ደህና ዋልሽ አልኳትኝ
የፈካውን ፊቷን በአይኖቼ እየካደምኩ
"እግዛቤር ይመስገን"
በጥፍጥ አንደበቷ በከንፈር ተማረኩ
"አንተስ እንዴት ከረምክ....ተስማማህ አየሩ"
ግርምታ እየያዛት ብመጣ በወሩ
"..ኧኧ....ይመስገን ጀሊሉ.."
"ይመስገን ጀሊሉ"
"ምነው ጠፋህሳ ከሄድክበት ግድም
እንደው ቢቻል...ቢቻል
አይደወልም አንድም"
"አፉ በይኝ አቦ....
ባይመቻችልኝ ነው መደወል መርሳቴ"
ተጠጋሁ ከፊቷ አሳረፍኩ አንጀቴን
"ይልቁንስ አንቺው
ከዛ ከሩቅ ሀገር ያመጣሁት አለ
ከተስማማሽ ላንቺ ብትለብሺው ምናለ"
"ማርያምን..?......የታለ.."
"አለ ከሰነኩት...ከሻንጣዬ ግድም
ቢሆን ለደብርሽ ለባዕልሽ ግልድም"
"ደስ ይለኛል....ወላዲቷን"
ደስ ብሏታል የእውነቷን
"በል ና ቅመስ የቡና ቁርስ
አልወረደም ገና አቦሉ"
"የለም ልሂድ.....ሌላ ጊዜ
ሳይብስብኝ ይህ ቀትሩ"
"ማይሆነውን....
እዚህ መተህ አትመለስ
የባታ ነው ፀበል ቅመስ"
"ወላሂ..ይቅርብኝ ሩቅ ነው መንገዴ
ባየሆን ልዝገን ካለው ባዶ እንዳይሆን ሆዴ"
ዘገንኩት ከቁርሱ ካፌ ላይ ወረወርኩ
ያመጣሁላትን ለገላዋ አስረከብኩ
"ባታ ትስጥልኝ አለሜ...."
"አሜን....ሙሃመዴ"
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
የፈካውን ፊቷን በአይኖቼ እየካደምኩ
"እግዛቤር ይመስገን"
በጥፍጥ አንደበቷ በከንፈር ተማረኩ
"አንተስ እንዴት ከረምክ....ተስማማህ አየሩ"
ግርምታ እየያዛት ብመጣ በወሩ
"..ኧኧ....ይመስገን ጀሊሉ.."
"ይመስገን ጀሊሉ"
"ምነው ጠፋህሳ ከሄድክበት ግድም
እንደው ቢቻል...ቢቻል
አይደወልም አንድም"
"አፉ በይኝ አቦ....
ባይመቻችልኝ ነው መደወል መርሳቴ"
ተጠጋሁ ከፊቷ አሳረፍኩ አንጀቴን
"ይልቁንስ አንቺው
ከዛ ከሩቅ ሀገር ያመጣሁት አለ
ከተስማማሽ ላንቺ ብትለብሺው ምናለ"
"ማርያምን..?......የታለ.."
"አለ ከሰነኩት...ከሻንጣዬ ግድም
ቢሆን ለደብርሽ ለባዕልሽ ግልድም"
"ደስ ይለኛል....ወላዲቷን"
ደስ ብሏታል የእውነቷን
"በል ና ቅመስ የቡና ቁርስ
አልወረደም ገና አቦሉ"
"የለም ልሂድ.....ሌላ ጊዜ
ሳይብስብኝ ይህ ቀትሩ"
"ማይሆነውን....
እዚህ መተህ አትመለስ
የባታ ነው ፀበል ቅመስ"
"ወላሂ..ይቅርብኝ ሩቅ ነው መንገዴ
ባየሆን ልዝገን ካለው ባዶ እንዳይሆን ሆዴ"
ዘገንኩት ከቁርሱ ካፌ ላይ ወረወርኩ
ያመጣሁላትን ለገላዋ አስረከብኩ
"ባታ ትስጥልኝ አለሜ...."
"አሜን....ሙሃመዴ"
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
አልከነፍኩም ስላፈቀርኩ
ተሰባበርኩ እንጂ የትም
መልስ የለሽም ለጥያቄ
ልብሽ እኔን አያካትም
ያንቺ ፍቅር አሳነሰኝ
ደጅ አስጠናኝ በዳጃፉ
ሰው እንደሆን ወሬ አያጣም
ይለቅመኛል ሁሌ ባፉ
ህመም ብቻ ውስጤ እሳቱ
አይዳፈን እየነደድኩ
መፈቀር ግን ህያው ሞት ነው
ስቃይ ብቻ ማፍቀር ልኩ
አላመንሽም ያንደበቴን
የማፍቀሬን ስር ትርጉሙን
አይወደኝም ሰርክ መልስሽ
አላወቅሽም ጥግ ህመሙን
ተፈቃሪ ምን ግድ አለው
ምን ቢፈቅር እንደሀገሩ
አፍቃሪ ነው ነገር ሚፈጅ
የሚማገድ ለወደሩ
ትገርሚያለሽ አንቺ ብቻ
አላመንሽም የኔን ፍቅር
አትወድህም ቢለኝም ሰው
ከደጃፍሽ ዛሬም አልቀር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ተሰባበርኩ እንጂ የትም
መልስ የለሽም ለጥያቄ
ልብሽ እኔን አያካትም
ያንቺ ፍቅር አሳነሰኝ
ደጅ አስጠናኝ በዳጃፉ
ሰው እንደሆን ወሬ አያጣም
ይለቅመኛል ሁሌ ባፉ
ህመም ብቻ ውስጤ እሳቱ
አይዳፈን እየነደድኩ
መፈቀር ግን ህያው ሞት ነው
ስቃይ ብቻ ማፍቀር ልኩ
አላመንሽም ያንደበቴን
የማፍቀሬን ስር ትርጉሙን
አይወደኝም ሰርክ መልስሽ
አላወቅሽም ጥግ ህመሙን
ተፈቃሪ ምን ግድ አለው
ምን ቢፈቅር እንደሀገሩ
አፍቃሪ ነው ነገር ሚፈጅ
የሚማገድ ለወደሩ
ትገርሚያለሽ አንቺ ብቻ
አላመንሽም የኔን ፍቅር
አትወድህም ቢለኝም ሰው
ከደጃፍሽ ዛሬም አልቀር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ቅጽርህ የእናት እቅፍ
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
አወቅሽኝ
አወኩሽ
.
.
.
ተዋወቅን
በፍቅር ነጠቅን
ጨረቃን ዳሰስናት ኮኮቦችን ቆጠርን
ቅዳሴ እና አዛንን
አስቀደስን አፈጠርን
አወኩሽ
ወደድኩሽ
ከልብ ተመኘሁሽ
ለነብሴ ፈለኩሽ
አጌጥን በፍቅራችን አስቀናን ላገሩ
ኮራን በመንደሩ
ወጣቶች ተያይተው
"ሲያምሩ...ሲያምሩ" እየተባባሉ
ወደድሽኝ
ወደድኩሽ
.
.
.
ተዋደድን
በፍቅር አበድን
ነጎድን...ነጎድን...ነጎድን
ከአፍ ባልወጣ ቃል
መፋቀራችንን ሀገር ምድሩ ያውቃል
መገረም መደነቅ ለኛ ምንም ነው
ተፋቅረን አየነው
ደላኝ ባንቺ ፍቅር
ደላሽ በኔ ፍቅር
እኔ ለንቺ
አንቺ ለኔ ካለን ሁሉም ነገር ይቅር
አፈቀርሽኝ
አፈቀርኩሽ
.
.
.
ተፋቀርን
የዛሬን ትዝታ ለነገ ወቀርን።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
አወኩሽ
.
.
.
ተዋወቅን
በፍቅር ነጠቅን
ጨረቃን ዳሰስናት ኮኮቦችን ቆጠርን
ቅዳሴ እና አዛንን
አስቀደስን አፈጠርን
አወኩሽ
ወደድኩሽ
ከልብ ተመኘሁሽ
ለነብሴ ፈለኩሽ
አጌጥን በፍቅራችን አስቀናን ላገሩ
ኮራን በመንደሩ
ወጣቶች ተያይተው
"ሲያምሩ...ሲያምሩ" እየተባባሉ
ወደድሽኝ
ወደድኩሽ
.
.
.
ተዋደድን
በፍቅር አበድን
ነጎድን...ነጎድን...ነጎድን
ከአፍ ባልወጣ ቃል
መፋቀራችንን ሀገር ምድሩ ያውቃል
መገረም መደነቅ ለኛ ምንም ነው
ተፋቅረን አየነው
ደላኝ ባንቺ ፍቅር
ደላሽ በኔ ፍቅር
እኔ ለንቺ
አንቺ ለኔ ካለን ሁሉም ነገር ይቅር
አፈቀርሽኝ
አፈቀርኩሽ
.
.
.
ተፋቀርን
የዛሬን ትዝታ ለነገ ወቀርን።
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
(የአብስራ ሳሙኤል)
ጥበብ ናት እሷ
ሽንሽን ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
ችቦ ናት ለአለም
ሳቋ
የድል ብስራት
ኩርፊያው እስራት
የአንገቷ ድሪ
ሸማ ቀሚሷ
ዜማ ናት እሷ
የህይወት ቃና
የመዳን ዜና
ከጡት ወተቷ
ከመቀነቷ
እያጎረሰች
ጎጆ የቀለሰች
ጥበብ ናት እሷ
ችቦ ነው ነፍሷ
ቁጣዋ ማዕበል
ዝም
ጭጭ ደርሶ
ክፋት ገርስሶ
ፍቅር የዘራ
ጥበብ ናት እሷ
የአምላክ ስራ
የእጅ የመዳፋ
እስትንፈስ የአፋ
የመዳን ድልድይ
የተስፋ ነብይ
መቀነት ፈታ
ጡቷን አሟሽታ
እያጎረሰች
ቀን ያደረሰች
ጥበብ ናት እሷ
ሸማ ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
ችቦ ናት የአለም
የመዳን ዜና
የመኖር ቃና
መራራ ወዟ
ድል ያስጎነጭን
የእኔን እንባዋ
ውስኪ ያራጨን
ቅድ ጥለቷ ገመና ጋርዶ
የመዳፍ ቁስሏ ትኩስ አብርዶ
ትውልድ ያኖረ
ችቦ ነው ሳቋ
ድል ያበሰረ
ጥበብ ናት እሷ
ሽንሽን ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
መርከብ የሆነች
ለጠፋች አለም
መቀነት ፈታ
ቀን ያሻገረሰች
ድል ያበሰረች
ጥበብ ናት እሷ
ዜማ ናት እሷ
ሷቋ
የድል ብስራት
ኩርፊያዋ አሰስራት
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ጥበብ ናት እሷ
ሽንሽን ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
ችቦ ናት ለአለም
ሳቋ
የድል ብስራት
ኩርፊያው እስራት
የአንገቷ ድሪ
ሸማ ቀሚሷ
ዜማ ናት እሷ
የህይወት ቃና
የመዳን ዜና
ከጡት ወተቷ
ከመቀነቷ
እያጎረሰች
ጎጆ የቀለሰች
ጥበብ ናት እሷ
ችቦ ነው ነፍሷ
ቁጣዋ ማዕበል
ዝም
ጭጭ ደርሶ
ክፋት ገርስሶ
ፍቅር የዘራ
ጥበብ ናት እሷ
የአምላክ ስራ
የእጅ የመዳፋ
እስትንፈስ የአፋ
የመዳን ድልድይ
የተስፋ ነብይ
መቀነት ፈታ
ጡቷን አሟሽታ
እያጎረሰች
ቀን ያደረሰች
ጥበብ ናት እሷ
ሸማ ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
ችቦ ናት የአለም
የመዳን ዜና
የመኖር ቃና
መራራ ወዟ
ድል ያስጎነጭን
የእኔን እንባዋ
ውስኪ ያራጨን
ቅድ ጥለቷ ገመና ጋርዶ
የመዳፍ ቁስሏ ትኩስ አብርዶ
ትውልድ ያኖረ
ችቦ ነው ሳቋ
ድል ያበሰረ
ጥበብ ናት እሷ
ሽንሽን ቀሚሷ
የዘመን ቀለም
መርከብ የሆነች
ለጠፋች አለም
መቀነት ፈታ
ቀን ያሻገረሰች
ድል ያበሰረች
ጥበብ ናት እሷ
ዜማ ናት እሷ
ሷቋ
የድል ብስራት
ኩርፊያዋ አሰስራት
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ተዘነጋሽ አይደል ገፍተው አናናቁሽ
ከሳምንታት በፊት ንግሥቴ እንዳላሉሽ
የኔማ ሽሮዬ ብለው እንዳልተቀኙ
ጥለውሽ ነጎዱ ሚሽቱን ሲያገኙ
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
.
እኔ የኔ አበባ
እኔን የኔ ንግስት
ሰው ብቻ አይደለም
ማግጧል ያም ብረት ድስት
.
ሁሉም ከድተውሻል
ሁሉም ትተውሻል
ትንሽ ብቻ ታገሽ 50 ቀን ቀርቶሻል
.
ያኔ ቀኑ ሲደርስ በእየንብርክካቸው
ማሪኝ ማሪኝ ሽሮ አይቀር ማለታቸው
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
አለፈልን ብለው ቢያናንቁሽም
አትፍረጂባቸው!
የድሃ ብረት ድስት መቼም አይለቅሽም
#ስሜታዊ_ሆነው_ነው
[ ጥሩቤል ]
@ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
ከሳምንታት በፊት ንግሥቴ እንዳላሉሽ
የኔማ ሽሮዬ ብለው እንዳልተቀኙ
ጥለውሽ ነጎዱ ሚሽቱን ሲያገኙ
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
.
እኔ የኔ አበባ
እኔን የኔ ንግስት
ሰው ብቻ አይደለም
ማግጧል ያም ብረት ድስት
.
ሁሉም ከድተውሻል
ሁሉም ትተውሻል
ትንሽ ብቻ ታገሽ 50 ቀን ቀርቶሻል
.
ያኔ ቀኑ ሲደርስ በእየንብርክካቸው
ማሪኝ ማሪኝ ሽሮ አይቀር ማለታቸው
.
እኔን የኔ አበባ
እኔን የኔ እመቤት
50 ቀን ቀርቶሻል ልትገቢ ዳግም ቤት
አለፈልን ብለው ቢያናንቁሽም
አትፍረጂባቸው!
የድሃ ብረት ድስት መቼም አይለቅሽም
#ስሜታዊ_ሆነው_ነው
[ ጥሩቤል ]
@ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
, ( ግዛትሽ ነኝ )
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
ሀቁን ሁሉም ሰው፡
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ግዴታ ሆኖ — ብለ፟ይሽ
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem