#ለእርጅና_እጅ_ያልሰጡት_አባት| ኡኩሞ ኦሳንጎ
#hawassa|
በደርግ ዘመን ወጣት እያሉ ነው ወደ ሐዋሳ የገቡት። እድሜያቸው ወደ ዘጠና ተቃርቧል። የሚታወቁት አሮጌው ገበያ የእጅ ጋሪያቸውን ይዘው ለወጣት የሚከብድ ሸክም ሸክፈው በተባሉበት ታማኝ ሆነው ገበያተኛን ሲያገለግሉ ነው።
አሳቸው እንደሚሉት ባለትዳርና ለስራ ያልደረሰች (አራት አመት) ህፃን ልጃቸውን ለማስተዳደር፤ ኑሮን ለማሸነፍ መስራት ግድ ሆኖባቸው ያቅማቸውን በመታተር ላይ ናቸው።
በስተርጅና ይሄን ከባድ የጉልበት ስራ ካልሰሩ ቤተሰባቸው በረሃብ መቀጣቱና ለችግር መዳረጋቸው ስለማይቀር ይጣሩ እንጅ አሁን አቅም እየከዳቸው፣ ጤናም እየራቃቸው ቢሆንም ከመስራት ወደኋላ አላሉም። ቢደላማ መጦሪያቸው ነበር!
ከዚህ ቀደም ባለቤታቸው የቀን ስራ (የግንበኛ ረዳት) በመሆን ያቅሟን እየሰራች፣ እርሳቸውም ጋሪ እየገፉ የእለት ጉርሳቸውን ሲሸፍኑ ቢቆዩም አሁን ግን ባለቤታቸው ጤና ስላጡ የቤቱን ወጭ መሸፈን በእሳቸው ብቻ የተወሰነ ሆኗል። "እያቃተኝ ህመሜን ችዬ ..." ይላሉ ያሉበትን ሁኔታ ሲገልፁ።
የጋሽኡኩሞ እድሜ እየጨመረ ጤናም በመጥፋቱ ዛሬ እንደበፊቱ ጠንክረው ሰርተው የለት ወጭ ለመሸፈን አዳጋች ሆኖባቸው፤ አንዴ ሲያገኙ አንዴ ሲያጡ በችግር መኖር ከጀመሩ አመታት ተቆጥረዋል።
"እስከምሞት ስራ አላቆምም" የሚሉን አባታችን ወጣት ሆኖ ስራ የማይሰሩና የሚለምኑ ሲያዩ እንደሚቆጩ ያብራራሉ። "ምናለ አቅም ባይከዳኝ!" ይላሉ። እኛ አቅም ላጡ አቅም አንሆንም ወገን?!
ጋሽ ኡኩሞን በደምበኝነት ለረዠም አመታት የሚያውቋቸው ሲገልፁ ጥንካሬና ታታሪነት ብቻ ሳይሆን ታማኝነታቸው የበለጠ የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ተረድተናል። አቅም እያለ ከስራ ማጭበርበርና ልመናን ስራ ላደረጉ ሁሉ ከአባታችን ብዙ ሊማሩ ይገባል። ለዚህም አለን በማለት ከጎናቸው እንሁን።
ውድ የሐዋሳ ትዝታ ቤተሰቦች፣ እኝህን አባታችንን ለ ፊታችን አዲስ አመት አዲስ ሐይል እንሆናቸውና፣ በተቻለ መጠን ደግፈን ከከባዱ የጉልበት ስራ አላቀን ቀላል ጀብሎ እንኳን ሰርተው መኖር የሚችሉበትን እድል በመፍጠር የታታሪነታቸውን ዋጋ በመደገፍ እንድንረባረብላቸው የከበረ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
#hawassa|
በደርግ ዘመን ወጣት እያሉ ነው ወደ ሐዋሳ የገቡት። እድሜያቸው ወደ ዘጠና ተቃርቧል። የሚታወቁት አሮጌው ገበያ የእጅ ጋሪያቸውን ይዘው ለወጣት የሚከብድ ሸክም ሸክፈው በተባሉበት ታማኝ ሆነው ገበያተኛን ሲያገለግሉ ነው።
አሳቸው እንደሚሉት ባለትዳርና ለስራ ያልደረሰች (አራት አመት) ህፃን ልጃቸውን ለማስተዳደር፤ ኑሮን ለማሸነፍ መስራት ግድ ሆኖባቸው ያቅማቸውን በመታተር ላይ ናቸው።
በስተርጅና ይሄን ከባድ የጉልበት ስራ ካልሰሩ ቤተሰባቸው በረሃብ መቀጣቱና ለችግር መዳረጋቸው ስለማይቀር ይጣሩ እንጅ አሁን አቅም እየከዳቸው፣ ጤናም እየራቃቸው ቢሆንም ከመስራት ወደኋላ አላሉም። ቢደላማ መጦሪያቸው ነበር!
ከዚህ ቀደም ባለቤታቸው የቀን ስራ (የግንበኛ ረዳት) በመሆን ያቅሟን እየሰራች፣ እርሳቸውም ጋሪ እየገፉ የእለት ጉርሳቸውን ሲሸፍኑ ቢቆዩም አሁን ግን ባለቤታቸው ጤና ስላጡ የቤቱን ወጭ መሸፈን በእሳቸው ብቻ የተወሰነ ሆኗል። "እያቃተኝ ህመሜን ችዬ ..." ይላሉ ያሉበትን ሁኔታ ሲገልፁ።
የጋሽኡኩሞ እድሜ እየጨመረ ጤናም በመጥፋቱ ዛሬ እንደበፊቱ ጠንክረው ሰርተው የለት ወጭ ለመሸፈን አዳጋች ሆኖባቸው፤ አንዴ ሲያገኙ አንዴ ሲያጡ በችግር መኖር ከጀመሩ አመታት ተቆጥረዋል።
"እስከምሞት ስራ አላቆምም" የሚሉን አባታችን ወጣት ሆኖ ስራ የማይሰሩና የሚለምኑ ሲያዩ እንደሚቆጩ ያብራራሉ። "ምናለ አቅም ባይከዳኝ!" ይላሉ። እኛ አቅም ላጡ አቅም አንሆንም ወገን?!
ጋሽ ኡኩሞን በደምበኝነት ለረዠም አመታት የሚያውቋቸው ሲገልፁ ጥንካሬና ታታሪነት ብቻ ሳይሆን ታማኝነታቸው የበለጠ የሚያስመሰግናቸው እንደሆነ ተረድተናል። አቅም እያለ ከስራ ማጭበርበርና ልመናን ስራ ላደረጉ ሁሉ ከአባታችን ብዙ ሊማሩ ይገባል። ለዚህም አለን በማለት ከጎናቸው እንሁን።
ውድ የሐዋሳ ትዝታ ቤተሰቦች፣ እኝህን አባታችንን ለ ፊታችን አዲስ አመት አዲስ ሐይል እንሆናቸውና፣ በተቻለ መጠን ደግፈን ከከባዱ የጉልበት ስራ አላቀን ቀላል ጀብሎ እንኳን ሰርተው መኖር የሚችሉበትን እድል በመፍጠር የታታሪነታቸውን ዋጋ በመደገፍ እንድንረባረብላቸው የከበረ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
#መልካም_ዜና| ለሐዋሳና አካባሲዋ ነዋሪዎች
#hawassa| #መስማት_የተሳናቸው ት/ቤት
በከተማችን ብቸኛ የሆነው መስማት የተሳናቸውን ወገኖች በትምህርት ሲደግፍ የቆየው #ቪዥን_ግሎባል_ኢምፓወርመንት_ሐዋሳ በየትምህርት ቤቶች የሚገኙ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ውስጥ መስማት የተሳናቸውን በርካታ ህፃናትና ታዳጊዎች በትምህርት ቁሳቁስ፣ እንዲሁም በሙያ ተማሪዎችን ያለምንም ክፍያ ሲደግፍ የቆየ ተቋም ሲሆን አሁን ደግሞ በቅድመ መደበኛ መስማት የተሳናቸውንና ሌሎች መደበኛ ተማሪዎችን ለማስተማር ፍቃድ አግኝቶ በምዝገባ ላይ ይገኛል።
የተቋሙ ዳይሬክተር አቶ ሐምሳሉ እንደገለፁት ተቋሙ መስማት የተሳናቸው ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ባለመስማታቸው የሚገጥማቸውን ችግር መቅረፍ እና ማህበራዊ ተግባቦታቸውን ማሻሻልን በዋናነት ትኩረት አድርጎ እየሰራ ያለ ሲሆን፣ ከዚህ ጎን ለጎን ለወላጆችና ፍላጎቱ ላላቸው ሰዎች #የምልክት_ቋንቋ ስልጠናም ሲሰጥ ቆይቷል።
ከትምህርት ስራው በተጨማሪ በብቁ ባለሙያና ዘመናዊ የጆሮ ምርመራ /hearing test በማከናወን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እየሰራ ይገኛል።
ውድ የሐዋሳ ትዝታ ቤተሰቦች #visions_global_empowerment_hawassa በማህበረሰብ ድጋፍ የጎላ ተሳትፎም ያለው ሲሆን ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሐዋሳ ትዝታ ለተማሪዎች የደብተርና ብዕር የማሰባሰብ መርሐ ግብር የበኩሉን ድጋፍ በማድረጉ በእናንተ ስም የከበረ ምስጋናችንን ለመግለፅ እንወዳለን።
ስለሆነም እርስዎ አልያም የሚያውቁት መስማት የተሳነው ወገን በአካባቢያችሁ ካለ ተቋሙን በቀጥታ (ቄራ ሜዳ በሚገኘው የተቋሙ ጊቢ) በመገኘት አልያም በመደወል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናሳውቃለን።
#hawassa| #መስማት_የተሳናቸው ት/ቤት
በከተማችን ብቸኛ የሆነው መስማት የተሳናቸውን ወገኖች በትምህርት ሲደግፍ የቆየው #ቪዥን_ግሎባል_ኢምፓወርመንት_ሐዋሳ በየትምህርት ቤቶች የሚገኙ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ውስጥ መስማት የተሳናቸውን በርካታ ህፃናትና ታዳጊዎች በትምህርት ቁሳቁስ፣ እንዲሁም በሙያ ተማሪዎችን ያለምንም ክፍያ ሲደግፍ የቆየ ተቋም ሲሆን አሁን ደግሞ በቅድመ መደበኛ መስማት የተሳናቸውንና ሌሎች መደበኛ ተማሪዎችን ለማስተማር ፍቃድ አግኝቶ በምዝገባ ላይ ይገኛል።
የተቋሙ ዳይሬክተር አቶ ሐምሳሉ እንደገለፁት ተቋሙ መስማት የተሳናቸው ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ባለመስማታቸው የሚገጥማቸውን ችግር መቅረፍ እና ማህበራዊ ተግባቦታቸውን ማሻሻልን በዋናነት ትኩረት አድርጎ እየሰራ ያለ ሲሆን፣ ከዚህ ጎን ለጎን ለወላጆችና ፍላጎቱ ላላቸው ሰዎች #የምልክት_ቋንቋ ስልጠናም ሲሰጥ ቆይቷል።
ከትምህርት ስራው በተጨማሪ በብቁ ባለሙያና ዘመናዊ የጆሮ ምርመራ /hearing test በማከናወን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እየሰራ ይገኛል።
ውድ የሐዋሳ ትዝታ ቤተሰቦች #visions_global_empowerment_hawassa በማህበረሰብ ድጋፍ የጎላ ተሳትፎም ያለው ሲሆን ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሐዋሳ ትዝታ ለተማሪዎች የደብተርና ብዕር የማሰባሰብ መርሐ ግብር የበኩሉን ድጋፍ በማድረጉ በእናንተ ስም የከበረ ምስጋናችንን ለመግለፅ እንወዳለን።
ስለሆነም እርስዎ አልያም የሚያውቁት መስማት የተሳነው ወገን በአካባቢያችሁ ካለ ተቋሙን በቀጥታ (ቄራ ሜዳ በሚገኘው የተቋሙ ጊቢ) በመገኘት አልያም በመደወል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናሳውቃለን።
#የአዲስ_አመት_ስጦታ| ቃል በተግባር
#hawassa| የሚጋባ ደስታ😍
ወድ ቤተሰቦች ያለውን አካፍሎ በፍቅር መኖር ልምዱ የሆነው የሐዋሳ ህዝብ ፍሬዎች ከሆኑት #አለማየሁና #አሸናፊ (ቾምቤ) ጋር በጋራ በመሆን አቅም ላጡ፣ ቤት ዘግተው በአልን ለማሳለፍ ግድ ለሆነባቸው አባትና እናት አረጋውያን የሚጋባ ደስታን በስጦታዎች ፈጥረዋል።
በመጀመሪያው ዙር ዶሮ፣ ዘይትና ሽንኩርት እንዲሁም ገንዘብ ለ12 አረጋውያን አድርሰናል።
"ከፈጣሪ ጋር ትናንት ስጣላ ነበር... እግዜር ፀሎቴን ሳይውል ሳያድር መለሰልኝ"
ያሉት አንድ እናት በተደረገላቸው ስጦታ መደሰታቸውን ሲገልፁ በእንባ ታጅበው ነበር። በፊታቸው ደስታንና ፈገግታን የጫራችሁ እናንተ ውድ የሐዋሳ ጀግኖች የአባትና እናቶች ምርቃት በናንተ ይደር ለማለት እንወዳለን።
በእለቱ ከሐዋሳ ትዝታ አባላት እና የዘውትር ተሳታፊዎቻችን አንዱ የሆነው ወጣት #ሐይለየሱስ በቦታው በመገኘት ለአንዳንድ ወጭ የሚሆን በማለት የገንዘብ ስጦታ ለእናቶቹ በተጨማሪነት ሰጥቷቸዋል። እግዜር በወጣ ይተካ።
በተለይ አሌክስና ቾምቤ ሁለት ቤተሰቦች ቋሚ በየወሩ የ2000 ብር ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን ከ70 ተማሪዎች በላይ ዩኒፎርምና የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም የመምህር ደሞዝ ክፍያ በመፈፀም አጀብ የሚያሰኝ ከልብ የመነጨ ደግነታቸው ፈጣሪ ይባርካቸው ህልማችሁ ይሳካ ድመቁ ለማለት እንወዳለን።
በተጨማሪ የሐዋሳ ትዝታ ማስተባበሪያ ቢሮ የሚገኝብ መሐል ክፍለከተማ ጵ/ቤት ጎን በሚገኘው ቤተልሄም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ም/ር መምህር የሆኑት ወ/ሮ ምህረት በመገኘት ስጦታውን በክብር እንግድነት ስላበረከቱልን እንዲሁም ለመልካም ስራ ሁሌም ተባባሪ በመሆናችሁ የት/ቤቱን አስተዳደር ከልብ እናመሰግናለን።
ሁለተኛው ስጦታችን ደግሞ ከቤት መውጣት ለማይችሉ #ታማሚና #አስታማሚ እናትና አባቶች ቤት ለቤት ያደረግነውን ጉብኝት ይዘን እንቀርባለን።
ውድ ቤተሰብ ለመልካምነት ጊዜው አይረፍድምና መስጠት ባንችል እንኳ የሰጡትን ታበረታቱልን፣ ታመሰግኑልን ዘንድ በአክብሮት እንጨይቃለን!
መልካም አዲስ አመት!😍😍
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
#hawassa| የሚጋባ ደስታ😍
ወድ ቤተሰቦች ያለውን አካፍሎ በፍቅር መኖር ልምዱ የሆነው የሐዋሳ ህዝብ ፍሬዎች ከሆኑት #አለማየሁና #አሸናፊ (ቾምቤ) ጋር በጋራ በመሆን አቅም ላጡ፣ ቤት ዘግተው በአልን ለማሳለፍ ግድ ለሆነባቸው አባትና እናት አረጋውያን የሚጋባ ደስታን በስጦታዎች ፈጥረዋል።
በመጀመሪያው ዙር ዶሮ፣ ዘይትና ሽንኩርት እንዲሁም ገንዘብ ለ12 አረጋውያን አድርሰናል።
"ከፈጣሪ ጋር ትናንት ስጣላ ነበር... እግዜር ፀሎቴን ሳይውል ሳያድር መለሰልኝ"
ያሉት አንድ እናት በተደረገላቸው ስጦታ መደሰታቸውን ሲገልፁ በእንባ ታጅበው ነበር። በፊታቸው ደስታንና ፈገግታን የጫራችሁ እናንተ ውድ የሐዋሳ ጀግኖች የአባትና እናቶች ምርቃት በናንተ ይደር ለማለት እንወዳለን።
በእለቱ ከሐዋሳ ትዝታ አባላት እና የዘውትር ተሳታፊዎቻችን አንዱ የሆነው ወጣት #ሐይለየሱስ በቦታው በመገኘት ለአንዳንድ ወጭ የሚሆን በማለት የገንዘብ ስጦታ ለእናቶቹ በተጨማሪነት ሰጥቷቸዋል። እግዜር በወጣ ይተካ።
በተለይ አሌክስና ቾምቤ ሁለት ቤተሰቦች ቋሚ በየወሩ የ2000 ብር ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን ከ70 ተማሪዎች በላይ ዩኒፎርምና የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም የመምህር ደሞዝ ክፍያ በመፈፀም አጀብ የሚያሰኝ ከልብ የመነጨ ደግነታቸው ፈጣሪ ይባርካቸው ህልማችሁ ይሳካ ድመቁ ለማለት እንወዳለን።
በተጨማሪ የሐዋሳ ትዝታ ማስተባበሪያ ቢሮ የሚገኝብ መሐል ክፍለከተማ ጵ/ቤት ጎን በሚገኘው ቤተልሄም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ም/ር መምህር የሆኑት ወ/ሮ ምህረት በመገኘት ስጦታውን በክብር እንግድነት ስላበረከቱልን እንዲሁም ለመልካም ስራ ሁሌም ተባባሪ በመሆናችሁ የት/ቤቱን አስተዳደር ከልብ እናመሰግናለን።
ሁለተኛው ስጦታችን ደግሞ ከቤት መውጣት ለማይችሉ #ታማሚና #አስታማሚ እናትና አባቶች ቤት ለቤት ያደረግነውን ጉብኝት ይዘን እንቀርባለን።
ውድ ቤተሰብ ለመልካምነት ጊዜው አይረፍድምና መስጠት ባንችል እንኳ የሰጡትን ታበረታቱልን፣ ታመሰግኑልን ዘንድ በአክብሮት እንጨይቃለን!
መልካም አዲስ አመት!😍😍
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
#ሀዋሳን_ማን_ለዚህ_አበቃት| ቀደምቶቹ
#hawassa| By Jone Fikre Berhe
፡፧፡፧፡፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨
(መረጃው ከተለያዩ ሰዎች ያገኘው ነውና የጎደለውን በመሙላት ወይ በማረም ማሟላት ይቻላል።)
1. ራስ መንገሻ ስዩም ከተማዊ ቅርፅ በመስጠት፤
2. የሲዳሞ ክ/ሀገር አስተዳደር ፅ/ቤት፡- አሁን ሳውዝ ስታር የተሰራበት ቦታ የበፊቱ እርሻ ጣቢያ፡፡ እኛን ከእንቅልፋችን የሚቀሰቅስ ሰዓት የነበረበት፡፡
3. የመጀመሪያዎቹ ሆቴሎች ኦሲስ እና ፕላዛ (እኛ ብላዛር ጓሮ የምንለው)
4. የመጀመሪያው ያማረ ሆቴል (አሁን ህንፃ እየተሰራበት ያለ) የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ስፖርት ፅ/ቤት ከዚያም የመንግስት መድሃኒት ቤት ከዚያም ሃቄ ስፖርት የነበረው፡፡
5. የመጀመሪያዎቹ ልብስ ሰፊዎች (አቶ ቤተማሪያም፣ አቶ ድማ ሄይ፣ አቶ ደንቦባ፣ ምንዳዬ አካሉ (ነፍስ ይማር)፣ በኋላ ጌታቸው ቀነዓ፣ ሲሳይ ባህሩ
6. የመጀመሪያዎቹ ሻይና ብስኩት ቤት የጀመሩ፡- ፍቅሬ ሃሰና፣ በቀለ ሀሰና (የነ ዳዊት ዳላስ አባት) ኃይሉ እንግዳወርቅ በኋላም የመጀመሪያው ቡቲክ የከፈተ)
7. ፈረስ ጋሪን ወደ ሃዋሳ ያስገቡና የነዱ፡- ጋሪና የጋሪ እቃዎች ከአዲስ አበባ ይመጣ ነበር፣ አቶ ደበሽ አባሰንጋ፣ አቶ ከፋ ነጋሽ አረብ ሰፈር አካባ የሚኖሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጋሪ በሃዋሳ ማምረት ጀምረዋል፣ ቀጥሎ ፒያሳ አካባ አቶ ሃብቴና ብርሃኑ ብርሃኑ ወልዴ፣ አቶ ወልዴ አሼቦ፣ ያለው አበበ፣ ዳንሴ ምትኩ፣ ይመር ሹሙ፣ አቶ ብርሃኑ
8. በሃዋሳ የመጀመሪያው የሴቶች ፀጉር ቤት አሁን አሚን ህንፃ ያለበት ወ/ሮ ወርቄና(የፒና ሆቴል ባለቤት) በሃዋሳ ታቦር አስተማሪ የነበረችው ወ/ሮ አሚና፣ አቶ ቱፋ ገመቹ፣ አቶ ሰለሞን አበጋዝ፣ አቶ ክንፈ ደንቢ
9. የመጀመሪያዎቹ የሆቴል ባለቤቶች፡- አቶ በቀለ ሞላ፣ አቶ ታረቀኝ ገብሬ(ሹፌሮች ሆቴል) አቶ አማረ ለማ (ያማረ ሆቴል) ቶታል፣ አቶ ኃይለ ጋሼ (ቶታል)፣ እንጆሪ ሆቴል (አቶ ታደሰ እንጆሪ)፣ መስከረም ሆቴል (አቶ ተሰማ) መናኸሪያ ሆቴል፣ ኮከብ ሆቴል፣ ገበሬዎች ሆቴል፣(አቶ አብረሃም) ጆሊ ባር፣ ምድረገነት ሆቴል፣ አንድነት ሆቴል፣ ነጋዴዎች ሆቴል፣ አቶ ድማሙ ሄይ)
10. የወንዶች ፀጉር ቤት አቶ አሰፋ፣ የ10 አለቃ አለሙ ተፈራ (የአፄ ኃይለስላሴ ፀጉር ከርካሚ የነበሩ)፣ አቶ ኤዴማ አላሮ፣ አቶ ተክሌ ጋጋ
11. ሙዚቃ ቤት፡- ሸገር ሙዚቃ ቤት፣ አዋሳ ሙዚቃ ቤት፣ ዙቤር ሙዚቃ ቤት፣ አዲስ ሙዚቃቤት፣ ቤርሙዳ ሙዚቃ ቤት
12. ኬክ ቤት፡- ፒና ኬክ ቤት(ወ/ሮ ወርቄ)፣ ሞሜንቶ (የእምነቴ ቤተሰቦች)
13. ቡቲክ፡- ኃይሉ እንግዳወርቅ፣ መሊ፣ ጀማል
14. ፖስተኛ፡- አቶ ሻንቆ
15. ግሮሰሪ፡- አቶ እስጢፋኖስ፣ አቶ አማረ አጎናፍር፣ አቶ ታደገ ታሪኩ
16. ምግብ ቤት (ወ/ሮ ማሚቴ እምሩ)
17. የመጀመሪያው ደላላ፡- አቶ ዳምጠው
18. ሳይክል ለመጀመሪያ ጊዜ ያስገቡ የሚያድሱና የሚያስነዱ፡አቶ ደለለኝ መኩሪያ፣ አቶ ረጋሳ ጩቃላ፣ አቶ ብሩ ማሞ፣ አቶ ተፈራ አለሙ፣ አቶ አሸብር አወቀ፣
19. ወፍጮ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ያስገቡ፡- አቶ ደንደና ቱፋ፣ አቶ ዘለቃው በለጠ፣ አቶ ሽኩሪ፣ አቶ ጌጡ
20. ሉካንዳ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የከፈቱ፡- አቶ ጩካላ፣ አቶ በረግ፣ አቶ ሽፈራው ሙሚቻ
21. የመጀመሪያዎቹ ከንቲባዎች፡-ባላምበራስ ዘርፉ ዳምጤ፣ አቶ ሙሉጌታ ኃይለስላሴ፣ አቶ ካሳሁን ተፈራ፣ (በሃዋሳ ታቦር መንገድና በአረብ ሰፈር መንገድ ላይ የመንገድ ዛፎችን ያስተከሉ ሰው ናቸው አብዛኛዎቹ ዛፎች በመንገድ ሰበብ የመጥረቢያ ራት ሆነዋል)ራስ መንገሻ ስዩም (ቀያሽ)
22. የመጀመሪያው ገበያ፡- አሁን ቼሜንታል አካባቢ (ጥቁር ውሃ)፣ አሁን ቃጫፋብሪካ አካባቢ(አጨቀቴ) ተብሎም ይጠራ ነበር፡፡ አረብ ሰፈር፣ ከዚያም አሁን ያማረ ሆቴል ፊት ለፊት መናፈሻ ጋ፣ ከዚያም ቶታል ሆቴል የአሁኑ አካባቢ፣ ከዚያም የአሁኑ ሲዳማ ባህል አዳራሽ፣ ከዚያም የአሁኑ ታደሰ እንጆሪ ፖሊስ ክበብ የነበረው አጠገብ፣ አሁን ያለበት ቦታ
23. የመጀመሪያዎቹ ፋብሪካዎች፡- ቃጫ ፋብሪካ፣ ዘይት መጭመቂያ(እርሻ ጣቢያ)፣ ጆጋርዲ ጣልያናዊ የስሚንቶ ውጤቶች ማምረቻ፣ አሁን ቼሜንታል
24. የትምህርት ተቋም፡- ታቦር ትምህርት ቤት (አንደኛ ደረጃ)፣ ቤተክህነት ት/ቤት፣ ከፍተኛ ህዝባዊ ኑሮ እድገት ማሰልጠኛ (የአሁኑ ግብርና ኮሌጅ)፣ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም (የአሁኑ ቲቲሲ)
25. ጅምላ ሸቀጥ ሱቅ፡-አረብ ሰፈር(1958)፣ ሱማሌ ሱቅ፣ መሃመድ ሱቅ፣ መንግስቱ ሱቅ
26. የመጀመሪያዎቹ የእምነት ተቋማት የመጀመሪያዎቹ፡- ገብርኤል (1953)፣ ሙስሊም በዚሁ ዓመት፣ ስላሴ ቤ/ክ፣ አድቬንቲስት፣ መካነ እየሱስ፣ ህይወት ብርሃን
27. የመጀመሪያዎቹ መስሪያ ቤቶች፡- የሃዋሳ ወረዳ ፍርድ ቤት(አሁን የሃዋሳ ንግድ ባንክ ዋና መስሪያቤት ያለበት)
28. የመጀመሪያው ፎቅ፡-በፊት ፊልም ቤት፣ ቀጥሎም የእርዳታ ማስተባሪያ ቢሮ የነበረው፣ የሃዋሳ መስጂድ ጎን የሚገኘው የቀድሞው የቀይሽብር መግረፊያ የሚባለው
29. መጀመሪያዎቹ ፎቶ ቤቶች፡- ግርማ አብቼ(ፒያሳ)፣ በቀለ ወ/ሰንበት (ፒያሳ)፣ ማሞ ወልደሰንበት (ቤርሙዳ ሰፈር)፣
30. ጭፈራ ቤት፡-ዘነበች ሃሰን፣ ማሚቴ እምሩ፣ ስሪ ዶርስ፣ ነጋዴዎች ሆቴል በባንድ የታገዘ ጭፈራ ቤት የነበራቸው(ገበሬዎች ሆቴል)
31. የመጀመሪያዎቹ ጠጅ ቤቶች፡- አቶ ተሾመ በላይነህ፣ አቶ ውብሸት፣ አቶ አሸብር አወቀ (በኋላ ጋይንት ሆቴል) ሳይክል ማከራየትና ማስነዳት የጀመሩ፣ ወ/ሮ ምንትዋብ ግዛው፣ አቶ ታደሰ ገዳ፣ አቶ ተሰማ (ፒያሳ)
32. የመጀመሪያዎቹ አናፂዎች፡- አቶ ወርቁ ያኢ፣ አቶ ወልዴ (ዋርካ አካባ)፣ አቶ ኃለሚካኤል ዋንሰራ፣ ወልደመድህን ዳዲሶ (እነዚህ ሰዎች፡-ቤተ ክህነት፣ ታቦር ትምህርት ቤትን፣ የለኩ ልብስ ስፌት ማህበርን፣ አብዛኛዎቹን የሃዋሳ መኖሪያ ቤቶችን የሰሩ ናቸው፡፡
33. የመጀመሪያዎቹ ግንበኞች፡- አቶ ተክሌ ነጋሽ፣ አቶ ተሸመ መኮንን፣ አቶ እሸቱ አለሙ ፎሌ፣ አቶ ከበደ በሽር፣ አቶ ታፈሰ ተሰማ
ምንጭ፡- ቃል በቃል ጠይቄ ያጠናከርኩት ሲሆን እዚህ ላይ ስማቸው የተጠቀሱ ሰዎች በሕይወት የሌሉ ስለሚበዙበት ነገር ግን ሃዋሳን ሃዋሳ በማድረግ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሰዎች የህሊና ፀሎት አድርጋችሁ እንድታስቧቸው እያሳሰብኩ በህይወት ያሉትን ደግሞ በማመስገን ታሪኩን እንድታስተላልፉ ስል እጠይቃለሁ በዚህ አጋጣሚ መረጃውን ለሰጡኝ፡-
አቶ ተፈራ አለሙ
አቶ በላይ ወጋሶ
አቶ አለማየሁ አበበ
አቶ ወልዴ ባቢሶ
አቶ ሻላሞ ዶያሞን
እድሜያችሁን ያርዝምልኝ እላለሁ የጎደለውን ጨምሩ!
ምንጭ:-
Jonny Fikre Ethiopian
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
መስከረም 2016
#hawassa| By Jone Fikre Berhe
፡፧፡፧፡፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨
(መረጃው ከተለያዩ ሰዎች ያገኘው ነውና የጎደለውን በመሙላት ወይ በማረም ማሟላት ይቻላል።)
1. ራስ መንገሻ ስዩም ከተማዊ ቅርፅ በመስጠት፤
2. የሲዳሞ ክ/ሀገር አስተዳደር ፅ/ቤት፡- አሁን ሳውዝ ስታር የተሰራበት ቦታ የበፊቱ እርሻ ጣቢያ፡፡ እኛን ከእንቅልፋችን የሚቀሰቅስ ሰዓት የነበረበት፡፡
3. የመጀመሪያዎቹ ሆቴሎች ኦሲስ እና ፕላዛ (እኛ ብላዛር ጓሮ የምንለው)
4. የመጀመሪያው ያማረ ሆቴል (አሁን ህንፃ እየተሰራበት ያለ) የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ስፖርት ፅ/ቤት ከዚያም የመንግስት መድሃኒት ቤት ከዚያም ሃቄ ስፖርት የነበረው፡፡
5. የመጀመሪያዎቹ ልብስ ሰፊዎች (አቶ ቤተማሪያም፣ አቶ ድማ ሄይ፣ አቶ ደንቦባ፣ ምንዳዬ አካሉ (ነፍስ ይማር)፣ በኋላ ጌታቸው ቀነዓ፣ ሲሳይ ባህሩ
6. የመጀመሪያዎቹ ሻይና ብስኩት ቤት የጀመሩ፡- ፍቅሬ ሃሰና፣ በቀለ ሀሰና (የነ ዳዊት ዳላስ አባት) ኃይሉ እንግዳወርቅ በኋላም የመጀመሪያው ቡቲክ የከፈተ)
7. ፈረስ ጋሪን ወደ ሃዋሳ ያስገቡና የነዱ፡- ጋሪና የጋሪ እቃዎች ከአዲስ አበባ ይመጣ ነበር፣ አቶ ደበሽ አባሰንጋ፣ አቶ ከፋ ነጋሽ አረብ ሰፈር አካባ የሚኖሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጋሪ በሃዋሳ ማምረት ጀምረዋል፣ ቀጥሎ ፒያሳ አካባ አቶ ሃብቴና ብርሃኑ ብርሃኑ ወልዴ፣ አቶ ወልዴ አሼቦ፣ ያለው አበበ፣ ዳንሴ ምትኩ፣ ይመር ሹሙ፣ አቶ ብርሃኑ
8. በሃዋሳ የመጀመሪያው የሴቶች ፀጉር ቤት አሁን አሚን ህንፃ ያለበት ወ/ሮ ወርቄና(የፒና ሆቴል ባለቤት) በሃዋሳ ታቦር አስተማሪ የነበረችው ወ/ሮ አሚና፣ አቶ ቱፋ ገመቹ፣ አቶ ሰለሞን አበጋዝ፣ አቶ ክንፈ ደንቢ
9. የመጀመሪያዎቹ የሆቴል ባለቤቶች፡- አቶ በቀለ ሞላ፣ አቶ ታረቀኝ ገብሬ(ሹፌሮች ሆቴል) አቶ አማረ ለማ (ያማረ ሆቴል) ቶታል፣ አቶ ኃይለ ጋሼ (ቶታል)፣ እንጆሪ ሆቴል (አቶ ታደሰ እንጆሪ)፣ መስከረም ሆቴል (አቶ ተሰማ) መናኸሪያ ሆቴል፣ ኮከብ ሆቴል፣ ገበሬዎች ሆቴል፣(አቶ አብረሃም) ጆሊ ባር፣ ምድረገነት ሆቴል፣ አንድነት ሆቴል፣ ነጋዴዎች ሆቴል፣ አቶ ድማሙ ሄይ)
10. የወንዶች ፀጉር ቤት አቶ አሰፋ፣ የ10 አለቃ አለሙ ተፈራ (የአፄ ኃይለስላሴ ፀጉር ከርካሚ የነበሩ)፣ አቶ ኤዴማ አላሮ፣ አቶ ተክሌ ጋጋ
11. ሙዚቃ ቤት፡- ሸገር ሙዚቃ ቤት፣ አዋሳ ሙዚቃ ቤት፣ ዙቤር ሙዚቃ ቤት፣ አዲስ ሙዚቃቤት፣ ቤርሙዳ ሙዚቃ ቤት
12. ኬክ ቤት፡- ፒና ኬክ ቤት(ወ/ሮ ወርቄ)፣ ሞሜንቶ (የእምነቴ ቤተሰቦች)
13. ቡቲክ፡- ኃይሉ እንግዳወርቅ፣ መሊ፣ ጀማል
14. ፖስተኛ፡- አቶ ሻንቆ
15. ግሮሰሪ፡- አቶ እስጢፋኖስ፣ አቶ አማረ አጎናፍር፣ አቶ ታደገ ታሪኩ
16. ምግብ ቤት (ወ/ሮ ማሚቴ እምሩ)
17. የመጀመሪያው ደላላ፡- አቶ ዳምጠው
18. ሳይክል ለመጀመሪያ ጊዜ ያስገቡ የሚያድሱና የሚያስነዱ፡አቶ ደለለኝ መኩሪያ፣ አቶ ረጋሳ ጩቃላ፣ አቶ ብሩ ማሞ፣ አቶ ተፈራ አለሙ፣ አቶ አሸብር አወቀ፣
19. ወፍጮ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ያስገቡ፡- አቶ ደንደና ቱፋ፣ አቶ ዘለቃው በለጠ፣ አቶ ሽኩሪ፣ አቶ ጌጡ
20. ሉካንዳ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የከፈቱ፡- አቶ ጩካላ፣ አቶ በረግ፣ አቶ ሽፈራው ሙሚቻ
21. የመጀመሪያዎቹ ከንቲባዎች፡-ባላምበራስ ዘርፉ ዳምጤ፣ አቶ ሙሉጌታ ኃይለስላሴ፣ አቶ ካሳሁን ተፈራ፣ (በሃዋሳ ታቦር መንገድና በአረብ ሰፈር መንገድ ላይ የመንገድ ዛፎችን ያስተከሉ ሰው ናቸው አብዛኛዎቹ ዛፎች በመንገድ ሰበብ የመጥረቢያ ራት ሆነዋል)ራስ መንገሻ ስዩም (ቀያሽ)
22. የመጀመሪያው ገበያ፡- አሁን ቼሜንታል አካባቢ (ጥቁር ውሃ)፣ አሁን ቃጫፋብሪካ አካባቢ(አጨቀቴ) ተብሎም ይጠራ ነበር፡፡ አረብ ሰፈር፣ ከዚያም አሁን ያማረ ሆቴል ፊት ለፊት መናፈሻ ጋ፣ ከዚያም ቶታል ሆቴል የአሁኑ አካባቢ፣ ከዚያም የአሁኑ ሲዳማ ባህል አዳራሽ፣ ከዚያም የአሁኑ ታደሰ እንጆሪ ፖሊስ ክበብ የነበረው አጠገብ፣ አሁን ያለበት ቦታ
23. የመጀመሪያዎቹ ፋብሪካዎች፡- ቃጫ ፋብሪካ፣ ዘይት መጭመቂያ(እርሻ ጣቢያ)፣ ጆጋርዲ ጣልያናዊ የስሚንቶ ውጤቶች ማምረቻ፣ አሁን ቼሜንታል
24. የትምህርት ተቋም፡- ታቦር ትምህርት ቤት (አንደኛ ደረጃ)፣ ቤተክህነት ት/ቤት፣ ከፍተኛ ህዝባዊ ኑሮ እድገት ማሰልጠኛ (የአሁኑ ግብርና ኮሌጅ)፣ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም (የአሁኑ ቲቲሲ)
25. ጅምላ ሸቀጥ ሱቅ፡-አረብ ሰፈር(1958)፣ ሱማሌ ሱቅ፣ መሃመድ ሱቅ፣ መንግስቱ ሱቅ
26. የመጀመሪያዎቹ የእምነት ተቋማት የመጀመሪያዎቹ፡- ገብርኤል (1953)፣ ሙስሊም በዚሁ ዓመት፣ ስላሴ ቤ/ክ፣ አድቬንቲስት፣ መካነ እየሱስ፣ ህይወት ብርሃን
27. የመጀመሪያዎቹ መስሪያ ቤቶች፡- የሃዋሳ ወረዳ ፍርድ ቤት(አሁን የሃዋሳ ንግድ ባንክ ዋና መስሪያቤት ያለበት)
28. የመጀመሪያው ፎቅ፡-በፊት ፊልም ቤት፣ ቀጥሎም የእርዳታ ማስተባሪያ ቢሮ የነበረው፣ የሃዋሳ መስጂድ ጎን የሚገኘው የቀድሞው የቀይሽብር መግረፊያ የሚባለው
29. መጀመሪያዎቹ ፎቶ ቤቶች፡- ግርማ አብቼ(ፒያሳ)፣ በቀለ ወ/ሰንበት (ፒያሳ)፣ ማሞ ወልደሰንበት (ቤርሙዳ ሰፈር)፣
30. ጭፈራ ቤት፡-ዘነበች ሃሰን፣ ማሚቴ እምሩ፣ ስሪ ዶርስ፣ ነጋዴዎች ሆቴል በባንድ የታገዘ ጭፈራ ቤት የነበራቸው(ገበሬዎች ሆቴል)
31. የመጀመሪያዎቹ ጠጅ ቤቶች፡- አቶ ተሾመ በላይነህ፣ አቶ ውብሸት፣ አቶ አሸብር አወቀ (በኋላ ጋይንት ሆቴል) ሳይክል ማከራየትና ማስነዳት የጀመሩ፣ ወ/ሮ ምንትዋብ ግዛው፣ አቶ ታደሰ ገዳ፣ አቶ ተሰማ (ፒያሳ)
32. የመጀመሪያዎቹ አናፂዎች፡- አቶ ወርቁ ያኢ፣ አቶ ወልዴ (ዋርካ አካባ)፣ አቶ ኃለሚካኤል ዋንሰራ፣ ወልደመድህን ዳዲሶ (እነዚህ ሰዎች፡-ቤተ ክህነት፣ ታቦር ትምህርት ቤትን፣ የለኩ ልብስ ስፌት ማህበርን፣ አብዛኛዎቹን የሃዋሳ መኖሪያ ቤቶችን የሰሩ ናቸው፡፡
33. የመጀመሪያዎቹ ግንበኞች፡- አቶ ተክሌ ነጋሽ፣ አቶ ተሸመ መኮንን፣ አቶ እሸቱ አለሙ ፎሌ፣ አቶ ከበደ በሽር፣ አቶ ታፈሰ ተሰማ
ምንጭ፡- ቃል በቃል ጠይቄ ያጠናከርኩት ሲሆን እዚህ ላይ ስማቸው የተጠቀሱ ሰዎች በሕይወት የሌሉ ስለሚበዙበት ነገር ግን ሃዋሳን ሃዋሳ በማድረግ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሰዎች የህሊና ፀሎት አድርጋችሁ እንድታስቧቸው እያሳሰብኩ በህይወት ያሉትን ደግሞ በማመስገን ታሪኩን እንድታስተላልፉ ስል እጠይቃለሁ በዚህ አጋጣሚ መረጃውን ለሰጡኝ፡-
አቶ ተፈራ አለሙ
አቶ በላይ ወጋሶ
አቶ አለማየሁ አበበ
አቶ ወልዴ ባቢሶ
አቶ ሻላሞ ዶያሞን
እድሜያችሁን ያርዝምልኝ እላለሁ የጎደለውን ጨምሩ!
ምንጭ:-
Jonny Fikre Ethiopian
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
መስከረም 2016