ምን አጥፍተን ይሆን
.
.
ዳገቱን ስንወጣ ወድቀን ተነስተናል፤
ከተራራው አናት አብረን ተጉዘናል፤
የጠዋቷን ፀሐይ በደስታ ሞቀናል፤
በዉቧ ጨረቃ በፍቅር ደምቀናል።
ግና ናፍቆቴዋ................
በዛች የቀን ምራጭ ሰይጣን ሹክ ቢልህ፤
ፈጥነህ ተቀበልከዉ እሺታህን ሰጥተህ።
ከእግዜር ተጣልቼ ቀኒቱን ጠላኋት፤
ባትፈጠር ብዬ አምርሬ ረገምኳት።
እናም አካላቴ ምን ተሰምቶህ ይሆን?
አትፈልጊኝ ስትል ሀዘን ገብቶህ ይሆን?
እኔማ ናፍቆቴ.................
ምክንያቱን ሳላዉቀዉ፤
አንተም ሳትረዳዉ።
እንለያይ ብለህ ከጎኔ ስትርቀኝ፤
በላዬ ተንዶ ምድር ተደፋብኝ፤
የማደርገዉ አጣሁ ቀኑ ጨለመብኝ፤
ብልሀቴ ጠፍቶ ማጣፊያው ራቀኝ።
ትናንት የቀኑብን ዛሬ እያሸሞሩ፤
ተለያዩ ብለዉ እንዲሰማ ሀገሩ፤
በቡና ሸፋፍነዉ ለፍፈዉ ነገሩ።
ሙጫ ነች እያሉ ፍርድ ይበይናሉ፤
ህመሜን ሳያዉቁ እንዲህ ነች ይላሉ።
ካንተ ጋ አብሮ ሄዷል ፈገግታና ስቄ፤
ዘወትር የምኖር ብሶቴን አምቄ።
ምን አጥፍተን ይሆን ?
እንዲህ የተቀጣን ?
እንደዉ በደፈናዉ በቃችሁ የተባልን፤
በናፍቆት ችንካራት የተቸነከርን።
መንገድህን መርጠህ ከእኔ ብትሸሽም፤
ተስቶህ ነው እንጂ በደልከኝ አልልም።
✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ዳገቱን ስንወጣ ወድቀን ተነስተናል፤
ከተራራው አናት አብረን ተጉዘናል፤
የጠዋቷን ፀሐይ በደስታ ሞቀናል፤
በዉቧ ጨረቃ በፍቅር ደምቀናል።
ግና ናፍቆቴዋ................
በዛች የቀን ምራጭ ሰይጣን ሹክ ቢልህ፤
ፈጥነህ ተቀበልከዉ እሺታህን ሰጥተህ።
ከእግዜር ተጣልቼ ቀኒቱን ጠላኋት፤
ባትፈጠር ብዬ አምርሬ ረገምኳት።
እናም አካላቴ ምን ተሰምቶህ ይሆን?
አትፈልጊኝ ስትል ሀዘን ገብቶህ ይሆን?
እኔማ ናፍቆቴ.................
ምክንያቱን ሳላዉቀዉ፤
አንተም ሳትረዳዉ።
እንለያይ ብለህ ከጎኔ ስትርቀኝ፤
በላዬ ተንዶ ምድር ተደፋብኝ፤
የማደርገዉ አጣሁ ቀኑ ጨለመብኝ፤
ብልሀቴ ጠፍቶ ማጣፊያው ራቀኝ።
ትናንት የቀኑብን ዛሬ እያሸሞሩ፤
ተለያዩ ብለዉ እንዲሰማ ሀገሩ፤
በቡና ሸፋፍነዉ ለፍፈዉ ነገሩ።
ሙጫ ነች እያሉ ፍርድ ይበይናሉ፤
ህመሜን ሳያዉቁ እንዲህ ነች ይላሉ።
ካንተ ጋ አብሮ ሄዷል ፈገግታና ስቄ፤
ዘወትር የምኖር ብሶቴን አምቄ።
ምን አጥፍተን ይሆን ?
እንዲህ የተቀጣን ?
