**የአብስራ ሳሙኤል**
**የማርያም መንገድ ስጪኝ**
ደክሚያለው አንቺው አውጪኝ!
የማርፍ የምሸሸግበት
ትንሽ ቦታ ትንሽ ህይወት
የስቃይ አውዱን ማለፊያ
የጊዜን መልህቅ መቅዘፊያ
**የማርያም መንገድ አበጂ**
የእድሜዬን ስንዝሯን ሂጂ
ኩሬ ነው ያልኩት ባህር ካከለ
ወዳጅ ነው ያልኩት ጦሩን ከሳለ
በምን ልታገል አቅም አነሰኝ
ያመንኩት ገላ ፍም ካንተራሰኝ
ካልሞላ ጽዋው የዘር እዳዬ
ወድቆ አፈር ይሁን በምን ተዳዬ
በምን ልጋፋው በምን ልታገል
መንገድሽን ስጪኝ እንድገላገል
ደካማ ጎኔን ልመሽግበት
ክፉ ቀናቴን ልሸሸግበት
አላውቅም ልበል የለሁም ልበል
አልችልም በቃኝ አቃተኝ ልበል
ወደ ማረፊያው ምሪኝ
ትግል ከሌለበት ጥሪኝ
የአበባ ገላ ከማይረግፍበት
ማላዳ ኮከብ ከማይጎልበት
**ሁሉ ባይሞላም ከማይጎድልበት**
**ምሪኝ ልሸሸግበት**
**የማርያም መንገድ ስጪኝ**
**ደክሚያለው አንቺው አውጪኝ!**
@getem
@getem
@paappii
የጉሊት እናት
መቀነቷን አጥብቃ ለልጆቿ ብላ
ኑሮን ለማሸነፍ የማይቻል ችላ
ከጠዋት እስከ ማታ እንጀራ ፍለጋ
ነገዋን ልትሰራ ጉልበቷ ሚተጋ
ብርቱ ሴት አንድ አለች
ጥቂት እቃ ይዛ መንገድ ዳር የዋለች፡፡
ዝናብ ሳያግዳት ሀሩር ሳይበግራት
ቁርስ እንኳ ሳትበላ ለልጆቿ እራት
ግልምጫው፣አሽሙሩ፣ሁሉን ተቋቁማ
በውድድር አለም ጨለማውን ቀድማ
ጎህ ሳይቀድ ወጥታ የምትገባ ሌሊት
ምስኪን እናት አለች የምትውል ጉሊት፡፡
ምንም ባታተርፍም ከባህሏ ሳትርቅ
ፍቅሯንና እቃ አብራ የምትመርቅ
የውስጧን አምቃ፣
በጥርሷ ደብቃ፣
ትልቅ ህልም ሰንቃ፤
ውላ የምትገባ በጥቂት ቸርችራ
ዕድሜዋን ሰውታ ቀልጣ ምታበራ
ከጉሊት መንደር ላይ አለች የሴት አውራ፡፡
by @Abuugida
@getem
@getem
@getem
መቀነቷን አጥብቃ ለልጆቿ ብላ
ኑሮን ለማሸነፍ የማይቻል ችላ
ከጠዋት እስከ ማታ እንጀራ ፍለጋ
ነገዋን ልትሰራ ጉልበቷ ሚተጋ
ብርቱ ሴት አንድ አለች
ጥቂት እቃ ይዛ መንገድ ዳር የዋለች፡፡
ዝናብ ሳያግዳት ሀሩር ሳይበግራት
ቁርስ እንኳ ሳትበላ ለልጆቿ እራት
ግልምጫው፣አሽሙሩ፣ሁሉን ተቋቁማ
በውድድር አለም ጨለማውን ቀድማ
ጎህ ሳይቀድ ወጥታ የምትገባ ሌሊት
ምስኪን እናት አለች የምትውል ጉሊት፡፡
ምንም ባታተርፍም ከባህሏ ሳትርቅ
ፍቅሯንና እቃ አብራ የምትመርቅ
የውስጧን አምቃ፣
በጥርሷ ደብቃ፣
ትልቅ ህልም ሰንቃ፤
ውላ የምትገባ በጥቂት ቸርችራ
ዕድሜዋን ሰውታ ቀልጣ ምታበራ
ከጉሊት መንደር ላይ አለች የሴት አውራ፡፡
by @Abuugida
@getem
@getem
@getem
እንዲሁም ኑር ኑር ይለኛል
ልክ ያለው ዝናብ አይቼ
የነፋስ ሽውታ ሰምቼ
የፍቅር መንገድ እርምጃ
መምጣት እንደሆን ገምቼ…
ብን የሚል የሰው ለሆሳስ
ቢጻፍም በደብዛዛ እርሳስ
(ሳይጠፋ እንደሚነበብ)
ገምቼ…
ቢደርቅም ለምለም ቅጠሉ
(እግረኛ ትንፋሽ ሲገርፈው
የመኖር ድምፅ እያወጣ
በመኖር እንደሚረግፈው)
ሲወድቅ እየጠበቁ
ለጆሮ እንደሚበቁ
(የመርገፍ የማረፍ ቃሎች)
ለሰውም ይሰማ የለ
እንኳን ለግዑዝ ሌሎች
እያልኹ…
ከጥቁር ከነጩ ሕይወት
የቱ ክንድ ማን ይለየኛል
እንኳንስ ተፈቅሬበት
እንዲሁም ኑር ኑር ይለኛል።
By yadel tizazu
@getem
@getem
@paappii
ልክ ያለው ዝናብ አይቼ
የነፋስ ሽውታ ሰምቼ
የፍቅር መንገድ እርምጃ
መምጣት እንደሆን ገምቼ…
ብን የሚል የሰው ለሆሳስ
ቢጻፍም በደብዛዛ እርሳስ
(ሳይጠፋ እንደሚነበብ)
ገምቼ…
ቢደርቅም ለምለም ቅጠሉ
(እግረኛ ትንፋሽ ሲገርፈው
የመኖር ድምፅ እያወጣ
በመኖር እንደሚረግፈው)
ሲወድቅ እየጠበቁ
ለጆሮ እንደሚበቁ
(የመርገፍ የማረፍ ቃሎች)
ለሰውም ይሰማ የለ
እንኳን ለግዑዝ ሌሎች
እያልኹ…
ከጥቁር ከነጩ ሕይወት
የቱ ክንድ ማን ይለየኛል
እንኳንስ ተፈቅሬበት
እንዲሁም ኑር ኑር ይለኛል።
By yadel tizazu
@getem
@getem
@paappii
✿༺ *የአብስራ ሳሙኤል* ༻✿
❁───────⋆⋅☆⋅⋆───────❁
⁜ [ ሀገር ነኝ አትበለኝ ] ⁜
⁜ [ ሀገር ሳትሆነኝ ] ⁜
⋆⋅☆⋅⋆───────⋆
♢ እንደ እንጦጦ ለሀፍረቴ ♢
♢ እንደ ኮንሶ ለማጀቴ ♢
❁───────⋆⋅☆⋅⋆───────❁
✧ [ ሀገር ሁነኝ ሀገር ልሁን ] ✧
⁑⁑⁑
✧ [ ሀገር ሁነኝ ሀገር ልሁን ] ✧
❁・゚゚・*:༅。.。༅:*゚:*:✼✿ *:༅。.。༅:*゚・゚゚・❁
@getem
@getem
@getem
❁───────⋆⋅☆⋅⋆───────❁
ሀገር ነኝ ይለኛል
ጠቦ እያየሁት በቋንቋ በመልኩ
እኔ ሀገር የለኝም
ሆዳም የሚቀርጻት የሰፋት በልኩ
⁜ [ ሀገር ነኝ አትበለኝ ] ⁜
⁜ [ ሀገር ሳትሆነኝ ] ⁜
ምስራቅ ሁነኝ ለህይወቴ
ጮራ ሆነህ ቁስሌን ዳሰው
አዋሽ ያርግ ወይም ጣና
የጠማኝ 'ለት የምቀምሰው
⋆⋅☆⋅⋆───────⋆
ልመንብህ እመንብኝ
ሳቅህ አሾህ እንዳያዝል
ከዳሽን ይጽኑ ቃላትህ
ደጀን ሁነኝ እኔ �ስዝል
♢ እንደ እንጦጦ ለሀፍረቴ ♢
♢ እንደ ኮንሶ ለማጀቴ ♢
ሳትሰስት ወይ ሳልሰስት
ልስጥ እልፋን እያበዛው
በማለዳ ይክዳ ዕንባህ
እንደ ለምለም እንደ ጤዛው
❁───────⋆⋅☆⋅⋆───────❁
✧ [ ሀገር ሁነኝ ሀገር ልሁን ] ✧
በማንም ልክ ያልተሰፋ
በማንም ልክ ያልቀረጹት
በከንቱ ቃል የማይጸና
"ነኝ"! በማለት ያላ'ነጹት!
⁑⁑⁑
ቢነጥፍ እንኳ
ያጠባን ጡቷን ሳንነክሰው
መኖሪያ አለን ከተስማማን
ይብቃ በለኝ ያገሬ ሰው
ባልኖርንበት ቢመዝኑን
በታሪክ ጭልፋ ቢጨልፋን
አለት ሁነን አንድንጸና
ንፋስ ሆነው ለሚገፉን
✧ [ ሀገር ሁነኝ ሀገር ልሁን ] ✧
"ነኝ" በሚል ቃል ያላነጹት
ባቀረሸ ታሪካቸው
ባዳፋቸው ያልቀረጹት።
❁・゚゚・*:༅。.。༅:*゚:*:✼✿ *:༅。.。༅:*゚・゚゚・❁
@getem
@getem
@getem
(የሞገሴ ልጅ)
ከቅንነት ማማ-
ከወዳጅ ልብ ላይ - ውብ ገላ ተሰርቶ፣
ብርቱካን ጨዋታ-
ፓፓያ ቁምነገር - አንዠርጎ አፍርቶ።
ትዝታ ጣለ እንጂ-
አሁንን ከነበር - ለይቶ ያወጣ፣
ተናፋቂ ፀባይ፣
ድንቅ ስብእናን - አየን ደርሶን እጣ።
ባለፉ ውብ ቀናት-
ደጃች ውቤ ሰፈር - ጎዳናዋ እስኪላጥ፣
ሳይደክመን የዞርነው፣
በሃሳብ ሽው ይላል - ከትዝታ ሊያሰምጥ።
ከዛ ቅን ልብ ላይ፣
ውበት ያለው ገላ - በአምላክ ተለጥፎ፣
አልያዝ አለ እና፣
ሳይበላ ቀረ ሳይዋጥ ተቀጥፎ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
ከቅንነት ማማ-
ከወዳጅ ልብ ላይ - ውብ ገላ ተሰርቶ፣
ብርቱካን ጨዋታ-
ፓፓያ ቁምነገር - አንዠርጎ አፍርቶ።
ትዝታ ጣለ እንጂ-
አሁንን ከነበር - ለይቶ ያወጣ፣
ተናፋቂ ፀባይ፣
ድንቅ ስብእናን - አየን ደርሶን እጣ።
ባለፉ ውብ ቀናት-
ደጃች ውቤ ሰፈር - ጎዳናዋ እስኪላጥ፣
ሳይደክመን የዞርነው፣
በሃሳብ ሽው ይላል - ከትዝታ ሊያሰምጥ።
ከዛ ቅን ልብ ላይ፣
ውበት ያለው ገላ - በአምላክ ተለጥፎ፣
አልያዝ አለ እና፣
ሳይበላ ቀረ ሳይዋጥ ተቀጥፎ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤
(የአብስራ �ሳሙኤል)
ሀሌ �ሉያ ብርሀን ሆነ
✦✦ ከጥርሶቿ ፍንጭት በኩል ✦✦
መሰከርኩኝ ፈገግ ብላ
❁❁ በዕሳት ላንቃ ምድሩን ስኩል ❁❁
ሀሌ �ሉያ መብረቅ ሳማት
✧ ሄሎሄ አሉኩኝ እኔ አያየው ✧
ለተአምር �ሲፈጥረኝ ነው
✷ ከእሷ መሀጸን የተገኘው ✷
ሀሌ �ሉያ እናቴ �ናት
✺ እልል አሉኩኝ ደስታ ቢያንቀኝ ✺
በረከቷ ምርያ ሀኖ ከመከራ ለጠበቀኝ
✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾
ተአምር ነው ራዕይ ነው
✸ ፋኖስ ሆነኝ አንዲት ነፍሷ ✸
ከህይወት መቅረዝ የሚኖሩት
❃ ብርሀን �ነው እስትንፋሷ ❃
ወፍ ሰፈረ ከጎጆዋ
✵ እ...ሽ አትልም መች ጨክና ✵
ስለመልኳ አዜ'ሙላት
✹ አዲስ ጀንበር ንጋት ሆና ✹
ሀሌ �ሉያ እናቴ ናት
❊ አጃኢብ አልኩ እኔ እያየው ❊
ለተአምር ሲፈጥረኝ ነው
