Telegram Web Link
በ44ኛው የሰበካ አጠቃላይ ጉባኤ ማኅበረ ቅዱሳን በተለያዩ አኅጉረ ስበከቶች በ2017 ዓ.ም የሠራቸው ሥራዎች ሪፖርት ቀረበ።

ማኅበሩ ከ41ሺ በላይ አዳዲስ አማኒያንን ማስጠመቁ የተገለጸ ሲሆን በካህናት እጥረት የተዘጉ 34 አብያተ ክርስቲያናት ካህናት በመቅጠር አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን ተገልጿል።

ማኅበረ ቅዱሳን በዩኒቨርሲቲና በኮሌጆች በሚሰጠው አገልግሎት ከ200ሺ በላይ የግቢ ጉበኤ ተማሪዎችን በሀገር ዉስጥና በውጭ ሀገራት በተለያዩ ቋንቋዎች እያስተማረ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 27,524 ተማሪዎች ደግሞ ባላቸው ሙያ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግሉ መሰማራታቸው ተገልጿል።

ሪፖርቱ 8418 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን የአብነት ትምህርት  በማስተማር 146ቱ ሥልጣነ ክህነት አንዲቀበሉ ማድረጉንም ጠቅሷል።

ማኅበሩ በሚሰጠው የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ከ41ሺ በላይ አዳዲስ አማኒያንን ማስጠመቁ የተገለጸ ሲሆን በካህናት እጥረት የተዘጉ 34 አብያተ ክርስቲያናት ካህናት በመቅጠር አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን ተገልጿል።

በስበከተ ወንጌልና በሐዋርያዊ አገልግሎት 58,673,518,00 ብር ወጪ በማድረግ 31 መጽሐፍትን በ94,544 ቅጅ በተለያዩ ቋንቋዎች አሳትሞ አሰራጭቷል።
3
በ173 የአብነት ትምህርተ ቤት ለሚገኙ ትምህርተ ቤቶች 239 መምህራንና ለ2,220 ደቀ መዛሙርት 10,713,090,00 ብር ወጪ በማድረግ ወርኃዊ ድጎማ አድርጓል።

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት በ44ተኛው የሰባካ አጠቃላይ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሪፖርት በአባ ጊዎርጊስ ዘ ጋስጫ በሚሰጠው ነጻ የትምህር እድል 37 ተማሪዎችን በማስተማር 427,945,00 ብር ወጪ በማድረግ ድጎማ ያደረገ ሲሆን በሀገራችን በተከሰተ ወቅታዊ ችግር ምክንያት በትግራይና በሌሎች አካባቢ ለሚገኙ ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች 6,834,100,00 ድጋፍ ተደርጓል ተብሏል።

በአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት 8,870,407 ብር፣ በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት 23,021,025 ብር፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ቡኖ በደሌ ሀገረ ስበከት 16,671,804, ,53 ብር ወጪ በማድረግ የአብነት ትምህርት ቤቶችና የገዳማት ገቢ ማስገኛ ሕንጻዎችን ማስገንባቱ በ44ተኛው የሰባካ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሦስቱም ግቢያት አዲስ ተማሪዎች አቀባበል መደረጉን ተገለጸ

ጥቅምት ፯/፳፻፲፰ ዓ. ም

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአራት ኪሎ ፣ የአምስት ኪሎ እና የስድስት ኪሎ ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች አቀባበል መደረጉን ተገልጿል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በግቢ ጉባኤ አገልግሎት ንቁ ተሳታፊ በመሆን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው መጠንከር እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

በአቀባበል ዝግጅቱ  ላይ የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ምክትል ሰብሳቢ አቶ በረከት መሠረት መልእክት ያስተላፉ ሲሆን በመልእክታቸው ተማሪዎች በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት ጠንክረው መማር እንደሚገባቸው ጠቁመው ከመጡበት ዓላማ አንጻር በአስኳላ ትምህርታቸው በመረዳዳት፣ አብሮ በማጥናት፣ የደከሙትን በማበርታት በወንድማማችነትና እኅትማማችነት መንፈስ ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ጠንክረው መሥራት አለባቸው ብለዋል።

ምክትል ሰብሳቢው አክለውም ከፀረ- ሃይማኖት እና ከፀረ-ባህል አስተሳሰቦች፣ ጠባያት እና ድርጊቶች በመራቅ ራሳቸውን እነዚህ ከሚያስከትሏቸው መጥፎ ውጤቶች ማለትም ከበሽታ፣ ከሱሰኝነት፣ ከዘረኝነት፣ ከዓለማዊነት በአጠቃላይ ክፉ ጓደኝነት እና የማኅበራዊ ሚዲያ አለአግባብ መጠቀም ከሚያመጣቸው አሉታዊ ተጽእኖዎች መራቅ እንደሚገባቸው መክረዋል።

በአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ እግር የማጠብ መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን ጸሎተ ወንጌል ፣ መዝሙር ፣ ቅኔ እና የጋራ ወረብ የቀረበ ሲሆን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ለተማሪዎቹ ትምህርት ሰጥተዋል።

ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ "በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻ አወጣን!" በሚል  ርእስ ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን በዚህም ርእሰ ጉዳይ በመመርኮዝ  ተማሪዎች ክርስቶስ በሰጠው ነጻ ፈቃድ ውስጥ በመሆን በአገልግሎት ሊተጉ እንደሚገባ በትምህርታቸው አንስተዋል።
3
የነጻነት ምንጩ እግዚአብሔር መሆኑን አውስተው በዚህም የሰው አፈጣጠር መሠረቱ በእግዚአብሔር አምሳልና አረአያ በነጻነት የተፈጠረ በመሆኑ ይህን ነጻነት ለመጠበቅ ለክርስትና ሕይወት በትጋት መሥራት እንደሚገባ በትምህርታቸው አብራርተዋል።

በዚህም እግዚአብሔር ነጻ አድርጎ የፈጠረን ትእዛዛቱን በፈቃዳችንና በፍቅር እንድናደርገው ስለሚገባ ነው ብለዋል።

እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ በመሆኑ ነጻነታችንን ተጠቅመን ተገቢውን ኀላፊነት በመወጣት በክርስትና ሕይወት ለመኖር በርትተን መሥራት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።

የእግዚአብሔር በመሆንና ክርስቶስን በመምሰል በብርቱ በመሥራት እና ቤተክርስቲያንን በማገልገል በትምህርታችን ብሎም በሕይወታችን ስኬትን መጎናጸፍ ይገባል ብለዋል።

እንዲሁም በተመሳሳይ የማኅበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል፣ ወሊሶ ማእከልና ሌሎች ማእከላት ለአዲስ ተማሪዎች አቀባበል አድርገዋል።👇👇👇👇👇👇👇
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://www.tg-me.com/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
:- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905
3
ማኅበረ ቅዱሳን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተረጎመውን "መጽሐፈ ግንዘት" እና "የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ ሁለት" መጻሕፍትን ሊያስመርቅ መሆኑን ገለጸ

ጥቅምት ፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተረጎመውን "መጽሐፈ ግንዘት" እና "የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ ሁለት" መጻሕፍትን ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በዋናው ማእከል ሕንጻ 3ተኛ ወለል ንቡረ እድ ድሜጥሮስ አዳራሽ ሊያስመርቅ መሆኑን ገልጿል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳት፣ መምህራነ ወንጌል፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ተጋባዥ እንግዶችና ምእመናን እንደሚገኙ ተመላክቷል።

በማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋም አስተዳደር የግዢና አቅርቦት መምሪያ ሥራ አስኪያጅ ቀሲስ አእምሮ ይሄይስ "መጽሐፈ ግንዘት" ከቤተ ክርስቲያናችን የጸሎት መጻሕፍት መካከል አንዱ የግእዝ ጸሎት መጽሐፍ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን ከሁለት ዓመት በፊት ወደ አማርኛ እንዲተረጎም ፕሮጀክት ቀርጾ በመሥራትና በማስተርጎም ለምርቃት እንዲበቃ ማድረጉን ገልጸዋል።

መጽሐፉ ለካህናት አገልግሎት በሚመች መልኩ ተሟልቶ የተዘጋጀ እንደሆነም ተናግረዋል።

በተጨማሪም የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ አንድ ከዚህ በፊት የተተረጎመ መሆኑን ገልጸው በነገው ዕለት ቅጽ ሁለት ትርጉምም እንደሚመረቅ ተናግረዋል።

በመጨረሻም ሥራ አስኪያጁ በምርቃት መርሐ ግብሩ ከላይ የተጠቀሱት ሁሉም ተጋባዦች እንዲገኙ መልእክት አስተላልፈዋል።

መጻሕፍቱን በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይና በሁሉም በማኅበሩ ሱቆች እንዲሁም በማእከላት ማግኘት እንደሚቻል ተጠቁሟል።
10
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes

https://www.tg-me.com/addlist/uBADfbTups5hY2Q0
https://www.tg-me.com/addlist/uBADfbTups5hY2Q0
https://www.tg-me.com/addlist/uBADfbTups5hY2Q0
1
Forwarded from Elohe pictures
🙏🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶🔶 📣

🤍🤍🤍🤍🤍

እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን እንጂ ፊትህን ለማየት የጠሉ ጀርባህን ለማየት ይናፍቃሉ 🗒




🅲🅻🅸🅲🅺 🅷🅴🆁🅴
ይህን ይጫኑት
🔼👆

ㅤ  📱ㅤ  ⬅️       💬   
Lᶦᵏᵉ   ˢᵃᵛᵉ  ˢʰᵃʳᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
🔽🔽🔽
⚠️ከነካችሁት አይቀር ላይክ ሳታደርጉ እንዳታልፉ ‼️

    ▶️ ꌗꃅꍏꋪꍟ ꌩꂦꀎꋪ ꎇꋪꀤꍟꈤꀸ

ይቀላቀሉን
https://www.tg-me.com/+Ci5F1FcleWtlZThk
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👍102
ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያትን አገልግሎት ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለማጠናከር ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ተግባራዊ ለማድረግ ይረዳው ዘንድ የገቢ ማስገኛ ትኬት ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ኅዳር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡ እርስዎም ይህንን ትኬት በመግዛትና በመደገፍ የድርሻዎን ይወጡ፡፡
19
2025/10/27 14:16:12
Back to Top
HTML Embed Code: