( ተደብቆ )
=========

ጠብ ካልሻቱ በቀር
እድሜ አይጠየቅም .. ሄዋንን አጥብቆ

መፈላለግ እንጂ
ፈገግታዋ መሐል ካለ ተደብቆ !!!

By @kiyorna

@getem
@getem
@paappii
"ፀሎት ወምኞት"
              (ግዮናይ ነኝ)!፧

ከሐምሌ ጨለማ  ከክረምቱ ቆፈን፣
ከበጋው በረሃ   ከግንቦት ወላፈን፣
እኔና አንችን ብቻ  አምላክ ያሳልፈን።
                  ......
ካሉባልታ ወሬ  ከምቀኛ ሐሜት፣
ሰይጣን ለሚጠራ  ካልተገራ ስሜት።
መንታ ምላስ ይዞ   ከሚሰነጥቀን፣
የፍቅራችን ጌታ   እሱ ይጠብቀን።
                  .......
ትዳር ስንክሳሩን  የሳልነው በምናብ፣
ከላይ ይፈሰስልን  እንደ ሐምሌ ዝናብ።
በህይወተ-ፍካት በኔና አንቺ ማማር፣
መስከረም ይቅናብን  ጥቅምት ከኛ ይማር።

@getem
@getem
@paappii
ደርሷል ያልሽኝ ፍሬ
በሳል ያልኩሽ ጥሬ
ሰላ ያልሽኝ ፍቅር
ፀና ያልኩሽ ውቅር
ተንዶ በድንገት
ለኔም ላንቺም እብለት
ላንቺም ለኔም ውሸት
እንጭጭ ሳለ ጥሬ
ለቀጠፍነው እሸት።
       

By @poetkidus

@getem
@getem
@getem
የአብስራ ሳሙኤል

ዘመን ባይቀድምም እዚህ ህይወት አለ 
ከመኖር ወጀብ በመውደድ ሰበዝ የተከለለ 

❀   ❀
እዚህ እናት አለች 
ልጇ ሲመጣ ፈገግ ትላለች 
እዚህ አባት አለ 
ደቂቅ ትከሻው ዝግባ ያከለ 
❀    ❀


እዚህ . . . . . 
እኔና አንቺ ባለንት 
ነፍስ በዘራንበት 

ጠባብ ጎጆ ድንክ ማገር 
ታሪክ አለ ለዘመናት የሚሻገር
ከገሀድ ጮራ ፈንጥቀን 
በፈጠርናት ህብረ ቀለም 

መዋደድ ነው የህይወት ቋንቋ 
ቤተሰብ ነው የ'ኛ አለም 

እዚህ በምታይው 
በመኳረፍ እልህ ጥልቅ ፍቅር አለ 
የጊዜን ግሳንግስ በሳቅ ያቀለለ 
ዕልፍ ተሰብስቦ ቡራኬ የሚቋደስ 

እዚህ �ህይወት አለ 
አንተ ብላ በሚል ጥጋብ የሚታደስ 

እንዴት እንዲህ ይወደዳል 
እንዴት እንዲህ ይዋደዳል 

የመኖርን �አጸድ በአንዱ ዳና መትከል 
ጨርቄን ማቄን ሳይሉ ላመኑት መከተል 

እዚህ ብቻ ነው ያለው 
ለ'ኛ ብቻ ነው ያደለን 

እዚህ ውስጥ ሁላችን አለን 
እናት ሆነን አባት ሆነን 
ወንድም ሆነን እህት ሆነን 

አንድ የመሆን ብዙ መልኮች 
የአንድ ሰፌድ ህብራዊ ሰበዝ ገጾች 

የህይወት መርህ ያጠላለፈን 
የመዋደድ ቅጽ ያደጋገፈን 

እዚህ . . . . . 
እኔና አንቺ ካለንበት 
ህያው ታሪክ አለበት

@getem
@getem
@paappii
---

የአብስራ ሳሙኤል 
*・꙳・꙳・꙳・꙳・・*

እጠራሀለው 
በስምህ አቤት በለኝ ከሰማኀው
"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር 
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልከው 

ከፀሀይ ጀርባ  ምን አለ?
ከህይወት አድማስ ባሻገር 
ሞት የህይወት ፍጻሜ ነው? 
ወይስ ድልድይ የሚሻገር? 
አላዛር ያኔ ቢጠየቅ 
የሞተ ግዜ የት ነበር? 

ወዴት ነው 
የመኖር ማብቂያው? 
ወዴት ነው መጠናቀቂያው? 
ነፍሴን የማጽናናበት 
ምኞቴን የምዳኝበት 
ምን አለ ከጸሀይ ጀርባ? 
ወዴት ነው ነፍሴ የምትሸሸው? 

ይብቃህ እረፍ ተብዬ 
የስቃይ ቀኔ የሚያመሸው 
አውቃለሁ እንደ ነገርከኝ 
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ 
ማ? በለኝና ማን ልመን 
ብዙ ነው ስምና ገጽህ 

*"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር・・・ራባይ* 
―☾―

አየሁኝ 
እውር አንበሣን 
አንካሳ ነብር ሲመራው 
እንዲህ ነው መንግስት የሚዘልቅ 
እንዲህ ነው ፍጡር የሚመራው 

ካልተማመነ 
መንገዱን በነብር አይን ተረድቶ 
መጠራጠር ይገላል 
አንዱን ከአንዱ አባልቶ 
ይኀው ነው የነፍሴ ጣሯ 
አታምነኝ ወይም አላምናት 
ማ? በለኝና ማን ልበል 
በየቱ ቃልህ ላባብላት 

ማመን ነው 
የተስፋ ምርኩዝ 
መከተል የአይኑ ብርሀን 
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው? 
ወዴት ይሆን የመራኀን? 
―✦―

እጠራሀለው 
በስም አቤት በለኝ  ከሰማኀው
ጠይቁ ብለህ አልነበር 
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልኀው 

ከጸሀይ ጀርባ  ምን አለ?
ኦና'ነት ወይ ፍጻሜ 
የት ይሆን ጅምር መቋጫው? 
ስንት ይሆን የመኖር እድሜ? 
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው? 
ወዴት ነው መጠናቀቂያው? 

አውቃለሁ 
እንደ ነገርከኝ 
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ 
ማ? በለኝና ማን ልመን 
ብዙ ነው ስምና ገጽህ 

*・☽・・・☾・・・*

@getem
@getem
@paappii
( ተይ ጡር አለው ... )
=================

መቅረት እኮ ብርቅ አይደለም
መጣሁ ያለ ሁሉ አይመጣም
መተው እኮ ጥንትም ነበር
አንዳች እክል ሰው አያጣም
አይደንቀኝም ወዶ ማጣት
አልከፋኝም በመጥፋትሽ
ግን ንገሪኝ ....
እንደማትመጭ እያወቅሽው
ለምን ይሆን ማስጠበቅሽ ?

አንድ ህይወት ነው የተሰጠኝ
የማልኖረው ደጋግሜ
ግፍ አይደል ወይ ..  ከዚችም ላይ
በጥበቃ መስረቅ እድሜ ??

ቅርብ አሳቢ ምስኪን ልብሽ
ባያስተውል ልብ ባይለው
በወደደው ለጨከነ
ላልራራለት ለከጀለው
የዘሩትን የሚያሳጭድ
ፍቅርም እኮ ተይ ጡር አለው !

