Telegram Web Link
"ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!"
ታላቁ ቅዱስ ጎሮጎርዮስ
"ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።"
#ቅዱስ_ሚናስ
#አዲስ_መረጃ

የgroup & የchannel Logo ስራልን ብላችሁ የጠየቃችሁ ! Nice creative ሰርቶ ስላበቀ ከነገ 20/1/2016 ዓ.ም ጀምሮ መጠየቅ ትችላላችሁ !

አሁን ቢሆን በነፃ ለ group ወይም ለ channel ማሰራት የምትፈልጉ 👉 @nice_creative_bot ያናግሩን ::
Forwarded from ኦርቶዶክስ bot
በነፃ Logo ለ group ወይም ለ channel ማሰራት ይፈልጋሉ ?
በአዲስ መርሐ ግብር በቅርቡ እንጀምራለን
አብርሃም ከሌላ ሴት(ከባርያው)የወለደው ልጅ ስሙ ማን ነው?
ገብርኤል ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን !

ሀገራችንን ሰላሟን ይመልስልን


ገብርኤል

@mehereni_dngl
አዳዲስ ነገሮችን ለማግኘት

Subscriber and share
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@all_football_1_?si=XXk_-ygKMa3B7NLp
መሐርኒ ድንግል pinned «አዳዲስ ነገሮችን ለማግኘት Subscriber and share 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@all_football_1_?si=XXk_-ygKMa3B7NLp»
††† እንኳን ለኢትዮዽያውያን ሰማዕታት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ኢትዮዽያውያን ሰማዕታት †††

††† በ1929 ዓ/ም: የካቲት 12 ቀን ከ30,000 በላይ ኢትዮዽያውያን አባቶች: እናቶች: ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ደማቸው ፈሷል:: እነዚሕ ወገኖቻችን ደማቸው እንደ ጐርፍ አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰው ስለ ሃገር ፍቅር ብቻ አልነበረም:: ስለ ቀናች ሃይማኖት ተዋሕዶ ጭምር ነው እንጂ::

††† ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግፃዌ ላይ ስማቸውን ጽፋ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር እንዲህ ታስባቸዋለች::

"አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ::
የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ::
የሚቀብራቸውም አጡ::"
(መዝ. 78:1)

††† ሰማዕታቱን እናስባቸው!

††† ሶምሶን ረዓይታዊ †††

††† እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን: 22ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ: በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ: ነቢይና ካህን አድርጐ: ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::

አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ100 ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::

ስለዚህም ምክንያት ለ5,500 ዓመታት ትንቢት ሲነገር: ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር: ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ: የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::

ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::

ከእርሱም ይስሐቅ: ከዚያም ያዕቆብ (ደጋጉ) ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ርሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::

በዚያም ለ215 ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::

ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ9 መቅሰፍት: በ10ኛ ሞተ በኩር: በ11ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::

አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ሶምሶን ረዓይታዊ ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት 4,200 ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::

በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሔርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::

በጊዜውም የእሥራኤል ኃጢአት ስለ በዛ ኢሎፍላውያን (ፍልስጤማውያን) 40 ዓመት በባርነት ገዟቸው:: ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ልጅ በማጣት ያዘኑ ማኑሄ እና ሚስቱ (እንትኩይ) : በቅዱስ ሚካኤል ተበሥረው ኃያሉን ሶምሶንን ወለዱላቸው::

እርሱም ናዝራዊ (ከእናቱ ማኅጸን ለጌታ የተለየ) ነበርና ፍልስጤማውያንን ቀጥቶ ወገኖቹን እስራኤልን ከባርነት : በአምላኩ ኃይል ታደገ:: ከኃይሉ ብዛት የተነሳም:-
¤አንበሳን እንደ ጠቦት ይገድል (መሣ. 14:5)
¤300 ቀበሮዎችን አባሮ ይይዝ (መሣ. 15:3)
¤በብርቱ ገመዶች ሲያስሩት እንደ ፈትል ይበጣጥሰው (መሣ. 15:14)
¤በአህያ መንጋጋ ሽህ ሰው ይገድል (መሣ. 15:15)
¤ጠባቂዎችን ከነ መቃናቸው ተሸክሞ ይወረውር ነበር:: (መሣ. 16:3)

ውሃ ሲጠማውም ከአህያ መንጋጋ ላይ ፈልቆለት ጠጥቷል:: (መሣ. 15:18) በፍጻሜው ግን ደሊላ በምትባል ሴት ተታልሎ ምሥጢሩን በመግለጡና ጸጉሩ በመላጨቱ ኃይሉን አጥቷል:: ጠላቶቹም ዐይኑን አውጥተው መዘባበቻ አድርገውታል::

በፍጻሜው ግን ኃይሉ እንዲመለስለት ፈጣሪውን ለምኖ : አሕዛብ ለጣኦት በዓል እንደተሰበሰቡ የአዳራሹን ምሰሶ አፍርሶ አጥፍቷቸው ዐርፏል:: (መሣ. 13--16)
ቅዱስ ሶምሶን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ (ምሳሌ) ነው::

††† በዘመኑ ሁሉ ቅዱስ ሚካኤል ረድቶታልና በዚህች ቀን መታሠቢያው ይደረግለታል::

††† የካቲት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1."30,000" ሰማዕታተ ኢትዮዽያ (ሮማዊው ፋሽስት የገደላቸው)
2.ቅዱስ ሶምሶን ረዓይታዊ (የእስራኤል መስፍን)
3.ቅዱስ አባ ገላስዮስ ገዳማዊ
4.ቅድስት ዶርቃስ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ
4.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
5.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
6.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
7.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
8.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ

††† አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† "ሶምሶንም:- 'ስለ ሁለቱ ዓይኖቼ ፍልስጥኤማውያንን አሁን እንድበቀል : እግዚአብሔር አምላክ ሆይ! እባክህ አስበኝ? አምላክ ሆይ! . . . እባክህ አበርታኝ?' ብሎ እግዚአብሔርን ጠራ:: . . . ሶምሶንም:- 'ከፍልስጤማውያን ጋር ልሙት' አለ:: ተጐንብሶም ምሰሶዎችን በሙሉ ኃይሉ ገፋ:: . . . በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ::"
(መሣ. 16:28)

††† "እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." †††
(ዕብ. 11:32)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
2024/05/23 21:52:03
Back to Top
HTML Embed Code: