(የአብስራ ሳሙኤል)
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
እዚህ እታች ሰፈር
ማዳበሪውን እንዳነገተ
ሀይላድ ሲለቅም
መኪና ገጭቶት አንድ ህጻን ሞተ
°°°°°°ይሙት ግድ የለም°°°°
ነበር አልን እንጂ
የኖረው ህይወት ህይወት አይደለም
ትራፊ እንጀራ ለዕልፍ አዕላፍ ያቀራመተ
ባርከው እያለህ
°°°°°°°°°°°ሳትባርክለት እርቦት የሞተ
ቀብሮት ወንድሙን
ከአይኑ አብሶ የእንባ ደሙኑ
።።።።።።ኑሮን ሊጋፋ።።።።።
ለሀይላንድ ልቃሚ አንገት ቢደፋ
"""" """"" """""
ያው እንደወጣ አልተመለሰም
እንደ ጥያቄው እንደ ምኞቱ
የሱን አልን እንጂ
ታሪኩ እራሱ ታሪክ ነው የስንቱ.....
፨፨፨
፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብክን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
[ደሞም አንዲት ሴት]
የቀሚስ ቅዷ የጭኗ ቁስል
የአርብ ዕለት ጌጥክን ግርፋት ምስል
እንደከተበ
አይኖ በምሬት
የራሄል እንባ እያዘነበ
ስታልጎመጉም እንዲ ትል ነበር
የጫንክብኝን የህይወት ቀንበር
<ችዬ ስጋፋው>
ስለምን ወንዱን ስሜት አስከፋው
<የገፋ ባሌን>
ዝሙት ሀጥያቱን ገና ሳለምደው
<ከሞት መራራ>
ብልቱ መርቶ የሚያራምደው
<በእናቱ እንጀራ>
በሰባ እጆቹ ጨፍልቆ ይዞ
የሴት ገላዬን በቁም ገንዞ
¡በድን ሲያስቀረኝ!
ቂም እንዳይመስልህ
በእንባ ዘለላ የሚያናግረኝ
<ይልቅ መዳፍክን>
የአንገት ማህተቤን ወሰድ ከህይወቴ
<አንቆ ሲደፍረኝ>
°°°°°°°°°°°ምስለ ስዕልህ ገዝፎ ከቤቴ
ተስፋ እንዳይሆነኝ
ስንቅ እንዳይሆነኝ
ኖረህ ዝምታ እያስደፈረኝ
ሆድ ይፍጀው እንጂ
ችዬ ያልነገርኩህ ብዙ ነበረኝ።.....
፨፨፨፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
......ደሞም ትዝ አለኝ......
አንዱ ፈላስፋ የተናገረው
ከትቦ ያኖረው
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
ውርቂያኖስ በእንባ እንደመለካት
ተጠማው ያለን በሀሞት ማርካት
<እየቀበሩ>
ማማረር ሀጥያት ብሎ መመካት
<ነድያን አልፎ>
ዲያቆን ፍለጋ መቅድስ ማንኳኳት
.......ደሞም ትዝ አለኝ
ትዝ አለኝ ብዙ........
በሀረግ በስንኝ እንዴት ይቋጠር
ጋን ተሸክሞል ሰው እንደጠጠር
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም ......ዝም
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
የትኛው ጠቢብ ደራሲ ደርሶት ?
የትኛው አምላክ እንባን አብሶት ?
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም..... ዝም
ሰሚ ሳይኖረን አንናዘዝም
፨፨፨፨፨፨
እናም በል እግዜር
መዝገብክን ዝጋው ጆሮ ዳባ አልብስ
የሰማ ሳይሆን
ስሙኝ ያለ ነው የሚያደባብስ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
እዚህ እታች ሰፈር
ማዳበሪውን እንዳነገተ
ሀይላድ ሲለቅም
መኪና ገጭቶት አንድ ህጻን ሞተ
°°°°°°ይሙት ግድ የለም°°°°
ነበር አልን እንጂ
የኖረው ህይወት ህይወት አይደለም
ትራፊ እንጀራ ለዕልፍ አዕላፍ ያቀራመተ
ባርከው እያለህ
°°°°°°°°°°°ሳትባርክለት እርቦት የሞተ
ቀብሮት ወንድሙን
ከአይኑ አብሶ የእንባ ደሙኑ
።።።።።።ኑሮን ሊጋፋ።።።።።
ለሀይላንድ ልቃሚ አንገት ቢደፋ
"""" """"" """""
ያው እንደወጣ አልተመለሰም
እንደ ጥያቄው እንደ ምኞቱ
የሱን አልን እንጂ
ታሪኩ እራሱ ታሪክ ነው የስንቱ.....
፨፨፨
፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብክን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
[ደሞም አንዲት ሴት]
የቀሚስ ቅዷ የጭኗ ቁስል
የአርብ ዕለት ጌጥክን ግርፋት ምስል
እንደከተበ
አይኖ በምሬት
የራሄል እንባ እያዘነበ
ስታልጎመጉም እንዲ ትል ነበር
የጫንክብኝን የህይወት ቀንበር
<ችዬ ስጋፋው>
ስለምን ወንዱን ስሜት አስከፋው
<የገፋ ባሌን>
ዝሙት ሀጥያቱን ገና ሳለምደው
<ከሞት መራራ>
ብልቱ መርቶ የሚያራምደው
<በእናቱ እንጀራ>
በሰባ እጆቹ ጨፍልቆ ይዞ
የሴት ገላዬን በቁም ገንዞ
¡በድን ሲያስቀረኝ!
ቂም እንዳይመስልህ
በእንባ ዘለላ የሚያናግረኝ
<ይልቅ መዳፍክን>
የአንገት ማህተቤን ወሰድ ከህይወቴ
<አንቆ ሲደፍረኝ>
°°°°°°°°°°°ምስለ ስዕልህ ገዝፎ ከቤቴ
ተስፋ እንዳይሆነኝ
ስንቅ እንዳይሆነኝ
ኖረህ ዝምታ እያስደፈረኝ
ሆድ ይፍጀው እንጂ
ችዬ ያልነገርኩህ ብዙ ነበረኝ።.....
፨፨፨፨፨፨፨
¶በል እንግዲ እግዜር¶
መዝገብህን ክፈት ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ ስጋና አጥንት የሚሰረስር
......ደሞም ትዝ አለኝ......
አንዱ ፈላስፋ የተናገረው
ከትቦ ያኖረው
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
ውርቂያኖስ በእንባ እንደመለካት
ተጠማው ያለን በሀሞት ማርካት
<እየቀበሩ>
ማማረር ሀጥያት ብሎ መመካት
<ነድያን አልፎ>
ዲያቆን ፍለጋ መቅድስ ማንኳኳት
.......ደሞም ትዝ አለኝ
ትዝ አለኝ ብዙ........
በሀረግ በስንኝ እንዴት ይቋጠር
ጋን ተሸክሞል ሰው እንደጠጠር
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም ......ዝም
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
የትኛው ጠቢብ ደራሲ ደርሶት ?
የትኛው አምላክ እንባን አብሶት ?
ይልቅ ዝም ነው
ሁሌም ዝም..... ዝም
ሰሚ ሳይኖረን አንናዘዝም
፨፨፨፨፨፨
እናም በል እግዜር
መዝገብክን ዝጋው ጆሮ ዳባ አልብስ
የሰማ ሳይሆን
ስሙኝ ያለ ነው የሚያደባብስ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
(የአብስራ ሳሙኤል)
አይገርምም ታፈቀርኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
አይገርም
ነጠላ ነፍሶች
በህይወት መንገድ ያልተቆራኙ
አይን ለአይን ሲገናኙ
ምን አሸፈተሽ ምን አሸፈተኝ
የመቅደስ ዕጣን ናርዶስ ሸተተኝ
መግነዜን ፈታሁ ቁስሌ ዳነ
አይገርምም
ግን ይሄ ሁሉ ስለምን ሆነ
.
.
.
.
አይገርም
በጤዛማ ሳር በረሰረሰ
አፌ ከንፈርሽን እንደ ጎረሰ
ጋደም ብለን
ሽቅብ እያየን ሰማይ ሰማይ...ዪን
ጨረቃ አታምርም ብለሽ ስትስቂ
የኮከብ ፍላጭ የአደይ ውዳቂ
የሆነ ገላሽ
ከፊል ተገልቦ አያቃተተኝ
ምን አዘሞተሽ ምን አዘሞተኝ
.
.
.
አይገርም ታፈቀረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
<ፍቅር የሚሉት ጦሶ>
በውደድ ጠልፎ እያቆራኘን
<ጠፈር ያለምነው>
ካፈቀርናት ሴት እቅፍ ተገኘን
"" "" እንኳን ተገኘነን!
ጥበብ ቢበዛ እውቀት በረቅም
የኖረው እንጂ
የፍቅርን ትርጉም ያልኖረው አያቅም ።
.
.
.
አይገርምም ታፈቅረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
አይገርምም ታፈቀርኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
አይገርም
ነጠላ ነፍሶች
በህይወት መንገድ ያልተቆራኙ
አይን ለአይን ሲገናኙ
ምን አሸፈተሽ ምን አሸፈተኝ
የመቅደስ ዕጣን ናርዶስ ሸተተኝ
መግነዜን ፈታሁ ቁስሌ ዳነ
አይገርምም
ግን ይሄ ሁሉ ስለምን ሆነ
.
.
.
.
አይገርም
በጤዛማ ሳር በረሰረሰ
አፌ ከንፈርሽን እንደ ጎረሰ
ጋደም ብለን
ሽቅብ እያየን ሰማይ ሰማይ...ዪን
ጨረቃ አታምርም ብለሽ ስትስቂ
የኮከብ ፍላጭ የአደይ ውዳቂ
የሆነ ገላሽ
ከፊል ተገልቦ አያቃተተኝ
ምን አዘሞተሽ ምን አዘሞተኝ
.
.
.
አይገርም ታፈቀረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
.
.
.
<ፍቅር የሚሉት ጦሶ>
በውደድ ጠልፎ እያቆራኘን
<ጠፈር ያለምነው>
ካፈቀርናት ሴት እቅፍ ተገኘን
"" "" እንኳን ተገኘነን!
ጥበብ ቢበዛ እውቀት በረቅም
የኖረው እንጂ
የፍቅርን ትርጉም ያልኖረው አያቅም ።
.
.
.
አይገርምም ታፈቅረኛለች
አይገርምም አፈቅራታለሁ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
እንደውም አንገሽግሾኛል
ጓዝሽን ጠቅልለሽ ውጪ
ስንት አመት የከረምሽበት
ልብ ኪራዬን ብቻ አምጪ
የትም ኬትም ኖረሽ
እንደተረፈው ሰው ፍቅር ስትበትኚ
አሁን ኪራዬን ስል
እንዳልኖረበት ሰው ተበዳይ አትሁኚ
ከፋፍዬው እንኳን
ሌላ ምስኪን እንስት እንዳላስገባበት
ልቤ ዳር እስከ ዳር
እንዳትነኩኝ የሚል ፡ ዳናሽ ነበረበት።
አሁን ጥርግ በይ
እንኳን ሌላ ሰው ልብ
እንጦሮጦስ ሂጂ፥
ብቻ ኡኡ ሳልል
ኪራዬን ውለጂ!!
❗️ @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ጓዝሽን ጠቅልለሽ ውጪ
ስንት አመት የከረምሽበት
ልብ ኪራዬን ብቻ አምጪ
የትም ኬትም ኖረሽ
እንደተረፈው ሰው ፍቅር ስትበትኚ
አሁን ኪራዬን ስል
እንዳልኖረበት ሰው ተበዳይ አትሁኚ
ከፋፍዬው እንኳን
ሌላ ምስኪን እንስት እንዳላስገባበት
ልቤ ዳር እስከ ዳር
እንዳትነኩኝ የሚል ፡ ዳናሽ ነበረበት።
አሁን ጥርግ በይ
እንኳን ሌላ ሰው ልብ
እንጦሮጦስ ሂጂ፥
ብቻ ኡኡ ሳልል
ኪራዬን ውለጂ!!
❗️ @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
¹
አላያትም እይልኝ
አልጠብቃት ጠብቅልኝ
ሳሳሁላት ፈራሁላት
አልደረስኩም ድረስላት ።
²
እኔ ከንቱ ሰው.....
የዓለምን እንጂ መውደድ ናፍቆቱን
መቼ ችዬበት የመለኮቱን ?!
ክንፍ የለኝ አልበር ሰይፍ አልሰጠኸኝ
ጎድያለሁ ስል ፍቅር ሞልተኸኝ
ደከምኩኝ አሁን ሆኜ አቅም አልባ
የቀረኝ ጥሪት ጸሎትና እንባ ።
³
ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው....
በድኩም ትከሻ ፍቅር ካነገተ
ትቀርባት የለም ወይ የፈጠርካት አንተ?!
⁴
ከፊቷ ገበታ ሳቋ እንዳይጓደል
ሳር እየመሰላት እንዳትገባ ገደል
(ክንፉን አንጥፎላት እንድትደላደል)
ገብርኤልን ብትልከው
እምቢ አይልህም አይደል?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
አላያትም እይልኝ
አልጠብቃት ጠብቅልኝ
ሳሳሁላት ፈራሁላት
አልደረስኩም ድረስላት ።
²
እኔ ከንቱ ሰው.....
የዓለምን እንጂ መውደድ ናፍቆቱን
መቼ ችዬበት የመለኮቱን ?!
ክንፍ የለኝ አልበር ሰይፍ አልሰጠኸኝ
ጎድያለሁ ስል ፍቅር ሞልተኸኝ
ደከምኩኝ አሁን ሆኜ አቅም አልባ
የቀረኝ ጥሪት ጸሎትና እንባ ።
³
ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው....
በድኩም ትከሻ ፍቅር ካነገተ
ትቀርባት የለም ወይ የፈጠርካት አንተ?!
⁴
ከፊቷ ገበታ ሳቋ እንዳይጓደል
ሳር እየመሰላት እንዳትገባ ገደል
(ክንፉን አንጥፎላት እንድትደላደል)
ገብርኤልን ብትልከው
እምቢ አይልህም አይደል?
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
(የአብስራ ሳሙኤል)
ይሄ የምታይው
የፈረሰ መንገድ ታሪክ እንዳይመስልሽ
እዚህ ጋ'ነው ቃሌ እዚህ ጋ'ነው ቃልሽ
ስጋ የለበሰው
እንደ ሰው እንደ ሰው
ግና......ዛሬ
ስጋሽም በሰበሰ
መንገዱም ፈረሰ
እኔና ትዝታ ብቻ ባለመኖር ውስጥ አለን
ከፈራረሰ ማንነት የህይወትን አጸድ ተክለን!
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
ይሄ የምታይው
የፈረሰ መንገድ ታሪክ እንዳይመስልሽ
እዚህ ጋ'ነው ቃሌ እዚህ ጋ'ነው ቃልሽ
ስጋ የለበሰው
እንደ ሰው እንደ ሰው
ግና......ዛሬ
ስጋሽም በሰበሰ
መንገዱም ፈረሰ
እኔና ትዝታ ብቻ ባለመኖር ውስጥ አለን
ከፈራረሰ ማንነት የህይወትን አጸድ ተክለን!
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@getem
( ያ ውሻ ... )
===========
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሀ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@getem
@getem
@paappii
===========
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሀ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@getem
@getem
@paappii
(የአብስራ ሳሙኤል)
ስንኝና ቀለም
ከምእናብ አለም
ገጣሚ ሲጽፍሽ
ሰአሊ ሲስልሽ
አርቅቀው
አድንቀው
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
እንዲ ብለው ነበር
ፍክት ያለች ጀምበር
ጨረቃ የምታቅፍ
ዉሀ ላይ የምትጽፍ
ድምጿ የወፍ ዜማ
ጸጉሯ ጥቁር ዞማ
አይኖቿ እንደ ባህር
ሳቋ የሚያሰግር
ከሴትም አንድ ሴት
..
....
የሀሳባቸው ደሴት
ጎዳሽን አልነካም
ማጣትሽን አልተካም
በሀሳባቸው ልክ
በታጠቁት ብዕር
ምኞት ስትሰክር
ያድሉሽ ጀመረ
ውበት ተሳከረ
እውነት ተሳከረ
የለሽም ጨረቃ
ጨለማ ናት ጠልቃ
ፀጉርሽ ተበታትኖ
መልክሽን አደፈ
ይሄ መች ተጻፈ
አልተሳለም ሀቅሽ
የጎደፈ ሳቅሽ
አለቱ ተራራ ቤትሽን የከለለ
ሊያፈርሰው ማን አለ?
ደርሶ ይደበቃል ከምዕናቡ አለም
ሊንደው በስንኝ ሊነቅለው በቀለም
ማን ነበር ከጓዳሽ ?
ማን ነበር የጎዳሽ ?
ሸራ ላይ ስቃሻል
ተጽፈሽ አልቀሻል
ደስታሽ ከአደባባይ
ለገበያ ዋለ
"አሰየው ተባለ"
"ሸጋ ነው ተባለ"
ደርሶ ያየሽ የለ
ባነበቡት ልኬት
ገላሽን ተመኙ
በተረዱሽ መጠን
ደርሰው እየተቀኙ
ያወድሱሽ ጀመር
መፋለስ ሲጀመር
ሀሳብ የወለዳት
አንዲት ስንኩል ፊደል
የሰኣሊው በደል
አምላክ መሆን ቀላል
ሰሪ መሆን ክፉ
ሀዘን ሲጠየፉ
አይዞሽ አላሉሽም
አላስታመሙሽም
ይልቅ በሃሳባቸው
ሸራ ላይ አሳቁሽ
በቃል አደመቁሽ
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
ጨረቃን አቅፈሻል
ሞተሽም ስቀሻል
በድን ቢሆን አንኳ
የሙት መንፈስ መልኳ
ተያቸው በምዕናብ
ካቀፉሽ በሀሳብ
ይፈላሰፉልሽ ቃል እየመረጡ
እንስራሽ ሲሉ ነው ስሪትሽን ያጡ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
ስንኝና ቀለም
ከምእናብ አለም
ገጣሚ ሲጽፍሽ
ሰአሊ ሲስልሽ
አርቅቀው
አድንቀው
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
እንዲ ብለው ነበር
ፍክት ያለች ጀምበር
ጨረቃ የምታቅፍ
ዉሀ ላይ የምትጽፍ
ድምጿ የወፍ ዜማ
ጸጉሯ ጥቁር ዞማ
አይኖቿ እንደ ባህር
ሳቋ የሚያሰግር
ከሴትም አንድ ሴት
..
....
የሀሳባቸው ደሴት
ጎዳሽን አልነካም
ማጣትሽን አልተካም
በሀሳባቸው ልክ
በታጠቁት ብዕር
ምኞት ስትሰክር
ያድሉሽ ጀመረ
ውበት ተሳከረ
እውነት ተሳከረ
የለሽም ጨረቃ
ጨለማ ናት ጠልቃ
ፀጉርሽ ተበታትኖ
መልክሽን አደፈ
ይሄ መች ተጻፈ
አልተሳለም ሀቅሽ
የጎደፈ ሳቅሽ
አለቱ ተራራ ቤትሽን የከለለ
ሊያፈርሰው ማን አለ?
ደርሶ ይደበቃል ከምዕናቡ አለም
ሊንደው በስንኝ ሊነቅለው በቀለም
ማን ነበር ከጓዳሽ ?
ማን ነበር የጎዳሽ ?
ሸራ ላይ ስቃሻል
ተጽፈሽ አልቀሻል
ደስታሽ ከአደባባይ
ለገበያ ዋለ
"አሰየው ተባለ"
"ሸጋ ነው ተባለ"
ደርሶ ያየሽ የለ
ባነበቡት ልኬት
ገላሽን ተመኙ
በተረዱሽ መጠን
ደርሰው እየተቀኙ
ያወድሱሽ ጀመር
መፋለስ ሲጀመር
ሀሳብ የወለዳት
አንዲት ስንኩል ፊደል
የሰኣሊው በደል
አምላክ መሆን ቀላል
ሰሪ መሆን ክፉ
ሀዘን ሲጠየፉ
አይዞሽ አላሉሽም
አላስታመሙሽም
ይልቅ በሃሳባቸው
ሸራ ላይ አሳቁሽ
በቃል አደመቁሽ
ለገሀድ ነጸብራቅ
የተፈጥሮሽን ሀቅ
እየተጣረሱ
አንቺን ሲያወድሱ
ጨረቃን አቅፈሻል
ሞተሽም ስቀሻል
በድን ቢሆን አንኳ
የሙት መንፈስ መልኳ
ተያቸው በምዕናብ
ካቀፉሽ በሀሳብ
ይፈላሰፉልሽ ቃል እየመረጡ
እንስራሽ ሲሉ ነው ስሪትሽን ያጡ
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
ይቅርታ !
ስታቀርቢኝ
ስለራቅኩሽ ፤
ስትወጂኝ
ችላ ስላልኩሽ ፤
ስታንሽልኝ
ስለናቅኩሽ ፤
ኮኮብ
ሰማይ
ፀሐይ
ጨረቃ ... ስታደርጊኝ
እንደ ሰው ስላልቆጠርኩሽ ፤
በነፍስሽ ላይ ስለቀለድኩ
በዕድሜሽ ላይ ስለተጫወትኩ ፤
ውብ ነፍስሽን ስላሳደፍኩ
ስስ ልብሽን ስለሰበርኩ ፤
ልኬ ድረስ ስትመጭ
ልክሽ ድረስ ስላልወረድኩ ፤
ገላሽን
እንደ ትቢያ አፈር
ነፍስሽን
እንደ ዕድፍ ምንጣፍ
ተራ አድርጌ ስለቆጠርኩ ፤
ይቅርታ !
____
አዬሽ
የሰው ስቃዩ ይሄው ነው፤
እኔም ለወደድኳት ያዬሁት መከራ
ያንቺኑ ያኽል ነው ።
By Tewodros kasa
@getem
@getem
@paappii
ስታቀርቢኝ
ስለራቅኩሽ ፤
ስትወጂኝ
ችላ ስላልኩሽ ፤
ስታንሽልኝ
ስለናቅኩሽ ፤
ኮኮብ
ሰማይ
ፀሐይ
ጨረቃ ... ስታደርጊኝ
እንደ ሰው ስላልቆጠርኩሽ ፤
በነፍስሽ ላይ ስለቀለድኩ
በዕድሜሽ ላይ ስለተጫወትኩ ፤
ውብ ነፍስሽን ስላሳደፍኩ
ስስ ልብሽን ስለሰበርኩ ፤
ልኬ ድረስ ስትመጭ
ልክሽ ድረስ ስላልወረድኩ ፤
ገላሽን
እንደ ትቢያ አፈር
ነፍስሽን
እንደ ዕድፍ ምንጣፍ
ተራ አድርጌ ስለቆጠርኩ ፤
ይቅርታ !
____
አዬሽ
የሰው ስቃዩ ይሄው ነው፤
እኔም ለወደድኳት ያዬሁት መከራ
ያንቺኑ ያኽል ነው ።
By Tewodros kasa
@getem
@getem
@paappii
__
የመኖር ምክንያቶች —
ምኞት ፍላጎቶች ከ
“ና” ያልኩት አይምጣ `ምጠብቀው ይቅር ።
ይሄ ሁሉ ቢሆን....
አይታወቀኝም — ( የሆነ አይመስለኝም)
እንኳንስ ልከፋ ፤
የካብኩት ይደርመስ ያገኘሁት ይጥፋ ።
የጣድኩት ይገንፍል — ያበረድኩት ይፍላ ፣
የምወዳት ጉብል — ትሂድ ወደ ሌላ ፣
ግድም አይሰጠኝም ከእንግዲህ በኋላ ።
እንዳሻው እንዳሻው —
ሁሉ እንደ መድረሻው እንደ ፍላጎቱ ፤
ዘመን ሽምጥ ይጋልብ..
ይሸከርከር ሰዓቱ ።
ምንም አይመስለኝም !