By @kiyorna

@getem
@getem
@getem
ብዙ ሳይጣጣር
እምብዛም ሳይለፋ
ከዓይን የራቀ
ከምናብ የሰፋ
ይህን ዓለም ሠራ
ያለ ጭንቀት ጥበት
ሆነለት “ሁን” ሲለው
እንዲሁ በዘበት

ሕዋውን በሙሉ
ግዑዙን ተፈጥሮ
በቃሉ ትዕዛዝ
እንዲህ አሳምሮ
ለድንጋዩ ራርቶ
የንብ መንጋ መርቶ
አበባን አፍክቶ
ወፊቱን አብልቶ

እኔ ትንሽ ነገር
ከሕይወት ቢጨንቀኝ
አደራህን ብለው
“እሺ ቆይ” እያለ
ይህን ሁሉ ዓመት
የሚያጠባብቀኝ
እንዴት ብከብደው ነው
ወይ እንዴት ቢንቀኝ ?
….

By henok bekele

@getem
@getem
@paappii
ሀ...ለ...ሐ...መ
ነገር አከተመ

ጥበብ በሁለቱ
በግጥም ስዕሉ
        ስታወናብደኝ
ህይወት ሚሉት ቋንቋ
ካንቺ ስር አዋለኝ።

መልክሽን በስዕል
መልክሽን በግጥም
       አተራመስኩልሽ
ይኸው አበድኩልሽ።

ጥበብና ህይወት...
ካንቺ ጋር አጋብተው ላያኖሩኝ ነገር
ለምን ይሰጣሉ
"ስሜት" ብለው ማፍቀር

አቤት አኳኋንሽ
አቤት አሳሳቅሽ
አቤት አረማመድ
ምንድነው መላመድ?
ለጥበበኛ ሰው መላመድ ትርፍ ነው
አይቶ ማፍቀር ብቻ ጥበብ እያረገው።

አይ ጥበብ አንዳንዴ
ደስ አለሽ ማበዴ!

የማልጨብጣትን ከምናብ አለም ሰው
        በፍቅር ሰቀልሽኝ
       ይኸው አሳበድሽኝ።

ሀ...ለ...ሐ...መ
በቃ ተፈፀመ።

ታሪክ ልስራ ብዬ...ታሪኬን ጨረስኩት
          ኑሮዬን አበድኩት

አይ ጥበብ አንዳንዴ
ደስ አለሽ ማበዴ!


ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
ጭውውት ከአይኖቿ
ጠ..ጠ..ር
እንደ ዳዊት ጠጠር፤
ወርወር፤
ጎላ ደግሞ ደመቅ፤
ደመና መሰንጠቅ፤
ጠንቀቅ፤
ወጋ ደግሞ ነቀል፤
ስሜትን መፈንቀል፤
ቀልቀል፤
ከብለል ከዛ ረጋ፤
ትንፋሿን ፍለጋ፤
ጠጋ።

By @poetkidus

@getem
@getem
@paappii
🌹 የአብስራ ሳሙኤል🕊


▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
መለያየት ሞት ነው ብላኝ እንዳልነበር 
ይኀው ተለያየን ሞታ ስትቀበር 
✞ አፈር ስትለብስ መሬት ሲደብቃት 
   የአዳም ዘር እዳ ከቅፌ ሲነጥቃት 
ጩኀት ለቅሶ ዋይታ አጅቧት ስጠፋ 
   ነፍስ ይማር የሚል ቃል ጆሮ ላይ ሲከፋ 

   ሞታ ስትቀበር 
   መለያየት ሞት ነው 
   ሞት መለያየት ነው 
ብላኝ እንዳልነበር 
   ይኀው ተለየቺኝ አፈር ስትለብስ 
   እንባም አይበቃኝም ላንቺ በምን ላልቅስ 


▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
የቀብርሽ እለት 
   በልብሰተ ክህኖ ገፁን ያሳመረ 
ጠይም ደርባባ ቄስ 
   ስለ ሞትሽ ትርጉም እንዲ ተናገረ 
  ተው አይለቀስም 
   ምን ሰራህ ተብሎ እግዜር ይወቀሳል 
   አፈር የተጫማ 
   ሊበሰብስ እንጂ ተጉዞ የት ይደርሳል 

 
▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
ህይው ልትሆን እንጂ 
   ✞ ከፈራሽ ገላዋ ነፍሷን የነጠቀ 
ያልሞተ አያፈራም ዘር ሆኖ ያልወደቀ 
   ትድን እደሆነ 
   ተዝካሯን አውጡላት ነድያን መግቡ 
   እሱ እንደው ሩህሩህ አይጨክንም ልቡ 
ብለው ቢናገሩ 
     ከበደኝ ቀብሩ 


▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
አንቺስ ፍቅርዬ 
   መለያየት ሞት ነው ብለሺኝ አልነበር 
በመሞት ከሆነ ህይወት የሚጀመር 
   ውልደትሽ ምን ነበር? 
   ከኔ ተለይተሽ 
   ጀነት ብትገቢ ብትቆሚ በቀኙ 
   ያንቺን እጣ ማግኘት ሙታን እዲመኙ 
🔥 ወይ ሲኦል ተጥለሽ እልፍ ብትቀጪ 
      ለየዕለት ሀጥያትሽ ፀፀት ብታምጪ
   ከልብሽ ላይ ችለው እኔን ላያወጡ 
   ስፍር አልባ ጋኔል ባንቺ ላይ ቢቆጡ


▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
ብታማትቢ እንኳ 
     የማይጠፋ ሴጣን ከሲኦል ቢገጥምሽ 
አውቃለሁ ፍቅርዬ 
     የሀጥያት ሰንሰለት እንደማይገድብሽ 
ስለዚህ ለአንቺ 
  🕊 ፍጹም እንቀይረው የመሞትን ፍቺ 
አንቺ እንደ ነገርሺኝ እኔም እንደማውቀው 
   ከሀዘናቸው ብዛት ባይቀብሩሽም ስቀው 

  🕊
▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
ስለመለየትሽ እንባ እያፈሰሱ 
    መአት ለቀስተኞች ከለቅሶሽ ደረሱ 
እኔም ከንቱ አፍቃሪሽ 
     ሞት ህያውነት ነው ብዬ እያመንኩኝ 
ህያው ሆኜ እንኳ ካንቺ የተነጠልኩኝ 
   💧 ሳስስ ስፈልገው የሞትሽን ትርጉም 
   ከእንባ ላይ አየሁት የሚተን እንደ ጉም 

┗━━━━•❃🌹    🌹❃•━━━━┛

@getem
@getem
@getem
መቼ ነው አንድ ቀን ??
===============

ስንጠጋው ሚሸሽ
ስንቀርበው ሚርቀን
ዕድሜያችንን ሁሉ
ስንኖር ሚናፍቀን
በተስፋ ጠቅልለው ይመጣል የሚሉን
መቼ ነው ' አንድ ቀን ' ??

By @kiyorna

@getem
@getem
@paappii
#እቱ_የሄድሽቱ
.
.

የዘንድሮስ መንገድ ሰማሁ ለሰለሰ፣
ወስዶት የነበረን እልፍ ሰው መለሰ።

አንቺ የሄድሽበቱ 'ሾህ ነው አሜኬላ፣
ምነው አልመለሰሽ ካስኬደሽ በኋላ።


     ዓቢይ ( @abiye12 )


@getem
@getem
@getem
ንጉስ ሲጨንቀው

የአንዲት ደሃ ሀገር፣ ዜጎቿ በሙሉ
መሄጃ ቢያሳጡት፣ 'ተራብን' እያሉ
ምስኪን ንጉሳቸው፣ እንዲህ ፀለየ አሉ፡-

‘’እባክህ አምላኬ!
የተራበ ህዝቤን፣ ሲያሻህ በነጠላ
ካሰኘህ በጅምላ፣
ከፊቴ አርቅና፣ ባህር ክተትልኝ
ከሐይቅ ጣልልኝ፡፡
ከዚያማ!
ያልቻሉት ሲሰምጡ፤
የቻሉት ለማምሻ፣ ዓሣ ይዘው ይውጡ!”

By bereket belayneh

@getem
@getem
@paappii
የአብስራ ሳሙኤል

⁓⁓⁓ 
ልውደድስ ቢሉ ⁓ እንዴት ተደርጎ ይወደዳል 
ደግሞ ልሽሽም ቢሉ ⁓ ከራስ ወዴት ይኬዳል 
ብቻ ህያው ነፍሴ ⁓ በሁለት ባላ ተወጥራ 
ለፍታ ደክማ ........ጥራ 

♡⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯⋯♡ 
ወዳንቺ ⁓ ትንጠራራለች 
በለሆሳስ ⁓ ታወራሻለች 

‧₊˚✧ 
አየሽ አበቦቹን ⁓ በሚወዷቸው ተከበው 
ጸድቀው ⁓ ፈክተው ⁓ አብበው 
❀  ❀  ❀ 
የመኖርን ጣዕም ⁓ ሲቀስሙ 
በቢራቢሮ ⁓ ሲሳሙ 

—⋅☾⋅— 
በእኔ ቀጋ ገላ ⁓ ትል ያዣል 
እንኳን ለሚወዱት ⁓ ለራስስ ምኑ ያስጎመዣል 

⁂ 
እናም ⁓ ቢሳካልሽ ⁓ ቢሆንልሽ 
ጭቃ ⁓ ጠፍጥፈሽ ⁓ በሀብና በአምሳልሽ 
◌ ◌ ◌ 
ብትፈጢርኝ ⁓ መች ይከፋኛል 
የአንቺ መሆን ⁓ ያስመኘኛል 

⋯♰⋯ 
ቢሆንም ⁓ ሂጅ ⁓ ግድየለም 
አንቺን ⁓ አትነፍግም ⁓ አለም 

—⋆— 
ህይወት ⁓ ቢረግፍም ⁓ በየመስኩ 
ላይችል ⁓ አይሰጥ ⁓ ያለ ልኩ 
⸻⸻⸻ 
እስጥሽ ምንም ⁓ የለኝም
እቸርሽ ⁓ አልሞላልኝም
ከኔ ዘንድ ⁓ አትጠውልጊ 
ከፈካው ⁓ አበባ ⁓ ተጠጊ 
⁓⁓⁓

@getem
@getem
@getem
አለሽ አለሁ
እወድሻለሁ።

ግና ያፌ ድንበር
ቀን እንዳልወጣለት
ለምን አንቺን ፈራ
ወድሻለሁ ማለት

ለምን ፅሁፍ ብቻ
ለምን በዚህ ግጥም
አንደበት ተዘግቶ
ለምን ምቀረጥም

እንጃ!

ብቻ

አለሽ....አለሁ።
እወድሻለሁ!

አለሁ.....አለሽ?
ትወጅኛለሽ?

ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
የአብስራ ሳሙኤል


  ውበት ኪነ-ጥበብ ናት 
   ከታደሏት ያጌጡባታል 
   ካልታደሏት ይመኟታል‧‧‧ 
   ያደንቋታል 

የአፍንጫ አወራረድ ቤት ይመታል 
   የጉንጮቿ ስርጉድ ቤት ይደፉል 

✧・゚゚:* ──── * ✧・゚:*

  ውብ እግዜር የጻፋት ግጥም ትመስላለች 
   ልብ ብሎ ላያት ሁሉ እንደ ግሉ ትፈታለች 

  አሁን ለምሳሌ እሷን ያዪ ሴቶች 
   ቻፒስቲካቸውን አንስተው 
   የ'ሷን አይነት ቀለም ይቀባሉ 

✦•≪───── ⋆⋅☽⋅⋆ ─────≫•✦

   ውበት ተዋረሰ ማለት ይሄ አደለ ቅሉ 
   ልቡ የከጀላት ጎልማሳ ደሞ 
   "ሚስትማ እንደ እሷ አይነት ነበር እንጂ" 
   ብሎ ሚስቱን ይገፉል 

   ውበት አይኑን ሲያውረው 
   ከማማር ዝሙት ያተርፋል 
   እሷ ብቻ ናት ማማሯን የማታውቀው 

✧・゚: ゚:* ──── * ✧・゚:*

  እንደ ግጥም ለራስ ተነባ 
   አትረካም ታዳሚ ትሻለች 
   አጀብ አጀብ ባይ አሞጋሽ ትፈልጋለች 

   ከስንኝ አኳላቶቿ 
   ግጥም እያዋቀረ የሚያወድሳት 
   ከሆነችበት ወዳ'ልሆነችበት 
   በምዕናብ የሚያደርሳት 

✧・゚・゚:* ──── *✧・゚✧・゚:*

  ምነው እንደጨረቃ 
   ባማርኩ ብሎ እንደትመኝ የሚያረጋት 
   ከመሆንና አለመሆን 
   በምኞት ወላፈን የሚያዋጋት 

✦•≪───── ⋆⋅☾⋅⋆ ─────≫•✦

  ታዲያ ይሄን ያዩ ቺኮች 
   አሁንም ገጻቸውን እንደ ጨረቃ ይቀባሉ 
   ስንቱን ተኩኖ ይቻላል 
   ስንቱን ይሆናሉ 

  ወደ ተንጠራራንበት ሁሉ 
   ፈጣሪ �|አይጠፋም 
   ቆርጦ የሚቀጥል ቀዶ 
   የሚሰፋ! አያለፋም ? 

✧・゚: * ──── * ✧・゚:*

ታዲያ ውበት ማለት ምን ማለት ይሆን 
   ያላለቀ ግጥም 
   ያላለቀ ድርሰት 

✾ መድረስ የሚችሉት ነው 
   ወይስ የቆሙበት 

✧・゚: * ──── * ✧・゚:*

   ሁሉም በሷ ከተለካ 
   እሷን ለመምሰል 
   ገጹን ሸራ ቢያደርገው 
   ምንድነው ክፋቱ 

    **ልኬቱ ሳይሆን 
   መለኪያው ነው ጥፋቱ** 

✦•≪─── ⋆⋅☆⋅⋆ ───≫•✦

   ቤት የማይመታ መልክ አለ ? 
   ቤት የማይደፋ ቁመና አለ ? 

  ገጣሚው ተሳሳተ 
   ላለማለት ለምን 
   ግጥሙ ይወቀሳል 
   ለምን ፊደል ይረክሳል 

   ሁሉም ስንኝ ቤት አይመታም 
   ልክ እንደዚህ ግጥም 

✧・゚・゚:* ──── * ✧・゚:*

  አያምርም ለማለት 
   መስፈርቱ ይህ ከሆነ 
   ቆርጣች ቀጥሏት 
   ቀዳችሁ ስፏት 

✾ ❀ ስለሆነችው ሳይሆን 
   እንድትሆን ወደምትፈልጉት 
   ምዕናባችሁ ምሯት ❀ 

✦•≪──── ⋆⋅🌙⋅⋆ ────≫•✦

@getem
@getem
@paappii
የሠው ጉርብትና
(የሞገሴ ልጅ)
ለመደጋገፉም-
ለመወራወሩም - ነፃ ፈቃድ ያለው፣
ራሱን አሳምኖ፣
ሲሻ የሚያነሳ - ሲሻ የሚጥለው።
ሠው የሚባል ፍጥረት-
በኅብረት በመኖር - ላንዱ አንዱ ሊደርስ፣
አንድነት መስርቶ፣
ጉርብትና ፈጥሮ - ሊማከር ሊዋቀስ።

ብዙ የኖረበት-
እየተጋገዘ - ዛሬን እየሰራ፣
ሊያቃጥል ይችላል፣
እንዲሞቅ ሲለኮስ - በርቶ እንዲያበራ።
ሲያክም የሚፈውስ-
ሲዋጋ ህመሙ -
ኃይሉ የሚጠና፣
ሲጠብቅ መከታ፣
ሲሻክር ስጋት ነው -የሠው ጉርብትና።

By @tafachgitm

@getem
@getem
@paappii
ነገር ስሩን ታውቂዋለሽ
አይጠበቅም የአፌ ቃል
አካኋኔ እንኳን ላንቺ
ላገር ምድሩ ያስታውቃል

ምን ስራ አለኝ ካንቺ ውጪ
ሌትም ቀንም ከደጃፍሽ
ሰርክ መዋል አይሰለቸኝ
ከጋላሽ ጋር ካንደበትሽ

ታውቂዋለሽ ስራ ጉዴን
አታጭኝም ከሄድሽበት
እኔን ማልፋት ደስ ይለሻል?
ባታደክሚኝ ምናለበት።

ቃሌን መስማት ከምላሴ
        ካሻሽ እንደው የትርጉሙን
ልብሽ ያውቃል ሁሉን ነገር
       የኔን ስቃይ ጥግ ህመሙን
ኪዳን ይዘሽ መጠየቁን
        ትችያለሽ ካላመንሽው
ዳሩ ፍቅር ዳሩ መውደድ
       ከልቤ ነው የታደልሽው
ንግስት አርጎ ሰርክ ያኖረሸ
       ይህ ልቤን ነው ያላመንሽው።

እውነት እውነት ስሜት አለው
         ያንቺን ፍቅር ያነገበ
ወትሮ ጊዜው መጨናነቅ
      ሌላ አካልን አልደረበ
ድምም ይላል ውስጥ መንፈሴ
      ቃል ስምሽን እየሰማ
ሻማ ማብራት አስጀምሯል
      ባወቀሽ ቀን እየጠራ
ለሊት አይሉት ወይ ቀትር ላይ
      አትታጪም ከሃሳቡ
ሁሌም አለሽ በ ህልሙ ውስጥ
    ልቤ አፍቅሮ ባክኖ ልቡ።

ተይ አታስደክሚኝ
ካወክሽው እከሚኝ!



ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
የባከነ ሌሊት!!!!
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::

By bewuketu seyoum

@getem
@getem
@paappii
የአብስራ ሳሙኤል

ከቤትሽ በር ላይ
ትንሽ ዘምበል ብሎ ቅጠሉ የረገፈ
አንቺ ስትወጪ የተንዘፈዘፈ
በአራራይ ዜማ
ጎንበስ ቀና ብሎ ውዳሴ የሚያሰማ

ዛፍ ካየሽ.......እኔ ነኝ
ደሞ ጮራ ከቦሽ
የጸሀዪ ንዳድ ገላሽን አልቦሽ
ማረፊያ ፍለጋ የተቀመጥሽበት

ስራ የፈታ ድንጋይ የዱርዬ መንበር
የኔ ገላ ነበር
ወይም ባለፈው 'ለት
በዕለተ ሰንበት ልደታን ስትስሚ
የተሽኮረመምሽው ምርቃት ስትሰሚ
ምንም ሳትሰጪ ሳትመጸውቺ
ህይወት ህይወት ጸዳል ለምትሸቺው ላንቺ

አሜን ሳትይ እንኳ የመረቀሽ ለማኝ
እኔ ነኝ

እናልሽ መቅደሴ
ሴያሻሽ እንደ ታዛ ሲያሻሽ እንደ ወንበር
ደጀ ሰላም ወድቆ ሲመርቅ የነበር

ከጎጆሽ ባይመጥን ከልብሽ ባይሞላ
በሄድሽበት ሁሉ በአምሳል እያጠላ

እንደ ንፍቀ ክበብ ሲዞርሽ የሚገኝ
እኔ ነኝ

@getem
@getem
@paappii
2025/06/25 13:29:14
Back to Top
HTML Embed Code: