.............
ትብታብ አይደለም ድግምት
ደብተራ አይደለም አስማት
ንጹሕ ፍቅር ነው ምናኔ
ለሚወዱት የመሞት ጭካኔ
እንኳን አሁን፤ከገላዬም ደም ቢነጥፍ
ደምስሬም ጅማቴም
ስምክን ነው የሚጥፍ
ዘረ ደሀ አፈቀርሽ
ዘራችንን አረከሽ
ብለው ቢያጠምቁኝም
ለፍቅርህ ስለሆን
የክፉዋች ጸበል፤መድን አይሆነኝም
ይልቅ በዛብህ፤አንጀትክን ሰብስብ
ከዛሬ ይልቅ፤ነገህን አስብ
አይዞህ በዛብህ፤ይህን ቀን ቻለው
ሰብለ ወንጌልህ
ከአትሮንስ ወርጄ ተጠፍሬያለው
ግን አትሳቀቅ፤ይህም ቀን ያልፈል
የክፉ ጅራፍ፤ጽናት ይጽፉል
የሚለው ቃሏን፤ከፍቅሩ ሰምቶ
በተስፋ አባብሎ፤ልቡን አጽናንቶ
ከተማ ገብቶ ቢጠብቃትም
ወንጌሉን ካሻው አላገኛትም
የእግዜር ኑዛዜ፤የእውነት ቃሉ
የአዳም ጥፋት፤የአምላክ አምሳሉ
የሄዌን ስህተት፤ክፉይ አካሉ
አትብላ ካለው፤ከፍሬው በልቶ
ፍቅርን በደለው፤የሞት ሞት ሞቶ
ግን በበዛብህ፤ቃሉ ልዩ ነው
ከህይወት መስቀል፤አዳኙ ማነው
አዳም ከበላው፤በለስ ሲያላምጥ
ከወንጌል ይልቅ፤ልቡን ሲያስበልጥ
ፍቅርን በደለው፤የኑሮ ጣጣው
በቃሉ አኑሮ በእውነቱ ቀጣው
ድሮም ያን ጊዜ፤በኦሪት ዘመን
ክፉ ጎልያድ፤በሀይል ሲዘምን
ጉልበቱን ነስቶ፤መሬት ያኖረ
ጠጠሩ ሳይሆን፤እምነት ነበረ
በማፍቀር እምነት፤ነፍሱን አጽንቶ
ቢጠብቃትም ከተማ ገብቶ
ወንጌሉን አጣት፤ከባዕድ ሀገር
የህመም ጥልቁን፤ለማን ይናገር
ህልሙን አለሙን፤ሁሉንም ትቶ
አቅሉን እስኪስት፤ወንበዴ እጅ ገብቶ
በፍቅር መስቀለ የተሰቀለ
ኤሎሄ አይደለም፤ሰብለ ነው ያለ
የእግዜር ማቅ ለባሽ፤አንቺ መነኩሴ ሴት
እረፍትን ፍለጋ፤ከገባሽበት ቤት
ካልጋ ያገኘሽው፤እሱ ነው ወንጌልሽ
ጣር ባሰረው ድምጸት
ሰ...ሰ..ሰብለ ብሎ የሚልሽ
እንዲ ነው ፍቅር፤እንዲ ነው ስቅለት
እንዲ ነው መሞት፤እንዲህ ነው ድህነት
ፍቅር ቢበድል፤የእውነት ልኩ
ወንጌል ያጣ ሰው፤ወንጌል ነው መልኩ
Based on ፍቅር እስከ መቃብር
by @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
ትብታብ አይደለም ድግምት
ደብተራ አይደለም አስማት
ንጹሕ ፍቅር ነው ምናኔ
ለሚወዱት የመሞት ጭካኔ
እንኳን አሁን፤ከገላዬም ደም ቢነጥፍ
ደምስሬም ጅማቴም
ስምክን ነው የሚጥፍ
ዘረ ደሀ አፈቀርሽ
ዘራችንን አረከሽ
ብለው ቢያጠምቁኝም
ለፍቅርህ ስለሆን
የክፉዋች ጸበል፤መድን አይሆነኝም
ይልቅ በዛብህ፤አንጀትክን ሰብስብ
ከዛሬ ይልቅ፤ነገህን አስብ
አይዞህ በዛብህ፤ይህን ቀን ቻለው
ሰብለ ወንጌልህ
ከአትሮንስ ወርጄ ተጠፍሬያለው
ግን አትሳቀቅ፤ይህም ቀን ያልፈል
የክፉ ጅራፍ፤ጽናት ይጽፉል
የሚለው ቃሏን፤ከፍቅሩ ሰምቶ
በተስፋ አባብሎ፤ልቡን አጽናንቶ
ከተማ ገብቶ ቢጠብቃትም
ወንጌሉን ካሻው አላገኛትም
የእግዜር ኑዛዜ፤የእውነት ቃሉ
የአዳም ጥፋት፤የአምላክ አምሳሉ
የሄዌን ስህተት፤ክፉይ አካሉ
አትብላ ካለው፤ከፍሬው በልቶ
ፍቅርን በደለው፤የሞት ሞት ሞቶ
ግን በበዛብህ፤ቃሉ ልዩ ነው
ከህይወት መስቀል፤አዳኙ ማነው
አዳም ከበላው፤በለስ ሲያላምጥ
ከወንጌል ይልቅ፤ልቡን ሲያስበልጥ
ፍቅርን በደለው፤የኑሮ ጣጣው
በቃሉ አኑሮ በእውነቱ ቀጣው
ድሮም ያን ጊዜ፤በኦሪት ዘመን
ክፉ ጎልያድ፤በሀይል ሲዘምን
ጉልበቱን ነስቶ፤መሬት ያኖረ
ጠጠሩ ሳይሆን፤እምነት ነበረ
በማፍቀር እምነት፤ነፍሱን አጽንቶ
ቢጠብቃትም ከተማ ገብቶ
ወንጌሉን አጣት፤ከባዕድ ሀገር
የህመም ጥልቁን፤ለማን ይናገር
ህልሙን አለሙን፤ሁሉንም ትቶ
አቅሉን እስኪስት፤ወንበዴ እጅ ገብቶ
በፍቅር መስቀለ የተሰቀለ
ኤሎሄ አይደለም፤ሰብለ ነው ያለ
የእግዜር ማቅ ለባሽ፤አንቺ መነኩሴ ሴት
እረፍትን ፍለጋ፤ከገባሽበት ቤት
ካልጋ ያገኘሽው፤እሱ ነው ወንጌልሽ
ጣር ባሰረው ድምጸት
ሰ...ሰ..ሰብለ ብሎ የሚልሽ
እንዲ ነው ፍቅር፤እንዲ ነው ስቅለት
እንዲ ነው መሞት፤እንዲህ ነው ድህነት
ፍቅር ቢበድል፤የእውነት ልኩ
ወንጌል ያጣ ሰው፤ወንጌል ነው መልኩ
Based on ፍቅር እስከ መቃብር
by @Mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍35❤31😁1
የነገዬ ምርኩዝ የትናንት መፅናኛ
የህይወቴ ትርጉም የጊዜ መዳኛ
መራመጃ መንገድ ህመምን አስረሽ
የፅልመቴ መብራት እኔን አስታዋሽ
ጣዕም ሰጭ ስኳር ህይወት ማጣፈጫ
የዛሬን ትካዜ
የዛሬን ፍዛዜ
በያልፋል ደስታ ስሜት መቀየጫ
የዋሻ ውስጥ ጮራ ፍንጣቂ ብርሀን
የህይወቴ ካርታ የመርከቤ ካፕቴን
ትርጉም አልባን እኔን ሀዘን የወረረኝ
ከጥልቅ ትካዜ ውስጥ ወዝውዞ ያነቃኝ
ተስፋ ነው ሻማዬ...
ተስፋ ነው ሻማዬ
የትናንትን ፅልመት ዛሬን ያበራልኝ
By ዘይድ ሁሴን
ታህሳስ -27 -2017
@getem
@getem
@getem
የህይወቴ ትርጉም የጊዜ መዳኛ
መራመጃ መንገድ ህመምን አስረሽ
የፅልመቴ መብራት እኔን አስታዋሽ
ጣዕም ሰጭ ስኳር ህይወት ማጣፈጫ
የዛሬን ትካዜ
የዛሬን ፍዛዜ
በያልፋል ደስታ ስሜት መቀየጫ
የዋሻ ውስጥ ጮራ ፍንጣቂ ብርሀን
የህይወቴ ካርታ የመርከቤ ካፕቴን
ትርጉም አልባን እኔን ሀዘን የወረረኝ
ከጥልቅ ትካዜ ውስጥ ወዝውዞ ያነቃኝ
ተስፋ ነው ሻማዬ...
ተስፋ ነው ሻማዬ
የትናንትን ፅልመት ዛሬን ያበራልኝ
By ዘይድ ሁሴን
ታህሳስ -27 -2017
@getem
@getem
@getem
❤33👍30😢4🔥1
ቢሆንም
ፍቅር ይሉት ጣጣ ሲፀነስ
ሰው ከሰውነቱ ላይ ሲቀነስ
አይተናል
አይተናል የነበር ፍቅር ሲለፈፍ
በከሸፈ ፍቅር ጤንነት ሲቀሰፍ
አይተናል
ፍቅር የመርገምት ቃል እስኪመስለን
ከእጦት በላይ ንቀታቸው ያቆሰለን
አይተናል
በጫማቸው በረገጡን
ከትቢያ ላይ ባስቀመጡን
ላቀመሱን የፍቅርን ፅዋ መራር ጣዕም
ልክፍት ነውና
ይሄው እስከዛሬ እንፅፋለን ግጥም
ቢሆንም
በዬ ዘፈኑ ሆድ የባሰን
የናፍቆት ህመም የዳበሰን
አንድ ሰው ለመውደድ ዘመናት ያነሰን
ስንት አፍቃሪ አለን
የትዝታ ፈረስ ወስዶ ሚመልሰን
የማይመጣ እንደሚጠብቁ ቢታወቅም ቅሉ
በአልኮል በሲጋራ በጫትም ገረባ የተጠለሉ
ከእልፍ አእላፍ የበዙ ስንት ልቦች አሉ ?
By kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
ፍቅር ይሉት ጣጣ ሲፀነስ
ሰው ከሰውነቱ ላይ ሲቀነስ
አይተናል
አይተናል የነበር ፍቅር ሲለፈፍ
በከሸፈ ፍቅር ጤንነት ሲቀሰፍ
አይተናል
ፍቅር የመርገምት ቃል እስኪመስለን
ከእጦት በላይ ንቀታቸው ያቆሰለን
አይተናል
በጫማቸው በረገጡን
ከትቢያ ላይ ባስቀመጡን
ላቀመሱን የፍቅርን ፅዋ መራር ጣዕም
ልክፍት ነውና
ይሄው እስከዛሬ እንፅፋለን ግጥም
ቢሆንም
በዬ ዘፈኑ ሆድ የባሰን
የናፍቆት ህመም የዳበሰን
አንድ ሰው ለመውደድ ዘመናት ያነሰን
ስንት አፍቃሪ አለን
የትዝታ ፈረስ ወስዶ ሚመልሰን
የማይመጣ እንደሚጠብቁ ቢታወቅም ቅሉ
በአልኮል በሲጋራ በጫትም ገረባ የተጠለሉ
ከእልፍ አእላፍ የበዙ ስንት ልቦች አሉ ?
By kerim
@poem2513
@getem
@getem
@getem
👍62❤23
ባያቸውስ ኖሮ ?
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እርግት ያለች ወተት
ስክን ያለች ቡና …
ይሄን ችኩል ዘመን
አልዋጀችምና …
ተንገበገብኩላት
ተሳተብኝ አቅሌ
ሆንኩላት ባተሌ ።
ጥልል እንደ ጠላ
ኩልል እንደ ጠበል
ከአንገቷ ስር ገነት
ገድ ጥሎኝ ብጠለል
አ..ን..ሰ…ፈ…ሰ…ፈ…ች….ኝ
አ…ር..ገ…ፈ...ገ…ፈ…ች…ኝ
ቃላት ሳ’ተነፍስ
ጥርሶቿን ሳትገልጥ
ቅቤ ሆነ ልቤ..
ገጽዋ ላይ ሲቀልጥ ፤
ያን ጊዜ ተቃናች !
ብታጣብኝ ኩራት
ስስ ጎኔ ቢገርማት
(ዓይኖቿ ፍም እሳት)
አንገቴን ሰበርኩኝ
ፈርቼው ይሄን ፍም
ቢሆንም …
ቢሆንም …
ለዓይኖቿ አፀፋ
መስጠት ሳልፈልግም
ለንቋሳው
……………………….. ተንጋለልሁ
ለዚ’ች ሞቃት ግርግም
:
ደረቷ ላይ ፍግም !
@getem
@getem
@paappii
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እርግት ያለች ወተት
ስክን ያለች ቡና …
ይሄን ችኩል ዘመን
አልዋጀችምና …
ተንገበገብኩላት
ተሳተብኝ አቅሌ
ሆንኩላት ባተሌ ።
ጥልል እንደ ጠላ
ኩልል እንደ ጠበል
ከአንገቷ ስር ገነት
ገድ ጥሎኝ ብጠለል
አ..ን..ሰ…ፈ…ሰ…ፈ…ች….ኝ
አ…ር..ገ…ፈ...ገ…ፈ…ች…ኝ
ቃላት ሳ’ተነፍስ
ጥርሶቿን ሳትገልጥ
ቅቤ ሆነ ልቤ..
ገጽዋ ላይ ሲቀልጥ ፤
ያን ጊዜ ተቃናች !
ብታጣብኝ ኩራት
ስስ ጎኔ ቢገርማት
(ዓይኖቿ ፍም እሳት)
አንገቴን ሰበርኩኝ
ፈርቼው ይሄን ፍም
ቢሆንም …
ቢሆንም …
ለዓይኖቿ አፀፋ
መስጠት ሳልፈልግም
ለንቋሳው
……………………….. ተንጋለልሁ
ለዚ’ች ሞቃት ግርግም
:
ደረቷ ላይ ፍግም !
@getem
@getem
@paappii
👍46❤8🤩2
መኖር መኖር መኖር!
(በእውቀቱ ስዩም)
በማይ በምሰማው
አንዳንዴ ስገረም
ህይወት ከናላማው
ስህተት ይሆን እንዴ፤ በሞት የሚታረም?
ማለት ይቃጣኛል
የዚህ ዓለም ኑሮ
ጥያቄ ወርውሮ
ምላሽ ያሳጣኛል፡፡
ደሞ አንዳንዴ ሳስብ
ስለሰው ልጅ ስራ
የሰናፍጭ ቅንጣት በምታክል ጥበብ
የሚንድ ተራራ
በጨለመ ምድር፤ ብርሃን እሚዘራ
በሰማይ ጎዳና፤ ወፍ የሚያሰማራ
ባህርን የሚያጠምድ ፤መብረቅ የሚገራ፤
ከቀለሞች መሀል ፤ ምስል የሚያነቃ
ከዝምታ መሀል፤ የሚያፈልቅ ሙዚቃ
በቃሉ በጣቱ
በቅመም ቅንጣቱ
ዘልቆ የሚያክመኝ
እንደ ሳንዱቅ ከፍቶ፤ መልሶ እሚገጥመኝ
ይህንን ሁሉ ሳይ፤ ህይወት እየጣመኝ
መኖር መኖር መኖር፤ መኖር ነው የምመኝ ፤
@getem
@getem
(በእውቀቱ ስዩም)
በማይ በምሰማው
አንዳንዴ ስገረም
ህይወት ከናላማው
ስህተት ይሆን እንዴ፤ በሞት የሚታረም?
ማለት ይቃጣኛል
የዚህ ዓለም ኑሮ
ጥያቄ ወርውሮ
ምላሽ ያሳጣኛል፡፡
ደሞ አንዳንዴ ሳስብ
ስለሰው ልጅ ስራ
የሰናፍጭ ቅንጣት በምታክል ጥበብ
የሚንድ ተራራ
በጨለመ ምድር፤ ብርሃን እሚዘራ
በሰማይ ጎዳና፤ ወፍ የሚያሰማራ
ባህርን የሚያጠምድ ፤መብረቅ የሚገራ፤
ከቀለሞች መሀል ፤ ምስል የሚያነቃ
ከዝምታ መሀል፤ የሚያፈልቅ ሙዚቃ
በቃሉ በጣቱ
በቅመም ቅንጣቱ
ዘልቆ የሚያክመኝ
እንደ ሳንዱቅ ከፍቶ፤ መልሶ እሚገጥመኝ
ይህንን ሁሉ ሳይ፤ ህይወት እየጣመኝ
መኖር መኖር መኖር፤ መኖር ነው የምመኝ ፤
@getem
@getem
❤44👍28🔥10😱2
አንተ እንባዬ ምረጥ
ልግለጥህ?
ልዋጥህ?
ላፍንህ?
ልልቀቅህ?
ላፍስስህ
ላምቅህ?
ምን ላርግህ? ምከረኝ
ምንድነህ? ንገረኝ
እህል ትሆን ጠፊ?
ወይስ ሽል ነህ ገፊ?
በጊዜ ልወቅህ...
ላቅርብ ወይ ላርቅህ...
አጫጅ ነህ አራሚ?
ተጓዥ ነህ ከራሚ?
አላፊ ነህ ቋሚ?
ምንድነህ?
ምን ላርግህ?
ላግድህ?
ላውርድህ?
ጋርጄ ልካድምህ?
አውርጄ ልካድህ?
ቢያፍኑህ ቀሪ ነህ?
ቢለቁህ ኗሪ ነህ?
እንባዬ ምን ላድርግህ?
ላስርግህ?
ልጥረግህ?
እንዳ'ይን እንዳ'ፍንጫ
ቋሚ መገለጫ
መታወቂያ መልኬ ፡ ሆነህ ትኖራለህ?
ወይስ ላ'ንዴ ወርደህ፡ በዚያው ትቀራለህ?
አንተ እንባዬ ምረጥ
ላብስህ?
ላልብስህ?
ወይስ እንዳላየ፡
ከኔ የወጣ ሁሉ፡
የኔ አይደለም ብዬ
ልተውህ እንባዬ?
ወይስ ልገላገል?
እውነቱን ልናገር?
እንዲህ ነህ እንዲያ ነህ
እያልኩኝ ከማበል
አላውቅህም ልበል?
By #red-8
@getem
@getem
@paappii
ልግለጥህ?
ልዋጥህ?
ላፍንህ?
ልልቀቅህ?
ላፍስስህ
ላምቅህ?
ምን ላርግህ? ምከረኝ
ምንድነህ? ንገረኝ
እህል ትሆን ጠፊ?
ወይስ ሽል ነህ ገፊ?
በጊዜ ልወቅህ...
ላቅርብ ወይ ላርቅህ...
አጫጅ ነህ አራሚ?
ተጓዥ ነህ ከራሚ?
አላፊ ነህ ቋሚ?
ምንድነህ?
ምን ላርግህ?
ላግድህ?
ላውርድህ?
ጋርጄ ልካድምህ?
አውርጄ ልካድህ?
ቢያፍኑህ ቀሪ ነህ?
ቢለቁህ ኗሪ ነህ?
እንባዬ ምን ላድርግህ?
ላስርግህ?
ልጥረግህ?
እንዳ'ይን እንዳ'ፍንጫ
ቋሚ መገለጫ
መታወቂያ መልኬ ፡ ሆነህ ትኖራለህ?
ወይስ ላ'ንዴ ወርደህ፡ በዚያው ትቀራለህ?
አንተ እንባዬ ምረጥ
ላብስህ?
ላልብስህ?
ወይስ እንዳላየ፡
ከኔ የወጣ ሁሉ፡
የኔ አይደለም ብዬ
ልተውህ እንባዬ?
ወይስ ልገላገል?
እውነቱን ልናገር?
እንዲህ ነህ እንዲያ ነህ
እያልኩኝ ከማበል
አላውቅህም ልበል?
By #red-8
@getem
@getem
@paappii
❤47👍38🔥8
አንቺን ያየ ምድር አንቺን ያየ ሰማይ
ስንት ዐመት ቀጠለ በስፍር ዕድሜው ላይ?
።።።።።።።።
በጠለቅሽበት ጥግ
መውጣት ስላቅ ሆነ ፀሐይ ቀረች አፍራ
እኔም ደስታ እንዳለው
ማልቀስ ይከብደኛል በሳቅሽበት ስፍራ።
የት ቆሜ እንባ ላፍስስ የት ልበል እዬዬ
በሳቅሽ የፈካ
አይታዘበኝም ዛፍ ቅጠሉ እያዬ?
ምድር እንዳይንቀኝ
በወንዙ በሀይቁ ቀልዬ እንዳልገኝ
በነፋሱ ትዝብት እንዳላንስ ወድቄ
ለፍጥረት እይታ በሳቅ አሸብርቄ
እስቃለሁ ለጉድ እንከተከታለሁ
እንጂማ
ሳቅሽ ዳር ብፈለግ የእውነት የታለሁ?
እና የኔ ኪዳን
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
እንዳያፍር ምድር እንዳያፍር ሰማይ
እግዜሩም አልሠራም ጠልቆ ሚቀር ፀሐይ!
አባባይ ሆንኩልሽ የእሹሩሩ ካድሬ
ጨለማውን በሳቅ ሳባብል አድሬ
እንቅልፍ ቢወስደው ከዛለ መዳፌ
እንባ እየናፈቁ መሳቅ ሆነ ትርፌ።
እንደሰው ሲደክመው ሌቱ ሲያንቀላፋ
አማጥኩኝ ለለቅሶ እህህህ አልኩኝ ለሳጌ
ሁሌ ምገኘው ግን ከፈገግታሽ ግርጌ።
የሳቅሽን ዘቢብ
ምን መልአክ ቀመሰው ምን አማልክት አየው
የፈገግታ ጭረት ፊቴ ማይለየው?
አንቺ…
ሕይወት ክንብል አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠ
By yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
ስንት ዐመት ቀጠለ በስፍር ዕድሜው ላይ?
።።።።።።።።
በጠለቅሽበት ጥግ
መውጣት ስላቅ ሆነ ፀሐይ ቀረች አፍራ
እኔም ደስታ እንዳለው
ማልቀስ ይከብደኛል በሳቅሽበት ስፍራ።
የት ቆሜ እንባ ላፍስስ የት ልበል እዬዬ
በሳቅሽ የፈካ
አይታዘበኝም ዛፍ ቅጠሉ እያዬ?
ምድር እንዳይንቀኝ
በወንዙ በሀይቁ ቀልዬ እንዳልገኝ
በነፋሱ ትዝብት እንዳላንስ ወድቄ
ለፍጥረት እይታ በሳቅ አሸብርቄ
እስቃለሁ ለጉድ እንከተከታለሁ
እንጂማ
ሳቅሽ ዳር ብፈለግ የእውነት የታለሁ?
እና የኔ ኪዳን
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
እንዳያፍር ምድር እንዳያፍር ሰማይ
እግዜሩም አልሠራም ጠልቆ ሚቀር ፀሐይ!
አባባይ ሆንኩልሽ የእሹሩሩ ካድሬ
ጨለማውን በሳቅ ሳባብል አድሬ
እንቅልፍ ቢወስደው ከዛለ መዳፌ
እንባ እየናፈቁ መሳቅ ሆነ ትርፌ።
እንደሰው ሲደክመው ሌቱ ሲያንቀላፋ
አማጥኩኝ ለለቅሶ እህህህ አልኩኝ ለሳጌ
ሁሌ ምገኘው ግን ከፈገግታሽ ግርጌ።
የሳቅሽን ዘቢብ
ምን መልአክ ቀመሰው ምን አማልክት አየው
የፈገግታ ጭረት ፊቴ ማይለየው?
አንቺ…
ሕይወት ክንብል አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠ
ራል አንድ ቀን ተስቆ?
ዙሪያዬን ሳቅ ከቦኝ እምን ላይ ልደገፍ
እንባዬ ያምረዋል እዚም እዛም መርገፍ።
ያሰኘኛል ዋይታ
ዕድሜዬን ማዋዛት በሀዘን ማለዘብ
ግን ትልቅ ሀጢአት ነው
ከቁርባን ፊት ቀርቦ ቁርባኑን መታዘብ።
ሜሮን ነበር ሳቅሽ ሀዳስ የሳቅ ጠበል
ፅድቅ ነበር ለሰው
ያንድ ቀን ደስታሽ ስር ዳስ ሠርቶ መጠለል።
መቼ ልትወጪ አሰብሽ?
መቼ ልትመጪ አሰብሽ?
በፍጥረት ልብ ላይ ጎጆውን ቀልሶ
ሳቅሽ አንጀት በላ እንዳራራይ ለቅሶ።
አበባው ይስቃል
ቅጠሉ ይስቃል
እሾሁ ይስቃል ድንጋዩ ይስቃል
አፈሩ፣ እሳቱ ነፋሱ ይስቃል
አንዴም ሳያነባ ሰው እንዴት ይፀድቃል?
ሳቅሽ ወንጌል ሆነ ምጻት መፋረጃ
ውስጤ እንባ ደርድሬ
ለብይን ብጠራ አቋቋሜን እንጃ!
አቤት አቤት አቤት
ከአምላክ ከፍጡር ከማነው ወገኑ
ሺህ ኩነኔ መሃል ሳቅሽ መጀገኑ!
አንቺ የሳቅ ኪዳን
ሩቅ ነሽ ለህመም ቅርብ ነሽ ለመዳን
እኔ ግን ተመኘሁ
በፈገግታሽ በኩል እንባዬን ልነካ
አንቺ…
ማልቀስ በመፈለግ ሳቅ ይረክሳል ለካ።
አንድ ቀን ስቃልኝ
ስፍር ዕድሜዬ ላይ ዕድሜ መርቃልኝ
የሰማይ የምድሩን መሳቅ አስለምዳው
ልክ እንዳመጣጧ ብትጠልቅ ወዲያው
ሕይወት ድፍት አለ ቆመ ተዘቅዝቆ
ዘላለም ይሠ
ራል አንድ ቀን ተስቆ?By yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
👍42❤29🤩4🔥2
ድንኳን አይጥሉለት፣
ጥየቃ አያውቀው፣
ሰአቱን መጠበቅ ቀን ማወቅ አይለቀው፤
ሁሌ አብሮ አይኖር፣
ሁሌ መጪ እንግዳ፣
ሁሌ ምቾት ነሺ የሰባት ቀን እዳ፤
ሁሌ ተባበይ ባይ፣
በመጣ በታየ፣
ሁሌ የመድሎ ልጅ በጾታ የለየ፤
ሁሌ ፊት አደብዛዥ፣
የዙር አመል ከላሽ፣
ሁሌ ተጠባቂ ሁሌ መቶ ረባሽ፤
የልምላሜ መልክ፣
ከመባረክ ጓዳ፣
የሔዋን እጣ ነው ክቡር የሤት እዳ።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
ጥየቃ አያውቀው፣
ሰአቱን መጠበቅ ቀን ማወቅ አይለቀው፤
ሁሌ አብሮ አይኖር፣
ሁሌ መጪ እንግዳ፣
ሁሌ ምቾት ነሺ የሰባት ቀን እዳ፤
ሁሌ ተባበይ ባይ፣
በመጣ በታየ፣
ሁሌ የመድሎ ልጅ በጾታ የለየ፤
ሁሌ ፊት አደብዛዥ፣
የዙር አመል ከላሽ፣
ሁሌ ተጠባቂ ሁሌ መቶ ረባሽ፤
የልምላሜ መልክ፣
ከመባረክ ጓዳ፣
የሔዋን እጣ ነው ክቡር የሤት እዳ።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
❤32👍16🤩5🔥3
ባዶ እኮ ነች።
(የሞገሤ ልጅ)
መጀመርያ፣
ኑ እንፍጠር በመባባል አምላክ ራሱን ሳያማክር፣
ዘረጋግቶ፣
እውን ሆነው እስኪታዩ እስኪኖሩ ምድር ጠፈር፤
ለባዶነት፣
ያጨው ነገር ለመኖሩ ስለማናውቅ ምንም ባንል፣
ምድራችን ግን፣
ከአካሏ ተቀናንሰው ሳር ቅጠሉን እስክታበቅል፤
አሁን ጠባ፣
በቤት ላይ ቤት እንዲሰራ ሠው ወገኗን ያስገደደች፣
ዛሬ ሳንደርስ፣
ጅማሮዋን ብቸኝነት ያካረማት ባዶ እኮ ነች።
ልክ እንደሷ፣
ሃ ማለቴን አፍ ሳይሆነው ጅማሮዬን አብሮት ሳይቆም፣
አሁን መቶ፣
ሄደሽ መቶ ባዶነቴ መከበቤ ቢደመደም፤
ባዶነቴ፣
አዲሥ ሕይወት አዲሥ መንገድ እንዲያመጣ ምድር ሆኜለት፣
መከፋቴን፣
መቀየሩ ስለማይቀር ባዶነቴን ገጠምኩበት።
ገጠምኩበት..
አልወደኩም፣
ሆኖ ሲታይ ባልጣለው ፊት ላልወደቁት ሲመሰክር፣
ያሳምናል፣
የአይን አዋጅ ለሆነበት ዝናን ማድመቅ ቀሪን መቅበር።
አንድ አንዴ ግን፣
ግዳጅ ጥሎ ፎካሪ ላይ ተሽመድምዶም መዘባበት፣
ቀን ያወጣል፣
ወድያ ወዲህ ተንጎራዳጅ አምላክ ፈቅዶ ከዞረበት።
ያን እለት ግን..
ራሱን ሆኖ ከጣለው እጅ ተፍገምግሞ የተነሳ፣
ባዶነቱን፣
ምርኩዝ ስጡኝ ባላለ አፍ መተኛቱን እስኪረሳ፤
ተመርኩዞ፣
ሲደጋግፍ ቆሞ ሊታይ የራሱ ቀኝ ራሱ ሆኖ፣
ባዶነቱ፣
ኃይል ይወልዳል ብርቱ ጉልበት ከድካሙ ተሰናስኖ።
ባዶ አረግሺኝ?
እንኳንም ሆንኩ!
አንቺን ይድላሽ፣
ግን ጨርሰሽ አትራቂው ብቸኝነት ከሚጠላሽ!
ለምን አልሺኝ?
ካልሺኝ እማ..
ምንም መሆን ምንም ነው፣
ለባዶነት ልኩ ያንሳል፣
አለመኖር ካጣ ፍጥረት ጉድለት ሞልቶት በዝቅታው ሺ ይብሳል።
ባዶነት ግን..
እርቃን መሆን ሸክሙ ከብዶ፣
ቋጠሮውን ለማላላት፣
አዲስ መንገድ ይፈልጋል፣
አዲሥ ነገር ለማሳየት።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
(የሞገሤ ልጅ)
መጀመርያ፣
ኑ እንፍጠር በመባባል አምላክ ራሱን ሳያማክር፣
ዘረጋግቶ፣
እውን ሆነው እስኪታዩ እስኪኖሩ ምድር ጠፈር፤
ለባዶነት፣
ያጨው ነገር ለመኖሩ ስለማናውቅ ምንም ባንል፣
ምድራችን ግን፣
ከአካሏ ተቀናንሰው ሳር ቅጠሉን እስክታበቅል፤
አሁን ጠባ፣
በቤት ላይ ቤት እንዲሰራ ሠው ወገኗን ያስገደደች፣
ዛሬ ሳንደርስ፣
ጅማሮዋን ብቸኝነት ያካረማት ባዶ እኮ ነች።
ልክ እንደሷ፣
ሃ ማለቴን አፍ ሳይሆነው ጅማሮዬን አብሮት ሳይቆም፣
አሁን መቶ፣
ሄደሽ መቶ ባዶነቴ መከበቤ ቢደመደም፤
ባዶነቴ፣
አዲሥ ሕይወት አዲሥ መንገድ እንዲያመጣ ምድር ሆኜለት፣
መከፋቴን፣
መቀየሩ ስለማይቀር ባዶነቴን ገጠምኩበት።
ገጠምኩበት..
አልወደኩም፣
ሆኖ ሲታይ ባልጣለው ፊት ላልወደቁት ሲመሰክር፣
ያሳምናል፣
የአይን አዋጅ ለሆነበት ዝናን ማድመቅ ቀሪን መቅበር።
አንድ አንዴ ግን፣
ግዳጅ ጥሎ ፎካሪ ላይ ተሽመድምዶም መዘባበት፣
ቀን ያወጣል፣
ወድያ ወዲህ ተንጎራዳጅ አምላክ ፈቅዶ ከዞረበት።
ያን እለት ግን..
ራሱን ሆኖ ከጣለው እጅ ተፍገምግሞ የተነሳ፣
ባዶነቱን፣
ምርኩዝ ስጡኝ ባላለ አፍ መተኛቱን እስኪረሳ፤
ተመርኩዞ፣
ሲደጋግፍ ቆሞ ሊታይ የራሱ ቀኝ ራሱ ሆኖ፣
ባዶነቱ፣
ኃይል ይወልዳል ብርቱ ጉልበት ከድካሙ ተሰናስኖ።
ባዶ አረግሺኝ?
እንኳንም ሆንኩ!
አንቺን ይድላሽ፣
ግን ጨርሰሽ አትራቂው ብቸኝነት ከሚጠላሽ!
ለምን አልሺኝ?
ካልሺኝ እማ..
ምንም መሆን ምንም ነው፣
ለባዶነት ልኩ ያንሳል፣
አለመኖር ካጣ ፍጥረት ጉድለት ሞልቶት በዝቅታው ሺ ይብሳል።
ባዶነት ግን..
እርቃን መሆን ሸክሙ ከብዶ፣
ቋጠሮውን ለማላላት፣
አዲስ መንገድ ይፈልጋል፣
አዲሥ ነገር ለማሳየት።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
👍32❤15😱3🤩2😢1
ፍቅርን ፈራን
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነት ለመድን
“ፈራን”
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
“ናቅን”
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
“ናቅን”
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
“ጠላን”
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
“ራቅን”
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
@getem
@getem
@paappii
(ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን)
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነት ለመድን
“ፈራን”
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
“ናቅን”
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
“ናቅን”
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
“ጠላን”
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
“ራቅን”
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
@getem
@getem
@paappii
❤63👍34🔥3😱3
ብቻህን
(የሞገሤ ልጅ)
ያለማንም ፍቃድ ባገኘሃት ሃገር፣
ያሰኘህን ስራ፣
ያሻህን ተናገር!
እሪ በል!
ኡኡ በል!
እሪ እሚያስብል ካለ፣
ድምጽህ ከታፈነ፣
ክብርህ ከጎደለ።
በራስህ አካሄድ፣
በሃቅህ ጎዳና፣
ሰሚ የታባቱ፣
ምን ይጠቅምህ እና!
ብቻህን ተናገር፣
ብቻህን ዝም በል,
ብቻህን አግዘህ፣
ብቻህን ተገልገል!
ስላለችህ እውነት፣
ብቻህን ተሰለፍ,
ከጓዳህ አቅራቢያ፣
ከኩሽናህ ደጅ_አፍ።
ታዲያ ሞኚ እንዳትሆን!
ጥፋት እንደሚቆም፣
ፍርድ እንደሚቀየር,
በደል እንደሚያከትም፣
ጉዳት እንደማይኖር;
አስበህ ኣትጓጓ፣
የሩቁን አትጎምጅ፣
እራስህ ስለሆንክ፣
የእራስህ ወዳጅ።
ደራሽ በማሰስህ፣
ድራሽህ ሊጠፋ፣
በማጣትህ ማግጠህ፣
ጉዳትህ ሊከፋ፤
አማረህ ላታገኝ፣
ጮኸህ ልትቀማ፣
ልብህ ቢነሳሳ፣
ለሁከት ለአድማ፤
ታግለህ ላታሸንፍ፣
ጥለህ ላትሻገር፣
ኖሮ ካላገዘህ፣
ማመልከት መናገር፤
ድካምህ ቢቀንስ፣
ሠው ከምትጣራ፣
ያለአንደበትህ፣
ልብህ ለዐምላክ ያውራ!
ደግሞስ ለምን ከፋህ?
ግዜ ካልፈቀደ፣
እንዳሻህ እንድትኖር፣
እንደተባልህ መሆን፣
ማድረግ ብትቸገር፤
ፊት የነሳህ እለት፣
ፊቱን እስኪመልስ፣
መሽቶ እስኪነጋ፣
ነገን ብትታገስ፤
በላብህ ብትበላ፣
በደምህ ብትኖር፣
ለአንተ የተባለው፣
ባልቀረብህ ነበር።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@getem
(የሞገሤ ልጅ)
ያለማንም ፍቃድ ባገኘሃት ሃገር፣
ያሰኘህን ስራ፣
ያሻህን ተናገር!
እሪ በል!
ኡኡ በል!
እሪ እሚያስብል ካለ፣
ድምጽህ ከታፈነ፣
ክብርህ ከጎደለ።
በራስህ አካሄድ፣
በሃቅህ ጎዳና፣
ሰሚ የታባቱ፣
ምን ይጠቅምህ እና!
ብቻህን ተናገር፣
ብቻህን ዝም በል,
ብቻህን አግዘህ፣
ብቻህን ተገልገል!
ስላለችህ እውነት፣
ብቻህን ተሰለፍ,
ከጓዳህ አቅራቢያ፣
ከኩሽናህ ደጅ_አፍ።
ታዲያ ሞኚ እንዳትሆን!
ጥፋት እንደሚቆም፣
ፍርድ እንደሚቀየር,
በደል እንደሚያከትም፣
ጉዳት እንደማይኖር;
አስበህ ኣትጓጓ፣
የሩቁን አትጎምጅ፣
እራስህ ስለሆንክ፣
የእራስህ ወዳጅ።
ደራሽ በማሰስህ፣
ድራሽህ ሊጠፋ፣
በማጣትህ ማግጠህ፣
ጉዳትህ ሊከፋ፤
አማረህ ላታገኝ፣
ጮኸህ ልትቀማ፣
ልብህ ቢነሳሳ፣
ለሁከት ለአድማ፤
ታግለህ ላታሸንፍ፣
ጥለህ ላትሻገር፣
ኖሮ ካላገዘህ፣
ማመልከት መናገር፤
ድካምህ ቢቀንስ፣
ሠው ከምትጣራ፣
ያለአንደበትህ፣
ልብህ ለዐምላክ ያውራ!
ደግሞስ ለምን ከፋህ?
ግዜ ካልፈቀደ፣
እንዳሻህ እንድትኖር፣
እንደተባልህ መሆን፣
ማድረግ ብትቸገር፤
ፊት የነሳህ እለት፣
ፊቱን እስኪመልስ፣
መሽቶ እስኪነጋ፣
ነገን ብትታገስ፤
በላብህ ብትበላ፣
በደምህ ብትኖር፣
ለአንተ የተባለው፣
ባልቀረብህ ነበር።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@getem
👍30❤16🔥2
እንዲገባሽ!
(የሞገሤ ልጅ)
ከመከፋት ያልፋል፣
ሃዘኔ ሃዘን ነው ይከምራል አጭዶ፣
ላላልቅ ያነደኛል፣
ከሃሳብ ወላፈን ናፍቆት እሳት ማግዶ።
ባታውቂ ነው እንጂ..
አልመጣም ማለትሽ በናፍቆት ያስምጣል፣
ከሰመመን ዘፍቆ ከቅዠት ያሰምጣል፣
ከራስ ስጋ አጣልቶ ከመንፈሥ ያርቃል፣
ሠው ማጣትም ከብዶ ሠው ማግኘት ይጨንቃል፣
ስሜት እንደ ጥይት ድንገት ይባርቃል፣
ያልበላን ሠውነት ረሃብ ያጠረቃል፣
የእስከአሁኑ እንዲህ ነው ነገንስ ማን ያውቃል?
ህ!
ህ!
እህህ!
ደሞ ያልነገርኩሽ..
ክርሥቶሥ የኛ ሺ ለሱ አንድ እለት፣
ለኔ ስትቀሪ..
አልመጣም ማለትሽ ቀኔን አርጎት ሳምንት፣
ባልነግርሽ ነው እንጂ..
ስላላወቅሽልኝ መምጣት የምትረሺው፣
ብነግርሽ ኖሮ እማ..
ባትመጪም እንኳን ከመቅረትሽ ጀርባ ጉዳቴን ባየሺው።
ደሞ የረሳሁት..
በአንድ የቀን ጉዱ አንቺነትሽ ወርሶኝ፣
እኩል እኔን ላንቺ ለማካፈል ቆርሶኝ፤
ድሮም አንድ አጥንቴ አንቺ ዘንድ ቀርቶ፣
እሱን እንደማግኘት መከፈሌ በዝቶ፤
ወይ ይዘሽ አልያዝሽው ደጅ ጥናት ጎዳው፣
ወይ ለኔ አልሆነ ራሴን ራሴ ከዳው፤
አንቺም ለመምጣትሽ አጠረኝ ማስረጃ፣
ሁለት አድርገሽኝ ሠው መሆኔን እንጃ።
እባክሽ መውደዴን ችለሽ አታኩርፊው፣
ልቤ ቆሞ ደክሟል ራርተሽ አሳርፊው፤
የኔ ብቻ ሁኚ የኔ ብቻ አለም፣
መድከሜ ላይቋጭ ላያልቅ አይርዘም፤
የኔ ብቻ ሁኚ ካምላክሽ ቀጥሎ፣
ላንቺም ግፍ ነው ማለፍ ታማሚሽን ጥሎ፤
ስለዕመቤቴ እሩሩዋ እናት፣
ቢጤሽን መጽውቺኝ ልብሽን ልመጽወት።
ያኔ እድናለሁ፣
እጠነክራለሁ አላለቃቅስም፣
አሁን ላይ ግን ከኔ፣
ማጥፋቴ ስም ሊያሰጥ አይነቃቀስም።
ተረዳሽኝ አይደል?
አዎ ተረድተሻል።
እንጂ እማ ወዳጁን፣
ካልታመመ በቀር ማስከፋት ማን ይሻል?
አዎ ተረድተሻል!
ይበልጥ እንዲገባሽ..
ምን ከቤት ቢገፋ፣
ባልለመደው ንፋስ ሊገረፍ ቢሰጥም፣
ያበደ ውሻ እንጂ፣
ያልታመመ ውሻ የጌታውን እግር ሊጎዳ አይነክስም።
አሁን ዘልቆ ገባሽ?
አዎ ተረድተሻል!
ስለዚህ እብድ ውሻሽ ለነከሰሽ ሊክስ ጤነኛ እንዲሆን ይቅርታሽን ይሻል።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
(የሞገሤ ልጅ)
ከመከፋት ያልፋል፣
ሃዘኔ ሃዘን ነው ይከምራል አጭዶ፣
ላላልቅ ያነደኛል፣
ከሃሳብ ወላፈን ናፍቆት እሳት ማግዶ።
ባታውቂ ነው እንጂ..
አልመጣም ማለትሽ በናፍቆት ያስምጣል፣
ከሰመመን ዘፍቆ ከቅዠት ያሰምጣል፣
ከራስ ስጋ አጣልቶ ከመንፈሥ ያርቃል፣
ሠው ማጣትም ከብዶ ሠው ማግኘት ይጨንቃል፣
ስሜት እንደ ጥይት ድንገት ይባርቃል፣
ያልበላን ሠውነት ረሃብ ያጠረቃል፣
የእስከአሁኑ እንዲህ ነው ነገንስ ማን ያውቃል?
ህ!
ህ!
እህህ!
ደሞ ያልነገርኩሽ..
ክርሥቶሥ የኛ ሺ ለሱ አንድ እለት፣
ለኔ ስትቀሪ..
አልመጣም ማለትሽ ቀኔን አርጎት ሳምንት፣
ባልነግርሽ ነው እንጂ..
ስላላወቅሽልኝ መምጣት የምትረሺው፣
ብነግርሽ ኖሮ እማ..
ባትመጪም እንኳን ከመቅረትሽ ጀርባ ጉዳቴን ባየሺው።
ደሞ የረሳሁት..
በአንድ የቀን ጉዱ አንቺነትሽ ወርሶኝ፣
እኩል እኔን ላንቺ ለማካፈል ቆርሶኝ፤
ድሮም አንድ አጥንቴ አንቺ ዘንድ ቀርቶ፣
እሱን እንደማግኘት መከፈሌ በዝቶ፤
ወይ ይዘሽ አልያዝሽው ደጅ ጥናት ጎዳው፣
ወይ ለኔ አልሆነ ራሴን ራሴ ከዳው፤
አንቺም ለመምጣትሽ አጠረኝ ማስረጃ፣
ሁለት አድርገሽኝ ሠው መሆኔን እንጃ።
እባክሽ መውደዴን ችለሽ አታኩርፊው፣
ልቤ ቆሞ ደክሟል ራርተሽ አሳርፊው፤
የኔ ብቻ ሁኚ የኔ ብቻ አለም፣
መድከሜ ላይቋጭ ላያልቅ አይርዘም፤
የኔ ብቻ ሁኚ ካምላክሽ ቀጥሎ፣
ላንቺም ግፍ ነው ማለፍ ታማሚሽን ጥሎ፤
ስለዕመቤቴ እሩሩዋ እናት፣
ቢጤሽን መጽውቺኝ ልብሽን ልመጽወት።
ያኔ እድናለሁ፣
እጠነክራለሁ አላለቃቅስም፣
አሁን ላይ ግን ከኔ፣
ማጥፋቴ ስም ሊያሰጥ አይነቃቀስም።
ተረዳሽኝ አይደል?
አዎ ተረድተሻል።
እንጂ እማ ወዳጁን፣
ካልታመመ በቀር ማስከፋት ማን ይሻል?
አዎ ተረድተሻል!
ይበልጥ እንዲገባሽ..
ምን ከቤት ቢገፋ፣
ባልለመደው ንፋስ ሊገረፍ ቢሰጥም፣
ያበደ ውሻ እንጂ፣
ያልታመመ ውሻ የጌታውን እግር ሊጎዳ አይነክስም።
አሁን ዘልቆ ገባሽ?
አዎ ተረድተሻል!
ስለዚህ እብድ ውሻሽ ለነከሰሽ ሊክስ ጤነኛ እንዲሆን ይቅርታሽን ይሻል።
By @eyadermoges1
@getem
@getem
@paappii
👍49❤15😢9
ይድረሰ:- ለኩርፊያ
(ሳሙኤል አለሙ)
°
°
የሻማው ብርሃን ደብዝዞ
የንፋስ ሽውታ ጠረገው፤
አፋችኑ ቃላት አርግዞ
አምጦ መውለድ አቃተው፤
ዝም...ዝም...ዝም
ጭልም-ልም-ልም
ገዘፈ ድቅድቁ ጨለማው፤
ቃላችንን ሾተላይ ቀማው።
°
°
እንደ'ኔና እንደ እሷ
ጀምበሩ ሳይነጋ
መሰሎቻችን ጋ
አፋቸውን ሊያዘጋ
ጥድፍ-ድፍ-ድፍ...ሲል
ርብት-ብት-ብት...ሲል
ደርሶ አፋችንን ቆልፎበት።
ደጃፉ ላይ ፥ ስደርስበት።
°
°
ቀኝህን ለሚመታ
ግራውን ስጡት እንዳለው ጌታ
ሳትነፍገው የእግዜሩን ሰላምታ
እንደ ዲዳ ዝም ካለህ
ላፍታም... ላፍታም.... ሳታመንታ
ኩርፊያን <እንኳን ደስ አለህ!>
በልልኝ!
°
°
ይኸው እኔና እሷ
ሰርክ ኩርፍ ኩ-ርፍ-ርፍ
ሰርክ እቅፍ እ-ቅፍ-ቅፍ
ይኸው እኔና እሷ
እንደ ቄጤማው ፥ እንደ አውዳመቱ፤
ድንገት ካየኸው ፥ የኩርፊያን ፊቱ፤
ትላንቱ ለምልሞ ፥ ዛሬ ክስመቱ።
°
°
እንደ ጳጉሜ ሶስት ዕለቱ
ዕንባውን አዘነብነው።
የሩፋኤል ፀበል አይደል
ክፋቱን አያድነው።
ከጫጫታው አልፈን
ነጎድጓዱን አክለነው።
ጭቅጭቁን አድ'ምጦ
በዜማ አቀነቀነው።
°
°
ተወው በክረምቱ ፥ ይርገጥ ዳንኪራ
ተወው በዕንባችን ፥ ይስከር ያሽካካ
በፀደዩ ብርሃን ፥ እንደምንፈካ
ዘንግቶታናልና!
°
°
የዛሬዋን ዕድል
ከቆጠረው ከድል
ትርኢት ያዘጋጅ
እንግዳም ይጥራ ፥ ድግሱንም ይደግሰው
እንደ ንጉስ አይዙር ፥ ግማሽ ቀኑን የሚነግሰው
ተወው!
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
°
°
የሻማው ብርሃን ደብዝዞ
የንፋስ ሽውታ ጠረገው፤
አፋችኑ ቃላት አርግዞ
አምጦ መውለድ አቃተው፤
ዝም...ዝም...ዝም
ጭልም-ልም-ልም
ገዘፈ ድቅድቁ ጨለማው፤
ቃላችንን ሾተላይ ቀማው።
°
°
እንደ'ኔና እንደ እሷ
ጀምበሩ ሳይነጋ
መሰሎቻችን ጋ
አፋቸውን ሊያዘጋ
ጥድፍ-ድፍ-ድፍ...ሲል
ርብት-ብት-ብት...ሲል
ደርሶ አፋችንን ቆልፎበት።
ደጃፉ ላይ ፥ ስደርስበት።
°
°
ቀኝህን ለሚመታ
ግራውን ስጡት እንዳለው ጌታ
ሳትነፍገው የእግዜሩን ሰላምታ
እንደ ዲዳ ዝም ካለህ
ላፍታም... ላፍታም.... ሳታመንታ
ኩርፊያን <እንኳን ደስ አለህ!>
በልልኝ!
°
°
ይኸው እኔና እሷ
ሰርክ ኩርፍ ኩ-ርፍ-ርፍ
ሰርክ እቅፍ እ-ቅፍ-ቅፍ
ይኸው እኔና እሷ
እንደ ቄጤማው ፥ እንደ አውዳመቱ፤
ድንገት ካየኸው ፥ የኩርፊያን ፊቱ፤
ትላንቱ ለምልሞ ፥ ዛሬ ክስመቱ።
°
°
እንደ ጳጉሜ ሶስት ዕለቱ
ዕንባውን አዘነብነው።
የሩፋኤል ፀበል አይደል
ክፋቱን አያድነው።
ከጫጫታው አልፈን
ነጎድጓዱን አክለነው።
ጭቅጭቁን አድ'ምጦ
በዜማ አቀነቀነው።
°
°
ተወው በክረምቱ ፥ ይርገጥ ዳንኪራ
ተወው በዕንባችን ፥ ይስከር ያሽካካ
በፀደዩ ብርሃን ፥ እንደምንፈካ
ዘንግቶታናልና!
°
°
የዛሬዋን ዕድል
ከቆጠረው ከድል
ትርኢት ያዘጋጅ
እንግዳም ይጥራ ፥ ድግሱንም ይደግሰው
እንደ ንጉስ አይዙር ፥ ግማሽ ቀኑን የሚነግሰው
ተወው!
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@getem
@getem
👍30❤9🔥1