ብዙ ብዙ ማለት እፈልጋለሁ...አሁን ግን አልችልም። ጅማሮው ላይ የተገኛችሁልኝ ሁሉ ውለታችሁ አለብኝ። ድጋፋችሁን ወድጄዋለሁ፣ መኖራችሁ ቀና እንድል አድርጎኛል። ክበሩልኝ!🙏
በመጨረሻም. . . .
ከአራት መንፈቀ-ዓመታት በላይ የለፋሁበት ሦስተኛው መጽሐፌ በትናንትናው ዕለት በተዘጋጀው የሊቀ-ቀንበር የወግ ድግስ ላይ ይፋ ኾኗል። ምናባዊ-ልቦለዶች(fantasies) በብዛት ያካተተው ይኽ ሥራ በቅድመ-ክፍያ የሚገዙትን ሦስት መቶ ሰዎች ይጠብቃል። በትናንትናው መድረክ የተወሰኑ ሰዎች አስቀድመው በመግዛት ወደ ህትመት ቤት የሚያደርገውን ጉዞ አስጀምረውታል። ሦስት መቶ ሰዎችን እንደማላጣ ተስፋ በማድረግ እነሆ በማህበራዊ ገጾችም ላይ ይፋ አድርጌዋለሁ። የአንዱ መጽሐፍ ዋጋ 500 ብር ብቻ ነው!
1000413125654 -Feysel Mohammed
የገዛችሁ ስክሪንሾት በማድረግ ላኩልኝ መጽሐፉ እንደታተመ በቅድሚያ ለእናንተ ይሠጣል!
#ሰንባች
.
@huluezih
@huluezih
ከአራት መንፈቀ-ዓመታት በላይ የለፋሁበት ሦስተኛው መጽሐፌ በትናንትናው ዕለት በተዘጋጀው የሊቀ-ቀንበር የወግ ድግስ ላይ ይፋ ኾኗል። ምናባዊ-ልቦለዶች(fantasies) በብዛት ያካተተው ይኽ ሥራ በቅድመ-ክፍያ የሚገዙትን ሦስት መቶ ሰዎች ይጠብቃል። በትናንትናው መድረክ የተወሰኑ ሰዎች አስቀድመው በመግዛት ወደ ህትመት ቤት የሚያደርገውን ጉዞ አስጀምረውታል። ሦስት መቶ ሰዎችን እንደማላጣ ተስፋ በማድረግ እነሆ በማህበራዊ ገጾችም ላይ ይፋ አድርጌዋለሁ። የአንዱ መጽሐፍ ዋጋ 500 ብር ብቻ ነው!
1000413125654 -Feysel Mohammed
የገዛችሁ ስክሪንሾት በማድረግ ላኩልኝ መጽሐፉ እንደታተመ በቅድሚያ ለእናንተ ይሠጣል!
#ሰንባች
.
@huluezih
@huluezih
አላውቅበትም!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ዘመኑ ግሪምቢጥ፤
ተጋግሮ እንደ ሊጥ!
የኋሊት ኾነና ነፍስ እያስነገደ፤
አያልፍለትም ማንም ለሰው ካልሰገደ!
.
ከፍ ብል በእሱ ነው፣
ዝቅም ብል ለአምላኬ፤
ሰው አክብሬ ነው እንጂ. . .
አላውቅም አምልኬ!
.
ተነጥሎ ቆሞ ይፋለማል ልቤ፤
ከዘመኑ አይደለም፣ከሰው ጋር ነው ፀቤ!
.
ይደናገረኛል!
በውሰት ሕሊና ፣አስልቶ መደምደም፣
ስለማልችልበት፣እየጣሉ መቅደም፤
ከውሻ አሳንሰው፣ነፈጉኝ ዕድሉን፣
ስለማላውቅበት ጭራ አቆላሉን!
.
ጥቅስ እያጣቀሱ፣
ቃለ-አምላክ እያነሱ፣
ቢሰብኩም ታግዘው፣ በሳይንስ በፈለክ፤
አንድ ኾነው አያውቁም
"ማክበር" እና "ማምለክ"!
.
@huluezih
@huluezih
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ዘመኑ ግሪምቢጥ፤
ተጋግሮ እንደ ሊጥ!
የኋሊት ኾነና ነፍስ እያስነገደ፤
አያልፍለትም ማንም ለሰው ካልሰገደ!
.
ከፍ ብል በእሱ ነው፣
ዝቅም ብል ለአምላኬ፤
ሰው አክብሬ ነው እንጂ. . .
አላውቅም አምልኬ!
.
ተነጥሎ ቆሞ ይፋለማል ልቤ፤
ከዘመኑ አይደለም፣ከሰው ጋር ነው ፀቤ!
.
ይደናገረኛል!
በውሰት ሕሊና ፣አስልቶ መደምደም፣
ስለማልችልበት፣እየጣሉ መቅደም፤
ከውሻ አሳንሰው፣ነፈጉኝ ዕድሉን፣
ስለማላውቅበት ጭራ አቆላሉን!
.
ጥቅስ እያጣቀሱ፣
ቃለ-አምላክ እያነሱ፣
ቢሰብኩም ታግዘው፣ በሳይንስ በፈለክ፤
አንድ ኾነው አያውቁም
"ማክበር" እና "ማምለክ"!
.
@huluezih
@huluezih
አዝናለሁ አልወደቅኩም!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
አንድ ኀሙስ እንደቀረው፣
የብሶት ዜማ የማንጎራጉረው፤
ስለጠፋኝ አይደለም. . .
መንገድ ስለቀረሁ!
ቀናነት ሳይከብድ፣
መኾን ሲቻል መልካም፤
ተንኮል ለመጎንጎን፣
ለደከሙት ድካም. . .
"እሪ!ኩም! ዘመዳ!
"ዘመዳ እሪ!ኩም!"
እኔ ግን. . .
አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
እበቅላለሁ እያልኩ. . .
በአፍ-ጢሜ ስተከል፤
ማቆጥቆጥ ሲመስለኝ፣
ከሥሬ መነቀል፤
ከአረም ጋራ ኾነ. . .
የእኔ አበቃቀል!
ሆድ ባይብሰኝም. . .
"እሪ!ኩም! ዘመዳ!
ዘመዳ እሪ!ኩም!"
አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
ግፊያና ግፍተራ የፍቅር መሰለኝ፤
እኔ እንደሁ' ስወድ. . .
ወትሮም ዓይን የለኝ!
ዝቅ ማለት ጎዳኝ፣
መች ዐውቃለሁ ብልጠት?
ላከበርኩት ሁሉ፣ማጅራቴን መሥጠት!
ሰው ነኝና. . .ተጓዥ!
መንገድ ነውና... ጎዝጓዥ!
ሞክሬ. . ዳክሬ. . .
ከጭቃ ውስጥ እሾህ አላመለጥኩም፤
ግን አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
የሌላውን ወድቀት አስበልጦ 'ሚሻው፤
ካቲማው አያምርም ዳሩ መጨረሻው፤
ብትካኑበትም...አጣጣል ብታውቁም፤
አዝናለሁ አልወደቅኩም!
.
@huluezih
@huluezih
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
አንድ ኀሙስ እንደቀረው፣
የብሶት ዜማ የማንጎራጉረው፤
ስለጠፋኝ አይደለም. . .
መንገድ ስለቀረሁ!
ቀናነት ሳይከብድ፣
መኾን ሲቻል መልካም፤
ተንኮል ለመጎንጎን፣
ለደከሙት ድካም. . .
"እሪ!ኩም! ዘመዳ!
"ዘመዳ እሪ!ኩም!"
እኔ ግን. . .
አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
እበቅላለሁ እያልኩ. . .
በአፍ-ጢሜ ስተከል፤
ማቆጥቆጥ ሲመስለኝ፣
ከሥሬ መነቀል፤
ከአረም ጋራ ኾነ. . .
የእኔ አበቃቀል!
ሆድ ባይብሰኝም. . .
"እሪ!ኩም! ዘመዳ!
ዘመዳ እሪ!ኩም!"
አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
ግፊያና ግፍተራ የፍቅር መሰለኝ፤
እኔ እንደሁ' ስወድ. . .
ወትሮም ዓይን የለኝ!
ዝቅ ማለት ጎዳኝ፣
መች ዐውቃለሁ ብልጠት?
ላከበርኩት ሁሉ፣ማጅራቴን መሥጠት!
ሰው ነኝና. . .ተጓዥ!
መንገድ ነውና... ጎዝጓዥ!
ሞክሬ. . ዳክሬ. . .
ከጭቃ ውስጥ እሾህ አላመለጥኩም፤
ግን አዝናለሁ! አልወደቅኩም!
.
የሌላውን ወድቀት አስበልጦ 'ሚሻው፤
ካቲማው አያምርም ዳሩ መጨረሻው፤
ብትካኑበትም...አጣጣል ብታውቁም፤
አዝናለሁ አልወደቅኩም!
.
@huluezih
@huluezih