❤ ከእሷ መሀጸን የተገኘው ❤
✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤
@getem
@getem
@getem
(የአብስራ �ሳሙኤል)
ሀሌ �ሉያ ብርሀን ሆነ
✦✦ ከጥርሶቿ ፍንጭት በኩል ✦✦
መሰከርኩኝ ፈገግ ብላ
❁❁ በዕሳት ላንቃ ምድሩን ስኩል ❁❁
ሀሌ �ሉያ መብረቅ ሳማት
✧ ሄሎሄ አሉኩኝ እኔ አያየው ✧
ለተአምር �ሲፈጥረኝ ነው
✷ ከእሷ መሀጸን የተገኘው ✷
ሀሌ �ሉያ እናቴ �ናት
✺ እልል አሉኩኝ ደስታ ቢያንቀኝ ✺
በረከቷ ምርያ ሀኖ ከመከራ ለጠበቀኝ
✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾✾
ተአምር ነው ራዕይ ነው
✸ ፋኖስ ሆነኝ አንዲት ነፍሷ ✸
ከህይወት መቅረዝ የሚኖሩት
❃ ብርሀን �ነው እስትንፋሷ ❃
ወፍ ሰፈረ ከጎጆዋ
✵ እ...ሽ አትልም መች ጨክና ✵
ስለመልኳ አዜ'ሙላት
✹ አዲስ ጀንበር ንጋት ሆና ✹
ሀሌ �ሉያ እናቴ ናት
❊ አጃኢብ አልኩ እኔ እያየው ❊
ለተአምር ሲፈጥረኝ ነው
❤ ከእሷ መሀጸን የተገኘው ❤
✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤✤
@getem
@getem
@getem
✤•⊰❉⊱•✤ የአብስራ ሳሙኤል ✤•⊰❉⊱•✤
☆ * * * * * * * * * * * * * * * ☆
ልብ በይ አለሜ
ንጋት እንዳይመስልሽ ወገግ ያለው ሁሉ
ጀንበር 'ና ጥላ ይመሳሰላሉ
☆ * * * * * * * * * * * * * * * ☆
☀️ 1. ለምሳሌ ☀️
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
አንቺ ከአለሽበት ሴት አዳሪ መንደር
ለዕሳት ዕራት ገላ ዕሳት ሲንደረደር
ጭኗን ለአደባባይ ከፍታ ያመሳቀለች
ጡቷን ለጎዳናው ሸርፋ የሰቀለች
ወንድ ስትራገም ደግሞም ስትጣራ
መንገዱ ሆኖበት በዚህ ለሚያመራ
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂
ማለዳ ጥላ ነው 'ሌት የህይወት መልኩ
የቄሳር ለቄሳር ብለው ለሚረኩ
▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
እናም በዚች መንደር
ከምስራቅ የወጣ ንጋት ያልሽው ጀንበር
ቀንና ለሊቱን እንዳፈራረቀ
ላይነጋ ይበራል ላይመሽ የጠለቀ
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
🌊 ምሳሌ.2 🌊
~~~~
ጉሊት ከምታይው መደብ ከመደበ
የሰማይ እጣቢ ፊቱ እየረገበ
ሸርፎ ሲወስድበት
ነጥቆ ሲያጎልበት
~~~~
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈
ጎርፍ አያሳድድም በውሀ ተሳፍሮ
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
ተመስገን ነው ህይወት
ተመስገን ነው ኑሮ
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
🌫️ ምሳሌ.3 🌫️
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
ብርሌውን አንቆ ከንፈሩን ለሚስም
ተርዚና ወጥሮ ቅጠል ለሚቀስም
ታታሪ ሱሰኛ ህላዌውን ገፊ
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
ጨለማ �ነው ሲልሽ
ጀንበር ወቷል እያልሽ ሀቁን አትጋፊ
▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃
ሳትሰክሪ አታ'ቂውም
ሳትቅሚ አይገባሽም
በሱሰኞች አለም
▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃
✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵
ሳይቃም አይነጋም
ለሰከረ አይመሽሞ
✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵
.·:·. .·:·. .·:·. .·:·.
ልብ በይ 'ሄን ሁሉ
ንጋት እንዳይመስልሽ ወገግ ያለው ሁሉ
.·:·. .·:·. .·:·. .·:·.
✧༺♥༻∞ ∞༺♥༻✧
አምኖ ላደረነው
አሀዱ ወይ አዛን ማለዶ የሚያነቃው
በቀን ለተረሱ
✦⋆✦ ንጋት ነው ኮከቡ ✦⋆✦
✦⋆✦ ንጋት ነው ጨረቃው ✦⋆✦
∞•🌙•✧•☀️•✧•🌙•∞
@getem
@getem
@getem
☆ * * * * * * * * * * * * * * * ☆
ልብ በይ አለሜ
ንጋት እንዳይመስልሽ ወገግ ያለው ሁሉ
ጀንበር 'ና ጥላ ይመሳሰላሉ
☆ * * * * * * * * * * * * * * * ☆
☀️ 1. ለምሳሌ ☀️
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
አንቺ ከአለሽበት ሴት አዳሪ መንደር
ለዕሳት ዕራት ገላ ዕሳት ሲንደረደር
ጭኗን ለአደባባይ ከፍታ ያመሳቀለች
ጡቷን ለጎዳናው ሸርፋ የሰቀለች
ወንድ ስትራገም ደግሞም ስትጣራ
መንገዱ ሆኖበት በዚህ ለሚያመራ
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂
ማለዳ ጥላ ነው 'ሌት የህይወት መልኩ
የቄሳር ለቄሳር ብለው ለሚረኩ
▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂▂
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
እናም በዚች መንደር
ከምስራቅ የወጣ ንጋት ያልሽው ጀንበር
ቀንና ለሊቱን እንዳፈራረቀ
ላይነጋ ይበራል ላይመሽ የጠለቀ
༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻༺༻
🌊 ምሳሌ.2 🌊
~~~~
ጉሊት ከምታይው መደብ ከመደበ
የሰማይ እጣቢ ፊቱ እየረገበ
ሸርፎ ሲወስድበት
ነጥቆ ሲያጎልበት
~~~~
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈
ጎርፍ አያሳድድም በውሀ ተሳፍሮ
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
ተመስገን ነው ህይወት
ተመስገን ነው ኑሮ
✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦✦
🌫️ ምሳሌ.3 🌫️
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
ብርሌውን አንቆ ከንፈሩን ለሚስም
ተርዚና ወጥሮ ቅጠል ለሚቀስም
ታታሪ ሱሰኛ ህላዌውን ገፊ
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
ጨለማ �ነው ሲልሽ
ጀንበር ወቷል እያልሽ ሀቁን አትጋፊ
▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃
ሳትሰክሪ አታ'ቂውም
ሳትቅሚ አይገባሽም
በሱሰኞች አለም
▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃▃
✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵
ሳይቃም አይነጋም
ለሰከረ አይመሽሞ
✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵ ✵
.·:·. .·:·. .·:·. .·:·.
ልብ በይ 'ሄን ሁሉ
ንጋት እንዳይመስልሽ ወገግ ያለው ሁሉ
.·:·. .·:·. .·:·. .·:·.
✧༺♥༻∞ ∞༺♥༻✧
አምኖ ላደረነው
አሀዱ ወይ አዛን ማለዶ የሚያነቃው
በቀን ለተረሱ
✦⋆✦ ንጋት ነው ኮከቡ ✦⋆✦
✦⋆✦ ንጋት ነው ጨረቃው ✦⋆✦
∞•🌙•✧•☀️•✧•🌙•∞
@getem
@getem
@getem
¹
ገና ወጣት ንፁህ ነበር .....
ያለ ግብሩ ወነጀሉት ፤
ይግባኝ ቢልም አልገባቸው
ግራ ቀኝ ሳይሉ ገ ደ ሉት ።
ከመሬት አጋድመው
አፈ ሙዝ ደግነው እየፎከሩበት
እሳት ያዘለ እርሳስ አርከፈከፉበት ።
²
የእሱስ ይሁን አንዴ ሄደ
እንደ ንፋስ ....ነፍሶ (ደርሶ)
አተረፈው ከሕይወቱ
(ከስቃይ አዳነው ሞቱ !)
ይብላኝ ለኗሪ እናቱ ።
³
ያኔ ፊትለፊቷ....
ልጇን በመስቀል ላይ የቸነከሩት ለት
ያሰረችበትን የወላድ አንጀቷን
አላቀበለቻት ማርያም መቀነቷን ።
ውስጥ ውስጡን ተከፍታ በሀዘን ዝላለች
ስዕሏ ፊት ቆማ እንዲህ ትላታለች
“ለደረሰበት ምኑ ሊነገር ?
ታውቂው የለም ወይ የልጅን ነገር !?
የልጅን ነገር ታውቂው የለም ወይ ?
አይተሽ የለም ወይ?
ወስደው ሲያዳፉት
አስረው ሲገርፉት
በምስማር ፊትሽ ሲቸነክሩት
አካል ገላውን በደም ሲነክሩት
አይተሽ የለም ወይ?
ታመሽ የለም ወይ?
.
.
.
«ያንቺስ ተነስቷል በሦስት ቀኑ
የኔ ግን ይሄው ስንት ዘመኑ
በአካል በስጋ መች ይገለጣል
ትዝታው ብቻ በሌት ይመጣል ።
እስኪ ንገሪኝ ?
እነዛ አይሁዶች አንቺን
እንደ
ድግስ ሲጠሩ
ትታደማለች ፤
እንደ ተፅናና ፈገግ ትላለች ።
ሀዘኗ ሳይሽር አውልቃው ማቋን ፤
ዕምባ ዕምባ ይላል ቢቀምሱት ሳቋን ።
እየዋሸች ነው እያስመሰለች
"እንደ ሚኖሩት ልኑር" እያለች ።
(አልተፅናናችም )
⁶
ተፅናናች እንዴ?
ፀኣዳ ቢሆን ከላይ ቀሚሷ
የሀዘን ማቋን ካልጣለች ነፍሷ
ውስጧ እንዳዘነ....
ልቧ ተከፍቶ ዘቅዝቆ ጥለት
‘ሞቶ መኖር’ ነው ....
“መፅናናት” ማለት ?
------
By @Bekalushumye
ነሃሴ 23 — 2016 ዓም
@getem
@getem
@getem
ገና ወጣት ንፁህ ነበር .....
ያለ ግብሩ ወነጀሉት ፤
ይግባኝ ቢልም አልገባቸው
ግራ ቀኝ ሳይሉ ገ ደ ሉት ።
ከመሬት አጋድመው
አፈ ሙዝ ደግነው እየፎከሩበት
እሳት ያዘለ እርሳስ አርከፈከፉበት ።
²
የእሱስ ይሁን አንዴ ሄደ
እንደ ንፋስ ....ነፍሶ (ደርሶ)
አተረፈው ከሕይወቱ
(ከስቃይ አዳነው ሞቱ !)
ይብላኝ ለኗሪ እናቱ ።
³
ያኔ ፊትለፊቷ....
ልጇን በመስቀል ላይ የቸነከሩት ለት
ያሰረችበትን የወላድ አንጀቷን
አላቀበለቻት ማርያም መቀነቷን ።
ውስጥ ውስጡን ተከፍታ በሀዘን ዝላለች
ስዕሏ ፊት ቆማ እንዲህ ትላታለች
“ለደረሰበት ምኑ ሊነገር ?
ታውቂው የለም ወይ የልጅን ነገር !?
የልጅን ነገር ታውቂው የለም ወይ ?
አይተሽ የለም ወይ?
ወስደው ሲያዳፉት
አስረው ሲገርፉት
በምስማር ፊትሽ ሲቸነክሩት
አካል ገላውን በደም ሲነክሩት
አይተሽ የለም ወይ?
ታመሽ የለም ወይ?
.
.
.
«ያንቺስ ተነስቷል በሦስት ቀኑ
የኔ ግን ይሄው ስንት ዘመኑ
በአካል በስጋ መች ይገለጣል
ትዝታው ብቻ በሌት ይመጣል ።
እስኪ ንገሪኝ ?
እነዛ አይሁዶች አንቺን
እንደ
ኔ በድለውሻል?
ልጅሽን ገድለው
አታልቅሽ ብለው
ከልክለውሻል?»
⁴
የታወቀ ነው.....
ደስታ ቢታሰር በሳቅ ያመልጣል
ሀዘን ፈንቅሎ በእንባ ይወጣል
(እሷ ትላለች ....)
«አልበቃ ብሎ ልጄን የነሱኝ
ባዋጅ በሕጉ እየመለሱኝ
እንደው በወጉ አላስለቀሱኝ »
⁵
ብዙ ቀን ሄዶ....ብዙ ቀን አልፎ
ከሕይወት ዛፍ ላይ ዘመን ረግፎ
ጎረቤቶቿ አብረው ሚኖሩ
በየሰርጉ ዳስ በየማ
በሩ ድግስ ሲጠሩ
ትታደማለች ፤
እንደ ተፅናና ፈገግ ትላለች ።
ሀዘኗ ሳይሽር አውልቃው ማቋን ፤
ዕምባ ዕምባ ይላል ቢቀምሱት ሳቋን ።
እየዋሸች ነው እያስመሰለች
"እንደ ሚኖሩት ልኑር" እያለች ።
(አልተፅናናችም )
⁶
ተፅናናች እንዴ?
ፀኣዳ ቢሆን ከላይ ቀሚሷ
የሀዘን ማቋን ካልጣለች ነፍሷ
ውስጧ እንዳዘነ....
ልቧ ተከፍቶ ዘቅዝቆ ጥለት
‘ሞቶ መኖር’ ነው ....
“መፅናናት” ማለት ?
------
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
እደውላለሁኝ የሚል ቃል ሳይወጣሽ
ስልኬን በፍጥጫ ቀለሟን ገፈፍኩት
ያለምንም ተስፋ በባዶ ሜዳ ላይ ተስፋዬን ሰነኩት
ጉድ እኮ ነው....
ወይ ደውለሽ ልቤ አረጋም
ወይ ትተሽኝ ቀኔ አልነጋም
እንዲ ስብከነከን እንደ ሰረቀ ሰው
ባጉል ተስፋ ኖሬ ሆዴን እንባ ባሰው።
ጉድ እኮ ነው....
ትንሽ ቆየሁና ስልኬን አስቀመትኩት
እርሳሴን አንስቼ ሃሳቤን አማጥኩት
ልግጠም
ልሳል
ልፃፍ
መርጊያ ምስ አጣሁኝ የመድረሻዬን ጫፍ
ልግጠምላት.....ስለምኗ?
ጠባይ መልኳን ወይንስ ላይኗ
ምኗን ልሳል.....ቀይ ከንፈሯን?
ሰውነቷን ወይንስ ጠጉሯን
ጉድ እኮ ነው....
እንዴት ልፃፍ ምን አንስቼ
እሷን ላግኝ እኔን ትቼ?
እጄን ላብ ጠመቀው
በጨበትኩት እርሳስ
ቆይ...ብትመጣስ?
ልትመጣ ነው!
ምን እየሆንኩ ልጠብቃት?
ምን ነበርኩኝ እሷን ሳቃት?
ኧረ እኔንጃ
ጉድ እኮ ነው....
ወይ አትደውል ወይ አትመጣ
እንዲ አያበድኩኝ ቀልቤን ስንቴ ልጣ
አሃ!
አሃሃ
አሃሃ አሃሃ አሃሃ!
አይ የኔ ነገር
ለካ አታውቀኝም...ኧረ እኔም አላውቃት
ታድያ ምን ቤት ሆና ልቤ ሚጠብቃት?
ጉድ እኮ ነው....
የት ነበር ያየኋት...?
ጎንደር ሸገር ጅማ ሽረ
የት ነው ያገኘኋት ልቤስ ነት ነበረ?
ወይ አታውቀኝ ወይ አላውቃት
ለምንድንው ምጠብቃት?
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ስልኬን በፍጥጫ ቀለሟን ገፈፍኩት
ያለምንም ተስፋ በባዶ ሜዳ ላይ ተስፋዬን ሰነኩት
ጉድ እኮ ነው....
ወይ ደውለሽ ልቤ አረጋም
ወይ ትተሽኝ ቀኔ አልነጋም
እንዲ ስብከነከን እንደ ሰረቀ ሰው
ባጉል ተስፋ ኖሬ ሆዴን እንባ ባሰው።
ጉድ እኮ ነው....
ትንሽ ቆየሁና ስልኬን አስቀመትኩት
እርሳሴን አንስቼ ሃሳቤን አማጥኩት
ልግጠም
ልሳል
ልፃፍ
መርጊያ ምስ አጣሁኝ የመድረሻዬን ጫፍ
ልግጠምላት.....ስለምኗ?
ጠባይ መልኳን ወይንስ ላይኗ
ምኗን ልሳል.....ቀይ ከንፈሯን?
ሰውነቷን ወይንስ ጠጉሯን
ጉድ እኮ ነው....
እንዴት ልፃፍ ምን አንስቼ
እሷን ላግኝ እኔን ትቼ?
እጄን ላብ ጠመቀው
በጨበትኩት እርሳስ
ቆይ...ብትመጣስ?
ልትመጣ ነው!
ምን እየሆንኩ ልጠብቃት?
ምን ነበርኩኝ እሷን ሳቃት?
ኧረ እኔንጃ
ጉድ እኮ ነው....
ወይ አትደውል ወይ አትመጣ
እንዲ አያበድኩኝ ቀልቤን ስንቴ ልጣ
አሃ!
አሃሃ
አሃሃ አሃሃ አሃሃ!
አይ የኔ ነገር
ለካ አታውቀኝም...ኧረ እኔም አላውቃት
ታድያ ምን ቤት ሆና ልቤ ሚጠብቃት?
ጉድ እኮ ነው....
የት ነበር ያየኋት...?
ጎንደር ሸገር ጅማ ሽረ
የት ነው ያገኘኋት ልቤስ ነት ነበረ?
ወይ አታውቀኝ ወይ አላውቃት
ለምንድንው ምጠብቃት?
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
የኔን ልንገርሽ
አፈቅርሻለሁ፣
እየኖርኩኝ ምቼ
እጠብቅሻለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ሀሳቤ ሆነሻል፣
አካሌ ተወርሶ
ልቤ ልብ ሰቶሻል።
የኔን ልንገርሽ
ባንቺ ሰግቻለሁ፣
ምን ሆነች እያልኩኝ
የትም አስባለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ለሰው አወራለሁ፣
የኔ ናት እያልኩኝ
ቀኔን አረዝማለሁ።
የኔን ልንገርሽ
መወሰን ከብዶኛል፣
እያጠፋሽ መተሽ
ይቅርታ ቀሎኛል።
የኔን ልንገርሽ
ሳላጠፋ ይቅርታ እላለሁ፣
አንቺን ባፈቀርኩኝ
ጌታን መስያለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ጨጓራዬ በስሏል፣
በቀናሁኝ ቁጥር
ጥላሸት ይመስላል።
የኔን ልንገርሽ
ቃላት አብዝቻለሁ፣
ፍቅር ፍቅር እያልኩ
መድረስ ጀምሬአለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ሰው ያለ አይመስለኝም፣
ሴትም ሰውም ውብም አንቺ
ሆነሽ ሌላ አይታየኝም።
የኔን ልንገርሽ
አይቀረኝ ሙሉቀን፣
አይቀረኝ ብዙአየሁ፣
አይቀረኝ ታምራት፣
አይቀረኝ ቴዲ አፍሮ፣
ማዳመጥ ነው ልምዴ
እየሰጠው ጆሮ👂፣
አያቅም እኔ ጋር ዘፈን ውሎ አድሮ ።
የአንቺን ግን ንገሪኝ ?
እንደኔ ሆነሻል፣
ወይስ እኔ እንደፃፍኩልሽ
ለአንዱ ሰው ፅፈሻል።
ምንጭ፡- የሷን መልስ በመጠበቅ ላይ ሆኜ የተፃፈ
ማጀቢያ ሙዚቃ ፡- ልዑል ሲሳይ ( የኔ አመል )
ገጣሚ፡- ፓፒኤል
@getem
@getem
@getem
አፈቅርሻለሁ፣
እየኖርኩኝ ምቼ
እጠብቅሻለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ሀሳቤ ሆነሻል፣
አካሌ ተወርሶ
ልቤ ልብ ሰቶሻል።
የኔን ልንገርሽ
ባንቺ ሰግቻለሁ፣
ምን ሆነች እያልኩኝ
የትም አስባለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ለሰው አወራለሁ፣
የኔ ናት እያልኩኝ
ቀኔን አረዝማለሁ።
የኔን ልንገርሽ
መወሰን ከብዶኛል፣
እያጠፋሽ መተሽ
ይቅርታ ቀሎኛል።
የኔን ልንገርሽ
ሳላጠፋ ይቅርታ እላለሁ፣
አንቺን ባፈቀርኩኝ
ጌታን መስያለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ጨጓራዬ በስሏል፣
በቀናሁኝ ቁጥር
ጥላሸት ይመስላል።
የኔን ልንገርሽ
ቃላት አብዝቻለሁ፣
ፍቅር ፍቅር እያልኩ
መድረስ ጀምሬአለሁ።
የኔን ልንገርሽ
ሰው ያለ አይመስለኝም፣
ሴትም ሰውም ውብም አንቺ
ሆነሽ ሌላ አይታየኝም።
የኔን ልንገርሽ
አይቀረኝ ሙሉቀን፣
አይቀረኝ ብዙአየሁ፣
አይቀረኝ ታምራት፣
አይቀረኝ ቴዲ አፍሮ፣
ማዳመጥ ነው ልምዴ
እየሰጠው ጆሮ👂፣
አያቅም እኔ ጋር ዘፈን ውሎ አድሮ ።
የአንቺን ግን ንገሪኝ ?
እንደኔ ሆነሻል፣
ወይስ እኔ እንደፃፍኩልሽ
ለአንዱ ሰው ፅፈሻል።
ምንጭ፡- የሷን መልስ በመጠበቅ ላይ ሆኜ የተፃፈ
ማጀቢያ ሙዚቃ ፡- ልዑል ሲሳይ ( የኔ አመል )
ገጣሚ፡- ፓፒኤል
@getem
@getem
@getem
አታውቋትም።።
(የሞገሴ ልጅ)
እህት ማለት-
ወንድምነት እንዲታወቅ - ወንድ መሆን ልኩ እንዲታይ፣
መስታወት ናት፣
በታየበት በኩል ሆና - ያልታየውን አይታ አሳይ።
የወላጆች-
ዘር አጋምዷት ሤትነቷ - ችግኝ ሆኖ የሚጠበቅ፣
እርስት ናት-
ውብ ስጦታ ከጎን ሆና - በየ እለቱ የምትናፍቅ።
እያላችሁ-
እህትነት የኅዝብ ሆኖ - በወል ሚዛን ብትለኳትም፣
እናት መሆን,
ለእህትነት ካልተሰጠ - የኔን እህት አታውቋትም።
አታውቋትም።።.
እንደእድሏ-
ነጋ መሸ በልጅ አቅሟ - ልጅ ማሳደግ እጣ ደርሷት፣
ለወንድሟ፣
እናት መምሰል መሆን ጋርዶት - አቻ ላቻ ከእህትነት።
የአንድ ሁለት-
የሁለት አንድ ምስጢር ሆና - ያለልብ አይን ብታዩአትም፣
አለም ሲኖር፣
በሚአይበት መነጽሩ - የእኔን እህት አታዩአትም.
አታዩአትም..
ስም ነው እና፣
እንበል እንጂ ለእህቴ - እህትነት አይገልጻትም.
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
(የሞገሴ ልጅ)
እህት ማለት-
ወንድምነት እንዲታወቅ - ወንድ መሆን ልኩ እንዲታይ፣
መስታወት ናት፣
በታየበት በኩል ሆና - ያልታየውን አይታ አሳይ።
የወላጆች-
ዘር አጋምዷት ሤትነቷ - ችግኝ ሆኖ የሚጠበቅ፣
እርስት ናት-
ውብ ስጦታ ከጎን ሆና - በየ እለቱ የምትናፍቅ።
እያላችሁ-
እህትነት የኅዝብ ሆኖ - በወል ሚዛን ብትለኳትም፣
እናት መሆን,
ለእህትነት ካልተሰጠ - የኔን እህት አታውቋትም።
አታውቋትም።።.
እንደእድሏ-
ነጋ መሸ በልጅ አቅሟ - ልጅ ማሳደግ እጣ ደርሷት፣
ለወንድሟ፣
እናት መምሰል መሆን ጋርዶት - አቻ ላቻ ከእህትነት።
የአንድ ሁለት-
የሁለት አንድ ምስጢር ሆና - ያለልብ አይን ብታዩአትም፣
አለም ሲኖር፣
በሚአይበት መነጽሩ - የእኔን እህት አታዩአትም.
አታዩአትም..
ስም ነው እና፣
እንበል እንጂ ለእህቴ - እህትነት አይገልጻትም.
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
( ልመርቅሽማ ... )
===============
እማ .....
የተረሳው ማንነቴን
እንዳወጣሽ ከጨለማ
ልትጠይቂው ያሰብሽውን
ቃል ሳይወጣሽ ጌታ ይስማ
እንደሸፈንሽ ገመናዬን
ስሜ ባገር ሳይ'ታማ
ኃፍረት አሳር ያገኘሽ ለት
ትከልልሽ ጸሐይ ጸልማ
ቀን ሲጥለኝ ላጽናናሽኝ
እስኪረሳኝ ክፉ ግብሬ
የሰማይ ዘብ መላዕክታን
ያረጋጉሽ በዝማሬ ...
ወድቄ አይተሽ እንዳልናቅሽኝ
ከሰው ተራ በታች ስገኝ
ቀን ሰምሮልኝ ከብሬ እንኳ
አገልጋይሽ ሎሌሽ ያርገኝ ...
አሜን !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@paappii
===============
እማ .....
የተረሳው ማንነቴን
እንዳወጣሽ ከጨለማ
ልትጠይቂው ያሰብሽውን
ቃል ሳይወጣሽ ጌታ ይስማ
እንደሸፈንሽ ገመናዬን
ስሜ ባገር ሳይ'ታማ
ኃፍረት አሳር ያገኘሽ ለት
ትከልልሽ ጸሐይ ጸልማ
ቀን ሲጥለኝ ላጽናናሽኝ
እስኪረሳኝ ክፉ ግብሬ
የሰማይ ዘብ መላዕክታን
ያረጋጉሽ በዝማሬ ...
ወድቄ አይተሽ እንዳልናቅሽኝ
ከሰው ተራ በታች ስገኝ
ቀን ሰምሮልኝ ከብሬ እንኳ
አገልጋይሽ ሎሌሽ ያርገኝ ...
አሜን !!!
By @kiyorna
@getem
@getem
@paappii
🕊️ የአብስራ ሳሙኤል 🕊️
ተይኝ ሞቴን ልሙት ትውልድ ምናምን አትበይኝ
በፏፏቴ በተራራው በሳር በቅጠል አደልይኝ
እማ ልጄን አትበይኝ
የታሪክ ስንክ ሳር ኋላ ታላቅነትሽን
የድል የድሎት ዘመንሽን
አባይ ሆኖ ጅረት ፈሶ ለሌላ እንጂ የሚ'ደርሰው
ለኔ ብኩን ደካማ ሰው
የዕንባ ብናኝ የደም ወዜን
ግልገል ወንዝሽ መች አርሶት
ለምለም ጤዛሽ መች አብሶት
መቼም ከተራራሽ ብብት
ድንጋይ ቢፋጭ ውሀ ቢላተም
እጇን በዘረጋች እናት አለም
ጸሎት ምልጃዋ ያውጣት እንጂ
ማን እጁን ወዳንቺ ይሰዳል
ምኞት ተስፋሽ ይማግዳል
እናም አልችለውና በሰው አቅም በሰው ገላ
ስጋ ነፍሴን ከ'ነ ህልሟ መሀጸንሽ ተቀብላ
ጸጸት ብሶቷን ታምጥ ግድ የለም
ልጄ አትበይኝ እናት አለም
ተይኝ ሞቴን ልሙት እማ ሆዴን አታባቢው
ተስፋ ምኞት አቀልቢው
መቼም ትታዘቢኝ ይሆናል ያዝናል ወላድ አንጀትሽ
ይነጥፋል ያጠባ ጡትሽ
ሽል ሆኜብሽ የዘር አምሳል አደራሽን ብሸሽም
እማ ትሙች ብሞት �ንጂ ኖሬም ምንም አልጠቅምሽም
እናም አንቺ ውለጅ መውለድ ይክሳል
የኔ አይነት እልፍ ተቀብሮ ከትቢያሽ ህይወት ይነሳል
የምኞትሽን ልጅ ይስጥሽ የተመኘውትን አትንሺኝ
አለወለድኩም ብለሽ እርሺኝ
ለ'ኔ አልሆነም ይሄ ትግል
ምልጃሽ ያውጣኝ በግልግል
ተይኝ ሞቴን ልሙት ትውልድ ምናምን አትበይኝ
በፏፏቴ በተራራው በሳር በቅጠል አደልይኝ
እማ �ጄን �ትበይኝ
_ንሸጣ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን_
_ተወኝ_
@getem
@getem
@getem
ተይኝ ሞቴን ልሙት ትውልድ ምናምን አትበይኝ
በፏፏቴ በተራራው በሳር በቅጠል አደልይኝ
እማ ልጄን አትበይኝ
የታሪክ ስንክ ሳር ኋላ ታላቅነትሽን
የድል የድሎት ዘመንሽን
አባይ ሆኖ ጅረት ፈሶ ለሌላ እንጂ የሚ'ደርሰው
ለኔ ብኩን ደካማ ሰው
የዕንባ ብናኝ የደም ወዜን
ግልገል ወንዝሽ መች አርሶት
ለምለም ጤዛሽ መች አብሶት
መቼም ከተራራሽ ብብት
ድንጋይ ቢፋጭ ውሀ ቢላተም
እጇን በዘረጋች እናት አለም
ጸሎት ምልጃዋ ያውጣት እንጂ
ማን እጁን ወዳንቺ ይሰዳል
ምኞት ተስፋሽ ይማግዳል
እናም አልችለውና በሰው አቅም በሰው ገላ
ስጋ ነፍሴን ከ'ነ ህልሟ መሀጸንሽ ተቀብላ
ጸጸት ብሶቷን ታምጥ ግድ የለም
ልጄ አትበይኝ እናት አለም
ተይኝ ሞቴን ልሙት እማ ሆዴን አታባቢው
ተስፋ ምኞት አቀልቢው
መቼም ትታዘቢኝ ይሆናል ያዝናል ወላድ አንጀትሽ
ይነጥፋል ያጠባ ጡትሽ
ሽል ሆኜብሽ የዘር አምሳል አደራሽን ብሸሽም
እማ ትሙች ብሞት �ንጂ ኖሬም ምንም አልጠቅምሽም
እናም አንቺ ውለጅ መውለድ ይክሳል
የኔ አይነት እልፍ ተቀብሮ ከትቢያሽ ህይወት ይነሳል
የምኞትሽን ልጅ ይስጥሽ የተመኘውትን አትንሺኝ
አለወለድኩም ብለሽ እርሺኝ
ለ'ኔ አልሆነም ይሄ ትግል
ምልጃሽ ያውጣኝ በግልግል
ተይኝ ሞቴን ልሙት ትውልድ ምናምን አትበይኝ
በፏፏቴ በተራራው በሳር በቅጠል አደልይኝ
እማ �ጄን �ትበይኝ
_ንሸጣ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን_
_ተወኝ_
@getem
@getem
@getem