እንደዉ በደፈናዉ በቃችሁ የተባልን፤
በናፍቆት ችንካራት የተቸነከርን።
መንገድህን መርጠህ ከእኔ ብትሸሽም፤
ተስቶህ ነው እንጂ በደልከኝ አልልም።
✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤40🔥4👍2
የአብስራ ሳሙኤል
፩.
ከቀጠራት ካፌ
የአባቧዋን ገላ እየቀነጠሰች
ጥሏት ከሄደበት
በሀሳብ ተከትላው በሀሳብ ተመለሰች
ያልጠጣውን ቡና እንፋሎት ታየለች
ጠረኑን ቀላቅሎ ብን'ብሎ ሲጠፋ
እንደ ጠዋት ጤዛ እንደ ቀቢጸ ተስፋ
የመሄዱን ዳና እያመሳሰለ
ከመኖር ጎደለ
―✦―
፪.
እንባ አቅርሯል አይኑ
ዞር ብሎም ለማየት አልቀናም ልቡናው
ያውቀዋል ህሊናው
ሰው አልመጠናትም
ያቀፈችው ሁሉ ትከሻው አልሞቃትም
አትገባም ለሱ
ሰው አልሆነም እሱ
ቢጽፍላት ቢቀኝላት
እልፍ ግጥም እልፍ ቅኔ
መልኳን ተሳልሞ መመለስ ነው
ቃል አያቅም የ'ሱ ወኔ
―✦―
፫.
እናም እሷም ካለችበት እሱም ከሄደበት
በቀስተ ደመና አድማስ የሚያጣምር
የማይኖሩት ፍቅር
ለምትኖረው ህይወት እስትንፋሱን ቸረ
ሄደ ያለችው ገላ ሲመራት ነበረ
―☾―
@getem
@getem
@getem
፩.
ከቀጠራት ካፌ
የአባቧዋን ገላ እየቀነጠሰች
ጥሏት ከሄደበት
በሀሳብ ተከትላው በሀሳብ ተመለሰች
ያልጠጣውን ቡና እንፋሎት ታየለች
ጠረኑን ቀላቅሎ ብን'ብሎ ሲጠፋ
እንደ ጠዋት ጤዛ እንደ ቀቢጸ ተስፋ
የመሄዱን ዳና እያመሳሰለ
ከመኖር ጎደለ
―✦―
፪.
እንባ አቅርሯል አይኑ
ዞር ብሎም ለማየት አልቀናም ልቡናው
ያውቀዋል ህሊናው
ሰው አልመጠናትም
ያቀፈችው ሁሉ ትከሻው አልሞቃትም
አትገባም ለሱ
ሰው አልሆነም እሱ
ቢጽፍላት ቢቀኝላት
እልፍ ግጥም እልፍ ቅኔ
መልኳን ተሳልሞ መመለስ ነው
ቃል አያቅም የ'ሱ ወኔ
―✦―
፫.
እናም እሷም ካለችበት እሱም ከሄደበት
በቀስተ ደመና አድማስ የሚያጣምር
የማይኖሩት ፍቅር
ለምትኖረው ህይወት እስትንፋሱን ቸረ
ሄደ ያለችው ገላ ሲመራት ነበረ
―☾―
@getem
@getem
@getem
❤31👍5🔥1
⁂
የአብስራ ሳሙኤል
⁂
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ
ማለፊያ ምግባር ምን ሰራህ
በኖርክባት ስንዝር እድሜ
ምን'ን ዘርተህ ምን አፈራህ
እንዴያው ሲያስበው ይጨንቀኛል
ነፍሴን እንዳል'ጥላት እፈራለሁ
ፈራሽ ገላ ተጫምቼ
ስንት ዘመን እኖራለሁ
የእንባ ብዕር ከሚጠቀስበት
መዝገብ እንዳላሰፍር
መሾ ከሚወርድበት
ክብሬን እንዳላሳፍር
ለመንግስትህ እጨኝ ባልልም
ከመከራው ጠብቀኝ
የኔ እውቀት አያድነኝም
መልካሙን አንተ አሳውቀኝ
ለማትሞላ ጎደሎ ምድር
ህልም ነው ወዳልከው ስትለፋ
ተስፋ ነው ወዳልከው ስትገፋ
ማረፍ አይቀርምና ታርፋለህ
መሞት አይቀርምና ትሞታለህ
ማለፊያ ምግባር የሚሆን
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ
የበገና ክር መወጠር
ለዜማው መጣም ነው'ና
ምስገና መባ እንዲሆን
የህይወትህ ጥኡም ቃና
ለመንግስትህ እጨን ባንልም
ከመከራው አንተ ጠብቀን
የ'ኛ እውቀት አያድነንም
መልካሙን አንተ አሳውቀን
⁂
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ ?
@getem
@getem
@getem
❤48🔥3🤩1
.
ከገነት ላለኸዉ
.
የ'ግር እሳት ሆኖ ቢገርፈኝ መለየት ፍም እሳቱ፤
ልቤን አቀጣጠላት የናፍቆትህ ስር ግለቱ፤
በዛች የቀን ጎዶሎ ጥቁር ሞት አንተን ሲጠራ፤
እኔንም ጠርቶኝ በነበር ብጓዝ ከፍቅሬ ጋራ፤
ካንተ መራቅ አይሆንልኝ፤
ሌጣ ሆኜ አያምርብኝ፤
ዘወትር..መቃብርህን አቅፌ ስስም 'ዉላለሁ፤
ነጋ ጠባ..ስምህን ስደጋግም አድራለሁ፤
ያዩኝ በሙሉ.........
አበደች እያሉ ሲያሸሙሩብኝ፤
ከመቃብር አድራ ተለከፈች ሲሉኝ፤
መች ጆሮ ሰጠሁኝ መች አዳመጥኳቸዉ፤
ሞቷል እርሽዉ ሲሉኝ ላይኔ ጠላኋቸዉ፤
አይገባቸዉማ..........
በድኔን አስቀርታኝ መከረኚት ልቤ፤
አብራህ እንደሄደች አያዉቁም አሳቤ፤
ነፍሴ ከነፍስህ ጋር እንደተሳሰረች፤
ዳግም ላትነጠል እንደተጋመደች፤
ከጎኔ ባለገኝህም አይዞሽ ባትለኝ አንዴ፤
ጠረንህ ቢናፍቀኝም ባታባብለኝ ዉዴ፤
መቼም ላይጠፋ ከእኔነቴ፤
ዛሬም ህያዉ ነው ፍቅርህ ናፍቆቴ።
በዔደን ታደሰ እንደተፃፈ
@topazionnn
@getem
@getem
❤17😢8👎1
መኖሬ ከሆነ
እግሬ እንዳይራመድ
ልቤ ሲያጠምድ ወጥመድ
ልርቅ ስል ከሁሉ
ሲቀርቡኝ በሙሉ
አሉልኝ ያልኩኝ ለት
ብትንትን ሲሉ
በቅፅበት ደስታ
ስረሳው ሀዘኔን
ትንሽ ፈገግ አልኩኝ
ላነባው ዘመኔን
ወይ አለምን ንቄ
አልመነንኩ ከደብሩ
ወይ አልተሳካልኝ
አልተመቸኝ ምድሩ
መኖሬ ከሆነ ይቅርብኝ
ግድየለም ውሰደኝ እግዜሩ ።
By ኢዮብ_ዮሚን
@getem
@getem
@paappii
እግሬ እንዳይራመድ
ልቤ ሲያጠምድ ወጥመድ
ልርቅ ስል ከሁሉ
ሲቀርቡኝ በሙሉ
አሉልኝ ያልኩኝ ለት
ብትንትን ሲሉ
በቅፅበት ደስታ
ስረሳው ሀዘኔን
ትንሽ ፈገግ አልኩኝ
ላነባው ዘመኔን
ወይ አለምን ንቄ
አልመነንኩ ከደብሩ
ወይ አልተሳካልኝ
አልተመቸኝ ምድሩ
መኖሬ ከሆነ ይቅርብኝ
ግድየለም ውሰደኝ እግዜሩ ።
By ኢዮብ_ዮሚን
@getem
@getem
@paappii
Telegram
✍ዮ_ሚን
ፈጠራዎችን እንደመምባቸዋለን ስለሀሳብ እንሰማለን፡፡ እናሰላስላለን፡፡ ሰክረን ሳይሆን ሰክነን፡፡ሀሳብን እናስበዋለን፡፡
ዘላለም የሚቆየው ሀሳብ ነው፡፡
@Yob_minn
ዘላለም የሚቆየው ሀሳብ ነው፡፡
@Yob_minn
❤40😢6🤩1
" አሜን"
( ግዮናይ ነኝ)!፧
አንቺ ጋር ለመኖር...
ሺ ቁልቁል ወርጄ ብዙ ዳገት ወጣሁ፣
ዳኛ ሳይፈርድብኝ...
እንደ ወንጀለኛ በኑሮ ተቀጣሁ፣
ያ'ርባ ቀን ዕድሌን እጣ ፈንቴን አጣሁ።
* * *
ህይወትን ተራብኩኝ...
እንጃ ስለ ፍቅር ጥላቻን ተጠማሁ፣
ይኸው ደሞ ዛሬ...
እንለያይ የሚል ካ'ንደበትሽ ሰማሁ።
አሜን ያደርግልኝ...
እዛ ማዶ ልጓዝ ፍቅርሽን አልፌ፣
(አልጋዬ የት ነበር?)...
እስኪ ጋደም ልበል ናፍቆኛል እንቅልፌ።
* * *
ሰውነቴ ሁሉ...
እንደ ብሉይ ኃጢያት ለምጻም ሰው መሰለ፣
ፈጣሪ ያውቀኛል...
ህይወቴ ላ'ንቺነት ብዙ እንደ ቆሰለ።
ልሽሽ ካለሽበት...
ምድር እስከምታልቅ በሌትና ቀትር፣
ባህር እንኳን ባገኝ...
ሙሴ ይሰጠኛል የመክፈያ በትር።
@getem
@getem
@paappii
( ግዮናይ ነኝ)!፧
አንቺ ጋር ለመኖር...
ሺ ቁልቁል ወርጄ ብዙ ዳገት ወጣሁ፣
ዳኛ ሳይፈርድብኝ...
እንደ ወንጀለኛ በኑሮ ተቀጣሁ፣
ያ'ርባ ቀን ዕድሌን እጣ ፈንቴን አጣሁ።
* * *
ህይወትን ተራብኩኝ...
እንጃ ስለ ፍቅር ጥላቻን ተጠማሁ፣
ይኸው ደሞ ዛሬ...
እንለያይ የሚል ካ'ንደበትሽ ሰማሁ።
አሜን ያደርግልኝ...
እዛ ማዶ ልጓዝ ፍቅርሽን አልፌ፣
(አልጋዬ የት ነበር?)...
እስኪ ጋደም ልበል ናፍቆኛል እንቅልፌ።
* * *
ሰውነቴ ሁሉ...
እንደ ብሉይ ኃጢያት ለምጻም ሰው መሰለ፣
ፈጣሪ ያውቀኛል...
ህይወቴ ላ'ንቺነት ብዙ እንደ ቆሰለ።
ልሽሽ ካለሽበት...
ምድር እስከምታልቅ በሌትና ቀትር፣
ባህር እንኳን ባገኝ...
ሙሴ ይሰጠኛል የመክፈያ በትር።
@getem
@getem
@paappii
❤29👍2🔥2🤩1
ድክም ብል በሂወት መንገድ
እግሬ ቢዝል ብሰናከል
ቆፈን ብለብስ ለገላዬ
ቁራሽ ዳቦ ብከለከል
ቀን ቢገፋኝ ካለሁበት
ከከፍታ ብወረወር
"አትመጥንም" ብባል በአፍ
ከአመት አመት በቀን በወር
አይኔ ደምን ሰርክ ቢያነባ
እቅድ ግቤ ቢፋለስም
ዳና ትግሌን አደብዝዘው
ያለ ስሜ ቢሰጡኝ ስም
አትጨናነቂ
ዝምብለሽ ሳቂ!
አታውቂምና ነው!
ቀን የገፋውን ሰው ቀን እንደሚያነሳው
ፈጣሪ ላልከዳው እሱ እንደማይረሳው
አታውቂምና ነው!
ዝቅ ያለ ሰው ሁሉ ከፍታ እንደሚያገኝ
ማርያም
ማርያም ላለ ፈጣሪ እንደሚገኝ
አታውቂምና ነው!
ሞን ያስለቅስሻል ለምን ትጨነቂ
ሁሉ በርሱ ይሆናል ዝም ብለሽ ሳቂ
ቀን ሳይገፋ አያልፍም ቀን
አልፈጠረብሽም ምንድነው ሰቀቀን
ለኔ ብለሽ አትድከሚ
አይብረድሽ ፍርሃት ቁር
ጊዜ አይፈጅም ለመልስማ
ካምላክ ሄጄ ብቆረቁር
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ተስፋ መቁረጥ አይነበብ ካካል ገፅሽ ከመልክሽ ላይ
ሀይል ብርታቴ ይጨምራል የፊትሽን ፈገግታ ሳይ።
አንዲት ቅንጣት እንባ እንዳላይ ተደርድሮ ከጉንጭሽ ስር
ቀን እንደሆን አመሏ ነው ልታነሳ ምትሰረስር።
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
እግሬ ቢዝል ብሰናከል
ቆፈን ብለብስ ለገላዬ
ቁራሽ ዳቦ ብከለከል
ቀን ቢገፋኝ ካለሁበት
ከከፍታ ብወረወር
"አትመጥንም" ብባል በአፍ
ከአመት አመት በቀን በወር
አይኔ ደምን ሰርክ ቢያነባ
እቅድ ግቤ ቢፋለስም
ዳና ትግሌን አደብዝዘው
ያለ ስሜ ቢሰጡኝ ስም
አትጨናነቂ
ዝምብለሽ ሳቂ!
አታውቂምና ነው!
ቀን የገፋውን ሰው ቀን እንደሚያነሳው
ፈጣሪ ላልከዳው እሱ እንደማይረሳው
አታውቂምና ነው!
ዝቅ ያለ ሰው ሁሉ ከፍታ እንደሚያገኝ
ማርያም
ማርያም ላለ ፈጣሪ እንደሚገኝ
አታውቂምና ነው!
ሞን ያስለቅስሻል ለምን ትጨነቂ
ሁሉ በርሱ ይሆናል ዝም ብለሽ ሳቂ
ቀን ሳይገፋ አያልፍም ቀን
አልፈጠረብሽም ምንድነው ሰቀቀን
ለኔ ብለሽ አትድከሚ
አይብረድሽ ፍርሃት ቁር
ጊዜ አይፈጅም ለመልስማ
ካምላክ ሄጄ ብቆረቁር
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ተስፋ መቁረጥ አይነበብ ካካል ገፅሽ ከመልክሽ ላይ
ሀይል ብርታቴ ይጨምራል የፊትሽን ፈገግታ ሳይ።
አንዲት ቅንጣት እንባ እንዳላይ ተደርድሮ ከጉንጭሽ ስር
ቀን እንደሆን አመሏ ነው ልታነሳ ምትሰረስር።
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤28👍3🔥1🎉1
የአብስራ ሳሙኤል
እስቲ ትንሽ እንፋለስ
እስቲ እግዜ'ርን እንሞግተው።
ህሊና ያለው ፍጡር መቼም
መልስ ቢያጣም ጥያቄ አይተው።
ስለምን ሰው እንደ ቅጠል
በየመስኩ እረገፈ?
ባለቤት አልባ ይመስል
በ"እኔ ነኝ" ባይ ተቀጠፈ?
—
ይቆረቁራል ጎዳናው
ደምና አጥንት መሰለኝ...
እንዴት አድርጌ ዝም ልበል?
ውስጤ "ጩኽ! ጩኽ!" እያለኝ!
—
ስለምን ጡት ያልጠባ ህጻን
ከእናቱ እቅፍ ተነጠቀ?
ለነፍሱ አጽናኝ ሳይኖረው
"በረብ! በቁር!" ማቀቀ...
ወደቀ...ወደቀ...ወደቀ...
—
ስለምን ምስኪን እናቱን
በኑሮ አካልበህ ደፋሀት?
የልጇን ጠረን ሳጠግበው
ከመቀመቅ ገፋሀት?
—
ህመም ሲቃ ጩኸት ነው
ንፋስ የሚንሾካሹከው...
እንደምን ይመጣል ብዬ
ምእመንህን ልስበከው?
—
"ያልፈል" ብሎ ቢጽናና
ቀን �ይዞት እያለፈ፤
ስለምን አማኝ ከእምነቱ
መፈተንን አተረፈ?
—
ዝምታው ተሰማኝ
አሁን ነገዬን ማሰብ ከበደኝ።
በየመስኩ በጎዳናው
የቁስል ጠረን እያወደኝ...
—
ከታሪክ አመሳክረናል
ወንጌል ላይ ነው ተአምርህ?
በዘመን ገጽ ስንቱን እንዳለፈ
እየነበርክ ምኑን ልንገርህ?
—
ስለምን ቸልታህ በዛ?
የስምህ ትርጉም ቀለለ?
በረሀብ ይሞታል ህዝብህ
ስለ እግዘብሔር እያለ!
—
ይቆረቁራል ጎዳናው
ደምና አጥንት መሰለኝ...
እንዴት አድርጌ ዝም ልበል?
ነፍሴ "ጩኽ! ጩኽ!" እያለኝ
. . . . . . . . . . . . .
@getem
@getem
@paappii
❤23🔥4👍2😢1
በምድር ፍትህ የለም
.........................
ለእውነት የሚቆም ራሱን የካደ
ከራሱ አስበልጦ አምሳሉን የወደደ
የአዳም ዘር ሆኖ በምድር ስለሌለ
ፍትህ በቃል ብቻ ተመዝግቦ ዋለ::✍
፠፠፠፠
ባለንባት አለም የኔም ያንተም ጠባይ
ለምድር ይቅርና ያስፈራል ለሰማይ::
እናም!... .
ፍትህ ለእገሊት!
ፍትህ ለእገሌ!
ፍትህ.......ፍትህ......!
ፍትህ........!
እያሉ መጮህ አንዳችም አይሰራም
እንኳንስ ለሰው ልጅ
ምንኖርባት ምድር ለንጉስ አትራራም፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@paappii
.........................
ለእውነት የሚቆም ራሱን የካደ
ከራሱ አስበልጦ አምሳሉን የወደደ
የአዳም ዘር ሆኖ በምድር ስለሌለ
ፍትህ በቃል ብቻ ተመዝግቦ ዋለ::✍
፠፠፠፠
ባለንባት አለም የኔም ያንተም ጠባይ
ለምድር ይቅርና ያስፈራል ለሰማይ::
እናም!... .
ፍትህ ለእገሊት!
ፍትህ ለእገሌ!
ፍትህ.......ፍትህ......!
ፍትህ........!
እያሉ መጮህ አንዳችም አይሰራም
እንኳንስ ለሰው ልጅ
ምንኖርባት ምድር ለንጉስ አትራራም፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@paappii
❤36😢12🔥4👍3
የአብስራ ሳሙኤል
ቀኑስ ከዳኝ እንዳላቅፍሽ
እንግዲህ ህልሜን ልለመነው
ወይ ወድጄሽ ላይሞላልኝ
ያገናኘን ለምንድነው
—
ኪዳን አለኝ ከለሊትሽ
ምስኪን ልቤን ሊያስተሳስር
በሰመመን ያደርሰኛል
ከመዳፍሽ ከእግሮችሽ ስር
—
ወብ ፈገግታሽ ተስረቅርቆ
እንደ ንፋስ ሊዳብሰኝ
ከጽናትሽ ተስፋን ሰርቆ
ለንጋት ጀንበር ሊያውሰኝ
—
ከልካ ይ የለው አጋጅ የለው
ወይ አይመሩት ወይ አይገሩት
ተኝቶም ቢሆን ይሄዳል....
ልብ እንደው ወዳ 'አፈቀሩት
—
አይዞሽ እዛ ትግል የለም
አረፍ በይ ከታዛው ስር
ህቡእ ፍቅሬን ታገኛለሽ
ህልሙን ከአንቺ ሲያስተሳስር
የእንቅልፉን በር ሲሰረስር።
—
አይዞሽ እዛ መራዝ የለም
የተራበ ሁሉ ይጠግባል
በህይወት የጠወለገው
አንቺን አይቶ ልቤ ያብባል
ተስፋ ምኞት ይቀለባል።
—
**ኪዳን አለኝ ከለሊትሽ
ምስኪን ልቤን ሊያስተሳስር
በሰመመን ያደርሰኛል
ከመዳፍሽ ከእግሮችሽ ስር
—
ቀኑስ ከዳኝ እንዳላቅፍሽ
እንግዲ'፣ ህልሜን ልለመነው
ወይ ወድጄሽ ላይሞላልኝ
ያገናኘን ለምንድነው.......
. . . . . . . . . . . . .
@getem
@getem
@getem
❤19🔥3👍1
ጨዋታዉ ፈረሰ
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
ቦጭቀን፤
ቦጫጭቀን፤
እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
ቦጭቀን፤
ቦጫጭቀን፤
እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤38👍3🔥2
የአብስራ ሳሙኤል
እንዲያው እንደ'ድንገት፣ እንዲሁ እንደ'ሁኑ፣
ደርሰን ስንገናኝ አይንሽን ብፈራ፣
"እረስቶኝ ነው" ብለሽ እንዳት'ጨነቂ፣
"ይጠላኛል" ብለሽ እንዳትጠብቂ።
* * *
አይን የማያይው፣ ጆሮ የማይሰማው፤
የልቤን ትርታ አፍኜ በልቤ፣
ወንድነት ቢያንሰኝ ነው፦
አይኔን መሰብሰቤ፣ ፊቴን መሸበቤ...
* * *
እንዲያው እንደ'ድንገት፣
እንዲያው እንደ'ነገው፣
ብዙ አመታት አልፎ፣ ቀን እና ቀን ተጠላልፎ፣
አዲስ ታሪክ ጽፎ፣ አዲስ ህይወት ነድፎ፣
መልክሽ እንደ አደይ፣ እንደ ጤዛ እረግፎ፣
የልጅነት ጊዜ ጭዋታና ፍቅሩን ስናፍቂ...
"ይጠላኛል" ብለሽ፣ "ይረሳኛል" ብለሽ እንዳትጠብቂ!
* * *
የዕድሜ መሰላሉን ብወጣ፣ ብሄድም፣
ህይወትን ብጓዘው፣
አለም ካጣበቡ እልፍ ሴቶች መሀል፦
ያንቺ ሳቅ ብቻ ነው፣ ቀልቤን የሚይዘው።
@getem
@getem
@paappii
❤18🔥3
•
[የውሃ ውርደቱ — የዥረት ቅሌቱ......
«መመለሱ ላይቀር ጎብጦ መደፋቱ ፤
"ፋውንቴን ነህ" ተብሎ ወደ ላይ መውጣቱ ።» ]
•
እኔ ገራም የምንጭ ውሃ .....
ኩልል ያልኩኝ ድምጽ አልባ “ማይ” ፤
ተራራ ላይ የቆምሽውን ክንፋም ውበት
በሩቅ የማይ ።
ክብርስ ለእኔ መውረድ ነው
መፍሰስ ቁልቁል በመሬት ፣
አንቺ ደግሞ ከከፍታው
በክንፍሽ አቅም መቆዬት ።
እንዳይሆን አርጎታል መቼም
ተፈጥሮ ነው እንቆቅልሽ ፤
እንዳንቺ ወደ ደመና
ከፍ ማለት ምን አውቅልሽ?!
ዥረት ነኝ እንዳ
•
መቼም ኗሪ ዝም አያውቅም ....
ይበልሽ ያሻውን ይፍረድ ፣
ዝቅ በይ “ውረጅ እንውረድ” ።
•
እንደዚህ ነግሬሽ እንጂ
መሪር ሀቁን አሳውቄ ፤
ውሃ ብሆን (እንዳ
ብሞክር እንኳን አልደርስም ፤
ተፈጥሮ ሕጉን አልጥስም ።
አንቺ ግን የመጣሽ እንደሁ.....
«ቤቷ ነበር ያ ደመና ....
ቤቷ ነበር ያ ተራራ ፣
እዩዋት ክንፍ እንደሌላት
በዥረት ጀርባ ተሳፍራ ፣
ወረደች! አይ ተዋረደች
አጃዒብ ፍቅር! » ይባላል
ማ`ናችን ብንቀል ይቀላል?
•
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
[የውሃ ውርደቱ — የዥረት ቅሌቱ......
«መመለሱ ላይቀር ጎብጦ መደፋቱ ፤
"ፋውንቴን ነህ" ተብሎ ወደ ላይ መውጣቱ ።» ]
•
እኔ ገራም የምንጭ ውሃ .....
ኩልል ያልኩኝ ድምጽ አልባ “ማይ” ፤
ተራራ ላይ የቆምሽውን ክንፋም ውበት
በሩቅ የማይ ።
ክብርስ ለእኔ መውረድ ነው
መፍሰስ ቁልቁል በመሬት ፣
አንቺ ደግሞ ከከፍታው
በክንፍሽ አቅም መቆዬት ።
እንዳይሆን አርጎታል መቼም
ተፈጥሮ ነው እንቆቅልሽ ፤
እንዳንቺ ወደ ደመና
ከፍ ማለት ምን አውቅልሽ?!
ዥረት ነኝ እንዳ
ኗኗሬ
"ውረጅ እንውረድ" ነው
ምልሽ ።•
መቼም ኗሪ ዝም አያውቅም ....
ይበልሽ ያሻውን ይፍረድ ፣
ዝቅ በይ “ውረጅ እንውረድ” ።
•
እንደዚህ ነግሬሽ እንጂ
መሪር ሀቁን አሳውቄ ፤
ውሃ ብሆን (እንዳ
መሌ)
አልወስድሽም አሳስቄ ።
•
ውብዬ ...
(ወደድኩም ብዬ.....)
ወዳ
ንቺ ሽቅብ ለመውጣት ብሞክር እንኳን አልደርስም ፤
ተፈጥሮ ሕጉን አልጥስም ።
አንቺ ግን የመጣሽ እንደሁ.....
«ቤቷ ነበር ያ ደመና ....
ቤቷ ነበር ያ ተራራ ፣
እዩዋት ክንፍ እንደሌላት
በዥረት ጀርባ ተሳፍራ ፣
ወረደች! አይ ተዋረደች
አጃዒብ ፍቅር! » ይባላል
ማ`ናችን ብንቀል ይቀላል?
•
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
❤16👍2
ጊዜው ተቀይሮ
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ
ብናኝ ትቢያ አክሎ
ሁሉ እንኳን ቢሆን ፥ የማይታመን
አንተ ግን እመን
አንተ ግን ታመን
አሁንም በግ ሁን ፥ በፍየል ዘመን ።
ግዴታ አይደለም
ወከባን መልመድ
ወቅትን መዛመድ
ከጊዜው እኩል ፥ አብሮ መራመድ
ስለዚህ ውረድ !
እምቢ በል ገግም
ቀስ ብለህ አዝግም ።
አጉል መሰልጠን አያስፈልግም ።
ክፋት የለውም
በወግ በወጉ
ለገዢ ሀሳብ ቦታ ቢለቁ
ያረጀን ነገር በአዲስ ቢተኩ
ግን ደሞ አሉ - የማይነኩ ።
በጊዜ ፍጥነት የማይለኩ ።
እስካሁን ከመጣው
ገናም ከሚያመጣው
ከቁስ ከማሽኑ
ዘመን የማይሽርህ ፥ አንተ ነህ ፋሽኑ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ
ብናኝ ትቢያ አክሎ
ሁሉ እንኳን ቢሆን ፥ የማይታመን
አንተ ግን እመን
አንተ ግን ታመን
አሁንም በግ ሁን ፥ በፍየል ዘመን ።
ግዴታ አይደለም
ወከባን መልመድ
ወቅትን መዛመድ
ከጊዜው እኩል ፥ አብሮ መራመድ
ስለዚህ ውረድ !
እምቢ በል ገግም
ቀስ ብለህ አዝግም ።
አጉል መሰልጠን አያስፈልግም ።
ክፋት የለውም
በወግ በወጉ
ለገዢ ሀሳብ ቦታ ቢለቁ
ያረጀን ነገር በአዲስ ቢተኩ
ግን ደሞ አሉ - የማይነኩ ።
በጊዜ ፍጥነት የማይለኩ ።
እስካሁን ከመጣው
ገናም ከሚያመጣው
ከቁስ ከማሽኑ
ዘመን የማይሽርህ ፥ አንተ ነህ ፋሽኑ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
❤21🔥3😱2
ዝብርቅርቅ ባለዉ በህይወት አዙሪት፤
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤9👍1