ላድርገው (ልድረሰው) የምለው የለኝም ።
ይሁን ልቤ ባዶ — ይሁን ልቤ ኦና፤
የሕይወትን መንገድ — ገና ሳልጀምረው
ደክሜያለሁና ።
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
የመኖር ምክንያቶች —
ምኞት ፍላጎቶች ከ
ኔ ላይ ይነሱ ፤
እንደ ጎርፍ — እንደ ወንዝ.....
በመሬት ይፍሰሱ ።
እኔ እንደሁ.... እኔ እንደሁ.....
ቢቃና ቢሰበር — ቢጎድል ቢሞላ ፤
አንዳች ግድ የለኝም ከእንግዲህ በኋላ ።
ጫጩት ምኞቶቼ —
ጅማሬ ህልሞቼ ባልጠና ክንፋቸው....
ከዛፉ ልቤ ላይ — ተነስተው ይብረሩ ፤
እኔ ምን ተዳዬ ወድቀው ቢሰበሩ ።
አረም ይብቀልበት —·· ሸረሪት ያድራበት
የምመኘው ኑሮ —
ምጓጓለት ፍቅር ፤“ና” ያልኩት አይምጣ `ምጠብቀው ይቅር ።
ይሄ ሁሉ ቢሆን....
አይታወቀኝም — ( የሆነ አይመስለኝም)
እንኳንስ ልከፋ ፤
የካብኩት ይደርመስ ያገኘሁት ይጥፋ ።
የጣድኩት ይገንፍል — ያበረድኩት ይፍላ ፣
የምወዳት ጉብል — ትሂድ ወደ ሌላ ፣
ግድም አይሰጠኝም ከእንግዲህ በኋላ ።
እንዳሻው እንዳሻው —
ሁሉ እንደ መድረሻው እንደ ፍላጎቱ ፤
ዘመን ሽምጥ ይጋልብ..
ይሸከርከር ሰዓቱ ።
ምንም አይመስለኝም !
ላድርገው (ልድረሰው) የምለው የለኝም ።
ይሁን ልቤ ባዶ — ይሁን ልቤ ኦና፤
የሕይወትን መንገድ — ገና ሳልጀምረው
ደክሜያለሁና ።
_
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@paappii
------ነው የምሆነው
"በሰማዩ ፈረስ ተጓዥን አድርሼ
በተካንኩት ጥበብ ታማሚን ፈውሼ
ለሀገሬ ቆሜ ማስጠራት ነው ስሜ
መሀንዲስ መሆን ነው የወደፊት ህልሜ
ብዬ ነበር ያኔ በልጅነት ወዜ
ሳድግ ምሆነውን በተጠየቅሁ ጊዜ።
ጥብቅና በመቆም ፍትህ ለተጠማ
እውነት እሰብካለሁ በውሸት ከተማ።
ብልሃተኛ ሆኜ ችግርን መርማሪ
በነጋ በጠባ ሰላምን አብሳሪ
ጥበብን ከቀለም ለትውልድ ነጋሪ።
ብዬ ነበር ያኔ በልጅነት ወዜ
ወዳጆቼ ሁሉ በጠየቁኝ ጊዜ፡፡
ወጥቼ እያደርኩ ለሀገር እሰ'ዋለሁ
ባይኖረኝም በትር ህዝብ አሻግራለሁ
ፍጥረቴ ሰው አይደል ለሰው እኖራለሁ።
አቀነቅናለሁ ለምንዱብ ድምፅ ሆኜ
በጥበቡ አለም ገሀዱን ተውኜ
በሰፈርኩት ቁና 'ሰፍራለሁ መዝኜ፡፡
በፍ'ቅር ሮጣለሁ ለሰንደቅ ዓለማ
የእምዬን ክብር ለአለም እንዲሰማ"።
ብዬ ነበር ያኔ በተጠየቅሁ ጊዜ
የወደፊት ህልሜ በልጅነት ወዜ።
by Abuugida
@getem
@getem
@getem
"በሰማዩ ፈረስ ተጓዥን አድርሼ
በተካንኩት ጥበብ ታማሚን ፈውሼ
ለሀገሬ ቆሜ ማስጠራት ነው ስሜ
መሀንዲስ መሆን ነው የወደፊት ህልሜ
ብዬ ነበር ያኔ በልጅነት ወዜ
ሳድግ ምሆነውን በተጠየቅሁ ጊዜ።
ጥብቅና በመቆም ፍትህ ለተጠማ
እውነት እሰብካለሁ በውሸት ከተማ።
ብልሃተኛ ሆኜ ችግርን መርማሪ
በነጋ በጠባ ሰላምን አብሳሪ
ጥበብን ከቀለም ለትውልድ ነጋሪ።
ብዬ ነበር ያኔ በልጅነት ወዜ
ወዳጆቼ ሁሉ በጠየቁኝ ጊዜ፡፡
ወጥቼ እያደርኩ ለሀገር እሰ'ዋለሁ
ባይኖረኝም በትር ህዝብ አሻግራለሁ
ፍጥረቴ ሰው አይደል ለሰው እኖራለሁ።
አቀነቅናለሁ ለምንዱብ ድምፅ ሆኜ
በጥበቡ አለም ገሀዱን ተውኜ
በሰፈርኩት ቁና 'ሰፍራለሁ መዝኜ፡፡
በፍ'ቅር ሮጣለሁ ለሰንደቅ ዓለማ
የእምዬን ክብር ለአለም እንዲሰማ"።
ብዬ ነበር ያኔ በተጠየቅሁ ጊዜ
የወደፊት ህልሜ በልጅነት ወዜ።
by Abuugida
@getem
@getem
@getem
፨
ካባ ጫንኩኝ ለሷ ብዬ፡
ዘውድ ገፋች ለኔ ብላ፥
የኋላዬን ኋሏ ትቼ
የተክሊሉን ምኞት ጥላ፤
አብረን ቆመን አስቀደስን
ተዋሃድን በኢየሱስ ደም፡
እሰይ አለፍን ተያይዘን
ያቃቃረን ወጥመድ ይውደም።
ሳያት ግና ደነገጥኩኝ
የናፍቆቴን ትንሽ ዞሬ
ይህ እምባዋን አላየውም
አብረን ሆነን እስከዛሬ
ጠይም መልኳ ማጀት ሆኖ
የባዶነት ግጥም ፅፏል
ወትሮ ሚስቅ ትንሽ አይኗ
ትኩስ እምባን አቸፍችፏል፤
መሪር ሀዘን የጥቁር ቅብ
የእምባ ጅረት ግድብ ላይኔ
ሀ,ለ የሚል፡ ቃል የሌለው
ያልተፈታ ባዶ ቅኔ።
ተሸበረ አንጀት ልቤ
ተሸሽጎ የነበረው
ፀፀት ወቶ በሀይል ገፋው፤
መቅደስ መሃል እንደቆምኩኝ
ካለውበት አለም ጠፋው።
ከሰማያት ሰማይ በላይ
በደመና ሽቅብ ሄጄ
ቁልቁል ነፍሴን ወረወርኩት፤
ከርሷ ጋራ ለመሆን ስል
አንድ ህልሟን ነው የነጠኩት።
ምንአለበት ፍቅር አይደለ
ባልቋደስ የሰው መባ
እንደህልሟ እናቷ ፊት
ተክሊል ደፍታ ብታገባ?
ምናለበት ባላገኛት
ባይበዛብኝ የኔ በደል
ለርሷ ሚሆን ትጉህ ንፁህ
በከተማው ሞልቶ አይደል?
ምን ነበረ ባላገኛት
ምን ነበረ ባልመኛት
እንዲህ እንዲህ ባለ ምሬት
ምትዋከብ ልቤ ጋለች
የኔ አበባ እኔን ስታይ
የውሸቷን ፈገግ አለች።
ከሰምኩላት
ወደኩላት
ንፁህ ፍቅሯ
መቅደስ መሃል
ዳግመኛ ልቤን ገዛው ፤
እዩዋት ጭንቄን ስታበዛው።
እዩዋት ፍርዴን ስታበዛው።
የዘመናት አንድያ ህልሟ
ያጠለልኩት እንደ ወንፊት
በምጢረ ተክሊል ከብሮ
መዳር ነበር አባቷ ፊት።
ላስተማራት የጌታን ቃል
ሽፍን አርጎ ካለም ስጋት
ለውለታው ምላሽ ነበር
አቅፎ ስሞ ላሳደጋት።
ጥሎሽ ድግስ ብልጭልጩ
አይፈልግም ለምን ጥቅም
ካህን አይደል ካንድ ልጁ
ከክብር ውጪ አይጠብቅም።
እሷም ብትሆን አልማለች
አንድ እያለች አመታቷን
እንደ ባሪያ ወርዳ ኖራ
ዛሬ ልትወስድ ሽልማቷን
ብትመጣም እምቢ አለች
እኔም ክፉ እጇን ያዝኩኝ
የተክሊሉ ኒሻን ቀርቶ
ሽልማቷ እኔ ሆንኩኝ።
ለምን እኔን ?
ለምን ለሷ?
አዳፋ አይደል ማንነቴ
ንፁህ አይደል ገላ ልብሷ
እሰጋለው ዛሬም እንኳን
ማንነቷን እንዳልቀማት
ጭራሽ በቃው ለሽልማት?
እሺ እምባዋስ?
እሺ አባቷስ?
ወዳጅ፣ ዘመድ ጎረቤቷስ?
አይ እዳዋ
ዝቅ ብላ አንገት ደፍታ
ምሽት ገብታ በሌት ወታ
አንዴ ዳዊት አንዴ ጥምቀት
አንዴ ቅኔ አንዴ ሰንበት
ብላ ኖራ ቤተ መቅደስ
እንደበራች የጧፍ ግማጅ
እምነት ፍቅሯን ሳትቀንሰው
ገላ ክብሯን ጠብቃ አድጋ
ሽልማቷ ፦ "ዘማዊ ሰው!"።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ካባ ጫንኩኝ ለሷ ብዬ፡
ዘውድ ገፋች ለኔ ብላ፥
የኋላዬን ኋሏ ትቼ
የተክሊሉን ምኞት ጥላ፤
አብረን ቆመን አስቀደስን
ተዋሃድን በኢየሱስ ደም፡
እሰይ አለፍን ተያይዘን
ያቃቃረን ወጥመድ ይውደም።
ሳያት ግና ደነገጥኩኝ
የናፍቆቴን ትንሽ ዞሬ
ይህ እምባዋን አላየውም
አብረን ሆነን እስከዛሬ
ጠይም መልኳ ማጀት ሆኖ
የባዶነት ግጥም ፅፏል
ወትሮ ሚስቅ ትንሽ አይኗ
ትኩስ እምባን አቸፍችፏል፤
መሪር ሀዘን የጥቁር ቅብ
የእምባ ጅረት ግድብ ላይኔ
ሀ,ለ የሚል፡ ቃል የሌለው
ያልተፈታ ባዶ ቅኔ።
ተሸበረ አንጀት ልቤ
ተሸሽጎ የነበረው
ፀፀት ወቶ በሀይል ገፋው፤
መቅደስ መሃል እንደቆምኩኝ
ካለውበት አለም ጠፋው።
ከሰማያት ሰማይ በላይ
በደመና ሽቅብ ሄጄ
ቁልቁል ነፍሴን ወረወርኩት፤
ከርሷ ጋራ ለመሆን ስል
አንድ ህልሟን ነው የነጠኩት።
ምንአለበት ፍቅር አይደለ
ባልቋደስ የሰው መባ
እንደህልሟ እናቷ ፊት
ተክሊል ደፍታ ብታገባ?
ምናለበት ባላገኛት
ባይበዛብኝ የኔ በደል
ለርሷ ሚሆን ትጉህ ንፁህ
በከተማው ሞልቶ አይደል?
ምን ነበረ ባላገኛት
ምን ነበረ ባልመኛት
እንዲህ እንዲህ ባለ ምሬት
ምትዋከብ ልቤ ጋለች
የኔ አበባ እኔን ስታይ
የውሸቷን ፈገግ አለች።
ከሰምኩላት
ወደኩላት
ንፁህ ፍቅሯ
መቅደስ መሃል
ዳግመኛ ልቤን ገዛው ፤
እዩዋት ጭንቄን ስታበዛው።
እዩዋት ፍርዴን ስታበዛው።
የዘመናት አንድያ ህልሟ
ያጠለልኩት እንደ ወንፊት
በምጢረ ተክሊል ከብሮ
መዳር ነበር አባቷ ፊት።
ላስተማራት የጌታን ቃል
ሽፍን አርጎ ካለም ስጋት
ለውለታው ምላሽ ነበር
አቅፎ ስሞ ላሳደጋት።
ጥሎሽ ድግስ ብልጭልጩ
አይፈልግም ለምን ጥቅም
ካህን አይደል ካንድ ልጁ
ከክብር ውጪ አይጠብቅም።
እሷም ብትሆን አልማለች
አንድ እያለች አመታቷን
እንደ ባሪያ ወርዳ ኖራ
ዛሬ ልትወስድ ሽልማቷን
ብትመጣም እምቢ አለች
እኔም ክፉ እጇን ያዝኩኝ
የተክሊሉ ኒሻን ቀርቶ
ሽልማቷ እኔ ሆንኩኝ።
ለምን እኔን ?
ለምን ለሷ?
አዳፋ አይደል ማንነቴ
ንፁህ አይደል ገላ ልብሷ
እሰጋለው ዛሬም እንኳን
ማንነቷን እንዳልቀማት
ጭራሽ በቃው ለሽልማት?
እሺ እምባዋስ?
እሺ አባቷስ?
ወዳጅ፣ ዘመድ ጎረቤቷስ?
አይ እዳዋ
ዝቅ ብላ አንገት ደፍታ
ምሽት ገብታ በሌት ወታ
አንዴ ዳዊት አንዴ ጥምቀት
አንዴ ቅኔ አንዴ ሰንበት
ብላ ኖራ ቤተ መቅደስ
እንደበራች የጧፍ ግማጅ
እምነት ፍቅሯን ሳትቀንሰው
ገላ ክብሯን ጠብቃ አድጋ
ሽልማቷ ፦ "ዘማዊ ሰው!"።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
(የአብስራ ሳሙኤል)
በለስ ሆነበት
እውነት
ስትነግረው
ሰበረው
ውሸት ምን ያህል ውብ ነበረ
ተሰበረ
የነፍሱን ሀቅ
ሳቅ
ነጠቀችው
ነገረችው
የሄደ ጊዜ
ነጠላ ረግጦ
አማግጦ
ጭኗን ሲተካው
ምርጫ ሲያስመካው
ጠረኗን ተፍቶ
ትቶ
የሄደ ጊዜ
የሄደ ለታ
ተስፋዋን ትታ
ዘሟች ፍቅሩን
ክብሩን
ልጠብቅ ብላ
እኔ ነኝ አለች
ፍቅሩን የገፋው
ስቼ ያጠፋው
የማገጥኩበት
ቁስል የሆንኩበት
እንጂማ የእሱ
ጻድቅ ነው ነፍሱ
አያቅም ነበር ክፉ ተናግሮ
ስድብ ወርውሮ
አያይም ነበር የሌላ ገላ
ከእኔ ሌላ
እንጂማ የእሱ
ጻድቅ ነው ነፍሱ
ለመጣሁ ሁሉ ምን ሆነሽ ላላት
ለስምህ የጻፈች ገድል ነበራት
የምትነግረው
የምታበስረው
መቼ ሆኖላት ስሙን አጥፍታ
አውርታ
ለመጣው ሁሉ ትኩውለው ነበር
ክፋ ማን ነበር ?
እሷ
የረከሰች ነፍሷ
በነገረቻቸው ልኬት
አበጁላት ስፌት
ነጠላዋን ቀደው
ክብሯን ንደው
የውርደት ቃል ነሰነሱ
እንጂማ የእሱ
እንጂማ የእሷ
ጣት ቀስሯ አታቅ
ታማኝ ነች ነፍሷ
ብቻ ለሱ ነገረችው
ይመጣ ይሆን ብላ መሰል
የሱን ሀጥያት እሷ መምሰል
የሱን ውርደት ዝሙት ሀቁን
እንዳለቀሰች ተውሳ ሳቁን
ሱሪ አስታጥቃው
ቀሚስ መቅደዷን
መዋረዷን
ለጠየቋት ሁሉ
እምነቷ መቅለሉ
ለሱ ብቻ ነገረችው
ያዝን ይሆን ብላ መሰል
ጽድቋን ችራ
የሱን ሀጥያት እሷ መምሰል
ብትነግረው
ሰበረው
ውሸት ምን ያህል ውብ ነበረ
ተሰበረ
በሀቋ
ባዳፋ ሳቋ
ስሟን አጉድፋ ስም ብትቸረው
ረግጧት ሲሄድ
የምትጽፍለት ገድል ነበረው
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
በለስ ሆነበት
እውነት
ስትነግረው
ሰበረው
ውሸት ምን ያህል ውብ ነበረ
ተሰበረ
የነፍሱን ሀቅ
ሳቅ
ነጠቀችው
ነገረችው
የሄደ ጊዜ
ነጠላ ረግጦ
አማግጦ
ጭኗን ሲተካው
ምርጫ ሲያስመካው
ጠረኗን ተፍቶ
ትቶ
የሄደ ጊዜ
የሄደ ለታ
ተስፋዋን ትታ
ዘሟች ፍቅሩን
ክብሩን
ልጠብቅ ብላ
እኔ ነኝ አለች
ፍቅሩን የገፋው
ስቼ ያጠፋው
የማገጥኩበት
ቁስል የሆንኩበት
እንጂማ የእሱ
ጻድቅ ነው ነፍሱ
አያቅም ነበር ክፉ ተናግሮ
ስድብ ወርውሮ
አያይም ነበር የሌላ ገላ
ከእኔ ሌላ
እንጂማ የእሱ
ጻድቅ ነው ነፍሱ
ለመጣሁ ሁሉ ምን ሆነሽ ላላት
ለስምህ የጻፈች ገድል ነበራት
የምትነግረው
የምታበስረው
መቼ ሆኖላት ስሙን አጥፍታ
አውርታ
ለመጣው ሁሉ ትኩውለው ነበር
ክፋ ማን ነበር ?
እሷ
የረከሰች ነፍሷ
በነገረቻቸው ልኬት
አበጁላት ስፌት
ነጠላዋን ቀደው
ክብሯን ንደው
የውርደት ቃል ነሰነሱ
እንጂማ የእሱ
እንጂማ የእሷ
ጣት ቀስሯ አታቅ
ታማኝ ነች ነፍሷ
ብቻ ለሱ ነገረችው
ይመጣ ይሆን ብላ መሰል
የሱን ሀጥያት እሷ መምሰል
የሱን ውርደት ዝሙት ሀቁን
እንዳለቀሰች ተውሳ ሳቁን
ሱሪ አስታጥቃው
ቀሚስ መቅደዷን
መዋረዷን
ለጠየቋት ሁሉ
እምነቷ መቅለሉ
ለሱ ብቻ ነገረችው
ያዝን ይሆን ብላ መሰል
ጽድቋን ችራ
የሱን ሀጥያት እሷ መምሰል
ብትነግረው
ሰበረው
ውሸት ምን ያህል ውብ ነበረ
ተሰበረ
በሀቋ
ባዳፋ ሳቋ
ስሟን አጉድፋ ስም ብትቸረው
ረግጧት ሲሄድ
የምትጽፍለት ገድል ነበረው
By @yabisrasamuel
@getem
@getem
@paappii
(የአብስራ ሳሙኤል)
ሰውና አምላኩ ሸንጎ ገጠሙ
ዳኛ እንዲሆኑ ጻድቃን ታደሙ
ገብርኤል ክንፉን እያናጠፈ
ሰጋሪው ውሀን እየቀዘፈ
ጸሀይ ከገባኦት
ጌታ ከጸባኦት
ህያዋን ሁሉ ተሰበሰቡ
እንዴት የሰው ልጅ
ጣት ለመቀሰር ደፈረ ልቡ
ጌታም ከዙፋን ቢያቀውም ድሉን
ይሞክር ብሎ ፍጡር የድሉን
ሸንጎ ቀረበ እንደገደፈ
°°°°°°°°°°°እንደቀጠፈ
ጸጥ እረጭ አለ ከንቱው ጫጫታ
መቼም ታላቅ ነው በል ጀምር ጌታ
1 .ተከሳሽ
በዕለተ ሰንበት ከመቅደስ ቆሜ
ወንጌል ሳስተምር ስሰብክ በስሜ
አንዲት መጻጉ ፩፮ አመት ደም የፈሰሳት
በጄ ዳስሼ እንድፈውሳት
መባ ጸሎቷ እውን እንዲሆን
እስቲ ትጠየቅ
ይሄን መፈጸም ቅጥፈት እንደሆን
2.ከሳሽ
መቼም ታቃለህ የልብ የሆዴን
ኖረህ ቃኝተሀል የዕድሜ መንገዴን
ለታመመ ሰው
በሰአት ስቅታ ደም ለሚፈሰው
ልጅነት ሳቁን በህመም በጣር ለተነጠቀ
ሄዋን ገላውን ፍቅር ተገፍቶ እንደወደቀ
በጭቃው ሰርቶ ምኞት ሀሳቡን
ትንፋሽ ስትነሳው የህይወት ቀለቡን
ሸንጎ ብሰይም ከቶ አትገረም
አረፈድክ እንጂ ቀረ አልተባለም
3.ዳኛ
ግራና ቀኙን እንዳደመጥነው
ጥፋተኛ ነው ብለን የወሰነው
ጌታን አይደለም
ሞልታ አትሞላም አንዲ ናት አለም
ስለዚህ ጌታን ወደዙፋኑ አሰናብተናል
ያንቺንም ሀዘን ሰምተን አዝነናል
4.????
ግን ምን ይደረግ
አማኞች ፈራጅ በሆኗት አለም
አሜን ነው እንጂ ለምን! ቃል የለም
@getem
@getem
@getem
ሰውና አምላኩ ሸንጎ ገጠሙ
ዳኛ እንዲሆኑ ጻድቃን ታደሙ
ገብርኤል ክንፉን እያናጠፈ
ሰጋሪው ውሀን እየቀዘፈ
ጸሀይ ከገባኦት
ጌታ ከጸባኦት
ህያዋን ሁሉ ተሰበሰቡ
እንዴት የሰው ልጅ
ጣት ለመቀሰር ደፈረ ልቡ
ጌታም ከዙፋን ቢያቀውም ድሉን
ይሞክር ብሎ ፍጡር የድሉን
ሸንጎ ቀረበ እንደገደፈ
°°°°°°°°°°°እንደቀጠፈ
ጸጥ እረጭ አለ ከንቱው ጫጫታ
መቼም ታላቅ ነው በል ጀምር ጌታ
1 .ተከሳሽ
በዕለተ ሰንበት ከመቅደስ ቆሜ
ወንጌል ሳስተምር ስሰብክ በስሜ
አንዲት መጻጉ ፩፮ አመት ደም የፈሰሳት
በጄ ዳስሼ እንድፈውሳት
መባ ጸሎቷ እውን እንዲሆን
እስቲ ትጠየቅ
ይሄን መፈጸም ቅጥፈት እንደሆን
2.ከሳሽ
መቼም ታቃለህ የልብ የሆዴን
ኖረህ ቃኝተሀል የዕድሜ መንገዴን
ለታመመ ሰው
በሰአት ስቅታ ደም ለሚፈሰው
ልጅነት ሳቁን በህመም በጣር ለተነጠቀ
ሄዋን ገላውን ፍቅር ተገፍቶ እንደወደቀ
በጭቃው ሰርቶ ምኞት ሀሳቡን
ትንፋሽ ስትነሳው የህይወት ቀለቡን
ሸንጎ ብሰይም ከቶ አትገረም
አረፈድክ እንጂ ቀረ አልተባለም
3.ዳኛ
ግራና ቀኙን እንዳደመጥነው
ጥፋተኛ ነው ብለን የወሰነው
ጌታን አይደለም
ሞልታ አትሞላም አንዲ ናት አለም
ስለዚህ ጌታን ወደዙፋኑ አሰናብተናል
ያንቺንም ሀዘን ሰምተን አዝነናል
4.????
ግን ምን ይደረግ
አማኞች ፈራጅ በሆኗት አለም
አሜን ነው እንጂ ለምን! ቃል የለም
@getem
@getem
@getem