኧረ አሜን ነው የምን እንቢ
ቀን ጣለልኝ ብሎ ጉራ
ሰው መሆኑ ከስጋ ያልፋል
ለወደቀ ሰው ሲራራ
ልመናዬ እዬ ዬ ዬ
አልነበረም ከንፈሮቼ
ከንፈርህን እንዲስሙ
አልነበረም ወይም ጥዬህ
ድል ማድረጌን እንዲሰሙ
ባንተ አዝኜ እንዳይጠፋኝ
ነበር ያልኩት የሰው መልኩ
ተመስገን ዛሬ አሳየህ
አላነሰም አልወረደም
ከሰውነት የሰው ልኩ ።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ቤተልሔም ታችበል
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ምንጭ ➸ የሚካኤል አስጨናቂ ግጥሞች
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨ #ዛሬን_ያነበበ ፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨ #ነገን_ይማራል❗️፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#ሰው_ብቻ
───────
አሁንማ ጀንበር ገባች
አይናችን ስር ተስፋ ሞተ
የመጀገን ቀን አበቃ
የስንፋናህ ዘመን ባተ
አልልህም ምን ብደክም
ርቃን እውነት አስገርፎኝ
በበደልህ ብታሸንፍ
ሀቄ በቁም ህይወት ገፎኝ
መኖርና መሞት መሀል
ያለን ጣዕም አስክረሳ
ባሳልፍም ብዙ ዘመን
እርጥብ ቁስል እልፍ አበሳ
ሙት አለሜ ደስ ብሎኛል!
ዋንዛ ልብህ እንደሙጃ
ሲልፈሰፈስ ተሸንፎ
ጥቅጥቅ ነፍስ ሲገላለጥ
ወና ሲሆን እንደቀፎ
ኧረ አሜን ነው
አሜን አሜን
ደግሞ አሜን አሜን ብዙ
"ይቅርታ" ሲል ይገለጣል
ትሁት ሲሆን የሰው ወዙ
ኧረ አሜን ነው የምን እንቢ
ቀን ጣለልኝ ብሎ ጉራ
ሰው መሆኑ ከስጋ ያልፋል
ለወደቀ ሰው ሲራራ
ልመናዬ እዬ ዬ ዬ
አልነበረም ከንፈሮቼ
ከንፈርህን እንዲስሙ
አልነበረም ወይም ጥዬህ
ድል ማድረጌን እንዲሰሙ
ባንተ አዝኜ እንዳይጠፋኝ
ነበር ያልኩት የሰው መልኩ
ተመስገን ዛሬ አሳየህ
አላነሰም አልወረደም
ከሰውነት የሰው ልኩ ።
┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
✍🏽© ቤተልሔም ታችበል
╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈
ምንጭ ➸ የሚካኤል አስጨናቂ ግጥሞች
ለመቀላቀል 👉🏽 @gGetem
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨ #ዛሬን_ያነበበ ፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨ #ነገን_ይማራል❗️፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የባከነ ሌሊት!!!!
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@gGetem
@gGetem
@leoyri
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@gGetem
@gGetem
@leoyri
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)