የማለዳ ማስታወሻ #150
.
በልብ እና በአዕምሮ ጦርነት መሐል ነው የምንኖረው። ልባችን የከጀለው ነገር፣ አዕምሯችን ከሚያውቀው እውነታ ጋር ሳይጣጣም ሲቀር የውስጣችን ሰላም ይደፈርሳል። አዕምሮ የመረጠው መንገድ የልባችንን መሻት እና ምኞት ስለሚሸርፍ የሚያቅበዘብዝ የልብ ምታት ውስጣችንን ያውካል። እንዲህ ነው የምንኖረው። እንዲህ ኾኖ መኖር ታዲያ ራስን አያስመሠግንም? ራስን አያስከብርም? "አሻም" አያስብልም? እኔ ራሴን "አሻም" እላለሁ!
.
ልቤ ተቀብሎት፣ ነፍስያዬ ከጅሎት ሩቅ እንደማያስኬደኝ ዐውቄ ልቤን ተጭኜ አዕምሮዬን ስለሰማሁት፣ ሰምቼም ቅር እየተሠኘሁ አቅጫዬን ስለለወጥኩ፣ በዛሬ ምቾትና ተድላ ነገዬን ስላልቀየርኩ. . "አሻም!" ለራሴ!
.
እንባዎች ቢረብሹኝም መንገድ ስላላሳቱኝ፣ ከራሴም አሻግሬ ለሰዎች ነገ ስል ራሴን ስለገደብኩ፤ ባላየሁት ቃል ላይ፣ ባልጣመኝ መስክ ላይ ጎጆ ስላልቀለስኩ፣ ልቤን ተጭኜ በአዕምሮዬ ስሌት ያለ እረፍት ጉዞዬን ስለቀጠልኩ. . ."አሻም!" ለራሴ!
.
ልቤን ያቆሰሉኝን እግሬ ሥር አግኝቼ ስላልተበቀልኩ፣ በገረፉኝ ጅራፍ ጎትቼ ከገደል ስላወጣኋቸው፣ የዋሹኝን ስላልዋሸሁ፣ የወጉኝን ስላከምኩ፣ ልቤን ሰምቼ ሒሳብ አወራራጅ አዕምሮዬን ተጭኜ የራቁኝን ባሉበት ደግ ስለተመኘሁላቸው፣ የጣሉኝን ስላነሣሁ . . "አሻም!" ለራሴ!
.
ግን አንዳንዴ. . . ሁሉም በጊዜው ቢኾንም... ያንን ትክክለኛ ጊዜ ሳላውቅ. . . "ልቤን? ወይስ አዕምሮዬን?" የቱን መከተል እንዳለብኝ ሳልወስን ለደፈርኩት አጥር፣ ለነካሁት ቁስል፣ ላስመሸሁት ትልም፣ ላደፈረስኩት እውነት፣ ላረፈድኩት ጥሪ፣ ላከሰምኩት ተስፋ፣ ላላላሁት ውጥን አዕምራችሁን ተጭናችሁ በልባችሁ፣ከልባችሁ ለሠጣችሁኝ "ይቅርታ" "አሻም!" ለእናንተ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
.
በልብ እና በአዕምሮ ጦርነት መሐል ነው የምንኖረው። ልባችን የከጀለው ነገር፣ አዕምሯችን ከሚያውቀው እውነታ ጋር ሳይጣጣም ሲቀር የውስጣችን ሰላም ይደፈርሳል። አዕምሮ የመረጠው መንገድ የልባችንን መሻት እና ምኞት ስለሚሸርፍ የሚያቅበዘብዝ የልብ ምታት ውስጣችንን ያውካል። እንዲህ ነው የምንኖረው። እንዲህ ኾኖ መኖር ታዲያ ራስን አያስመሠግንም? ራስን አያስከብርም? "አሻም" አያስብልም? እኔ ራሴን "አሻም" እላለሁ!
.
ልቤ ተቀብሎት፣ ነፍስያዬ ከጅሎት ሩቅ እንደማያስኬደኝ ዐውቄ ልቤን ተጭኜ አዕምሮዬን ስለሰማሁት፣ ሰምቼም ቅር እየተሠኘሁ አቅጫዬን ስለለወጥኩ፣ በዛሬ ምቾትና ተድላ ነገዬን ስላልቀየርኩ. . "አሻም!" ለራሴ!
.
እንባዎች ቢረብሹኝም መንገድ ስላላሳቱኝ፣ ከራሴም አሻግሬ ለሰዎች ነገ ስል ራሴን ስለገደብኩ፤ ባላየሁት ቃል ላይ፣ ባልጣመኝ መስክ ላይ ጎጆ ስላልቀለስኩ፣ ልቤን ተጭኜ በአዕምሮዬ ስሌት ያለ እረፍት ጉዞዬን ስለቀጠልኩ. . ."አሻም!" ለራሴ!
.
ልቤን ያቆሰሉኝን እግሬ ሥር አግኝቼ ስላልተበቀልኩ፣ በገረፉኝ ጅራፍ ጎትቼ ከገደል ስላወጣኋቸው፣ የዋሹኝን ስላልዋሸሁ፣ የወጉኝን ስላከምኩ፣ ልቤን ሰምቼ ሒሳብ አወራራጅ አዕምሮዬን ተጭኜ የራቁኝን ባሉበት ደግ ስለተመኘሁላቸው፣ የጣሉኝን ስላነሣሁ . . "አሻም!" ለራሴ!
.
ግን አንዳንዴ. . . ሁሉም በጊዜው ቢኾንም... ያንን ትክክለኛ ጊዜ ሳላውቅ. . . "ልቤን? ወይስ አዕምሮዬን?" የቱን መከተል እንዳለብኝ ሳልወስን ለደፈርኩት አጥር፣ ለነካሁት ቁስል፣ ላስመሸሁት ትልም፣ ላደፈረስኩት እውነት፣ ላረፈድኩት ጥሪ፣ ላከሰምኩት ተስፋ፣ ላላላሁት ውጥን አዕምራችሁን ተጭናችሁ በልባችሁ፣ከልባችሁ ለሠጣችሁኝ "ይቅርታ" "አሻም!" ለእናንተ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
እናትነት የወለዱትን ማሳደግ ብቻ አይደለም!
.
አሳም በተባለ የሕንድ ቀበሌ ውስጥ አንድ ሰው ከአንድ ወዳጁ ላም ይገዛል።ላሟ ከተገዛች በኋላ ግን በአካባቢው ያልተለመደ እና የበረከተ የውሻ ጩኸት ገዢውን ሰውዬ አላስተኛ አለው። ምክንያቱን ማጣራት አለብኝ በማለት ሰውዬ ላሟ ያለችበት ሥፍራ ላይ ካሜራ ገጠመ። ከካሜራው ያገኘው ምስል ግን የማይታመን ነበር።
.
ዘወትር በሌሊቱ አጋማሽ አንድ ነብር ወደ ላሟ ይመጣና ሰላምታ ሠጥቶ፣ግንባሯን ልሶ ሥሯ ይወሸቃል። ላሟም ሥሯ አስቀምጣው ፀጉሩን ትልሳለች። ሌሊቱ ሊያልቅ ጥቂት ሲቀረው፣ ሰዎች የእንቅልፋቸው ማገባደጃ ላይ ሲደርሱ ነብሩ ላሟን በስስት ተሰናብቶ ወደ ጫካው ገብቶ ይሰወራል።
.
በዚህ የተገረመው የላሟ ገዢ ላሟን የሸጠለት ሰው ጋር ሔዶ ነገሩን ይነግረዋል። ሻጩ የነገረው ታሪክ አስደናቂ ነው።
.
የነብሩ እናት በሰዎች ስትገደል ይኽ ነብር ገና የ20 ቀን ዕድሜ ያለው ጨቅላ ነበር።ታዲያ ይኽች የእናት አንጀት የታደለች ላም የጡቷን ወተት እየሠጠች ሕይወቱን እንዲተርፍ ሰበብ ኾነችው።እናት ላጣ ነብር እናት ኾና ክፉ ቀኑን አሳለፈችለት። ዛሬ አድጎ፣ ጡንቻውን አፈርጥሞ ጫካ ቢገባም በእያንዳንዷ ሌሊት የላሟን ጠረን ተከትሎ እየመጣ ባለውለታውን ያመሠግናል። ዐየህ! እናት መኾን ማለት የወለዱትን ብቻ ማሳደግ አይደለም። እናት ለሚፈልግ ኹሉ እናት መኾን ማለትም ጭምር ነው!
.
@huluezih
@huluezih
.
አሳም በተባለ የሕንድ ቀበሌ ውስጥ አንድ ሰው ከአንድ ወዳጁ ላም ይገዛል።ላሟ ከተገዛች በኋላ ግን በአካባቢው ያልተለመደ እና የበረከተ የውሻ ጩኸት ገዢውን ሰውዬ አላስተኛ አለው። ምክንያቱን ማጣራት አለብኝ በማለት ሰውዬ ላሟ ያለችበት ሥፍራ ላይ ካሜራ ገጠመ። ከካሜራው ያገኘው ምስል ግን የማይታመን ነበር።
.
ዘወትር በሌሊቱ አጋማሽ አንድ ነብር ወደ ላሟ ይመጣና ሰላምታ ሠጥቶ፣ግንባሯን ልሶ ሥሯ ይወሸቃል። ላሟም ሥሯ አስቀምጣው ፀጉሩን ትልሳለች። ሌሊቱ ሊያልቅ ጥቂት ሲቀረው፣ ሰዎች የእንቅልፋቸው ማገባደጃ ላይ ሲደርሱ ነብሩ ላሟን በስስት ተሰናብቶ ወደ ጫካው ገብቶ ይሰወራል።
.
በዚህ የተገረመው የላሟ ገዢ ላሟን የሸጠለት ሰው ጋር ሔዶ ነገሩን ይነግረዋል። ሻጩ የነገረው ታሪክ አስደናቂ ነው።
.
የነብሩ እናት በሰዎች ስትገደል ይኽ ነብር ገና የ20 ቀን ዕድሜ ያለው ጨቅላ ነበር።ታዲያ ይኽች የእናት አንጀት የታደለች ላም የጡቷን ወተት እየሠጠች ሕይወቱን እንዲተርፍ ሰበብ ኾነችው።እናት ላጣ ነብር እናት ኾና ክፉ ቀኑን አሳለፈችለት። ዛሬ አድጎ፣ ጡንቻውን አፈርጥሞ ጫካ ቢገባም በእያንዳንዷ ሌሊት የላሟን ጠረን ተከትሎ እየመጣ ባለውለታውን ያመሠግናል። ዐየህ! እናት መኾን ማለት የወለዱትን ብቻ ማሳደግ አይደለም። እናት ለሚፈልግ ኹሉ እናት መኾን ማለትም ጭምር ነው!
.
@huluezih
@huluezih
❤1
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
በሰው ያለኝ ተስፋ፣
ከምድር ሊጠፋ፣
የመኖር ጉጉቴ ባዶ እጄን ሊያስቀረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ሁሉን ውጦ መቻል፣
ሁሌም ይሰለቻል፣
የሞት ሞት ትግሌ፣"በቃ"ን ሊያስጀምረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ክቦ ክቦ ማፍረስ፣
አፍርሶ መቀለስ፣
በልቤ መጫወት፣ከኮሶ መረረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ሔጄ ሔጄ ጨቅላ፣
ዞሬ እምቦቀቅላ፣
ሳልኖረው ያለቀው፣ልጅነት አማረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
መብሰክሰክ. . .
መብሰልሰል. . .
ቀመርና ስሌት፣ሳስበው ቀለለኝ፤
"ትንሽ ነው" ያልኩትም. . .
ብዙ ነው መሰለኝ!
.
@huluezih
@huluezih
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
በሰው ያለኝ ተስፋ፣
ከምድር ሊጠፋ፣
የመኖር ጉጉቴ ባዶ እጄን ሊያስቀረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ሁሉን ውጦ መቻል፣
ሁሌም ይሰለቻል፣
የሞት ሞት ትግሌ፣"በቃ"ን ሊያስጀምረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ክቦ ክቦ ማፍረስ፣
አፍርሶ መቀለስ፣
በልቤ መጫወት፣ከኮሶ መረረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
ሔጄ ሔጄ ጨቅላ፣
ዞሬ እምቦቀቅላ፣
ሳልኖረው ያለቀው፣ልጅነት አማረኝ፤
ትንሽ ነው የቀረኝ!
.
መብሰክሰክ. . .
መብሰልሰል. . .
ቀመርና ስሌት፣ሳስበው ቀለለኝ፤
"ትንሽ ነው" ያልኩትም. . .
ብዙ ነው መሰለኝ!
.
@huluezih
@huluezih
እችልበታለሁ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
በርግጥ ጉራ አይደለም. . .
ግን. . .ያላየሁት የለም!
ከሕይወት ተምሬያለሁ. . .
ለክቶ መወሰን፣
እችልበታለሁ!
ስሕተትና ጊዜ ከከተቱኝ እሣት፤
ሳልከስል መነሣት፣
በጎዶሎ ስሜት ላይ. . .
በትክክል መሳሳት!
እችልበታለሁ!
.
አንቺም ብትሔጂ. . .
እርግጠኛ ነኝ፣ልቤን እንደማደነድን፣
ሔደሽ ሳትጨርሺ፣ቆስዬ እንደምድን፣
አዎ! እርግጠኛ ነኝ!
በመብረቅ ፍጥነት፣
በብርሃን ፍጥነት፣እንደማገግም፣
ቢኾንም. . .
ቢኾንም. . .
ላጣሽ አልፈልግም!
.
@huluezih
@huluezih
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
በርግጥ ጉራ አይደለም. . .
ግን. . .ያላየሁት የለም!
ከሕይወት ተምሬያለሁ. . .
ለክቶ መወሰን፣
እችልበታለሁ!
ስሕተትና ጊዜ ከከተቱኝ እሣት፤
ሳልከስል መነሣት፣
በጎዶሎ ስሜት ላይ. . .
በትክክል መሳሳት!
እችልበታለሁ!
.
አንቺም ብትሔጂ. . .
እርግጠኛ ነኝ፣ልቤን እንደማደነድን፣
ሔደሽ ሳትጨርሺ፣ቆስዬ እንደምድን፣
አዎ! እርግጠኛ ነኝ!
በመብረቅ ፍጥነት፣
በብርሃን ፍጥነት፣እንደማገግም፣
ቢኾንም. . .
ቢኾንም. . .
ላጣሽ አልፈልግም!
.
@huluezih
@huluezih