"...ክርስቲያኖች ግን ክርስቲያኖች ለመኾናቸው መታወቅ የሚገባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ምሥጢራትን ሲቀበሉ ብቻ ሳይኾን የትም ቦታ በሚኖሩት የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በአፍአ የከበሩ ሰዎች በአፍአ ከሚያሳዩት ምልክት እንደሚታወቁ ኹሉ፥ እኛም ልንታወቅ የሚገባን በነፍሳችን ክብር ነው፡፡ በሌላ አገላለጥ አንድ ክርስቲያን መታወቅ ያለበት በተሰጠው ልጅነት ብቻ ሳይኾን ለልጅነቱ እንደሚገባ በሚያሳየው አዲስ ሕይወትም ጭምር ሊኾን ይገባል፡፡ ይህ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃንና ጨው ሊኾን ይገባዋል፡፡ ለዓለም ብርሃን መኾንህስ ይቅርና ለራስህ እንኳን ብርሃን መኾን ካልተቻለህ፣ የሚሰፋ ቁስልህን በዘይት ማሰርም ካቃተህ፥ ክርስቲያን መኾንህን የምናውቀው እንዴት ነው? ወደ ተቀደሰው ውኃ ገብተህ በመጠመቅህ ነውን? በዚህስ አይደለም ! ይህስ እንዲያውም ዕዳ ፍዳ ይኾንብሃል [እንጂ ክርስቲያን መኾንህን እንድናውቅህ አያደርገንም]፡፡ ይህ ሀብት (ልጅነት) ታላቅ ነውና ለዚህ ሀብት እንደሚገባ ለማይኖሩት ሰዎች ዕዳ ፍዳ መጨመሪያ ነው፡፡ አዎን፥ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃኑን ማብራት ያለበት ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ ብቻ ሳይኾን እርሱ ራሱም ድርሻውን በመወጣት ነውና፡፡ ክርስቲያን ካልኾኑት ይልቅ በኹለንተናው በአረማመዱ፣ በአተያዩ፣ በአለባበሱ፣ በአነጋገሩ ብልጫ ሲኖረው ነውና፡፡ ይህንም የምለው ልጅነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች ልጅነትን ተቀበሉ በመባል ብቻ ሳይኾን የሌሎች ሰዎች ረብ ጥቅም ይኾን ዘንድ ለተቀበሉት ልጅነት የሚገባና ሥርዓት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ ስለምሻ ነው፡፡
አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡
ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ [በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡] ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?"
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ድርሳን 4፥14-15 ገጽ 80-82 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
አሁን ግን ከሌሎች ከማያምኑት ብልጫ ኖሮህ እንዳየው በምፈልገው ሕይወት፥ በኹሉም ረገድ ተቃራኒ ኾነህ አይሃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከቦታ አንጻር፥ ቀኑን ኹሉ የፈረስ እሽቅድምድምንና ተውኔትን፣ ነውርን የተሞሉ ትርኢቶችንና የክፉዎችን ማኅበር፣ ርኵሰትንም የተሞሉ ሰዎችን ስትመለከት እንደምትውል አይሃለሁ፡፡ ከፊትህ አንጻር፥ ዘወትር ያለ ልክና እንደ አመንዝራ ሴት ስትስቅ እመለከትሃለሁ፡፡ ከአለባበስህ አንጻር፥ ከተዋንያንና ጠቢባን ነን ከሚሉ ሰዎች ምንም እንደማትለይ አስተውልሃለሁ፡፡ ከሚከተሉህ ሰዎች አንጻር፥ ብዙ ውዳሴ ከንቱንና ሽንገላን እንደምትሻ አይሃለሁ፡፡ ከንግግርህ አንጻር፥ ምንም ደኅና ነገር፣ በቁዔት ያለው ቃል፣ ለሕይወታችን የሚረባ ንግግር እንደሌለብህ አደምጣለሁ፡፡ ከማዕድህ አንጻርም ከዚያ ጽኑዕ የኾነ ወቀሳ የሚያመጣብህ እንደ ኾነ አያለሁ፡፡
ታዲያ እስኪ ንገረኝ ! ክርስቲያንን ክርስቲያን ከሚያስብሉት ነገሮች እጅግ የራቅህ ኾነህ እያለ፥ ክርስቲያን መኾንህን መለየት የምችለው በምንድን ነው? ክርስቲያን መባልህስ ይቅርና፥ ሰው ብዬ ልጠራህ የምችለውስ እንዴት ነው? እንደ አህያ ትራገጣለህና፤ እንደ ኮርማ ትሴስናለህና፤ እንደ ፈረስ ከሴቶች ኋላ ኾነህ ታሽካካለህና፤ እንደ ድብ ሆዳም ነህና ፤ ሥጋህን እንደ በቅሎ ሥጋ ትሰገስጋለህና፤ እንደ ግመል ቂም ትይዛለህና፤ እንደ ተኵላ ትነጥቃለህና፤ እንደ እባብ ትቈጣለህና፤ እንደ ጊንጥ ትናደፋለህና፤ እንደ ቀበሮ ተንኰለኛ ነህና፤ እንደ እባብ ወይም እንደ እፉኝት በጕረሮህ መርዝ አለና፤ እንደ ክፉ ጋኔን ከወንድምህ ጋር ትጣላለህና፡፡ ታዲያ ክርስቲያን የሚለውስ ይቅርና፥ በምንህ ሰው ብዬ ልጥራህ? ሰው የሚያስብል ምልክት ሳይኖርህ እንዴት ብዬ ከሰው ዘንድ ልቊጠርህ? የንኡሰ ክርስቲያኖችና የክርስቲያኖች ልዩነት ባሰብሁ ጊዜ ልዩነቱ የሰውና የአርዌ ገዳም ያህል ይኾንብኛል፡፡ ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? አርዌ ገዳም ብዬ ልጥራህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጭካኔህ ከአራዊተ ገዳም በላይ ነውና፤ [በሌላ መልኩ ደግሞ እነርሱ እንደዚያ የኾኑት ከተፈጥሮአቸው የተነሣ እንጂ እንደ አንተ ወደውና ፈቅደው አይደለምና፡፡] ታዲያ ምን ብዬ ልጥራህ? ጋኔን ልበልህን? እንዲህስ አልልህም፤ ጋኔን የሆድ ባሪያ አይደለምና፤ ፍቅረ ንዋይም የለበትምና፡፡ ታዲያ ከአራዊተ ገዳምም ከአጋንንትም የሚብስ ክፉ ግብር ከያዝህ፥ ንገረኝ - ሰው ብዬ እጠራህ ዘንድ ይገባኛልን? ሰው ለመባል እንኳን የሚበቃ ምግባር ከሌለህስ፥ ክርስቲያን ብለን ልንጠራህ የምንችለው እንዴት ነው?"
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ድርሳን 4፥14-15 ገጽ 80-82 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም - #ጥር_21
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦
"ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሀዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን፤ በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘተዋሕዶ - #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
አበው ስለ #እመቤታችን_ዕረፍት እንዲህ አሉ፦
"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ
(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)
"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ
(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)
"እስኪ ከእኔ ጋር ሆናችሁ ቅዱስ ዳዊት ምን ያህል እግዚአብሔርን ከልቡ ይወደው እንደነበር እናስተውል። ቀን ቀን ያስባቸው ዘንድ ግድ የሚሉት የመሪዎች፣ የአዛዦች፣ የመንግሥታቱ፣ የሕዝቡ፣ የሠራዊቱና ስለ ጦርነት ውሎዎቹ፣ ስለ ሰላም፣ ስለ ፖለቲካውና በቤቱ ውስጥ ወይም ከቤቱ ውጪ ወይም በጎረቤቶቹ ዘንድ ስላለው ችግር ማውጣት ማውረዱ ልቡን ከፍለው ይወስዱበታል።
በዕረፍት ጊዜው እያንዳንዱ ሰው ለመኝታው የሚጠቀምበትን ሰዓት እርሱ ደግሞ ለንስሐ ለጸሎትና ዕንባውን ለማፍሰስ ይጠቀምበታል፡፡ እንዲህ ያለ ተግባሩን የሚፈጽመው ዛሬን አድርጎ ነገን ሳያደርግ አይደለም። ወይም ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት ሌሊት በማለፍ አይደለም፤ በእያንዳንዷ ሌሊት እንጂ፡፡ «ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ መኝታዬንም በዕንባዬ አርሳለሁ።» የሚለው ቃል የዕንባውን ብዛትና ዕንባው አለማቋረጡን ይገልጽልናል፡፡
እያንዳንዱ ፀጥ ባለ ዕረፍት ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ እርሱ ግን እግዚአብሔርን ብቻውን አግኝቶ ለዕንቅልፍ ባልተከደኑ ዓይኖቹ ያለቀስና ያዘነ የግል ኃጢአቶቹን ይነግረዋል፡፡ አንተም ብትሆን እንዲህ ዓይነቱን አልጋ ለራስህ ታበጅ ዘንድ ይገባሃል። በወርቅና ብር ተከበህ መተኛት ከሰዎች ቅናትን ከአርያም ደግሞ ቁጣን ይቀሰቅስብሃል፡፡ እንደ ዳዊት ያለ ዕንባ ግን የሲዖልን እሳት ያጠፋል፡፡
ሌላ አልጋ ደግሞ ላሳይህን? ይህ አልጋ የያዕቆብ ነው። ለስውነቱ ባዶ መሬትን ለትራሱ ደግሞ ድንጋይን የተጠቀመበት አልጋ! ይህ በመሆኑም ያን መንፈሳዊ ድንጋይና ያቺን መላእክት ሲወጡባትና ሲወርዱባት የነበረችውን መሰላል ሊመለከት ችሏል፡፡ (ዘፍ 28፣ ከ1ኛ ቆሮ 10፥4 ጋር አዛምድ፡፡) በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ድንጋዮች ለክርስቶስ ምሳሌ ሆነው ተጠቅሰዋል፡፡ እኛም እንዲህ ያሉ ሕልሞች እናይ ዘንድ ሕሊናችንን እንደዚህ ባሉት አልጋዎች ላይ እናሳርፍ፡፡ ነገር ግን ከብር በተሠሩ አልጋዎች ላይ ብንተኛ ደስታን ብቻ ሳይሆን የምናጣው ችግርንም እንጋፈጣለን፡፡
እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በሆነ እኩለ ሌሊት አንተ በአልጋህ ውስጥ ተኝተህ ሳለህ ድሀው ሰው ግን በጭድ ክምር ላይ በደጅህ ወድቆ በብርድ እየተንቀጠቀጠና በረሀብ እየተገረፈ ተዘርግቷል:: አንተ ከስዎች ሁሉ ልበ ደንዳና ብትሆን እንኳ ለዚህ ለድሀ የሚገባውን ሳታደርግለት ለራስህ አላስፈላጊ ምቾቶችን መፍቀድህ እርግጠኛ ነኝ ራስህን እንድትረግም ያደርግሃል። «የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያቆላልፍም።» (2ኛ ጢሞ. 2፥4) ተብሎ ተጽፏልና፡፡
አንተም መንፈሳዊ ወታደር ነህ፡፡ እንዲህ ያለ ወታደር ደግሞ በመሬት ላይ ይተኛል እንጂ ከዝሆን ጥርስ በተሠራ አልጋ ላይ አይተኛም፤ እጅግ ያማረ ሽቶም ኣይቀባም፡፡ እንዲህ ያለው ተግባር በመድረክ ላይ እየተወኑ በግድ የለሽነት ከሚኖሩና ከጋለሞታ ሴቶች ጋር ጊዜያቸውን በማባከን የሚኖሩ የምግባረ ብልሹ ሰዎች ተግባር ነው፡፡ የእኛ ጥሩ መዓዛ ግን ሽቱ ሳይሆን መልካም ሥራ ሊሆን ይገባል፡፡ በሽቱ መዓዛ ከሚመጣው ጠንቅ የበለጠ ነፍስን የሚያቆሽሽ ነገር አይኖርም፡፡ በአብዛኛው አፍአዊ (ውጪያዊ) መልካም መዓዛ የሰው ውስጣዊ ማንነት ማደፍና መቆሸሽ ምልክት ነው፡፡
ዲያብሎስ ነፍስን በራስ ወዳድነት ተዋግቶ ሲያሸንፋትና በታላቅ ከንቱነት ሲሞላት አስቀድሞ አቆሽሾት ወይም አጉድፎት ወይም አበልዞት የነበረውን ሰውነት በሽቶ ያጸዳዋል:: ልክ በጉንፋን እንደተያዙና ያለማቋረጥ በአፍንጫቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ለማጽዳት ልብሳቸውን፣ እጆቻቸውንና ፊታቸውን እንደሚያጎድፉ ሁሉ እንዲህ ያለው የክፉ ስው ነፍስም ሰይጣን በሰውነቱ ላይ ያፈሰሰበትን ኃጢአት ለማጽዳት ይሞክራል፡፡ ሽቶ ሽቶ ከሚያውድ፣ ከጋለሞታ ጋር ወዳጅነት ከመሠረተ፣ የዳንኪረኛነት ሕይወትን ከሚመራ ሰው ማን ጨዋና መልካም ነገርን መጠበቅ ይችላል? እስቲ ነፍስህ መንፈሳዊ መዓዛን ትተንፍስና ለአንተም ሆነ ለወዳጆችህ ታላቅ በረከትን ታድላቸው፡፡"
(ሀብታምና ድሀ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሰበከው -ገጽ 21-23 አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው)
በዕረፍት ጊዜው እያንዳንዱ ሰው ለመኝታው የሚጠቀምበትን ሰዓት እርሱ ደግሞ ለንስሐ ለጸሎትና ዕንባውን ለማፍሰስ ይጠቀምበታል፡፡ እንዲህ ያለ ተግባሩን የሚፈጽመው ዛሬን አድርጎ ነገን ሳያደርግ አይደለም። ወይም ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት ሌሊት በማለፍ አይደለም፤ በእያንዳንዷ ሌሊት እንጂ፡፡ «ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፣ መኝታዬንም በዕንባዬ አርሳለሁ።» የሚለው ቃል የዕንባውን ብዛትና ዕንባው አለማቋረጡን ይገልጽልናል፡፡
እያንዳንዱ ፀጥ ባለ ዕረፍት ውስጥ በሚሆንበት ጊዜ እርሱ ግን እግዚአብሔርን ብቻውን አግኝቶ ለዕንቅልፍ ባልተከደኑ ዓይኖቹ ያለቀስና ያዘነ የግል ኃጢአቶቹን ይነግረዋል፡፡ አንተም ብትሆን እንዲህ ዓይነቱን አልጋ ለራስህ ታበጅ ዘንድ ይገባሃል። በወርቅና ብር ተከበህ መተኛት ከሰዎች ቅናትን ከአርያም ደግሞ ቁጣን ይቀሰቅስብሃል፡፡ እንደ ዳዊት ያለ ዕንባ ግን የሲዖልን እሳት ያጠፋል፡፡
ሌላ አልጋ ደግሞ ላሳይህን? ይህ አልጋ የያዕቆብ ነው። ለስውነቱ ባዶ መሬትን ለትራሱ ደግሞ ድንጋይን የተጠቀመበት አልጋ! ይህ በመሆኑም ያን መንፈሳዊ ድንጋይና ያቺን መላእክት ሲወጡባትና ሲወርዱባት የነበረችውን መሰላል ሊመለከት ችሏል፡፡ (ዘፍ 28፣ ከ1ኛ ቆሮ 10፥4 ጋር አዛምድ፡፡) በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ድንጋዮች ለክርስቶስ ምሳሌ ሆነው ተጠቅሰዋል፡፡ እኛም እንዲህ ያሉ ሕልሞች እናይ ዘንድ ሕሊናችንን እንደዚህ ባሉት አልጋዎች ላይ እናሳርፍ፡፡ ነገር ግን ከብር በተሠሩ አልጋዎች ላይ ብንተኛ ደስታን ብቻ ሳይሆን የምናጣው ችግርንም እንጋፈጣለን፡፡
እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በሆነ እኩለ ሌሊት አንተ በአልጋህ ውስጥ ተኝተህ ሳለህ ድሀው ሰው ግን በጭድ ክምር ላይ በደጅህ ወድቆ በብርድ እየተንቀጠቀጠና በረሀብ እየተገረፈ ተዘርግቷል:: አንተ ከስዎች ሁሉ ልበ ደንዳና ብትሆን እንኳ ለዚህ ለድሀ የሚገባውን ሳታደርግለት ለራስህ አላስፈላጊ ምቾቶችን መፍቀድህ እርግጠኛ ነኝ ራስህን እንድትረግም ያደርግሃል። «የሚዘምተው ሁሉ ለጦር ያስከተተውን ደስ ያሰኝ ዘንድ ትዳር በሚገኝበት ንግድ ራሱን አያቆላልፍም።» (2ኛ ጢሞ. 2፥4) ተብሎ ተጽፏልና፡፡
አንተም መንፈሳዊ ወታደር ነህ፡፡ እንዲህ ያለ ወታደር ደግሞ በመሬት ላይ ይተኛል እንጂ ከዝሆን ጥርስ በተሠራ አልጋ ላይ አይተኛም፤ እጅግ ያማረ ሽቶም ኣይቀባም፡፡ እንዲህ ያለው ተግባር በመድረክ ላይ እየተወኑ በግድ የለሽነት ከሚኖሩና ከጋለሞታ ሴቶች ጋር ጊዜያቸውን በማባከን የሚኖሩ የምግባረ ብልሹ ሰዎች ተግባር ነው፡፡ የእኛ ጥሩ መዓዛ ግን ሽቱ ሳይሆን መልካም ሥራ ሊሆን ይገባል፡፡ በሽቱ መዓዛ ከሚመጣው ጠንቅ የበለጠ ነፍስን የሚያቆሽሽ ነገር አይኖርም፡፡ በአብዛኛው አፍአዊ (ውጪያዊ) መልካም መዓዛ የሰው ውስጣዊ ማንነት ማደፍና መቆሸሽ ምልክት ነው፡፡
ዲያብሎስ ነፍስን በራስ ወዳድነት ተዋግቶ ሲያሸንፋትና በታላቅ ከንቱነት ሲሞላት አስቀድሞ አቆሽሾት ወይም አጉድፎት ወይም አበልዞት የነበረውን ሰውነት በሽቶ ያጸዳዋል:: ልክ በጉንፋን እንደተያዙና ያለማቋረጥ በአፍንጫቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ለማጽዳት ልብሳቸውን፣ እጆቻቸውንና ፊታቸውን እንደሚያጎድፉ ሁሉ እንዲህ ያለው የክፉ ስው ነፍስም ሰይጣን በሰውነቱ ላይ ያፈሰሰበትን ኃጢአት ለማጽዳት ይሞክራል፡፡ ሽቶ ሽቶ ከሚያውድ፣ ከጋለሞታ ጋር ወዳጅነት ከመሠረተ፣ የዳንኪረኛነት ሕይወትን ከሚመራ ሰው ማን ጨዋና መልካም ነገርን መጠበቅ ይችላል? እስቲ ነፍስህ መንፈሳዊ መዓዛን ትተንፍስና ለአንተም ሆነ ለወዳጆችህ ታላቅ በረከትን ታድላቸው፡፡"
(ሀብታምና ድሀ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሰበከው -ገጽ 21-23 አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው)
ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል
ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል:: ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!"
ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::
ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5)
ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር::
ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር። ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ከኃጢአትህ እንጂ ካንተ ጋር ጸብ የለውም::
"በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23)
እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ::
ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ ቀን ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን?
ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህች ዕለት ቤትህን አስተካክል:: እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው::
ከቁስልህ የምትፈወስበት ጊዜ እንደደረሰ ዕወቅ:: ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ከንስሓ በቀር መፍትሔ የለውም:: እንደ ሕዝቅያስ አሁኑኑ ቤትህን በንስሓ አስተካክል::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል:: ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!"
ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::
ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5)
ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር::
ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር። ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ከኃጢአትህ እንጂ ካንተ ጋር ጸብ የለውም::
"በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23)
እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ::
ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ ቀን ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን?
ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህች ዕለት ቤትህን አስተካክል:: እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው::
ከቁስልህ የምትፈወስበት ጊዜ እንደደረሰ ዕወቅ:: ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ከንስሓ በቀር መፍትሔ የለውም:: እንደ ሕዝቅያስ አሁኑኑ ቤትህን በንስሓ አስተካክል::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ልንናደድ_የሚገባን_ማን_ላይ_ነው?
ብዙ ኃጢአቶችንና ወንጀሎችን የሠራ አንድ ሰው ለሠራው ኃጢአትና ወንጀል ሳይቀጣ ሲቀር አይተን ብዙዎቻችን እንበሳጫለን፡፡ ያ ሰው እንዲጠየቅና እንዲቀጣ እንፈልጋለን፡፡ ይህ ሳይኾን ከቀረ ግን ቅር እንሰኛለን፤ እንናደዳለን፡፡
እንዲህ የምንኾነው ግን የገዛ ራሳችንን ግብር ስለማንመለከት ነው፡፡ መበሳጨትና መናደድ ቅርም መሰኘት የሚገባን በገዛ ራሳችን ላይ ነውና፡፡ እያንዳንዳችን ለራሳችን እንዲህ ብለን ልንጠይቅ ይገባናል፦ "በሌሎች ሰዎች ላይ ስንት በደል ፈጸምሁ? ለዚህ በደሌስ ስንቴ ሳልቀጣ ቀረሁ?"
በራሳችን ላይ ብዙ ምሳሌዎችን እንደምናገኝ ጥርጥር የለውም፡፡ ይህን ማወቃችን ደግሞ በሌሎች ሰዎች ላይ የተቆጣነው ቁጣና የተበሳጨነው ብስጭት እንደ ጢስ ተኖ እንደ ትቢያ በንኖ እንዲጠፋ ያደርጓል፡፡ ከዚህም በላይ ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር እንድናዞር ስለ በደልነውም በደል ይቅርታንና ቸርነትን እንድንለምን ያደርገናል፡፡
እንዲያውም እኛ በበደልነው በደልና ሌሎች ሰዎች በሠሩት ኃጢአት ልዩነቱን እናስተውለው ይኾናል፡፡ ምናልባት የእኛ በደል የተሰወረና ለሌሎች ሰዎች የማይታይ ሕቡዕ ይኾናል፤ በአንጻሩ ደግሞ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት በግልጽ የሚታይ ይኾናል፡፡
ታዲያ በዚህ ኹኔታ የእኛ በደል ንኡስ፥ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት ግን ዐቢይ እንደ ኾነ ልናስብ ይገባናልን? በጭራሽ! ምክንያቱም በስውር የሚሠ'ራና ሌላ ሰው የማያየው በደል ብዙውን ጊዜ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ስርቆትንና ቀማኛነትን የመሳሰሉ በግልጽ የሚታዩ ኃጢአቶች ኃጢአት መኾናቸው በቀላሉ ይታወቃሉ፡፡ መታወቃቸው ብቻም ሳይኾን በቀላሉ ንስሐ ሊገባባቸውና ሊወገዱ የሚችሉ ናቸው፡፡ ውሸትን፣ ሐሜትንና በስውር ማታለልን የመሳሰሉ በስዉር የሚሠሩ በደሎች ግን በደል መኾናቸውን ለማወቅም ስለ እነዚህ ንስሐ ገብቶ ለማስወገድም እጅግ ክቡዳን ናቸው፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች ገጽ 98-99)
ብዙ ኃጢአቶችንና ወንጀሎችን የሠራ አንድ ሰው ለሠራው ኃጢአትና ወንጀል ሳይቀጣ ሲቀር አይተን ብዙዎቻችን እንበሳጫለን፡፡ ያ ሰው እንዲጠየቅና እንዲቀጣ እንፈልጋለን፡፡ ይህ ሳይኾን ከቀረ ግን ቅር እንሰኛለን፤ እንናደዳለን፡፡
እንዲህ የምንኾነው ግን የገዛ ራሳችንን ግብር ስለማንመለከት ነው፡፡ መበሳጨትና መናደድ ቅርም መሰኘት የሚገባን በገዛ ራሳችን ላይ ነውና፡፡ እያንዳንዳችን ለራሳችን እንዲህ ብለን ልንጠይቅ ይገባናል፦ "በሌሎች ሰዎች ላይ ስንት በደል ፈጸምሁ? ለዚህ በደሌስ ስንቴ ሳልቀጣ ቀረሁ?"
በራሳችን ላይ ብዙ ምሳሌዎችን እንደምናገኝ ጥርጥር የለውም፡፡ ይህን ማወቃችን ደግሞ በሌሎች ሰዎች ላይ የተቆጣነው ቁጣና የተበሳጨነው ብስጭት እንደ ጢስ ተኖ እንደ ትቢያ በንኖ እንዲጠፋ ያደርጓል፡፡ ከዚህም በላይ ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር እንድናዞር ስለ በደልነውም በደል ይቅርታንና ቸርነትን እንድንለምን ያደርገናል፡፡
እንዲያውም እኛ በበደልነው በደልና ሌሎች ሰዎች በሠሩት ኃጢአት ልዩነቱን እናስተውለው ይኾናል፡፡ ምናልባት የእኛ በደል የተሰወረና ለሌሎች ሰዎች የማይታይ ሕቡዕ ይኾናል፤ በአንጻሩ ደግሞ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት በግልጽ የሚታይ ይኾናል፡፡
ታዲያ በዚህ ኹኔታ የእኛ በደል ንኡስ፥ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት ግን ዐቢይ እንደ ኾነ ልናስብ ይገባናልን? በጭራሽ! ምክንያቱም በስውር የሚሠ'ራና ሌላ ሰው የማያየው በደል ብዙውን ጊዜ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ ስርቆትንና ቀማኛነትን የመሳሰሉ በግልጽ የሚታዩ ኃጢአቶች ኃጢአት መኾናቸው በቀላሉ ይታወቃሉ፡፡ መታወቃቸው ብቻም ሳይኾን በቀላሉ ንስሐ ሊገባባቸውና ሊወገዱ የሚችሉ ናቸው፡፡ ውሸትን፣ ሐሜትንና በስውር ማታለልን የመሳሰሉ በስዉር የሚሠሩ በደሎች ግን በደል መኾናቸውን ለማወቅም ስለ እነዚህ ንስሐ ገብቶ ለማስወገድም እጅግ ክቡዳን ናቸው፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች ገጽ 98-99)
♦⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️
👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
📖▓⇨→avido ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
👇👇
https://www.tg-me.com/+lVXHSARuil5kZDU0
👇🏽ከእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በYOUTUBE👇🏽
👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
https://www.tg-me.com/+lVXHSARuil5kZDU0
👏 የቸብቸቦ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🎻 የበገና መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
👑 የቅዱሳን መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
⛪️ የንግስ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🤲 የምስጋና መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🙏 የንስሐ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
💍 የሠርግ መዝሙራት
📖▓⇨→avido ⇨ግጥም
🌦 ወቅታዊ መዝሙራት
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
🇪🇹 ለአገር የተዘመሩ
📖▓⇨→vido ⇨ግጥም
👇👇
https://www.tg-me.com/+lVXHSARuil5kZDU0
👇🏽ከእስልምና ወደ ክርስትና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በYOUTUBE👇🏽
👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
https://www.tg-me.com/+lVXHSARuil5kZDU0
Telegram
ማኅቶት ፕሮሞሽን💓
You’ve been invited to add the folder “ማኅቶት ፕሮሞሽን💓”, which includes 100 chats.
✝ዐቢይ ጾም
ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡
ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-
➡️ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ
➡️በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ
➡️ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡
በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-
1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡
2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡
3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡
4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡
5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡
6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡
7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡
8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
ጾሙን የበረከት ጾም እንዲያደርግልን የእርሱ
መልካም ፍቃድ ይሁንልን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡
ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-
➡️ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ
➡️በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ
➡️ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ ነዋይ' ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡
በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡-
1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡
2. ቅድስት
ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡
3. ምኩራብ
ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡
4. መጻጉዕ
ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡
5. ደብረ ዘይት
ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡
6. ገብርኄር
ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡
7. ኒቆዲሞስ
ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡
8. ሆሳዕና
ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡ በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
ጾሙን የበረከት ጾም እንዲያደርግልን የእርሱ
መልካም ፍቃድ ይሁንልን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Telegram
ፍሬ ተዋህዶ FRE TEWAHDO
✝ዐቢይ ጾም
ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡
ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-
➡️ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ
➡️በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ
➡️ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ…
ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ አቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡
ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡-
➡️ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም ስለሆነ
➡️በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ
➡️ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም 'ትዕቢት' 'ስስት' 'ፍቅረ…
ድርሳነ ኤፍሬም
ተግሣፅ
ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንዲያውስ ትህትናን ተለማመድ፣ ያለትህትና ተገቢውን ህይወት መምራት አይቻልም። ስራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር። ያን ጊዜ ፍሬዎች ወደ መንግስተ ሰማያት ያደርሳሉ። ሰው ከትህትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው። እግዚአብሔርን የተወ ሰው ርኩስ መንፈስ እንደ ሳኦል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው። በማር ጣዕም የሚማርክ ሰው ሀዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትህትናን ውደዱ፣ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም። በትህትና ክንፍ በበረራችው ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ። ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፣ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው። አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ በወጣበት ከፍታ ወድያውኑ ይወድቃል። በመልካም ሀሳብ ልቦናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፣ ክብሩም ታላቅ እና ዘላለማዊ ነው ።
እንግዲ እራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር፣ ያን ጊዜ ኃጢያታችንን እንረዳለን።ያን ጊዜም ሁልጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፣ እንደ እባብ በእብሪት መወጠር እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን። እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግ እንውደድ፣ በንፁህ ልቦና ሆነን ምን አልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል። መልካም ጸሎት በሳግ ና በእንባ የታጀበ ነው፣ በተለይ ደግሞ በምስጢር የሚፈስ እንባ። በልቦናው ከፍታ ሆኖ የሚፀልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረው እና የምንሄደው በርሱ ፍቃድ ነውና። ልቦናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ የእውቀትን ብርሀን ይገልጥላችዋል፣ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብን ይሰጣችኋል። ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሔርን ታሳዝናለህ፣ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርክ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለ። ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበለክ።
ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ ፣ እንግዲ የተበሳጬትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፣ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋ ላይ አስተኛ፣ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣እንጀራህንም ከርሱ ጋር ተካፈል፣ ፅዋህንም ስጠው። እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሀልና፣ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሀሰል፣ ትጠጣው ዘንድ ደሙን አፍስሷል።
ትርጉም እና ሐተታ
ዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው
ተግሣፅ
ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንዲያውስ ትህትናን ተለማመድ፣ ያለትህትና ተገቢውን ህይወት መምራት አይቻልም። ስራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር። ያን ጊዜ ፍሬዎች ወደ መንግስተ ሰማያት ያደርሳሉ። ሰው ከትህትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው። እግዚአብሔርን የተወ ሰው ርኩስ መንፈስ እንደ ሳኦል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው። በማር ጣዕም የሚማርክ ሰው ሀዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትህትናን ውደዱ፣ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም። በትህትና ክንፍ በበረራችው ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ። ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፣ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው። አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ በወጣበት ከፍታ ወድያውኑ ይወድቃል። በመልካም ሀሳብ ልቦናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፣ ክብሩም ታላቅ እና ዘላለማዊ ነው ።
እንግዲ እራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር፣ ያን ጊዜ ኃጢያታችንን እንረዳለን።ያን ጊዜም ሁልጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፣ እንደ እባብ በእብሪት መወጠር እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን። እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግ እንውደድ፣ በንፁህ ልቦና ሆነን ምን አልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል። መልካም ጸሎት በሳግ ና በእንባ የታጀበ ነው፣ በተለይ ደግሞ በምስጢር የሚፈስ እንባ። በልቦናው ከፍታ ሆኖ የሚፀልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረው እና የምንሄደው በርሱ ፍቃድ ነውና። ልቦናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ የእውቀትን ብርሀን ይገልጥላችዋል፣ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብን ይሰጣችኋል። ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሔርን ታሳዝናለህ፣ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርክ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለ። ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበለክ።
ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ ፣ እንግዲ የተበሳጬትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፣ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋ ላይ አስተኛ፣ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣እንጀራህንም ከርሱ ጋር ተካፈል፣ ፅዋህንም ስጠው። እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሀልና፣ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሀሰል፣ ትጠጣው ዘንድ ደሙን አፍስሷል።
ትርጉም እና ሐተታ
ዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው
መቋሚያ
ብዙውን ከእንጨት የሚዘጋጅ እንደ በትር ዘለግ ያለ ከወደ ጫፉ መስቀል ቅርጽ ያለው ነው፤ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የ "ፐ" ቅርጽ ያለው አሊያም ድቡልቡል የሆነ ነው፤ ከወደ ጫፉ የሚደረገው ነገር የብር ፣የነሐስ ፣የወርቅ፣ የብረት፣ የቀንድ ና የእንጨት ሊሆን ይችላል
አገልግሎቱም
መደገፊያ ፣ መሞርኮዧ ና መዘመሚያ ሲሆን ይህም ከከበሮ እና ጸናጽል ጋር እንዲሁም ብቻውን ከማህሌት ላይ በዝማሜና በሽብሸባ ያገለግላል
ምስጢሩ
መቋሚያ የአዳም ተስፋና ከእመቤታችን ተወልዶ በዕጸ መስቀል ላይ የተሰቀለው የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው።
👉 አንድም መቋሚያ ያዕቆብ ትምህርተ መስቀል ያለበት በትር በፊቱ እያቆመ ይሰግድና ይጸልይ የነበረበት ምሳሌ ነው
👉ካህናት መቋሚያን በትከሻቸው አድርገው ወዲህ ወዲያ ማለታቸው አይሁድ በዕለተ አርብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ መመውሰዳቸው
ዝማሜ ሚመሰለው በህማማተ ክርስቶስ ነው። መቋሚያው በመስቀል ይመሰላል።ካህናቱ መቋሚያቸው ከዜማ ጋር አስማምተው በዝማሜ ወቅት መቋሚያውን ወደ ግራ ወደ ቀኝ ማድረጋቸው አይሁድ ኢየሱስን አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ ከነመስቀሉ ማንገላታታቸውን ለማስታወስ ነው። ከዛ ወደታች መሬቱን መምታታቸው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ግርፋቱ ሲበዛበት መሬት ላይ መውደቁን ያሳያል።
ጽናጽል
ከብር ከነሐስ-ከሌላም ብረት የሚሰራ፤ እንዲሿሿ ከብረት ቅጠል የሚደረግበት ሲሆን አገልግሎቱም ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል። ጽናጽል ከከበሮ ጋር አብር የሚሄድ የዜማ መሳሪያ ነው
የብረት ቅጠሎቹ ሲያንሱ 5 ሲበዙ 7 ይሆናሉ። 5 ሲሆን አምስቱ አዕማደ ሚስጢር 7 ሲሆን በሰባቱ ሰማያት ይመሰላል።
👉2 የብረት ዘንጎች(የብረት ቅጠሎቹን የሚይዙት) ላይ ከታችኛው ላይ 2 የብረት ቅጠሎች የሚኖሩ ሲሆን ይህም ጌታችን ልደቶች ማለትም ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፤ ድህረ ዓለም ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው
👉 የብረት ቅጠሎቹ 3 መሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው
👉ድምጹ ያማረና መልካም መሆኑ በመላእክት ዜማ ይመሰላል (ሰብሕዎ በጽናጽል ዘሠናይ ቃሉ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 150)
👉ጽናጽል ወዲህ ወዲያ ማለቱ ጌታችን የመንገላታቱ ምሳሌ ነው
ከበሮ
ከእንጨት ተዘጋጅቶ በጠፍርና በቆዳ የሚለጎም የዜማ መሳሪያ ነው።
ለክብረ በዓል ለበዓል ለበዓለ ንግሥ ዕለት ለእግዚአብሔር ክብር የሚመታ የሚመዘመርበት ነው
በከበሮ ወበመዝሙር ይዜምሩ ሎቱ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 149
ምስጢሩ-
አፉ ሁለት ነው፤ ጠባብ እና ሰፊ
ሰፊው- ቁመት ደረት ምሉዕ በኩለሄ/እግዚአብሔር በሁሉ ሙሉ መሆኑን ሲሆን
ጠባቡ- ደግሞ ወልድ በአጭር ቁመት መወሰኑን የሚያመለክት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው
እንጨቱ ከቆዳ የተለጎመበት ጠፍር- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የገረፉበት የግርፋቱ (የገላው ሰንበር) ምሳሌ ነው
ከበሮ የሚለብሰው ሱቲ ጌታችን የለበሰው ቀይ ግምጃ ምሳሌ ነው
የከበሮ አመታት ምስጢር
መጀመሪያ ከበሮ ተቀምጦ ቀስ እየተባለ ነው የሚመታው።
👉በመሬት መመታቱ ጌታችን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸውን
👉በግራ እና በቀኝ ሲመታ ከቀኝ ሲመታ ወደ ግራ ከግራ ሲመታ ወደ ቀኝ ማዘንበሉን ለማስታወስ ነው
👉ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ከወደቀበት እንደመቱት ፤በፍጥነት ሲመታ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሰቀል ሲቃረብ በፍጥነት መምታታቸውን ያስታውሰናል
የማሕሌት ተወዛዋዦች
ዛሬ ለወጉ ማሕሌት አንቀርም ፣ ቸብቸቦ ይጀመራል ፣ ወጣቶች ከበሮውን ለማንሳት ሪከርድ በሚያሻሽል ፍጥነት የከበሮውን ገመድ ከጀርባቸው ያዋሕዱታል (እንዲያው ወጣቶች ስንል በእድሜ ማለታችን አይደለም ቆብ የደፉ መስቀል የጨበጡ ቀጣይ በምናየው መልኩ የሚሳተፉትንም የሚገልጽ ቃል ነው እንጅ ) : አፍታም ሳይቆይ እንደ አሎሎ ወርዋሪ መሽከርከር ይጀመራል : አንድ እጅ ተዘርግቶ እስክስታው ይቀልጣል: ሁለት እግር ከፍ እያለ መዝለል ይጀመራል : አሁን በአንደበት የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ነው መሬት ላይ ደግሞ ኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ ሁኗል : ነፍስ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዘንግታለች : ስጋ ግን እየተንቀጠቀጠ ነው : የስሜት እሳት ተቀጣጥሏል : እሽሽሽሽሽሽ የሚል ማጀቢያ መሆኑ ነው ከአንደበት አትጠፋም : የሙቀቱ መጠን ከቁጥጥር እየወጣ ነው : ወደ ሴቶች ጉዞ ይጀመራል : አሁን ሴቶች በቅርበት እየተመለከቱ ነው ከበሮው ላይ ብትሩ ይበረታል : የዝላዩ ከፍታ ይጨምራል : ጿጿጿጿጿ የሚል የጽናጽል ድምጽ የሚያሰማ ቢኖርም ፈገግ ተብሎ ታልፎ ጭፈራው ይደራል : ሊቃውንቱ ቢናገሩም የተጠሉ ይሆናሉ : ነፍስ ከተኛች ቆይታለች ከዱካካዋ ልትነቃ አልቻለችም : ከጎን ከበሮ የሚመታው ጓደኛ በመቺው ትዕዛዝ አመታቱን እየቀረጸ ነው : Tik Tok ቀጣዩ የቪዲኦው መሰራጫ መድረክ ነው : የታይታ ክርስትና ! እንደ ፈሪሳውያን ሰው እንዲያይ ብሎ መዘመር ! ተቃራኒ ጾታ እያዩ መስፈንጠር ! በከበሮ ትዳር አይፈለግም ! መዝለል ፣ መሽከርከር ፣ መስፈንጠር፣ መንቀጥቀጥ ፣ እሽሽሽሽሽ ማለት ፣ ወደ ተቃራኒ ጾታ አንጋጦ መዞር ይቁሙ !
ሁለት እጅ ስላለህ እና መምታት ስለቻልክ ብቻ ከበሮ አትሸከም ምስጢሩን ተረዳ ያኔ ሲገባህ ዕንባህ ከዐይንህ ያለማቋረጥ ጉንጮችህን መወረጃ አድርጎ ሲጎርፍ ይታወቅሀል : ያኔ ልብህ እንጅ እግርህ አይዘልም : ያኔ የምትንቀጠቀጠው እግዚአብሔርን በመፍራት ይሆናል: ያኔ ስትዘል አፍአዊ ላብ ሳይሆን ሕሊናህ ይሆናል በተመስጦ የሚያልበው : ያኔ እንደ መላእክት የሰማይ የመቅደሱ በር እስኪከፈት እንዲዘምሩ አንተም የልቦናህ በር ተከፍቶ ለምስጋና ትታትራለህ ። አየኋት : አወቅኳት : ወደድኳት ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የመላዕክትን ዝማሬ ሰምቶ መጦ ባቀናት ቤተክርስቲያን ምድራዊ ተወዛዋዦች ገብተናልና ወደ ልቦናችን እንመለስ ።
በወንዶች ብቻ የሚቆም ግብር አይደለም በአንስቶችም ተመሳሳይ ፍሬ አፍርቶ ተንዠርቅቆ እናገኘዋለን : በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲሁ በአደባባይ በዓላት ቁጥራቸው ትቂት ያልሆኑ በከበሮ ላይ መከራ አጽንተው በመከራ ድር ተተብትበው ይኖራሉ : አንቲ ተቃራኒ ጾታሽ እንዲያይሽ ካልሆነ ምን ያሽከረክርሻል ? ምን ያዘልልሻል ? ወደ እነማን ፊትሽን ዙረሽስ ትመቻለሽ ? ወደፊት ወደ ኋላ ስትይ የክርስቶስን መገፋት ታስቢያለሽ ወይስ ወደፊት ሄደሽ ልብሽ የወደደውን ትፈቅጃለሽ ? ከንቱ ውዳሴን ሽተሽ በሰፈሩ የከበሮ አመታትሽ እንዲወራ ከሆነ እኅቴ ሆይ የገሀነም ደጃፍ ላይ ነሽና ሳትገቢ ተመለሽ! በአደባባይ ምድርን የሚያበራ እሳት ከማቀጣጠል በሕሊና መቅረዝ ትቂት መንፈሳዊ ማኅቶት ማብራት ይሻላል ! በእውነት እናስተውል ! እነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እኮ በዝማሬያቸው ሕሙም ይፈውሱ ነበር በእኛስ? ዘመርን ብለን እራሳችን ሕሙም ሆነን እንመለሳለን ! ወደ እነእንተና ለይቶልን በኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ እግዚአብሔር ቢመለክ ምን ችግር አለው ብለን የኅብረት ዘፋኞች ከመሆናችን በፊት ለብው ! አምላከ ያሬድ ወዳዊት ወእዝራ የቀናውን መንፈስ ያድለን ! የቅዱሳኑ ዝማሬ ወላዲተ ቃል ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን።
ብዙውን ከእንጨት የሚዘጋጅ እንደ በትር ዘለግ ያለ ከወደ ጫፉ መስቀል ቅርጽ ያለው ነው፤ በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የ "ፐ" ቅርጽ ያለው አሊያም ድቡልቡል የሆነ ነው፤ ከወደ ጫፉ የሚደረገው ነገር የብር ፣የነሐስ ፣የወርቅ፣ የብረት፣ የቀንድ ና የእንጨት ሊሆን ይችላል
አገልግሎቱም
መደገፊያ ፣ መሞርኮዧ ና መዘመሚያ ሲሆን ይህም ከከበሮ እና ጸናጽል ጋር እንዲሁም ብቻውን ከማህሌት ላይ በዝማሜና በሽብሸባ ያገለግላል
ምስጢሩ
መቋሚያ የአዳም ተስፋና ከእመቤታችን ተወልዶ በዕጸ መስቀል ላይ የተሰቀለው የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው።
👉 አንድም መቋሚያ ያዕቆብ ትምህርተ መስቀል ያለበት በትር በፊቱ እያቆመ ይሰግድና ይጸልይ የነበረበት ምሳሌ ነው
👉ካህናት መቋሚያን በትከሻቸው አድርገው ወዲህ ወዲያ ማለታቸው አይሁድ በዕለተ አርብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ መመውሰዳቸው
ዝማሜ ሚመሰለው በህማማተ ክርስቶስ ነው። መቋሚያው በመስቀል ይመሰላል።ካህናቱ መቋሚያቸው ከዜማ ጋር አስማምተው በዝማሜ ወቅት መቋሚያውን ወደ ግራ ወደ ቀኝ ማድረጋቸው አይሁድ ኢየሱስን አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ ከነመስቀሉ ማንገላታታቸውን ለማስታወስ ነው። ከዛ ወደታች መሬቱን መምታታቸው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ግርፋቱ ሲበዛበት መሬት ላይ መውደቁን ያሳያል።
ጽናጽል
ከብር ከነሐስ-ከሌላም ብረት የሚሰራ፤ እንዲሿሿ ከብረት ቅጠል የሚደረግበት ሲሆን አገልግሎቱም ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል። ጽናጽል ከከበሮ ጋር አብር የሚሄድ የዜማ መሳሪያ ነው
የብረት ቅጠሎቹ ሲያንሱ 5 ሲበዙ 7 ይሆናሉ። 5 ሲሆን አምስቱ አዕማደ ሚስጢር 7 ሲሆን በሰባቱ ሰማያት ይመሰላል።
👉2 የብረት ዘንጎች(የብረት ቅጠሎቹን የሚይዙት) ላይ ከታችኛው ላይ 2 የብረት ቅጠሎች የሚኖሩ ሲሆን ይህም ጌታችን ልደቶች ማለትም ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ፤ ድህረ ዓለም ደግሞ ያለ አባት ከእመቤታችን መወለዱ ምሳሌ ነው
👉 የብረት ቅጠሎቹ 3 መሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው
👉ድምጹ ያማረና መልካም መሆኑ በመላእክት ዜማ ይመሰላል (ሰብሕዎ በጽናጽል ዘሠናይ ቃሉ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 150)
👉ጽናጽል ወዲህ ወዲያ ማለቱ ጌታችን የመንገላታቱ ምሳሌ ነው
ከበሮ
ከእንጨት ተዘጋጅቶ በጠፍርና በቆዳ የሚለጎም የዜማ መሳሪያ ነው።
ለክብረ በዓል ለበዓል ለበዓለ ንግሥ ዕለት ለእግዚአብሔር ክብር የሚመታ የሚመዘመርበት ነው
በከበሮ ወበመዝሙር ይዜምሩ ሎቱ እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት በመዝሙር 149
ምስጢሩ-
አፉ ሁለት ነው፤ ጠባብ እና ሰፊ
ሰፊው- ቁመት ደረት ምሉዕ በኩለሄ/እግዚአብሔር በሁሉ ሙሉ መሆኑን ሲሆን
ጠባቡ- ደግሞ ወልድ በአጭር ቁመት መወሰኑን የሚያመለክት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው
እንጨቱ ከቆዳ የተለጎመበት ጠፍር- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ የገረፉበት የግርፋቱ (የገላው ሰንበር) ምሳሌ ነው
ከበሮ የሚለብሰው ሱቲ ጌታችን የለበሰው ቀይ ግምጃ ምሳሌ ነው
የከበሮ አመታት ምስጢር
መጀመሪያ ከበሮ ተቀምጦ ቀስ እየተባለ ነው የሚመታው።
👉በመሬት መመታቱ ጌታችን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸውን
👉በግራ እና በቀኝ ሲመታ ከቀኝ ሲመታ ወደ ግራ ከግራ ሲመታ ወደ ቀኝ ማዘንበሉን ለማስታወስ ነው
👉ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ከወደቀበት እንደመቱት ፤በፍጥነት ሲመታ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሊሰቀል ሲቃረብ በፍጥነት መምታታቸውን ያስታውሰናል
የማሕሌት ተወዛዋዦች
ዛሬ ለወጉ ማሕሌት አንቀርም ፣ ቸብቸቦ ይጀመራል ፣ ወጣቶች ከበሮውን ለማንሳት ሪከርድ በሚያሻሽል ፍጥነት የከበሮውን ገመድ ከጀርባቸው ያዋሕዱታል (እንዲያው ወጣቶች ስንል በእድሜ ማለታችን አይደለም ቆብ የደፉ መስቀል የጨበጡ ቀጣይ በምናየው መልኩ የሚሳተፉትንም የሚገልጽ ቃል ነው እንጅ ) : አፍታም ሳይቆይ እንደ አሎሎ ወርዋሪ መሽከርከር ይጀመራል : አንድ እጅ ተዘርግቶ እስክስታው ይቀልጣል: ሁለት እግር ከፍ እያለ መዝለል ይጀመራል : አሁን በአንደበት የሚነገረው ስብሐተ እግዚአብሔር ነው መሬት ላይ ደግሞ ኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ ሁኗል : ነፍስ ምን እየተካሄደ እንዳለ ዘንግታለች : ስጋ ግን እየተንቀጠቀጠ ነው : የስሜት እሳት ተቀጣጥሏል : እሽሽሽሽሽሽ የሚል ማጀቢያ መሆኑ ነው ከአንደበት አትጠፋም : የሙቀቱ መጠን ከቁጥጥር እየወጣ ነው : ወደ ሴቶች ጉዞ ይጀመራል : አሁን ሴቶች በቅርበት እየተመለከቱ ነው ከበሮው ላይ ብትሩ ይበረታል : የዝላዩ ከፍታ ይጨምራል : ጿጿጿጿጿ የሚል የጽናጽል ድምጽ የሚያሰማ ቢኖርም ፈገግ ተብሎ ታልፎ ጭፈራው ይደራል : ሊቃውንቱ ቢናገሩም የተጠሉ ይሆናሉ : ነፍስ ከተኛች ቆይታለች ከዱካካዋ ልትነቃ አልቻለችም : ከጎን ከበሮ የሚመታው ጓደኛ በመቺው ትዕዛዝ አመታቱን እየቀረጸ ነው : Tik Tok ቀጣዩ የቪዲኦው መሰራጫ መድረክ ነው : የታይታ ክርስትና ! እንደ ፈሪሳውያን ሰው እንዲያይ ብሎ መዘመር ! ተቃራኒ ጾታ እያዩ መስፈንጠር ! በከበሮ ትዳር አይፈለግም ! መዝለል ፣ መሽከርከር ፣ መስፈንጠር፣ መንቀጥቀጥ ፣ እሽሽሽሽሽ ማለት ፣ ወደ ተቃራኒ ጾታ አንጋጦ መዞር ይቁሙ !
ሁለት እጅ ስላለህ እና መምታት ስለቻልክ ብቻ ከበሮ አትሸከም ምስጢሩን ተረዳ ያኔ ሲገባህ ዕንባህ ከዐይንህ ያለማቋረጥ ጉንጮችህን መወረጃ አድርጎ ሲጎርፍ ይታወቅሀል : ያኔ ልብህ እንጅ እግርህ አይዘልም : ያኔ የምትንቀጠቀጠው እግዚአብሔርን በመፍራት ይሆናል: ያኔ ስትዘል አፍአዊ ላብ ሳይሆን ሕሊናህ ይሆናል በተመስጦ የሚያልበው : ያኔ እንደ መላእክት የሰማይ የመቅደሱ በር እስኪከፈት እንዲዘምሩ አንተም የልቦናህ በር ተከፍቶ ለምስጋና ትታትራለህ ። አየኋት : አወቅኳት : ወደድኳት ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የመላዕክትን ዝማሬ ሰምቶ መጦ ባቀናት ቤተክርስቲያን ምድራዊ ተወዛዋዦች ገብተናልና ወደ ልቦናችን እንመለስ ።
በወንዶች ብቻ የሚቆም ግብር አይደለም በአንስቶችም ተመሳሳይ ፍሬ አፍርቶ ተንዠርቅቆ እናገኘዋለን : በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲሁ በአደባባይ በዓላት ቁጥራቸው ትቂት ያልሆኑ በከበሮ ላይ መከራ አጽንተው በመከራ ድር ተተብትበው ይኖራሉ : አንቲ ተቃራኒ ጾታሽ እንዲያይሽ ካልሆነ ምን ያሽከረክርሻል ? ምን ያዘልልሻል ? ወደ እነማን ፊትሽን ዙረሽስ ትመቻለሽ ? ወደፊት ወደ ኋላ ስትይ የክርስቶስን መገፋት ታስቢያለሽ ወይስ ወደፊት ሄደሽ ልብሽ የወደደውን ትፈቅጃለሽ ? ከንቱ ውዳሴን ሽተሽ በሰፈሩ የከበሮ አመታትሽ እንዲወራ ከሆነ እኅቴ ሆይ የገሀነም ደጃፍ ላይ ነሽና ሳትገቢ ተመለሽ! በአደባባይ ምድርን የሚያበራ እሳት ከማቀጣጠል በሕሊና መቅረዝ ትቂት መንፈሳዊ ማኅቶት ማብራት ይሻላል ! በእውነት እናስተውል ! እነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እኮ በዝማሬያቸው ሕሙም ይፈውሱ ነበር በእኛስ? ዘመርን ብለን እራሳችን ሕሙም ሆነን እንመለሳለን ! ወደ እነእንተና ለይቶልን በኅብረ ብሔራዊ ጭፈራ እግዚአብሔር ቢመለክ ምን ችግር አለው ብለን የኅብረት ዘፋኞች ከመሆናችን በፊት ለብው ! አምላከ ያሬድ ወዳዊት ወእዝራ የቀናውን መንፈስ ያድለን ! የቅዱሳኑ ዝማሬ ወላዲተ ቃል ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ እውነተኛ ጾም፤ የሰውን ሥጋ ከመብላት በላይ ክፉ ስለ ኾነው ሐሜት በተናገረበት ድርሳኑ እንዲህ አለ፦
ወዳጄ ሆይ! ሰው አስፈራርቶሃልን? በሰማያት ወዳለው ጌታ ተፋጠን፤ ምንም ክፉ ነገርም አይደርስብህም፡፡ እንዲህ በማድረጋቸው የቀደሙ ሰዎች ከመከራቸው ሊድኑ ችለዋል፤ ወንዶች ብቻ አይደሉም፤ ሴቶችም ጭምር እንጂ፡፡ አስቴር የምትባል አንዲት ዕብራዊት ሴት ነበረች፡፡ ይህቺ አስቴርሊጠፉ ሲሉ በዚሁ ዘዴ መላው እስራኤላውያንን ታድጋቸዋለች፡፡ የፋርስ ንጉሥ ኹሉም እስራኤላውያን በአስቸኳይ እንዲገደሉ ትእዛዝ ባስተላለፈና በቊጣው ፊት ሊቆም የሚችል ማንም ባልነበረበት ጊዜ+ ይህቺ ሴት የደስታ ልብሷን አውልቃ የኀዘን ልብሷን ስትለብስ፣ በራሷ ላይ ዐመድና ትቢያ ስትነሰንስ፣ ወደ ንጉሡ ስትኼድ ጊዜ ቸሩ እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር እንዲኾን ስትማጸን፤ ጸሎቷንም ስታቀርብ የተናገረቻቸው ቃላት እነዚህ ነበሩ “ጌታ ሆይ! ቃሎቼ በአንተ ዘንድ የተወደዱ ይኹኑ፣ በአንደበቴም በጎ ነገርን አድርግ" (አስቴ.4፡17)፡፡ ስለ መምህራችን ወደ እግዚአብሔር የምናቀርበው የእኛ ጸሎትም ይህ ሊኾን ይገባል፡፡ አንዲት ሴት ስለ እስራኤላውያን ስለ ጸለየች የአረማውያንን ንጉሥ ቊጣ ካበረደችው ከዚህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ጋር ኾኖ ስለ ታላቂቱ ከተማ የሚለምነው መምህራችንም ከዚህ በበለጠ መልኩ ትሑቱንና ርኅሩኁን ንጉሥ ማሳመን ይችላል፡፡
እግዚአብሔርን በመበደል የተሠሩትን ኃጢአቶች የመፍታት ሥልጣን ካለው ሰውን [ንጉሡን] የበደሉትን ደግሞ ይበልጥ ሊፈታቸውና ከቊጣው ሊስውራቸው ይቻሏል፡፡ እርሱ ራሱም ገዢ ነው! ገዢነቱም ከሌላው [ኹሉ] የከበረ ነው፡፡ ምክንያቱም በንጉሡ ላይ ተፈጻሚ የሚኾኑ ቅዱሳት ሕጎችም ቢኾኑ ተፈጻሚ የሚኾኑት በእርሱ ነውና፡፡ ከላይ ከአርያም በጎ ነገርን ሲፈልግ ንጉሡ ወደ ካህኑ ይኼድ ዘንድ አለው፤ ካህኑ ግን ይህን ፈልጎ ወደ ንጉሡ አይኼድም፡፡ [እንዴት ያልከኝ እንደ ኾነም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ] እርሱም ጥሩር አለውና ይኸውም የጽድቅ ጥሩር ነው፡፡ መታጠቂያ [ቀበቶ] አለው፤ እርሱም የእውነት መታጠቂያ ነው፡፡ እጅግ የተከበረ ጫማ አለው፤ እርሱም የሰላም ወንጌል ነው፡፡ ሰይፍ አለው፤ ከብረት የተሠራ ግን አይደለም፤ ከመንፈስ እንጂ፡፡ ዳግመኛም በራሱ ላይ ቁር አለው፡፡ ይህ የትጥቅ ልብስ እጅግ ግርማ ሞገስ ያለው ነው፡፡ የጦር ዕቃዎቹ እጅግ ውብ ናቸው (ኤፌ.6፡11-17)። የንግግር ችሎታው ታላቅ እንደዚሁም ኃይልን lots የተሞላ ነው፡፡ ስለዚህ ከሥልጣኑ ከፍተኛነት፣ ከሰውነቱ ታላቅነት፣ ከኹሉም በላይ ደግሞ በእግዚአብሔር ባለው ተስፋ ንጉሡን በነጻነትና በማስተዋል ያናግሯል፡፡
ስለዚህ እንጸልይ፤ ልመናችንን እናቅርብ፤ እንማጸን፤ ወደ ሰማያዊው ንጉሥም ብዙ ዕንባን የተመላ መልእክተኛችንን እንላክ እንጂ ስለ ደኅንነታችን አንሥጋ! ይህን በጎ ምልጃ በምናደርግበት ጊዜ እንደ ወዳጅና ረዳት ኾኖ የሚደግፈንም ይህ ጾም አለልን፡፡
ክረምት አልፎ በጋ ሲመጣ ነጋዴው መርከቡን ወደ ባሕሩ ያስገባል፣ ወታደር የጦር መሣሪያውን ይሰነግላል የውጊያ ፈረሱንም ለጦርነቱ ያዘጋጃል! ገበሬው ማጭዱን ይስላል መንገደኛው በድፍረት ረጅም መንገድን ይጓዛል፤ አርበኛው (wrestler) ልብሱን አወላልቆ ለትግሉ ይዘጋጃል፡፡ እኛም ልክ እንደዚሁ ጾም ሲመጣ መንፈሳዊ በጋ እንደ ገባ በማሰብ እንደ ወታደሩ የጦር ዕቃ መሣሪያዎቻችንን እንሰንግላቸው፤ እንደ ገበሬው ማጭዳችንን እንሳል! እንደ ነጋዴዎቹ አሳቦቻችን ከልክ በላይ በኾኑ የፍላጎቶቻችን ሞገዶች ላይ እንዘዛቸው፤ እንደ መንገድ ተጓዦቹ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምትወስደውን መንገድ እንጀምር፣ እንደ አርበኛውም ለተጋድሎው እንዘጋጅ፡፡ ክርስቲያን በአንድ ጊዜ ገበሬም፣ ነጋዴም፣ ወታደርም፣ አርበኛም ተጓዥም ነውና፡፡ እንዲህም ስለ ኾነ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ አለ፡- "መጋደላችን ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምና ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ነው እንጂ፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔርዕቃ ጦር ኹሉ ልበሱ" (ኤፌ.6፡12)፡፡ አርበኛ ሰው አይተሃልን? ወታደርስ ተመለክተሃልን? እንኪያስ አንተም አርበኛ ከኾንክ ለትግሉ ተዘጋጅተህ ዕራቁትህን ልትኾን ያስፈልግሃል፡፡ ወታደር ከኾንክም ኹለንተናህን ታጥቀህ በውጊያው መስመር ላይ ልትሰለፍ ይገባ'ሃል፡፡ “እነዚህ ኹለቱ ነገሮችስ ማለትም ዕራቁት መኾንም ትጥቅ መልበስም በአንድ ጊዜ እንዴት ሊኾኑ ይችላሉ?" የሚል ጥያቄ በአእምሮህ ይመላለስ ይኾናል፤ ግድ የለም እኔ እነግርሃለሁ፡፡
ከዚህ ዓለም አሳብ ራስህን አውጣ፤ ያን ጊዜ አርበኛ ትኾናለህ፡፡ መንፈሳዊዉን የጦር ዕቃ ልበስ፤ ያን ጊዜም ወታደር ትኾናለህ፡፡ ወቅቱ አርበኛ ኾነህ የምትታገልበት ወቅት ነውና የዚህ ዓለም ፍላጎቶችህን አውልቀህ ጣል፡፡ ከአጋንንት ጋር የምናደርገው ጽነ ፍልሚያም አለንና መንፈሳዊ ትጥቅህን ልበስ፡፡ ስለዚህ ዲያብሎስ ከእኛ ጋር ትግል በሚገጥምበት ጊዜ የሚይዘውን እንዲያጣ ዕራቁት መኾን አስፈላጊ ነው፤ ድል የሚያደርግበትን ምት እንዳይመታንም በኹሉም አቅጣጫ በደንብ መታጠቅ ይኖርብናል፡፡
ሰውነትህን ኮትኩተው፡፡ እሾኾቹን መንጥራቸው፡፡ የመልካምነት ዘር ቃልም ዝራበት፡፡ እውነተኞቹን መንፈሳውያን ጥበባትን በታላቅ ጥንቃቄ ኾነህ አፍላቸው፤ ተንከባከባቸውም፤ ይህን ያደረግህ እንደኾነም እውነተኛ ገበሬ ትኾናለህ፡፡ ይህን ስታደርግም ተወዳጅ ጳውሎስ እንዲህ ይልሃል፡-“የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ እንዲኾን ይገባዋል" (2ኛ ጢሞ.2፡6)፡፡ እርሱ ራሱ ይህን ዘዴ ይጠቀምበት ነበር፡፡ በመኾኑም ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ሲጽፍላቸው እንዲህ አለ፡- “እኔ ተከልሁ፤ አጵሎስም አጠጣ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ያሳድግ ነበር" (1ኛ ቆሮ.3፡6)፡፡
በሆዳምነትህ የደነዘው ማጭድህን በጾም ሳለው፡፡ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምትወስደውን መንገድ ተመልከታት፡፡ ውጣ ውረድ ያለባት፣ ጠባብና መከራ የበዛባት መኾኗን አስተውለህ በእርሷ ኺድ፡፡ እነዚህን ነገሮችስ እንዴት አድርገህ ልታደርጋቸው ትችላለህ? ሰውነትህን በመግዛትና [በጾም] በመቆንጠጥ! መንገዱ ጠባብ ስለኾነ ከሆዳምነቱ የተነሣ የወፈረ ሊያልፍባት አይቻለውምና፡፡
ገደብ የለሽ የፍላጎቶችህ ሞገዶችን ቀንሳቸው፡፡ የክፉ አሳቦች ፈተናን ከአንተ አርቅ፡፡ የንግድ መርከብህን ጠብቃት፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ክኅሎትህን ተጠቀም፤ ያን ጊዜም የመርከብ አለቃ ትባላለህ፡፡ በእነዚህ ኹሉም ነገሮች ላይ ግን እንደ መሠረትና እንደ መሪ ጾምን ልንይዝ ግድ ይላል፡፡
ይቀጥላል...
(ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ገጽ 79-96 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
ወዳጄ ሆይ! ሰው አስፈራርቶሃልን? በሰማያት ወዳለው ጌታ ተፋጠን፤ ምንም ክፉ ነገርም አይደርስብህም፡፡ እንዲህ በማድረጋቸው የቀደሙ ሰዎች ከመከራቸው ሊድኑ ችለዋል፤ ወንዶች ብቻ አይደሉም፤ ሴቶችም ጭምር እንጂ፡፡ አስቴር የምትባል አንዲት ዕብራዊት ሴት ነበረች፡፡ ይህቺ አስቴርሊጠፉ ሲሉ በዚሁ ዘዴ መላው እስራኤላውያንን ታድጋቸዋለች፡፡ የፋርስ ንጉሥ ኹሉም እስራኤላውያን በአስቸኳይ እንዲገደሉ ትእዛዝ ባስተላለፈና በቊጣው ፊት ሊቆም የሚችል ማንም ባልነበረበት ጊዜ+ ይህቺ ሴት የደስታ ልብሷን አውልቃ የኀዘን ልብሷን ስትለብስ፣ በራሷ ላይ ዐመድና ትቢያ ስትነሰንስ፣ ወደ ንጉሡ ስትኼድ ጊዜ ቸሩ እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር እንዲኾን ስትማጸን፤ ጸሎቷንም ስታቀርብ የተናገረቻቸው ቃላት እነዚህ ነበሩ “ጌታ ሆይ! ቃሎቼ በአንተ ዘንድ የተወደዱ ይኹኑ፣ በአንደበቴም በጎ ነገርን አድርግ" (አስቴ.4፡17)፡፡ ስለ መምህራችን ወደ እግዚአብሔር የምናቀርበው የእኛ ጸሎትም ይህ ሊኾን ይገባል፡፡ አንዲት ሴት ስለ እስራኤላውያን ስለ ጸለየች የአረማውያንን ንጉሥ ቊጣ ካበረደችው ከዚህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ጋር ኾኖ ስለ ታላቂቱ ከተማ የሚለምነው መምህራችንም ከዚህ በበለጠ መልኩ ትሑቱንና ርኅሩኁን ንጉሥ ማሳመን ይችላል፡፡
እግዚአብሔርን በመበደል የተሠሩትን ኃጢአቶች የመፍታት ሥልጣን ካለው ሰውን [ንጉሡን] የበደሉትን ደግሞ ይበልጥ ሊፈታቸውና ከቊጣው ሊስውራቸው ይቻሏል፡፡ እርሱ ራሱም ገዢ ነው! ገዢነቱም ከሌላው [ኹሉ] የከበረ ነው፡፡ ምክንያቱም በንጉሡ ላይ ተፈጻሚ የሚኾኑ ቅዱሳት ሕጎችም ቢኾኑ ተፈጻሚ የሚኾኑት በእርሱ ነውና፡፡ ከላይ ከአርያም በጎ ነገርን ሲፈልግ ንጉሡ ወደ ካህኑ ይኼድ ዘንድ አለው፤ ካህኑ ግን ይህን ፈልጎ ወደ ንጉሡ አይኼድም፡፡ [እንዴት ያልከኝ እንደ ኾነም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ] እርሱም ጥሩር አለውና ይኸውም የጽድቅ ጥሩር ነው፡፡ መታጠቂያ [ቀበቶ] አለው፤ እርሱም የእውነት መታጠቂያ ነው፡፡ እጅግ የተከበረ ጫማ አለው፤ እርሱም የሰላም ወንጌል ነው፡፡ ሰይፍ አለው፤ ከብረት የተሠራ ግን አይደለም፤ ከመንፈስ እንጂ፡፡ ዳግመኛም በራሱ ላይ ቁር አለው፡፡ ይህ የትጥቅ ልብስ እጅግ ግርማ ሞገስ ያለው ነው፡፡ የጦር ዕቃዎቹ እጅግ ውብ ናቸው (ኤፌ.6፡11-17)። የንግግር ችሎታው ታላቅ እንደዚሁም ኃይልን lots የተሞላ ነው፡፡ ስለዚህ ከሥልጣኑ ከፍተኛነት፣ ከሰውነቱ ታላቅነት፣ ከኹሉም በላይ ደግሞ በእግዚአብሔር ባለው ተስፋ ንጉሡን በነጻነትና በማስተዋል ያናግሯል፡፡
ስለዚህ እንጸልይ፤ ልመናችንን እናቅርብ፤ እንማጸን፤ ወደ ሰማያዊው ንጉሥም ብዙ ዕንባን የተመላ መልእክተኛችንን እንላክ እንጂ ስለ ደኅንነታችን አንሥጋ! ይህን በጎ ምልጃ በምናደርግበት ጊዜ እንደ ወዳጅና ረዳት ኾኖ የሚደግፈንም ይህ ጾም አለልን፡፡
ክረምት አልፎ በጋ ሲመጣ ነጋዴው መርከቡን ወደ ባሕሩ ያስገባል፣ ወታደር የጦር መሣሪያውን ይሰነግላል የውጊያ ፈረሱንም ለጦርነቱ ያዘጋጃል! ገበሬው ማጭዱን ይስላል መንገደኛው በድፍረት ረጅም መንገድን ይጓዛል፤ አርበኛው (wrestler) ልብሱን አወላልቆ ለትግሉ ይዘጋጃል፡፡ እኛም ልክ እንደዚሁ ጾም ሲመጣ መንፈሳዊ በጋ እንደ ገባ በማሰብ እንደ ወታደሩ የጦር ዕቃ መሣሪያዎቻችንን እንሰንግላቸው፤ እንደ ገበሬው ማጭዳችንን እንሳል! እንደ ነጋዴዎቹ አሳቦቻችን ከልክ በላይ በኾኑ የፍላጎቶቻችን ሞገዶች ላይ እንዘዛቸው፤ እንደ መንገድ ተጓዦቹ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምትወስደውን መንገድ እንጀምር፣ እንደ አርበኛውም ለተጋድሎው እንዘጋጅ፡፡ ክርስቲያን በአንድ ጊዜ ገበሬም፣ ነጋዴም፣ ወታደርም፣ አርበኛም ተጓዥም ነውና፡፡ እንዲህም ስለ ኾነ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ አለ፡- "መጋደላችን ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምና ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ነው እንጂ፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔርዕቃ ጦር ኹሉ ልበሱ" (ኤፌ.6፡12)፡፡ አርበኛ ሰው አይተሃልን? ወታደርስ ተመለክተሃልን? እንኪያስ አንተም አርበኛ ከኾንክ ለትግሉ ተዘጋጅተህ ዕራቁትህን ልትኾን ያስፈልግሃል፡፡ ወታደር ከኾንክም ኹለንተናህን ታጥቀህ በውጊያው መስመር ላይ ልትሰለፍ ይገባ'ሃል፡፡ “እነዚህ ኹለቱ ነገሮችስ ማለትም ዕራቁት መኾንም ትጥቅ መልበስም በአንድ ጊዜ እንዴት ሊኾኑ ይችላሉ?" የሚል ጥያቄ በአእምሮህ ይመላለስ ይኾናል፤ ግድ የለም እኔ እነግርሃለሁ፡፡
ከዚህ ዓለም አሳብ ራስህን አውጣ፤ ያን ጊዜ አርበኛ ትኾናለህ፡፡ መንፈሳዊዉን የጦር ዕቃ ልበስ፤ ያን ጊዜም ወታደር ትኾናለህ፡፡ ወቅቱ አርበኛ ኾነህ የምትታገልበት ወቅት ነውና የዚህ ዓለም ፍላጎቶችህን አውልቀህ ጣል፡፡ ከአጋንንት ጋር የምናደርገው ጽነ ፍልሚያም አለንና መንፈሳዊ ትጥቅህን ልበስ፡፡ ስለዚህ ዲያብሎስ ከእኛ ጋር ትግል በሚገጥምበት ጊዜ የሚይዘውን እንዲያጣ ዕራቁት መኾን አስፈላጊ ነው፤ ድል የሚያደርግበትን ምት እንዳይመታንም በኹሉም አቅጣጫ በደንብ መታጠቅ ይኖርብናል፡፡
ሰውነትህን ኮትኩተው፡፡ እሾኾቹን መንጥራቸው፡፡ የመልካምነት ዘር ቃልም ዝራበት፡፡ እውነተኞቹን መንፈሳውያን ጥበባትን በታላቅ ጥንቃቄ ኾነህ አፍላቸው፤ ተንከባከባቸውም፤ ይህን ያደረግህ እንደኾነም እውነተኛ ገበሬ ትኾናለህ፡፡ ይህን ስታደርግም ተወዳጅ ጳውሎስ እንዲህ ይልሃል፡-“የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ እንዲኾን ይገባዋል" (2ኛ ጢሞ.2፡6)፡፡ እርሱ ራሱ ይህን ዘዴ ይጠቀምበት ነበር፡፡ በመኾኑም ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ሲጽፍላቸው እንዲህ አለ፡- “እኔ ተከልሁ፤ አጵሎስም አጠጣ፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ያሳድግ ነበር" (1ኛ ቆሮ.3፡6)፡፡
በሆዳምነትህ የደነዘው ማጭድህን በጾም ሳለው፡፡ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምትወስደውን መንገድ ተመልከታት፡፡ ውጣ ውረድ ያለባት፣ ጠባብና መከራ የበዛባት መኾኗን አስተውለህ በእርሷ ኺድ፡፡ እነዚህን ነገሮችስ እንዴት አድርገህ ልታደርጋቸው ትችላለህ? ሰውነትህን በመግዛትና [በጾም] በመቆንጠጥ! መንገዱ ጠባብ ስለኾነ ከሆዳምነቱ የተነሣ የወፈረ ሊያልፍባት አይቻለውምና፡፡
ገደብ የለሽ የፍላጎቶችህ ሞገዶችን ቀንሳቸው፡፡ የክፉ አሳቦች ፈተናን ከአንተ አርቅ፡፡ የንግድ መርከብህን ጠብቃት፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ክኅሎትህን ተጠቀም፤ ያን ጊዜም የመርከብ አለቃ ትባላለህ፡፡ በእነዚህ ኹሉም ነገሮች ላይ ግን እንደ መሠረትና እንደ መሪ ጾምን ልንይዝ ግድ ይላል፡፡
ይቀጥላል...
(ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ገጽ 79-96 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
"በትንሹ እግዚአብሔርን ካማረራችሁ ስቃያችሁ ብዙ ሲሆን በብዙ አምላካችሁን ትሳደባላችሁ ብሎ ያስባልና፣ ሰይጣን ቁስላችሁን አብዝቶ ይረግጠዋል። ነገር ግን ህመማችሁን በትዕግስት ተሸክማችሁ ቢያይ፣ ከሥቃዩም ብዛት አንጻር እግዚአብሔርን እያመሰገናችሁ ትቀጥላላችሁና ተስፋ ይቆርጣል፤ በከንቱ ነው ያጠቃችሁና ከእናንተ ይሸሻል።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
''እውነተኛ ጿሚ ራሱን ከክፉ ምግባራት የከለከለ፤ ከንቱ የሆኑ ንግግሮችን ከመናገር የተቆጠበ፣ ሐሰትን የማይናገር፣ ሐሜተኛ ያልሆነ፣ በማንም ላይ የማይፈርድ፣ ሽንገላን የማይወድና እኒህንም ከመሰሉ ነገሮች ራሱን የተጠበቀ ፣የማይቆጣ፣ የማይበሳጭ ፣ተንኮለኛ ያልሆነ፣ ቂመኛ ያልሆነና፣ እነዚህን ከመሳሰሉ ክፋቶች ሁሉ የራቀ ሰው ነው፡፡
ሕሊናህ ኃጢአትን ከማሰብ ይጡም፡ አእምሮህም ኃጢአትን ከማስታወስ ይከልከል፡፡ ክፉን ከመመኘት ሁሉ ጡም፡፡ ዐይኖችህ ከንቱ የሆኑ ነገሮችን ከመመልከት፣ ጆሮህም ከንቱ ከሆኑ ዘፈኖችና ከሐሜተኞች ሹክሹክታዎች ጠብቅ፡፡ አንደበትህ ከሐሜት፣ በሌላው ላይ ከመፍረድ ፣ ከስድብ፣ ከውሸት ፣ከማታለል፣ከሽንገላ ንግግሮች እንዲሁም ከማይጠቅሙና አጸያፊ ከሆኑ ቃላት ይጡሙ፡፡ እጆችህም ሰውን ከመግደልና የሌላውን ንብረት ከመዝረፍ ይጡሙ፡፡ እግሮችህም ኃጢአትን ለመፈጸም ከመሄድ ይጡሙ፡፡ ከክፉ ተመለስ መልካምንም ፈጽም፡፡''
(ቅዱስ ኤፍሬም)
እኛስ እውነተኛ ጿሚ መባል ይገባን ይሆን?
ሕሊናህ ኃጢአትን ከማሰብ ይጡም፡ አእምሮህም ኃጢአትን ከማስታወስ ይከልከል፡፡ ክፉን ከመመኘት ሁሉ ጡም፡፡ ዐይኖችህ ከንቱ የሆኑ ነገሮችን ከመመልከት፣ ጆሮህም ከንቱ ከሆኑ ዘፈኖችና ከሐሜተኞች ሹክሹክታዎች ጠብቅ፡፡ አንደበትህ ከሐሜት፣ በሌላው ላይ ከመፍረድ ፣ ከስድብ፣ ከውሸት ፣ከማታለል፣ከሽንገላ ንግግሮች እንዲሁም ከማይጠቅሙና አጸያፊ ከሆኑ ቃላት ይጡሙ፡፡ እጆችህም ሰውን ከመግደልና የሌላውን ንብረት ከመዝረፍ ይጡሙ፡፡ እግሮችህም ኃጢአትን ለመፈጸም ከመሄድ ይጡሙ፡፡ ከክፉ ተመለስ መልካምንም ፈጽም፡፡''
(ቅዱስ ኤፍሬም)
እኛስ እውነተኛ ጿሚ መባል ይገባን ይሆን?
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
ድንግል ሆይ
ልጅሽ የጎሰቆለውን ብላቴና እንደተቀበለ እኔንም ደግሞ ይቀበለኝ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ ልጅሽ ቸር ይቅር ባይ ርኅሩኅ ነውና፡፡ (ሉቃስ ፲፭፣ ፲፬-፲፮)
የተራበ ሆድ ለምግብ እንዲቸኩል ክርስቶስ ደግሞ ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡
ይህንንም ማለቴ ለጥምቀት ልጆች በፍጹም ንስሐ በተቃጠለም የእግዚአብሔር ፍቅር ለተመለሱት ነው ላልተመለሱት ግን ይቅርታ የላቸውም፡፡
✅ ድንግል ሆይ
የልጅሽ የሥጋው መታረጃ የደሙ መቅጃ ወደሚሆን መጋረጃ ውስጥ ያስገባኝ ዘንድ እታመናለሁ
✅ ድንግል ሆይ
የምስሢር ጠረጴዛ ወደተዘጋጀበት በላዩም የመለኮት ማዕድ የሚሆን የሰማይ እንጀራ በተሠራበት ስፍራ ያስቀምጠኝ ዘንድ እታመናለሁ በጌታችን፡፡
የምሥጢሩ ጽዋዕ ከመለኮት ትስብእት ጎን የመነጨው አምላካዊ ወይን ወደተመላበት ያስቀምጠኝ ዘንድ እታመናለሁ፡፡
✅ ድንግል ሆይ
ነፍስና ሥጋን ባንድነት የሚፈውሰውን ቅዱስ ምሥጢር ያሳትፈኝ ዘንድ እታመናለሁ ድንግል ሆይ መለኮታዊውን ቁርባን ሥጋው ደሙን ለመቀበል እንዲያበቃኝ ደጅ እጸናለሁ፡፡
በተቀበልሁትም ጊዜ ለወቀሳ ለመፈራረጃ አይሁንብኝ ለነፍሴና ለሥጋዬ መድኃኒት ይሁነኝ እንጂ
ድንግል ሆይ
እድል ፈንታዬ ጽዋ ተርታዬም የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ ዕንቋችሁንም በዕሪያዎች ፊት አታኑሩ ከተባለባቸው ጋር አይሁን
ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ ሞት አያገኘውም ቢሞትም ይድናል ለዘለዓለምም ይኖራል ተብሎ ከተነገረላቸው ጋራ እንዲሆን ደጅ እጸናለሁ፡፡ (ማቴ ፯፣ ፮)
የእመብርሃን በረከት አይለየን ❣️
ልጅሽ የጎሰቆለውን ብላቴና እንደተቀበለ እኔንም ደግሞ ይቀበለኝ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ ልጅሽ ቸር ይቅር ባይ ርኅሩኅ ነውና፡፡ (ሉቃስ ፲፭፣ ፲፬-፲፮)
የተራበ ሆድ ለምግብ እንዲቸኩል ክርስቶስ ደግሞ ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡
ይህንንም ማለቴ ለጥምቀት ልጆች በፍጹም ንስሐ በተቃጠለም የእግዚአብሔር ፍቅር ለተመለሱት ነው ላልተመለሱት ግን ይቅርታ የላቸውም፡፡
✅ ድንግል ሆይ
የልጅሽ የሥጋው መታረጃ የደሙ መቅጃ ወደሚሆን መጋረጃ ውስጥ ያስገባኝ ዘንድ እታመናለሁ
✅ ድንግል ሆይ
የምስሢር ጠረጴዛ ወደተዘጋጀበት በላዩም የመለኮት ማዕድ የሚሆን የሰማይ እንጀራ በተሠራበት ስፍራ ያስቀምጠኝ ዘንድ እታመናለሁ በጌታችን፡፡
የምሥጢሩ ጽዋዕ ከመለኮት ትስብእት ጎን የመነጨው አምላካዊ ወይን ወደተመላበት ያስቀምጠኝ ዘንድ እታመናለሁ፡፡
✅ ድንግል ሆይ
ነፍስና ሥጋን ባንድነት የሚፈውሰውን ቅዱስ ምሥጢር ያሳትፈኝ ዘንድ እታመናለሁ ድንግል ሆይ መለኮታዊውን ቁርባን ሥጋው ደሙን ለመቀበል እንዲያበቃኝ ደጅ እጸናለሁ፡፡
በተቀበልሁትም ጊዜ ለወቀሳ ለመፈራረጃ አይሁንብኝ ለነፍሴና ለሥጋዬ መድኃኒት ይሁነኝ እንጂ
ድንግል ሆይ
እድል ፈንታዬ ጽዋ ተርታዬም የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ ዕንቋችሁንም በዕሪያዎች ፊት አታኑሩ ከተባለባቸው ጋር አይሁን
ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ ሞት አያገኘውም ቢሞትም ይድናል ለዘለዓለምም ይኖራል ተብሎ ከተነገረላቸው ጋራ እንዲሆን ደጅ እጸናለሁ፡፡ (ማቴ ፯፣ ፮)
የእመብርሃን በረከት አይለየን ❣️
ጸሎት ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግስት የምታደርስ ቀጭኗ ጎዳና ናት፡፡ ከኃጢአት በመራቅ የሚቀርብ ጸሎት ፍጹም የሆነ ሥራን ይሰራል፡፡ ከባልንጀራህ ጋር በጠብ እየኖርክ በእግዚአብሔር ስም ለጸሎት የምትቆም ከሆነ እርሱን እንደመሳደብ ይቆጠርብሃል፡፡ ህሊናህም ከጸሎትህ አንዳች ፍሬ እንደማታገኝ ያስታውቅሃል፡፡ በጸሎት ተመስጠህ ልብህን ወደ እግዚአብሔር አንሳ፡፡
አጠገብህ ስሌለው ሰው ድክመት በተናገርክ ቁጥር ሰይጣን ይዘፍንበት ዘንድ ምላስህን በገና አድርገህ እንደሰጠኸው ቁጥር ነው፡፡ ጥላቻ በልቦናህ ነግሶ ከሆነ የዳቢሎስ እርዳታ እጅግ ታላቅ ይሆናል፡፡
የተንኮል ቃልን አትናገር፤ ለባልንጀራህ ጉድጓድ አትቆፍር፤ ወደ አመንዝራም ሴት አትመልከት የፊቷም ደምግባት አያጥምድህ፡፡ በእርሷ መረብ እንዳትጠመድ ከአንደበቷ ከሚፈልቁት ጣፋጭ ቃሎች ተከልከል፡፡ ከእርሷ ፈጽሞ ሽሽ፡፡
በሰዎች ውድቀት አትደሰት፡፡ በደለኛ እንዳትሆን ጠላትህ ክፉ ሲደርስበት አይተህ ደስ አይበልህ፡፡ ጠላትህ በኃጢአት ተሰነካክሎ ብታይ ስለ እርሱ እዘንለት አልቅስለት፡፡ እጆችህን ለሥራ አትጋቸው፤ ከንቱ ንግግር አትውደድ ለነፍስና ለሥጋ ብሩህነት በሥራ መጠመድን ውደድ፡፡
አጠገብህ ስሌለው ሰው ድክመት በተናገርክ ቁጥር ሰይጣን ይዘፍንበት ዘንድ ምላስህን በገና አድርገህ እንደሰጠኸው ቁጥር ነው፡፡ ጥላቻ በልቦናህ ነግሶ ከሆነ የዳቢሎስ እርዳታ እጅግ ታላቅ ይሆናል፡፡
የተንኮል ቃልን አትናገር፤ ለባልንጀራህ ጉድጓድ አትቆፍር፤ ወደ አመንዝራም ሴት አትመልከት የፊቷም ደምግባት አያጥምድህ፡፡ በእርሷ መረብ እንዳትጠመድ ከአንደበቷ ከሚፈልቁት ጣፋጭ ቃሎች ተከልከል፡፡ ከእርሷ ፈጽሞ ሽሽ፡፡
በሰዎች ውድቀት አትደሰት፡፡ በደለኛ እንዳትሆን ጠላትህ ክፉ ሲደርስበት አይተህ ደስ አይበልህ፡፡ ጠላትህ በኃጢአት ተሰነካክሎ ብታይ ስለ እርሱ እዘንለት አልቅስለት፡፡ እጆችህን ለሥራ አትጋቸው፤ ከንቱ ንግግር አትውደድ ለነፍስና ለሥጋ ብሩህነት በሥራ መጠመድን ውደድ፡፡
ፍቅርን የምትወድ ሁን
“በፍቅር ተመላለሱ” (ኤፌ. 512)
ይህ የሁሉም ነገር መሠረት ነው! ፍቅር ባለበት ቦታ ቁጣ፣ ጩኸት፣ ስድብ የለም፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ተወግደዋል፡፡ ጳውሎስ አሳዳጅ ሳለ በእግዚአብሔር ፍቅር ድኗል፡፡ አንተስ ስለምን የእግዚአብሔር ልጅ ሆንክ? ምክንያቱም ይቅር ስለተባልክ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ዋጋው የማይተመን ስጦታ ተቀብለህ፣ እንዴት ለሌሎች አላካፍልም ትላለህ?
ይህን አስብ! ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንጀሎች ተሸክመህ በእስር ቤት ተጣልክ፤ እናም አንድ ስው ከዚህ አውጥቶ ቤተ መንግሥት አስገባህ። ወይም ሌላ ምሳሌ ለመጠቀም፣ በጠና ታምመህ ለሞት ተቃርበህ ነበርና አንድ ሰው በመድኃኒት አዳነህ። ያን ሰው ከማንም በላይ ከፍ አድርገህ አትመለከተውም? የመድኃኒቱን ስም ስትሰማ እንኳ ደስ አይልህም? ከሥጋ ስቃይ ያዳነንን ከፍ አድርገን የምንወደው ከሆነ፣ ነፍሳችንን የሚያድኑትን መንፈሳዊ ስጦታዎች ምን ያህል እንወዳቸው ይሆን?
ፍቅርን የምትወድ ሁን፤ የዳንከው የእግዚአብሔር ልጅ ባደረገልህ ፍቅር ነውና! ሌላውን የማዳን፣ የመርዳት እድል ካለህስ ይህን ተመሳሳይ መድኃኒት አትሰጠውምን? “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤" እንደተባለው (ማቴ. 6፥14) በዚህ መንገድ አንዳችን የሌላኛችን አበርቺ፣ የሌላኛችን አመስጋኝ መሆናችን የተከበረ እና የለጋስ ልብ ምልክት ይሆንልናል።
ጳውሎስ በመቀጠል “ክርስቶስ ደግሞ እንደ ወደዳችሁ" ይለናል፡፡ እኛ ይቅር ማለት ያቃተን ወዳጆቻችንን ነው፡፡ ክርስቶስ ግን ጠላቶቹን ይቅር ብሏል፡፡ ከጌታችን የተቀበልነው ስጦታ ምንኛ ይበልጣል! ክርስቶስ እንደወደደን መውደድ ከፈለግን ለጠላቶቻችን እንኳን መልካም ማድረግ አለብን፡፡
ጳውሎስ “ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።" በማለት አክሎ ተናግሯል፡፡
ተመልከት… ስለሌሎች መከራ መቀበል ለጠላቶችም ቢሆን ጥሩ መዓዛ ያለው መባ ሲሆን፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ነው፡፡ ለሌሎች ብትሞት በእውነት መስዋእት ትሆናለህ፡፡ እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ይህ ነው፡፡ እስከ መሥዋዕት መውደድ፣ በነጻ ይቅር ማለት፤ ክርስቶስ እንደ ተመላለሰ በፍቅር መመላለስ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 'ለነፍስህ ቤት ስራላት' ገጽ 44-45 በፍሉይ ዓለም የተተረጎመ)
“በፍቅር ተመላለሱ” (ኤፌ. 512)
ይህ የሁሉም ነገር መሠረት ነው! ፍቅር ባለበት ቦታ ቁጣ፣ ጩኸት፣ ስድብ የለም፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ተወግደዋል፡፡ ጳውሎስ አሳዳጅ ሳለ በእግዚአብሔር ፍቅር ድኗል፡፡ አንተስ ስለምን የእግዚአብሔር ልጅ ሆንክ? ምክንያቱም ይቅር ስለተባልክ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ዋጋው የማይተመን ስጦታ ተቀብለህ፣ እንዴት ለሌሎች አላካፍልም ትላለህ?
ይህን አስብ! ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንጀሎች ተሸክመህ በእስር ቤት ተጣልክ፤ እናም አንድ ስው ከዚህ አውጥቶ ቤተ መንግሥት አስገባህ። ወይም ሌላ ምሳሌ ለመጠቀም፣ በጠና ታምመህ ለሞት ተቃርበህ ነበርና አንድ ሰው በመድኃኒት አዳነህ። ያን ሰው ከማንም በላይ ከፍ አድርገህ አትመለከተውም? የመድኃኒቱን ስም ስትሰማ እንኳ ደስ አይልህም? ከሥጋ ስቃይ ያዳነንን ከፍ አድርገን የምንወደው ከሆነ፣ ነፍሳችንን የሚያድኑትን መንፈሳዊ ስጦታዎች ምን ያህል እንወዳቸው ይሆን?
ፍቅርን የምትወድ ሁን፤ የዳንከው የእግዚአብሔር ልጅ ባደረገልህ ፍቅር ነውና! ሌላውን የማዳን፣ የመርዳት እድል ካለህስ ይህን ተመሳሳይ መድኃኒት አትሰጠውምን? “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤" እንደተባለው (ማቴ. 6፥14) በዚህ መንገድ አንዳችን የሌላኛችን አበርቺ፣ የሌላኛችን አመስጋኝ መሆናችን የተከበረ እና የለጋስ ልብ ምልክት ይሆንልናል።
ጳውሎስ በመቀጠል “ክርስቶስ ደግሞ እንደ ወደዳችሁ" ይለናል፡፡ እኛ ይቅር ማለት ያቃተን ወዳጆቻችንን ነው፡፡ ክርስቶስ ግን ጠላቶቹን ይቅር ብሏል፡፡ ከጌታችን የተቀበልነው ስጦታ ምንኛ ይበልጣል! ክርስቶስ እንደወደደን መውደድ ከፈለግን ለጠላቶቻችን እንኳን መልካም ማድረግ አለብን፡፡
ጳውሎስ “ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።" በማለት አክሎ ተናግሯል፡፡
ተመልከት… ስለሌሎች መከራ መቀበል ለጠላቶችም ቢሆን ጥሩ መዓዛ ያለው መባ ሲሆን፣ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት ነው፡፡ ለሌሎች ብትሞት በእውነት መስዋእት ትሆናለህ፡፡ እግዚአብሔርን መምሰል ማለት ይህ ነው፡፡ እስከ መሥዋዕት መውደድ፣ በነጻ ይቅር ማለት፤ ክርስቶስ እንደ ተመላለሰ በፍቅር መመላለስ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 'ለነፍስህ ቤት ስራላት' ገጽ 44-45 በፍሉይ ዓለም የተተረጎመ)
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
የእውነተኛ ምጽዋት መለኪያ
የምጽዋት ብዛት የሚመዘነው በሚሰጠው ገንዘብ ቁጥር መጠን ሳይኾን ስጦታውን በሚሰጥ የልብ ስፋት ነው፡፡ አንዲት ድኻ ሴት ያላትን ጥቂት እንጀራ ምንም ከሌላት ከሌላ ሴት ጋር ተካፍላ የምትበላ ከኾነ፥ ወርቅን በሙዳዬ ምጽዋት ከሚጨምር ባለጸጋ ሰው ይልቅ እጅግ ትበልጣለች፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን ይህ እውነት እንደ ኾነ ብዙ ክርስቲያኖች ቢያውቁም፥ ምስጋና የሚሰጡት ወርቅ ለሰጠው ነው፡፡
አንድ ባለጸጋ ጠቀም ያለ ገንዘብ ለቤተ ክርስቲያን ቢሰጥ እጅግ ያመሰግኑታል፤ ካለው የሀብት ብዛት የተነሣ ያንን በመስጠቱ ምንም ባይጎድልበትም እንኳ፥ በሰዎች ዘንድ እጅግ ቸር እንደ ኾነ ተደርጎ ይንቆለጳጰሳል፡፡ ድኻው ጥቂት ገንዘብ ቢሰጥ ግን ሰዎች ስለ እርሱ ምንም ትንፍሽ አይሉም፡፡ ምናልባት ያቺ የሰጣት ገንዘብ’ኮ በኋላ እርስዋን በማጣቱ ምክንያት ተርቦ እንዲያድር ልታደርገው የምትችል ትኾን ይኾናል፤ ነገር ግን ይህን በማድረጉ የሚያመሰግነው አንድ ሰውስ እንኳ አይገኝም፡፡ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም ሳይጎድልበት የሰጠው ባለጸጋውን አመስግኖ ያለውን ኹሉ የሰጠውን ድኻ ሳያመሰግኑ ከሚቀሩ ከእነ ጭራሹ ምስጋና ባይኖር ይሻል ነበር፡፡
ስለዚህ እውነተኛ ምጽዋት የሚባለው የባለጸጋውም ይኹን የድኻው በአግባቡና በሥርዓቱ ልናውቀው ይገባናል፡፡ ማመስገን የሚገባንም ከዚያ በኋላ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የምስጋናችን ስጦታም ሰዎች ከልባቸው ከሚሰጡት ገንዘብ ብዛት አንጻር ሊኾን ይገባል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"አምስቱ የንስሐ መንገዶች" መጽሐፍ
በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ
የምጽዋት ብዛት የሚመዘነው በሚሰጠው ገንዘብ ቁጥር መጠን ሳይኾን ስጦታውን በሚሰጥ የልብ ስፋት ነው፡፡ አንዲት ድኻ ሴት ያላትን ጥቂት እንጀራ ምንም ከሌላት ከሌላ ሴት ጋር ተካፍላ የምትበላ ከኾነ፥ ወርቅን በሙዳዬ ምጽዋት ከሚጨምር ባለጸጋ ሰው ይልቅ እጅግ ትበልጣለች፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን ይህ እውነት እንደ ኾነ ብዙ ክርስቲያኖች ቢያውቁም፥ ምስጋና የሚሰጡት ወርቅ ለሰጠው ነው፡፡
አንድ ባለጸጋ ጠቀም ያለ ገንዘብ ለቤተ ክርስቲያን ቢሰጥ እጅግ ያመሰግኑታል፤ ካለው የሀብት ብዛት የተነሣ ያንን በመስጠቱ ምንም ባይጎድልበትም እንኳ፥ በሰዎች ዘንድ እጅግ ቸር እንደ ኾነ ተደርጎ ይንቆለጳጰሳል፡፡ ድኻው ጥቂት ገንዘብ ቢሰጥ ግን ሰዎች ስለ እርሱ ምንም ትንፍሽ አይሉም፡፡ ምናልባት ያቺ የሰጣት ገንዘብ’ኮ በኋላ እርስዋን በማጣቱ ምክንያት ተርቦ እንዲያድር ልታደርገው የምትችል ትኾን ይኾናል፤ ነገር ግን ይህን በማድረጉ የሚያመሰግነው አንድ ሰውስ እንኳ አይገኝም፡፡ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም ሳይጎድልበት የሰጠው ባለጸጋውን አመስግኖ ያለውን ኹሉ የሰጠውን ድኻ ሳያመሰግኑ ከሚቀሩ ከእነ ጭራሹ ምስጋና ባይኖር ይሻል ነበር፡፡
ስለዚህ እውነተኛ ምጽዋት የሚባለው የባለጸጋውም ይኹን የድኻው በአግባቡና በሥርዓቱ ልናውቀው ይገባናል፡፡ ማመስገን የሚገባንም ከዚያ በኋላ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የምስጋናችን ስጦታም ሰዎች ከልባቸው ከሚሰጡት ገንዘብ ብዛት አንጻር ሊኾን ይገባል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"አምስቱ የንስሐ መንገዶች" መጽሐፍ
በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ
Telegram
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
አቤቱ፥ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።
1 Have mercy upon me, O God, according to thy lovingkindness: according unto the multitude of thy tender mercies blot out my transgressions.
2 ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኃጢአቴም አንጻኝ
2 Wash me throughly from mine iniquity, and cleanse me from my sin.
3 እኔ መተላለፌን አውቃለሁና፥ ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና። 4 አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።
3 For I acknowledge my transgressions: and my sin is ever before me.
4 Against thee, thee only, have I sinned, and done this evil in thy sight: that thou mightest be justified when thou speakest, and be clear when thou judgest.
5 እነሆ፥ በዓመፃ ተፀነስሁ፥ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ።
5 Behold, I was shapen in iniquity; and in sin did my mother conceive me.
6 እነሆ፥ እውነትን ወደድህ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።
6 Behold, thou desirest truth in the inward parts: and in the hidden part thou shalt make me to know wisdom.
7 በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
7 Purge me with hyssop, and I shall be clean: wash me, and I shall be whiter than snow.
8 ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፥ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።
8 Make me to hear joy and gladness; that the bones which thou hast broken may rejoice.
9 ከኃጢአቴ ፊትህን መልስ፥ በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።
9 Hide thy face from my sins, and blot out all mine iniquities.
10 አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።
10 Create in me a clean heart, O God; and renew a right spirit within me.
11 ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።
11 Cast me not away from thy presence; and take not thy holy spirit from me.
12 የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።
12 Restore unto me the joy of thy salvation; and uphold me with thy free spirit.
13 ለሕግ ተላላፎች መንገድህን አስተምራለሁ፥ ኃጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።
13 Then will I teach transgressors thy ways; and sinners shall be converted unto thee.
14 የመድኃኒቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከደም አድነኝ፥ አንደበቴም በአንተ ጽድቅ ትደሰታለች።
14 Deliver me from bloodguiltiness, O God, thou God of my salvation: and my tongue shall sing aloud of thy righteousness.
15 አቤቱ፥ ከንፈሮቼን ክፈት፥ አፌም ምስጋናህን ያወራል።
15 O Lord, open thou my lips; and my mouth shall shew forth thy praise.
16 መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም።
16 For thou desirest not sacrifice; else would I give it: thou delightest not in burnt offering.
17 የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።
17 The sacrifices of God are a broken spirit: a broken and a contrite heart, O God, thou wilt not despise.
18 አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ።
18 Do good in thy good pleasure unto Zion: build thou the walls of Jerusalem.
19 የጽድቁን መሥዋዕት መባውንም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በወደድህ ጊዜ፥ ያን ጊዜ በመሠዊያህ ላይ ፍሪዳዎችን ይሠዋሉ።
19 Then shalt thou be pleased with the sacrifices of righteousness, with burnt offering and whole burnt offering: then shall they offer bullocks upon thine altar
1 Have mercy upon me, O God, according to thy lovingkindness: according unto the multitude of thy tender mercies blot out my transgressions.
2 ከበደሌ ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኃጢአቴም አንጻኝ
2 Wash me throughly from mine iniquity, and cleanse me from my sin.
3 እኔ መተላለፌን አውቃለሁና፥ ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና። 4 አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ፥ በነገርህም ትጸድቅ ዘንድ በፍርድህም ንጹሕ ትሆን ዘንድ።
3 For I acknowledge my transgressions: and my sin is ever before me.
4 Against thee, thee only, have I sinned, and done this evil in thy sight: that thou mightest be justified when thou speakest, and be clear when thou judgest.
5 እነሆ፥ በዓመፃ ተፀነስሁ፥ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ።
5 Behold, I was shapen in iniquity; and in sin did my mother conceive me.
6 እነሆ፥ እውነትን ወደድህ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።
6 Behold, thou desirest truth in the inward parts: and in the hidden part thou shalt make me to know wisdom.
7 በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
7 Purge me with hyssop, and I shall be clean: wash me, and I shall be whiter than snow.
8 ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፥ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።
8 Make me to hear joy and gladness; that the bones which thou hast broken may rejoice.
9 ከኃጢአቴ ፊትህን መልስ፥ በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።
9 Hide thy face from my sins, and blot out all mine iniquities.
10 አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።
10 Create in me a clean heart, O God; and renew a right spirit within me.
11 ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።
11 Cast me not away from thy presence; and take not thy holy spirit from me.
12 የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።
12 Restore unto me the joy of thy salvation; and uphold me with thy free spirit.
13 ለሕግ ተላላፎች መንገድህን አስተምራለሁ፥ ኃጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።
13 Then will I teach transgressors thy ways; and sinners shall be converted unto thee.
14 የመድኃኒቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከደም አድነኝ፥ አንደበቴም በአንተ ጽድቅ ትደሰታለች።
14 Deliver me from bloodguiltiness, O God, thou God of my salvation: and my tongue shall sing aloud of thy righteousness.
15 አቤቱ፥ ከንፈሮቼን ክፈት፥ አፌም ምስጋናህን ያወራል።
15 O Lord, open thou my lips; and my mouth shall shew forth thy praise.
16 መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም።
16 For thou desirest not sacrifice; else would I give it: thou delightest not in burnt offering.
17 የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።
17 The sacrifices of God are a broken spirit: a broken and a contrite heart, O God, thou wilt not despise.
18 አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት የኢየሩሳሌምንም ቅጽሮች ሥራ።
18 Do good in thy good pleasure unto Zion: build thou the walls of Jerusalem.
19 የጽድቁን መሥዋዕት መባውንም የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በወደድህ ጊዜ፥ ያን ጊዜ በመሠዊያህ ላይ ፍሪዳዎችን ይሠዋሉ።
19 Then shalt thou be pleased with the sacrifices of righteousness, with burnt offering and whole burnt offering: then shall they offer bullocks upon thine altar