Telegram Web Link
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!

https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
+ ረቢ ወዴት ትኖራለህ? +

ከመጥምቁ ዮሐንስ ተማሪዎች መካከል ሁለቱ "የእግዚአብሔር በግ እነሆ" የሚለውን የመምህራቸውን ስብከት ሰምተው ጌታን ተከተሉት::

"ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ፦ ምን ትፈልጋላችሁ? አላቸው። እነርሱም፦ ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ መጥታችሁ እዩ፡ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ፥ በዚያም ቀን በእርሱ ዘንድ ዋሉ፤ አሥር ሰዓት ያህል ነበረ" ዮሐ. 1:37-39

ጌታን ተከትለው የሚኖርበትን ካዩት ደቀ መዛሙርት አንደኛው ስም እንድርያስ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የራሱን ስም በወንጌሉ ላይ እኔ የማይጽፈውና ቤተ ክርስቲያን ግን የራሱን ነገር ሲገልፅ በሚጠቀመው ቋንቋ የምታውቀው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነበረ::

"ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ? አሉት፤ መጥታችሁ እዩ፡ አላቸው። መጥተው የሚኖርበትን አዩ" የሚለው ቃል በእርግጥ በጣም አስገራሚ ነው:: የክርስቶስን መኖሪያ ማየት መፈለጋቸው ፈልገው እንዳያጡት አድራሻውን ለማወቅ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ነበረ::
ሆኖም ክርስቶስ በምድር ላይ ሲኖር ቋሚ አድራሻ አልነበረውም:: ራሱ እንደተናገረ :-ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም" (ማቴ. 8:20)

እነዚህ ሁለት ደቀ መዛሙርት የጠየቁት "ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ?" የሚለው ጥያቄ አድራሻ ከመጠየቅ ከፍ ያለ ጥልቅ ጥያቄ ነው:: ነቢያቱ "የጥበብ ሀገርዋ ወዴት ነው? ማደሪያዋስ ወዴት ነው?" ብለው የተጨነቁለት የጥበብ ክርስቶስ ማደሪያ የት እንደሆነ ማወቅ የነፍስ ዕረፍት ነውና ተራ ጥያቄ አይደለም?
ይህ ጥያቄ ዳዊት ለዓይኖቹ እንቅልፍ ለሽፋሽፍቶቹ ዕረፍት ያልሠጠበት "የያዕቆብ አምላክን ማደሪያ እስኪያገኝ ድረስ" የለመነበት ጥያቄ ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? የሚለው ጥያቄ እንድርያስና ዮሐንስ በአንድ ቀን ብቻ የሚመለስ ጥያቄ መስሎአቸው አብረውት ሔደው አብረውት ዋሉ እንጂ የጌታ መኖሪያ ግን ያን ቀን የዋለበት ብቻ አይደለም::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ?
"ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፥ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ" መዝ. 43:3

ረቢ ወዴት ትኖራለህ?  "ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ። እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥  በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች" መዝ. 139:8 ለአድራሻ የሚያስቸግረው የረቢ መኖሪያው ብዙ ስለሆነ የት ትኖራለህ ለሚለው ጥያቄ መልሱ "መጥታችሁ እዩ" ብቻ ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ብለው ለጠየቁት ደቀ መዛሙርቱ ቦታውን ከመናገር ይልቅ  "መጥታችሁ እዩ" ያለው ጌታ እርሱን ጸንተው እስከተከተሉ ድረስ በሕይወታቸው ዘመን ሁሉ አልፎም ከሞቱ በኋላ የሚያዩት ብዙ መኖሪያ ስላለው ነበር::

የረቢ መኖሪያው ብዙ ነው:: "የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል፡ ወደ እርሱም እንመጣለን፡ በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን" እንዳለ ቃሉን የሚጠብቅ ሰው ሰውነትም የእርሱ ማደሪያ ነው:: (ዮሐ. 14:23)

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? " በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና" ስትል ሰምተንህ ነበር:: (ዮሐ. 14:2) የአንተ መኖሪያ መንግሥተ ሰማያት አይደለምን?  ቅዱስ ጳውሎስ "ልሔድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ" ሲል እንደሰማነው እስከ ዐሥር ሰዓት ድረስ እንደመዋል ዐሥሩ መዓርጋት ላይ የደረሱ በጽድቅ መንገድ የሔዱ የሚያዩት ማደሪያህ መንግሥተ ሰማያት አይደለምን? መጥተን ለማየት "እናንተ የአባቴ ቡሩካን ወደ እኔ ኑ" እስክትለን በተስፋ እየጠበቅን አይደለምን?

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ካሉት ጠያቂዎች መካከል አንዱ ዮሐንስ መሆኑን ሳስብ ደግሞ ዮሐንስ ያያቸው የረቢ መኖሪያዎች ከገሊላ እስከ ታቦር ተራራ ፣ ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ ፣ ከወንጌል እስከ ራእይ እጅግ ብዙ እንደነበሩ ታየኝ::

"ወዴት ትኖራለህ?" ብሎ ጠይቆ ጌታን የተከተለው ዮሐንስ "መጥተህ እይ" በተባለው መሠረት የጌታን መኖሪያ የእርሱን ያህል ያየም ሰው የለም::

ዮሐንስ "ረቢ ወዴት ትኖራለህ?" ለሚል ጥያቄው ግን አንጀት የሚያርስ ልብ የሚያሳርፍ መልስ ያገኘው አርብ ዕለት መስቀሉ ሥር ነበር:: ወዴት ትኖራለህ? ላለው ዮሐንስ የዘጠኝ ወር ከተማውን የዘላለም ማረፊያውን "እነኋት እናትህ" ብሎ ሲሠጠው መጥቶ ካያቸው የረቢ መኖሪያዎች ሁሉ የምትበልጠውን መኖሪያ አየ:: "እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦  ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ" ብሎ የመረጣትን ማደሪያ ከማየት በላይ ምን ክብር አለ? (መዝ. 132:13)

ዮሐንስ ይህችን የረቢ መኖሪያ ወዲያው ወደ ቤቱ ወሰዳት:: ዮሴፍ ሊወስዳት ስላልፈራ ምን እንዳገኘ ያውቃልና እርሱም ይህችን የዕንቁ ሳጥን ወደ ቤቱ ወስዶ ቢዝቁት የማያልቅ ጸጋን ተጎናጸፈ::

ጌታ እናቱን ለዮሐንስ መሥጠቱ የሁለት ድንግልናዎች ማስረጃ ሆነ:: የድንግል ማርያም ዘላለማዊ ድንግልናም የዮሐንስ ድንግልናም በጌታ ንግግር ታወቀ:: 

አንዳንዶች እንደሚመስላቸው ድንግል ማርያም ከጌታ ሌላ ልጆች ቢኖሩአት ኖሮ "እናቴን ከልጆችዋ ነጥለህ ወደ ቤትህ ውሰዳት" "አንቺም ልጆችሽን ይዘሽ ወደ ሰው ቤት ሒጂ" ብሎ ለዮሐንስ አይሠጣትም ነበር:: ድንግል ማርያም የአብን አንድያ ልጅ አንድያ ልጅዋ አድርጋለችና አምላክ ባደረበት ዙፋን ሌላ ፍጡር ያላስቀመጠች የአምላክ ብቸኛ ዙፋን ፣ እግዚአብሔርን አስገብታ በርዋን የዘጋች ዘላለማዊት ድንግል መሆንዋ ለዮሐንስ በመሠጠትዋ ታወቀ:: ዮሐንስም ቤት ንብረት የሌለው መናኝ ባይሆንና ሚስት ድስት ያለው ሰው ቢሆን ድንገት ወደ ቤቱ ይዞአት እንዲሔድ እናቱን ባልሠጠው ነበር::

የሰው ልጅ ድኅነት ታሪክ በሁለት "እነሆ"ዎች መሃል መከናወኑ እጅግ ይደንቃል:: የሰው መዳን የተጀመረው "እነሆኝ የጌታ ባሪያ" ብላ ራስዋን ለፈጣሪ በሠጠችው ድንግል ቃል ሲሆን የተጠናቀቀው ደግሞ "እነኋት እናትህ" ብሎ በደም በታጠበ አንደበቱ በነገረን የኑዛዜ ቃል ነው::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ? ለእኛም አታሳየን ይሆን? እስከ ዐሥር ሰዓት መዋል ፣ ዐሠርቱን ትእዛዛትህን ፣ ዐሥሩን የቅድስና ደረጃዎችን መውጣት ላቃተን ለእኛስ መኖሪያህን ታሳየን ይሆን? መጥታችሁ እዩ የሚለውን ጥሪ ሰምተን ለማምጣት አቅም ላነሰን መጻጉዕዎች ፣ ዓይን ላጣን በርጤሜዎሶች ተነሡ እዩ ብለህ መኖሪያህን አታሳየን ይሆን? መቅደስህን እንመለከት ዘንድ ፣ መኖሪያህን መንግሥትህን እናያት ዘንድ ፣ ዮሐንስ ያያትን መኖሪያህ እናትህን እናይ ዘንድ እንመኛለን::

ረቢ ወዴት ትኖራለህ?
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🌿በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሕዱ አምላክ አሜን።🌿

ክርስቶስ ተንሥአ እምሙታን በዐቢይ ኃይል ወስልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍስሐ ወሠላም።

             🔆ልደታ ለማርያም🔆

💠{ መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን }💠
                🕯መዝ 86÷1🕯

እመቤታችን ልደቷ እንደእንግዳ ደራሽ እንደውኃ ፈሳሽ ሆኖ ሳይነገር ሳይታወቅ ሳይጠበቅ የመጣ አይደለም፤ እንደልጇ ሁሉ አበው ሲሿት በምሳሌ ጥላነት ሲያዩዋት፣ ነቢያቱ ሲተነበዩላት ዳዊት ልጄ ሆይ ስሚኝ በማለት ሰሎሞንሞ እቴ ሙሽራዬ እያለ በትንቢት መነጽርነት ሲያናገራት የነበረች ናት እንጂ ።

አስቀድሞ ለአዳም በገባለት ቃልኪዳን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንኃለው በማለት እርሱ ይወለድባት ዘንድ ያላት የመረጣት የአዳም የልጅ ልጅ እንደምትወለድና ከእርሷም እንደሚወለድ ነግሮታል።

ከዚህ በጎላ እና በተረዳ ግን ነቢዩ ኢሳይያስ "ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዓዐርግ ጽጌ እምኔሃ" ... ከእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከግንዱ ይወጣል ... በማለት በትር ብሎ በትረ አሮን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእሴይ ሥር ከዳዊት እንደምትወለድና ከእርሷም ጽጌ የተባለ ክርስቶስ እንደሚወለድ ተናግሯል።

የእመቤታችን ልደት ሊቁ "መኑ ይእቲ እንተ ትሔውጽ ከመጎኅ ያላት" ... ይህች እንደማለዳ ፀሐይ ያለች ማናት ... በማለት የገለጣት ለአማናዊው ፀሐይ ጎኅ፤ ለአማናዊው ወንጌል ንዑስ ወንጌል የሆነች የእመቤታችን ልደቷ ለልደተ ክርስቶስ ጎኅ ሆኖልን፤ በእርሷ መወለድ የእርሱን ሰው ሆኖ መወለድ እውን ሆኖልን ያረጋገጥንበት ነው።

ደራሲም ድንግል በልደቷ ለአዳምና ለልጆቹ ከመርገሙ መዳኛ ስለመሆኗ እንዲህ ብሎ ይጠቅሳል :-

ማርያም ድንግል በልደትኪ መጠነ አቅሙ፤
አዳም ይዌድስኪ ምስለ ደቂቀ ኩሎሙ፤
እስመ ለአዳም ብኪ ተስእረ መርገሙ።
        🕯መልክአ ልደታ🕯

የእመቤታችን ልደት ከአምስቱ ልደታት አንዱ የሆነው እንደ ልደተ አቤል ያለ ይኸውም ከእናትና ከአባት የሚወለዱት ልደት ነው። ልደቷም መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን... መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው..  በማለት ቅዱስ ደዊት "አድባር ቅዱሳን" ብሎ ከገለጣቸው በምድር  ከተነሱት ሁሉ በግብራቸው በጽድቃቸው በትሩፋት በክብር  እንደ ተራራ ከፍ ብለው ከሚታዩት ከተነሱት ከታላላቅ ቅዱሳን ወገን ነው።🌱ታሪክ በእንተ ልደተ ማርያም🌱

ጰጥሪቃና ቴክታ የሚባሉ ደጋግ ቅዱሳን ባለጸጋ ለእንሶቻቸው የወርቅ ጉትቻ እስኪያረጉ ድረስ ሁሉ የተትረፈረፋቸው ሰዎች ነበሩ። እነርሱም መካን በመሆናቸው ያዝኑ ነበር። አብዝተውም እግዚአብሔርን ለመኑት ጠየቁትም  በኋላም ሕልምን አዩ።

ሕልሙንም ሕልም ፈቺ ዘንድ ሔደው ፍቺውን ጠየቁት። እርሱም ነጭ ጥጃ መልኳ ደምግባቷ ያማረ ምግባሯ የተወደደ ሴት ልጅ ናት። እንዲህ አይነቷ እሷን የምትመስል እየወለደች ትሔዳለች፤ የመጨረሻዋ ጥጃ ጨረቃ መውለዷም ከሰማይ ዝቅ ከምድር እና ከፍጥረታት ወገን ግን ከፍ ያለች ልጅ ናት የፀሐዩ ነገር ግን አልተገለጠልኝም አላቸው። እነርሱም ይህንኑ ሰምተው ሄዱ። ሄኤማንን ወለዱ። ሄኤሜን ዴርዴንን፣ ዴርዴን ቶናን፣ ቶና ሲካርን፣ ሲካር ሔርሜላን ወለደች። ሔርሜላና ማጣትም የጌታ አያቱ የምትሆን ሐናን ወለዱ።

💠ኢያቄም እና ሐና

ከነገሥታቱ ከይሁዳ ወገን የሚሆን ኢያቄም ቀለዮጳ የሚባል አንድ ባለጸጋ ሰው ነበር። እርሱም ከካህናቱ ከነገደ ሌዊ የምትወለደውን ሐናን አገባ። እነርሱም የተቀደሱ ደጋግ ነበሩ። በደቂቀ እሥራኤል ዘንድም አብዝተው መስዋዕትን ያቀርቡ ነበር።

ከእለታት አንድ ቀንም ከደቂቀ እሥራኤል ወገን የሆነ ሮቤል የተባለ ሰው መጣና " በእኛ ፊት መሥዋዕትን ታቀርብ ዘንድ አይገባም፤ በእሥራኤል መካከል ዘር የለህምና" አለው። አይሁድ እና ካህናቱም ልጅ ስለሌላቸው ይንቋቸው ይጠሏቸው፤ መሥዋዕታቸውንም ለመቀበል እምቢ ይሉ ነበር።

ኢያቄምም ፈጽሞ አዘነና ስእለቴን እስኪሰጠኝ ወደእኔና ወደሚስቴም እስኪያይ ድረስ አልመገብም አልጠጣምም ብሎ ሱባኤ ለመያዝ ወደ ገዳም /በረሓ ወጣ። ሰባቱ ሰማያት እንደመጋረጃ ተገልጠው ነጭ ወፍ ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥ በራእይ አየ።

ታላቁ የፋሲካ በዓል በደረሰ ጊዜ አንዲት የመንደሩ ሴት ወደሐና መጥታ ለምን ታዝኛለሽ? ራስሽንስ ለምን ትጎጃለሽ? በዓል ስለደረሰ መምህሬ የሰጠኝን ይህንን ልብስ ልበሺ ልብሱ የነገሥታት ልብስ ነውና አንቺ ትለብሽው ዘንድ ይገባሻል አለቻት።

ሐና ግን አዝና ነበርና ብቸኛ በመሆኔ፣ ልጅም ስለሌለኝ ኀዘንተኛ ነኝና ያማረ ልብስን አለብስም፤ ደግሞም ማን እንደሰጠሽ በምን አውቃለሁ? እኔንም ከኃጢአትሽ ልትጨምሪኝ ነውን? አለቻት። ሴቲቱም በምላሹ ተናዳ እግዚአብሔር ማኅጸንሽን በመዝጋቱ ደግ አድርጓል አለቻት።

ሐናም ከቀድሞው አብልጣ አዘነች። ፈጥና ተነስታም ወደቤተ መቅደስ ሔደች። አእዋፋትንም ከልጆቻቸው ጋር ባየች ጊዜ አንስሳት አራዊት ልጆች አላቸው፤ ምድር እንኳን ፍሬ አላት ለእኔ ግን ልጅ የለኝም፤ ለሁሉ ልጅ አለውና ለእነርሱ ልጅን የሰጠህ ወደእኔ ተመልከት ልጅንም ስጠኝ ብላ እያለቀሰች ትጠይቅ ነበር።

ቅድስት ሐና ሆይ እግዚአብሔርስ አንቺን ሳይመለከት ቀርቶ አይደለም። ከተናገረው ቀን ሳያጓድል ይመጣ ይወርድ ይወለድ ዘንድ ያለበትን ጊዜ እየጠበቀ ነበር እንጂ። እነሆም ቀኑ ደረሰ እግዚአብሔርም ወደአንቺ አየ ስእለትሽን ሰማ ልመናሽንም ተቀበለ ልጅንም ሰጠሽ፤ በአንቺም ዘንድ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም "ነጸረ አብ እምሰማይ ወኢረክበ ዘከማኪ" ያላትን ከፍጡራን መካከል አምሳያ የሚተካከል የሌላትን አንድያ እናቱን አገኘ።

ቅድስት ሐናም ነጭ ርግብ መጥታ በራሷ ላይ ተቀምጣ ከራሷ ላይም ወርዳ በጆሮዋ ገብታ በማሕፀኗ ስትተኛ በራእይ ተመለከተች። እነሆም በሐምሌ 30 ቀን የጌታ መልአክ (ቅዱስ ገብርኤል) ከሰማይ ወርዶ በፊቷ ቆመ፤ ጸሎትሽ ተሰምቷል ልምናሽንም ተቀብሏል ትፀንሻለሽ አላት። እርሷም ልጅን ከሰጠኝስ እስከ ዘመኑ ፍጻሜው ድረስ እንዲያገለግል ለእግዚአብሔር እሰጣለሁ አለች። መልአኩም ወደ ኢያቄምም ሔዶ ይህንን ብሥራቱን አበሠረው።ኢያቄምም ተደስቶ ሁለት በጎችንና 12 ላሞችን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።

አንድ ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ እመቤታችን ቅድስት ንጽሕት ብጽእት ድንግል ማርያምም ነሐሴ 7 ቀን በብሥራተ መልአከ በንጹሕ መኝታ ተጸነሰች። ስለ ጽንሰቷም የብሕንሳው ሊቀጳጳስ አባ ኅርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ላይ "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ .... ድንግል ሆይ ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነሽ አይደለሽም በሕግ በንጹሕ መኝታ ከኢያቄምና ከሐና ተወለድሽ እንጂ... በማለት ንጹሕ ከሆነ አልጋ ንጹሕ ከሆነ መኝታ መገኘቷን ይናገራል። ጠቢቡ ሰሎሞንም.. ወዳጄ ሆይ ሁለንተናሽ ውብ ነው፥ ምንም ነውር የለብሽም።.. (መኃ 4፥7) ብሎ ከማኅጸን ጀምሮ ጥንተ አብሶ እንደሌለባት ያስረዳናል።#ተአምረ_ማርያም_እምማኅፀነ_ሐና
ሐናና ኢያቄም ይባረኩ ዘንድ ወደ ቤተመቅደስ ሔዱ። ዘካርያስም መልአኩ ለሐና እንዲነግራት ያዘዘውን ልትባረክ ስትመጣ ይነግራት ጀመረ።"ሐና የምነግርሽን ነገር ስሚ፤ በልቦናሽም ጠብቂው ከዚህ በኋላ ከባልሽ ከኢያቄም ጋር አትተኚ፤ በማኅጸንሽ ያለው ፍሬ ለእግዚአብሔር ንጹሕ መሥዋዕት ነውና። ይኸውም በዚያን ዘመን ሙሴ የተመለከተው ዕጽ ነው። በውስጡም እሳት ይነድ ነበር፤ ፍሬውንም አላቃጠለውም፤ ይኽም በበረሓው ድንኳን ውስጥ ያስቀመጡትን የወርቅ መሶብ፣ ከሰማይ የወረደ፣ ለዓለሙ ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ የተሰወረ መና ያለበት ነው። ዛሬም ለእግዚአብሔር የተቀደሰና ንጹሕ ቁርባንን እስከምትወልጂ ድረስ (ከጉድፍ) ከጉስቁልና ትጠበቂ ዘንድ አዝዝሻለው። ሥራውንም ለዓለሙ ሁሉ ለልጅ ልጅ ይናገራሉ አላት።" ሐናም ይኽን ነገር በልቧ እየጠበቀች በረከትን ተቀብላ ወደቤቷ ሔደች።

ዘመዶቿና ጎረቤቶቿም በሐና መጽነስ ተደስተው ይጎበኟቸው ነበር። ከእነዚህም መካከል ሀና ቤርሳቤህ የተባለች የአጎቷ የአርሳባን ልጅ ተደንቃ ማኅጸኗን ስትዳስሳት አይኗ በርቶላታል።

ሌላም ሐና የምትወደው ሳሚናስ ወልደ ጦሊቅ በሞተ ጊዜ ተግንዞ ወደተኛበት ሄዳ የአልጋውን ሸንኮር ይዞ በምታለቅስበት ወቅት ጥላዋ ቢያርፍበት ከተኛበት ተነስቶ .. ሰማይንና ምድርን ለፈጠረው አምላክ አያቱ የተባልሽ ሐና ሰላም ላንቺ  ይሁን .. አላት፤ አይሁድም ደንግጠው ምን አይተህ እንዲህ አልክ? አሉት።

እርሱም "ከዚህ ከሐና ማኅጸን የምትወለደው ሕጻን ሰማይ ምድርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኗት ሰማኋቸው፤ እኔንም ያነሣችኝ እርሷ ናት" አለ በዚህም አይሁድ በማኅጸን ባለች ጽንሷ እንዲህ ካደረገች በእኛ ልትሰለጥን አይደለምን ብለው በምቀኝነት ተነሳሱባት። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ለኢያቄም ተገልጾ ሐናን ሊባኖስ ወደሚባል ተራራ እንዲወስዳት ነገረው።#ጊዜ_ልደት_በደብረ ሊባኖስ

ሐናና ኢያቄምም በደብረ ሊባኖስ እያሉ ግንቦት 1 ቀን ሐና እመቤታችንን ወለደች። ቅዱስ ያሬድም ይህንን በማሰብ ...ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ፤ ሰማዮሙኒ አስረቀት ፀሐየ። ኢያቄምና ሀና ሰማይን ወለዱ፤ ሰማይቱም ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስን አወጣችልን  ... አለ።

ስለ ጊዜ ልደቷም ሲናገር "በእንተ ልደታ ለማርያም አድባር ኮኑ ኅብስተ ሕይወት ወእምዕጸወ ገዳምኒ ፈረዩ አስካለ በረከት" .. ድንግል ማርያም ስትወለድ ድንጋዮቹ ተራሮቹ ሁሉ የሕይወት እንጀራ (ምግብ) ሆኑ እጽዋትም ሁሉ የሕይወት ፍሬ አፈሩ በማለት ይገልጽልናል።

ሐናና ኢያቄምስ ወላጅነታችሁ ድንቅ ነው። በእውነት በመጽሐፍስ መካን የነበሩ ብዙ ደጋግ ቅዱሳን የተባረከ ልጅን ወልደዋል። እናንተ ግን ለፍጥረተ ዓለም በጸጋ፤ ለፈጣሪ ደግሞ በግብር እናት የምትሆንን ልጅ ወልዳቹሃልና። ለእናንተ ልጅ ናት ለኢየሱስ ክርስቶስ ግን አንድያ እናቱ ናት።

አብርሃምና ሣራ ብሩክ ዘር የሚሆን ይስሐቅን ወለዱ፤ ሐናና ኢያቄም ግን የምድርን አሕዛብ ይባርክ ዘንድ አምላክ የሚወለድባትን ዘር ለዓለም ሰጡ።

ሐና አልቅሳ ለእሥራኤል መስፍን ለቤተ መቅደስም አገልጋይ የሚሆን ሳሙኤልን ወለደች፤ ሐናና ኢያቄም ግን ለአማናዊው ድኅነት መፈጸሚያ የሆነች ቤተመቅደስን ወለዱ።

ራሔል አልቅሳ ያዕቆብንና ዘሩን ከምድራዊ ረኃብ ከጊዜያዊ ሞት ለጊዜው የሚቤዣቸውን ዮሴፍን ወለደች፤ ሐናና ኢያቄም ግን አዳምን ከነልጆቹ ከዘለዓለማዊው ሞት አንስቶ ለዘለዓለማዊ ድኅነት በማብቃት የሚቤዣቸውን ክርስቶስን  የምታስገኘውን፤ እርሷም በፍቅሯ እየጠራች ስለኃጢአታቸውም ምሕረትን እየለመነች የምታድናቸውን መድኃኒት ወለዱ።

ሐናና ኢያቄምስ ከዚህ በፊት ከነበሩት ወላጆች ሁሉ ከበሩ፤ በክብር በሞገስም ከፍ ከፍ አሉ ለአምላክ አያቱ ሆነዋልና፤ ዘርን በማስቀረት ረድኤቱን በማድረግ ለአዳምና ለልጆቹ ሲሰጥ ለነበረ አምላክ እናቱን ስጦታ/መባዕ አድርጋችሁ ሰጥታቹሃልና። ይኸውም መባዕ ቅድሚያ ብቸኛ እናት ልትሆነው የምትችለውን (እስከ እርጅና ያለልጅ የቀራችሁበትን ጊዜ በእምነት ታግሳችሁ ከሌላ ሳትሄዱ) በመውለዳችሁ፤ ሁለተኛም ለእርሱ አገልጋይ ሆና ነየ አመቱ ለእግዚእነ ... እኔ ለጌታ ባሪያው ነኝ .. የምትል ለታላቂቱ አገልግሎት (ለድኅነተ አዳም) የተመረጠች ልጅን ስለሰጣችሁ ነው።

"ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ነዪ፤ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና (ሃይማኖት) ራስ ከሳኔርና ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች።"

              🕯መኃ 4፥8🕯

ጠቢቡ ሰሎሞን በትንቢት መነጽር ልደቷን ተመልክቶ በሊባኖስ እንደምትወለድ በሳኔር በተመሰለ ከኢያቄም በኤርሞንም በተመሰለች ከሐናም እንደምትወለድ፤ የአንበሶች የነብሮች ተራራ በማለት ከሁለቱ ኃያላን ከቤተ መንግሥት እና ከቤተ ክህነት ወገን እንደምትወለድ ተናግሯል።

የእመቤታችን ልደት የተከናወነው በደጅ፤ ከፍ ባለ ተራራ ላይ ነው። በዚህ መወለዷም የእርሷ ልደት ለዓለም ሁሉ ጥንተ መድኃኒት መሆኑና ለሁሉ የተሰጠች ስጦታ መሆኑን ለማመልከት ነው።

በስደት ላይ ያለ ሰው የላመ የተዘጋጀ ምግብ የለውምና ሐናና ኢያቄም ንፍሮ እየበሉ እመቤታችንን በደብረ ሊባኖስ መውለዳቸውን በማሰብ በዓሉን ከደጅ ወጥተን ንፍሮ በመብላት እናከብረዋለን። በበዓሉም ምዕመናን ለከርሞ ብንደርስ በማለት ብጽዓት/ ስእለት ይሳላሉ። ዕለቱን ከኪዳን ከማኅሌት ከቅዳሴው በመሳተፍ፣ ቅዱስ ቁርባኑን በመቀበል፣ ጸበል በመጠጣት በመጠመቅ፣ የእመቤታችንን የምስጋና መጻሕፍትን በተለይም መልክአ ልደቷን በማድረስ፣ በመመጽወት የታመሙትን የታሰሩትን በመጠየቅ ማክበር ይገባናል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።                                 
                              ዋቢ መጻሕፍት
1.መጽሐፍ ቅዱስ የ፳፻ ዕትም
2.ድርሳነ ማርያም
3. መኃልይ መኃልይ ዘሰሎሞን ማብራሪያ በመጋቤ ሐዲስ ስቡሐ አዳምጤ
4. መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ ትንሳኤ ዘጉባኤ እትም
5.የእመቤታችን በዓላት በመ/ር ተስፋሁን ነጋሽና መ/ር ኤርምያስ ወ/ኪሮስ
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!

https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
https://www.tg-me.com/addlist/hVsJ5h6oKyk1NDRk
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!

https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!

https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
https://www.tg-me.com/addlist/kAVvN-thJG44YzA0
ግንቦት12 ዳንኤል በአንበሳ ጉድጓድ በተጣለ ጊዜ ቅ.ሚካኤል ነብዩ ዕንባቆምን በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደእርሱ ወስዶት ምግብ እንዲመገብ አድርጎታል
ዳግመኛም የአቡነ ተክለሃይማኖት አጽማቸው የፈለሰበት፣ የቅ.ክርስቶስ ሠምራ ልደቷና ከሲኦል ነፍሳትን ያወጣችበት፣ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ ያረፈበት ዓመታዊ ክብረ በዓላት ናቸው
ምን ጥቂት ነገር አለህ?

       ጌታችን እርሱን ተከትለው የወጡትን የአምስት ገበያ ህዝብ(አምስት ሺ አባውራ) አመሻሹ ላይ ሐዋርያት የሚበላ ስለሌላቸው እንዲያሰናብታቸው ጠየቁት።  እርሱ ግን የሚበሉት እንዲሰጧቸው ነገራቸው አሁን ጌታችን ያላቸው ምግብ ለህዝቡ እንደማይበቃ ጠፍቶት አይደለም ነገር ግን ችግራችንን ጉድለታችንን ሊሞላልን ሲፈልግ አስቀድመን ችግራችንን ልንነግረው ይፈልጋልና ሐዋርያቱ ያላቸው ምግብ ትንሽ መሆኑን እንዲነግሩት ነበር ። ወዳጄ አንተስ ችግርህ ምንድን ነው? ልታደርገው አቅደህ አልበቃ ያለህ ምንድን ነው? በአገልግሎት በመንፈሳዊ ህይወት ልትተጋ አስበህ ምን ጎሎህ ነው የነበሩህን እቅዶች ለመሸኘት የተገደድከው? ከቃሉ ከአገልግሎቱ  የራከው ምን አንሶህ ነው? ጊዜ አጥሮህ ነውንን? ትጋት አጥሮህ ነውን? ትዕግስት አጥተህ ነውን? ምንድን ነው ያነሰህ? ብቻ ችግርህን ንገረው እርሱ ያነሰህን ነገር አበርክቶ  ተትረፍርፎህ ታየዋለህ።

           ለጌታችን ሐዋርያት ያለን ሁለት ዓሳና አምስት እንጀራ ብቻ ነው አሉት። አሁን ይህ ምግብ  እንኳንስ ለህዝቡ ይቅርና ጌታችንንና ደቀመዛሙርቱን እንኳን በቅጡ የሚያጠግብ  አልነበረም ነገር ግን ሐዋርያቱ እጅ ላይ የነበረውን  ጥቂቷን ነገር ሠጡት እርሱም ባርኮ አበርክቶ አምስትሺውን ህዝብ አብልቶ 12መሶብ ከተረፈው ተሰበሰበ።

         ወዳጄ እጅህ ላይ ምን አለ? በእጅህስ የያዝከው ምን አለ? ጥቂት ነው ለምንም አይበቃም ያልከው ምናልባት መኖሩንም የረሳኸው ሊሆን ይችላል እርሱን ይዘህ ቅረብ ለእርሱም ስጠው እርሱ ባርኮ መልሶ ይሰጥኻል። ከብዙ የዓለም መባዘን የተረፈህ ትንሽ ጊዜ አለህ እርሱን እስኪ ለእግዚአብሔር ስጠው ያን ይባርክልኻል። ጉልበት አለህ እርሱንም ለእግዚአብሔር ስጠው አገልግልበት እውቀት አለህ እርሱንም ቢሆን ለእግዚአብሔር ስጠው። ያለህን ጥቂት ነገርም ቢሆን ስጠው እርሱ ባርኮ ሲመልስል ትልቅና ካሰብከውም በላይ ነው።እመ ሣሙኤል ሃናን ተመልከት ህፃኑን ሣሙኤል ለእግዚአብሔር ሰጠችው እርሱም በሞገስና በጥበብ አሳድጎ ታላቅ ነቢይ የእስራኤልም አባት ንጉስን ቀብቶ የሚሾም አደረገው ። ኢያቄምና ሃናንም ተመልከት የ3 ዓመት ህፃን እመቤታችንን ሰጡት እርሱም የዓለም እናት አድርጎ ሠጣቸው የወለዷት እናት ሆነቻቸው መርታም ወደ ገነት አስገባቻቸው። አንተም ያለህን ጥቂት ነው የምትለውንም ቢሆን ስጠው ካሰብከው በላይ አድርጎ ይሰጥኻልና። ወዳጄ ሆይ አንተስ ምን አለህ? መቼም ምንም የለኝም አትለኝም ሰጪው እግዚአብሔርን በሐሰት መክሰስ ይሆንብሃልና ቢያንስ ሕይወት አለህ፤ ይህን ጹሑፍ ማንበብህ በራሱ ማንበብ የምትችል በመሆንህ ነው። ልክ እንደዚሁ ሁሉ አንተ መኖሩን እንኳን የረሳኸው ያም ባይሆን ጥቂት ነው ይህማ ለምንም አይበቃም ያልከው ነገር አይጠፋምና እርሱን ይዘህ ወደ እግዚአብሔር ቅረብ ያ ጥቂት ነው ያልከው ተትረፍርፎ ትመለከታለህ።

ወዳጄ ሆይ ጥቂትም ብትሆን ምን አለህ?
ግንቦት 21 ጌታችን በተነሳ በአርባኛ ቀኑ ሐዋርያት እያዩት ያረገበት ቀን ሲሆን ዳግመኛ ከእመቤታችን 33ቱ አበይት በዓላት መካከል የሆነው ከግንቦት21-25 እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ5 ተከታታይ ቀናት በአካል ትገለጥበት የነበረው በዓል መታሰቢያ አመታዊ ክብረ በዓሎች ናቸው
ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes

https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
Forwarded from Elohe pictures
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes

https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
https://www.tg-me.com/addlist/Ka6_NP6UoaYyOWZk
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes

https://www.tg-me.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://www.tg-me.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
https://www.tg-me.com/addlist/A7U6XVGLALJlNjI0
ተመልከተኝ

          ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያች እለተ ምስጢር (በእለተ ሐሙስ) ስለሚገጥመው መከራ እያነሳ ሲነግራቸው ከሐዋርያቱ መካከል ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ “ ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ ”ሉቃስ 22፥33 እያለ ቢናገርም ጌታ ግን መልሶ እንዲህ ብሎታል፦“ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው።” ይህ ሆነ በኋላ በዚች ምሽት ጌታችን ከተያዘ በኋላ በጲላጦስ ግቢ ከደቀመዛሙርቱ መካከል የተገኙት ሁሉቱ ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ዮሐንስ ብቻ ነበሩ።

           ቅዱስ ጴጥሮስ እሳት ለመሞቅ ወደ እሳቱ ቢጠጋ አንዲት ታናሽ አገልጋይ(ገረድ) ቀርባ ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለች። እርሱ ግን አንቺ ሴት አላውቀውም ሲል  መረቡን በአሳ የሞላለትን አማቱን ከንዳድ የፈወሰለትን አምላክ ካደ። ከጥቂት ቆይታ በኋላም ደግሞ አንዱ አይቶት አንተ ደግሞ ከእርሱ ወገን ነህ አለው። አንተ ሰው እኔ አይደለሁም ብሎ ከአንተ ወደ ማን እንሔዳለን አንተ የዘለዓለም የህይወት ቃል አለህ ብሎ የመሰከረለትን አምላክ በደብረ ታቦር ለጥቂት ደቂቃ  ብርሃነ መለኮቱን ገልጦ ቢያሳየው ከእርሱ ጋር ለዘለዓለምን መኖር ሽቱ 'በዚህ መኖር መልካም ነው።' እንዳላለ  ከእርሱ ጋር የነበርኩ እኔ አይደለሁም ሲል በድጋሚ ካደ። ከአንድ ሰዓት በኋላ ሌላኛውም መጥቶ፦እርሱ የገሊላ ሰው ነውና በእውነት ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለ። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ከቀድሞ አብልጦ እየማለና እየተገዘተ ከአሳ ማጥመድ አውጥቶ ሰው አጥማጅ ያደረገውን የመንግስተ ሰማይ ቁልፍ የሰጠውን አምላክ ሙት ያስነሳ ህሙማንን ይፈውስ አጋንንትን ያስወጣ ዘንድ ሥልጣን የሰጠውን ከአንተ ጋር ለመሞትም ዝግጁ ነኝ ያለውን አምላክ አላውቀም  አለ።

         ጴጥሮስ ለሶስተኛ ጊዜ አላውቀውም ብሎ ገና ሲናገር ዶሮ ጮኸ።በዚህ ጊዜ  ጌታ ጴጥሮስን ዘወር ብሎ ተመለከተው። ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ። ጴጥሮስ ሆይ ያስለቀሰህ ምን ይሆን ዐይንህን በእንባ የሞላው ልቦናህን ለጸጸት ያተጋው እግርህንስ ለንስሐ ያሮጠው ምንድን ነው?  የሂፖ ሊቀ ጳጳስ አውግስጢኖስ ስለዚህ ነገር እንዲህ ይላል "ክርስቶስ ባይመለከተው ኖሮ ባላለቀሰ ነበር።" ጴጥሮስን ለጸጸት ለእንባ ለንስሐ ያሮጠው የክርስቶስ መመልከት ነበር። ጌታዬ ሆይ አለቅስ ዘንድ የምትመለከተኝ መቼ ነው? ለበደሌ የምትተወኝ እስከመቼ ነው?  ስንቴ ስበድልህስ ይሆን ዞረህ የምትመለከተኝ? ቁጥር አልባ ጊዜ በግብሬ ህልውናህን ክጃለው ታዲያ እኔን አትመለከተኝምን? ያ ጴጥሮስ ሊቋቋመው ያልቻለውን ዐይንህን የምታሳየኝ አንተስ የምትመለከተኝ መቼ ነው?

         ጌታዬ ሆይ እባክህን ተመልከተኝ ያለ አንተ ከዚህ ጎስቋላ ህይወት ከኃጢአትም ኑሮ ሊታደገኝ የሚችል የለምና።  የቅዱሱን አባት ጸሎትም ጸሎቴ አድርጌ እማጸንሀለው፦ "አቤቱ በደሌንና ነውሬን የሚያጥብ ዕንባን ሥጠኝ፤ አቤቱ አንተን የሚያገለግል ዕንባን ሥጠኝ፤ አቤቱ የሚያቃጥል ዕንባን ስጠኝ፤ አቤቱ ከዐይኔ ፈስሶ የአካሌን እድፍ የሚያጥብልኝን ዕንባን ስጠኝ፤ የተጸጸቱ ሰዎችን ዕንባ የምትቀበል  ጌታ ሆይ አንተ የተቀበልከውን ጽኑ ልቅሶ እንዳለቀሰ እንደ ጴጥሮስ ያለ ዕንባን ሥጠኝ፤ አቤቲ እንደ ባህር የምትፈስስ እንባን እጠበኝ የማያቋርጥ የዕንባን ጎርፍ አፍስስልኝ" (ውዳሴ አምላክ ዘእሁድ) ጌታዬ ሆይ ኃጢአቴን አስቤ በእንባ እታጠብ ዘንድ እባክህን ጴጥሮስን በተመለከትክበት ዐይንህ ተመልከተኝ።

"ጌታችን ሆይ ወደ እኛም ተመልከት ስለ ኃጢአታችንም እንድናለቅስ አድርገን" ሊቁ አምብሮስ
2025/06/28 02:12:44
Back to Top
HTML Embed Code: