Telegram Web Link
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል!

@melkam_enaseb
9789240053052-eng.pdf
5.2 MB
The WHO guidelines on mental health at work

The WHO guidelines on mental health at work provide evidence-based recommendations to promote mental health, prevent mental health conditions, and enable people living with mental health conditions to participate and thrive in work. The recommendations cover organizational interventions, manager training and worker training, individual interventions, return to work, and gaining employment. The guidelines on mental health at work aim to improve the implementation of evidence-based interventions for mental health at work.

@melkam_enaseb
#ምሉዕፋውንዴሽን

ምሉዕ ፋውንዴሽን ሀገርበቀል የበጎአድራጎት ድርጅት ሲሆን ባለትዳሮቹ ወ/ሮ ትዕግስት ኃይሉ እና አቶ ክንፈ ጽጌ የበኩር ልጅ በኦቲዝም ጥላ ስር የሚኖር ታዳጊ በመሆኑ እርሱን በማሳደግ ሂደት ያጋጠሟቸው ውጣ ውረዶችና ያካበቷቸውን ልምዶች ለሌሎች ለማጋራት በማሰብ እንዲሁም በሥራ አጋጣሚ ያካበቱትን ልምድና ዕውቀት በመጠቀም የተቀናጀ ማሕበረሰብ ለመፍጠር በማሰብ የተቋቋመ ድርጅት ነው።

ምሉዕ ፋውንዴሽን በአሁኑ ጊዜ ለማሕበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር፣ እንዲሁም ወላጆችን በማማከር፣ ለተንከባካቢዎች፣ ለትምህርት ቤቶች እና አገልግሎት ሰጪዎች ስልጠና በመስጠት በተጨማሪም በማዕከሉ ቤተመጻሕፍት በማቋቋም ማህበረሰቡን በማገልገል ላይ ይገኛል።

በተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥም ሰፊ ጥናት በማካሄድ ለልዩ ፍላጎት ልጆችና ወላጆቻቸው የሚሆን የቴራፒ ማዕከል ለማቋቋም እየሰራ ይገኛል። የቴራፒ ማዕከሉን ለማቋቋም የሚያስፈልገው ከፍተኛ ገንዘብ በመሆኑ ወጪውን ለመሸፈን ጥር 25/2015 በሸራተን ሆቴል የእርዳታ ማሰባሰቢያ የእራት መርሐ ግብር አዘጋጅቷል። ለዚህ ዓላማ ዕውን መሆን እያንዳንዳችን የድርሻችንን እንወጣ ዘንድ ጥሪውን ያቀርባል።

በስልክ ቁጥር 0906243432/ 0941024444 ይደውሉልን።

ፕሮጀክቱን ለመደገፍ: አቢሲኒያ ባንክ
አካውንት ቁጥር 75031963
ስዊፍት ኮድ ABYSETAA

#Mentalwellness

@melkam_enaseb
#የመጽሐፍጥቆማ

"በህዝብ ፊት የመናገር ክህሎት" በሚል ርዕስ በብሩክ ወልዴ የተዘጋጀው መጽሐፍ ለአንባቢያን ቀርቧል።

ይህ መጽሐፍ በህዝብ ፊት የመናገር ጠቃሚ ክህሎት ማዳበር የምትችልባቸውን መመሪያዎች በግልጽ ያቀርብልሃል፡፡

መጽሐፉ የሚያነሳቸው ነጥቦች፦

1.በህዝብ ፊት የመናገር ክህሎት መሠረታዊያን
2.የመልዕክትን ርዕስ መምረጥ እና ግብን መቅረጽ
3.ድጋፍ ሰጪ ሃሳቦችን ማደራጀት
4.የመድረክ ንግግር ቅድመ ዝግጅት
5.መልዕክትን ማዋቀርና አስተዋጽዎ መንደፍ
6.መግቢያ እና መደምደሚያን ማዘጋጀት
7.የቋንቋ አጠቃቀም
8.አካላዊ ቋንቋን አጠቃቀም
9.የድምጽ አጠቃቀም
10.ልምምድ
11.በህዝብ ፊት የመናገር ፍርሃትን መገንዘብና መቆጣጠር
12.አስረጅ ምሳሌዎችን ስለመጠቀም
13.የፓወር ፖይንት አጠቃቀም
14.ጥያቄና መልስን በብቃት ማስተናገድ
15.የመድረክ ተናጋሪ ሥነ-ምግባር

መጽሐፉን ጃዕፈር መጻሕፍት መደብር ያገኙታል። አድራሻ: ለገሃር ኖክ ነዳጅ ማደያው አጠገብ ተወልደ ሕንጻ ስር።

@melkam_enaseb
የመንፈስ ጭንቀትን ለማስወገድ!

የመንፈስ ጭንቀት በማንኛውም ዕድሜ እና በማንኛውም ሰው ላይ ሊደርስ ይችላል። ሰዎች የመንፈስ ጭንቀትን ለማከም እንደ ፀረ-ጭንቀት ያሉ መድሃኒቶችን ይወስዳሉ፤ ነገር ግን የተለያዩ የተፈጥሮ ዘዴዎች ምልክቶቹን ለመቆጣጠር እና የወደፊት አደጋ ለመቀነስ ይረዳሉ።

እንግዲያውስ ቀጣዮቹን የባለሙያ ምክሮች ይከተሉ፦

- ትኩረት የምናደርግበትን ነገር መምረጥ፣

- የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን መመጠን፣ የምንሰማውን ዜና መምረጥ፣

- በቂ የእረፍትና የመዝናኛ ጊዜ መውሰድ፣

- በቂ እንቅልፍ ማግኘት፣

- አልኮል እና አደንዛዥ ዕፅ አለመጠቀም፣

- ትክክለኛውን ሰዓት የጠበቀና የተመጣጠነ አመጋገብን መከተል፣

- መጽሐፍ ማንበብ እና በቂ የአካል እንቅስቃሴ (ስፖርት) ማድረግ፣

- ጊዜንና ሰዓትን በአግባቡና በልኩ መጠቀም መልመድ፣

- መጨነቅ በማይገቡን ነገሮች አለመጨናነቅ፣

- ከችግሩ ይልቅ መፍትሔው ላይ ትኩርት ማድረግ፣

- ከቅርብ ቤተሰብና ወዳጆች ጋር በቂ ጊዜን ማሳለፍ፣

- ባለሙያ በማማከር የንግግር ሕክምና (Psychotherapy) ያግኙ።

መልካም እለተ ሰንበት!

@melkam_enaseb
“ሕይወት ብስክሌት እንደመንዳት ነው፡፡ ሚዛንህን ለመጠበቅ ካለማቋረጥ መንቀሳቀስ የግድ ነው” - Albert Einstein

መልካም የሥራ ሣምንት!

@melkam_enaseb
ዲስሌክሲያ| Dyslexia

ዲስሌክሲያ ማለት የንግግር ድምፆችን በመለየት፣ ደብዳቤዎች እና ቃላት የመማር ችግሮችንና ንባብን የሚያካትት የመማር ችግር ነው፡፡

ዲስሌክሲያ ቋንቋን በሚሠሩ የአንጎል አካባቢዎች ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል። ዲስሌክሲያ ያለባቸው ሰዎች መደበኛ የማሰብ ችሎታ ያላቸው እና ብዙውን ጊዜ መደበኛ የማየት ችሎታ አላቸው።

ምልክቶች፦

- የዲስሌክሲያ ምልክቶች ልጅዎ ትምህርት ቤት ከመግባቱ በፊት ለመለየት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል፤ ግን አንዳንድ የመጀመሪያ ፍንጮች ችግርን ሊያመለክቱ ይችላሉ፡፡

- አንዴ ልጅዎ ዕድሜው ለትምህርት ከደረሰ በኋላ ይሄን ችግር ለማስተዋል የልጅዎ አስተማሪ የመጀመሪያ ሊሆን ይችላል፡፡

- የዲስሌክሲያ ክብደት ይለያያል፤ ነገር ግን አንድ ልጅ ማንበብ መማር ሲጀምር ሁኔታው ​​ብዙ ጊዜ ይገለጣል።

ከትምህርት ቤት በፊት

አንድ ትንሽ ልጅ ዲስሌክሲያ የመያዝ እክል ሊያጋጥመው እንደሚችል የሚያሳዩት ምልክቶች የሚከተሉትን ያጠቃልላሉ፡፡

- ዘግይቶ ማውራት
- አዳዲስ ቃላትን በቀስታ መማር
- ቃላትን በትክክል የመፍጠር ችግሮች

ለምሳሌ፦ በቃላት ውስጥ ያሉ ድምፆችን መለወጥ ወይም በተመሳሳይ ድምጽ ቃላትን መተካት ችግሮች።

- ፊደሎችን፣ ቁጥሮችን እና ቀለሞችን የማስታወስ ወይም የመሰየም ችግሮች።

በትምህርት ዕድሜ
 
አንዴ ልጅዎ ትምህርት ቤት ውስጥ ከገባ የዲስሌክሲያ ምልክቶች የበለጠ ግልጽ ሊሆኑ ይችላሉ። ለምሳሌ፦

- የሚሰማውን የመስራት እና የመረዳት ችግሮች
- ትክክለኛውን ቃል የማግኘት ችግር
- ለጥያቄዎች መልስ የመስጠት ችግር
- የነገሮችን ቅደም ተከተል የማስታወስ ችግሮች
- በፊደላት እና በቃላት ተመሳሳይነት እና ልዩነቶች የማየት አልፎ አልፎም የመስማት ችግር
- የማይታወቅ ቃል አጠራር ድምፁን ማሰማት አለመቻል
- የፊደል አፃፃፍ ችግር
- ንባብን ወይም መጻፍን የሚመለከቱ ነገሮችን ወደ ጎን መተው
- ስራዎችን ባልተለመደ ሁኔታ ረዘም ላለ ጊዜ ማሳለፍ
- ንባብን የሚያካትቱ እንቅስቃሴዎችን ማስወገድ

ወጣቶች እና ጎልማሶች

በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ እና በአዋቂዎች ላይ የሚከሰት ዲስሌክሲያ ምልክቶች በልጆች ላይ ካሉት ምልክቶች ጋር ተመሳሳይ ናቸው።

በአሥራዎቹ ዕድሜ እና በአዋቂዎች ውስጥ አንዳንድ የተለመዱ ዲስሌክሲያ ምልክቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

- ጮክ ብሎ ማንበብን ጨምሮ የማንበብ ችግር
- ቀርፋፋ እና ጉልበት-ተኮር ንባብ እና ጽሑፍ
- የፊደል አጻጻፍ ችግሮች
- ንባብን የሚያካትቱ እንቅስቃሴዎችን ማስወገድ
- ስሞችን ወይም ቃላትን በስህተት መግለጽ ወይም ቃላትን ሰርስሮ የማውጣት ችግሮች
- ከተለዩ ቃላት (ፈሊጦች) በቀላሉ የማይገባ ትርጓሜ ያላቸውን ቀልዶች ወይም አገላለጾችን የመረዳት ችግር
- ንባብን ወይም መጻፍን የሚመለከቱ ስራዎችን ባልተለመደ ሁኔታ ረዘም ላለ ጊዜ ማሳለፍ
- ታሪክን የማጠቃለል ችግር
- የውጭ ቋንቋ መማር ላይ ችግር
- የማስታወስ ችግር
- የሂሳብ ስሌቶችን የመስራት ችግር

ዲስሌክሲያ በቤተሰብ ወይም በዘር ይሄዳል፡፡

የዲስሌክሲያ የሚያስከትሉ ምክንያቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦

- ዲስሌክሲያ ወይም ሌላ የመማር ችግር ያለባቸው የቤተሰብ ታሪክ
- ያለጊዜው መወለድ ወይም ዝቅተኛ ክብደት
- በእርግዝና ወቅት ለኒኮቲን፣ ለአደንዛዥ ዕፅ፣ ለአልኮል ወይም ለጽንሱ የአንጎል እድገትን ሊለውጥ ለሚችል ኢንፌክሽን መጋለጥ
- ንባብን በሚያስችሉት በአንጎል ክፍሎች ውስጥ ችግሮች

ዲስሌክሌሲያ የሚከተሉትን ችግሮች ጨምሮ በርካታ ችግሮችን ያስከትላል፦

- የመማር ችግር
- ማህበራዊ ችግሮች
- የባህሪ ችግሮች

ዲስሌክሲያ ያለባቸው ልጆች በትኩረት ማነስ/ ከመጠን በላይ የመነቃቃት ችግር ADHD የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው። በተቃራኒው ደግሞ ኤ.ዲ.ኤች. ዲ ዲስሌክሲያ ለማከም አስቸጋሪ እንዲሆን የሚያደርግ ትኩረትን እንዲሁም ከመጠን በላይ የመነቃቃት እና ስሜታዊነት ባህሪን የማስቀጠል ችግርን ያስከትላል፡፡

ህክምና

ዲስሌክሲያ መመርመር የሚችል አንድ ነጠላ ምርመራ የለም፡፡ የልጅዎ እድገት፣ የትምህርት ጉዳዮች እና የህክምና ታሪክ ምርመራ ውስጥ ይካተታሉ።

ዲስሌክሲያ የሚያስከትለውን መሠረታዊ የአንጎል ያልተለመደ ሁኔታ ለማስተካከል የሚታወቅ መንገድ የለም።

ዲስሌክሲያ የዕድሜ ልክ ችግር ነው፤ ሆኖም የተወሰኑ ፍላጎቶችን እና ተገቢ ህክምናን ለመወሰን ቅድመ ምርመራ እና ግምገማ ስኬታማነትን ሊያሻሽል ይችላል፡፡

የንግግር እና ቋንቋ ህክምና (Speech and Language Therapy) ባለሙያዎች ለዲስሌክሲያ ሕክምና ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ።

የንግግር እና ቋንቋ ህክምና ለማግኘት፦

ስልክ: 0978806778/ 0974088763

Akalu assefa (speech pathologist)

@melkam_enaseb
#የአእምሮጤና

ታሪኳን ለአል ዐይን አማርኛ ያጋራች ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች የአዕምሮ ህመምተኛ “የአዕምሮ ህመምተኛ እንደሆንኩ አላውቅም ነበር፤ ለምን ይህ አልሆነም እያልኩ አለቅስ ነበር፣ ቤተሰቦቼ አይወዱኝም ብዬም አስባለሁ፣ ለሁሉም ጥፋቴ በዙሪያዬ ባሉ ሰዎች ላይ አመካኝ ነበር” ትላለች።

“ባንድ ጓደኛዬ እርዳታ ከአንድ የአዕምሮ ሀኪም ጋር ተገናኝቼ ህክምናውን አገኘሁ” የምትለው ይህች ባለታሪክ” ህክምናውን ካገኘች ጊዜ ጀምሮ ደስተኛ እና አመስጋኝ መሆኗን ነግራናለች።

“ህክምናውን ባለመረዳቴ አልያም ቤተሰቦቼን ጨምሮ ብዙዎች ወደ አዕምሮ ህክምና እንድሄድ ባለማድረጋቸው ለብዙ ዓመታት ህይወቴ በስቃይ የተሞላ እንዲሆን አድርጎት ነበር፣ ባንድ ወቅት ራሴን ላጠፋ ጫፍ ላይ ደርሼ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ወደ ጤናዬ ተመልሼ ስራዬን እና ህይወቴን በሚገባ እየመራሁ ነው” ብላለች።

“ይሁንና ህክምናው ውድ እና ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ለማማከር እና መድሃኒት ዋጋ በሳምንት ከ800 ብር እስከ 2ሺህ ብር እያወጣሁ ነው ይህ እጅግ እየፈተነኝ ነው” ብላናለች።

አንድ ዜጋ ማንኛውንም አይነት ህመም ተሰምቶት በቀላሉ ባቅራቢያው ወዳለ የህክምና ተቋም ሄዶ እንደሚታከመው ሁሉ የዓዕምሮ ህመም ህክምናም ሊቀል ይገባል፣ ለዚህ ደግሞ መንግስት ለሌሎች ህመሞች ትኩረት በሰጠው ልክ ለአዕምሮ ህመም ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቃለች።

ወላጆች እና ማህበረሰቡ ጋር ስለ አዕምሮ ህመም ያለው አስተሳሰብ ትክክል አለመሆኑን የምትናገረው ይህች ባለታሪክ ሰዎች የአዕምሮ ህመም ሲያጋጥማቸው ታክመው መዳን እንደሚችሉ ማመን አለባቸውም ብላለች።

ብዙዎች ሰዎች በአመለካከት እና ተስፋ በመቁረጣቸው ምክንያት ራሳቸውን የሚያጠፉ፣ ቤት ተዘግቶባቸው በጨለማ የሚኖሩ እና በየቤተ እምነቶች ከነ ስቃያቸው የሚኖሩ እንዳሉም ነግራናለች።

ቤተሰቦቼ የተማሩ የሚባሉ ቢሆንም የአዕምሮዬ ጤና ሲታወክ ሰይጣን ይዟት ነው፣ ጸባያዋ ተበላሸ እና ትታሰር ይሉ ነበር የምትለው ይህች ባለታሪክ ስለ ህመሙ ለውጥ እንዲመጣ ከተፈለገ በሰፊው ማስተማር እንደሚያስፈልግም ጠቁማለች።

በአዲስ አበባ የአዕምሮ ህክመና እና ማማከር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት የስነ ልቦና እና የማህበረሰብ ጤና አማካሪ ሙሉ መኮንን፤ የአዕምሮ ህመም እየተስፋፋ እና በዛው ልክ ትኩረት ያልተሰጠው የማህበረሰብ ጤና እክል መሆኑን ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

አንድ ሰው የዕለት ተዕለት ጉዳዩን መፈጸም ሳይችል ሲቀር የአዕምሮ ህመም አጋጥሞታል ይባላል የሚሉት አማካሪዋ ሰዎች እንዲህ አይነት ነገር ሲገጥማቸው ሳይብስ ወደ አዕምሮ ሀኪም ጋር እንዲሄዱ አሳስበዋል።

እንደ አማካሪዋ ገለጻ በኢትዮጵያ የአዕምሮ ህመምተኞች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ብዙ አስረጂ ማስረጃዎች የሚያሳዩ ሲሆን ጭንቀት፣ ድብርት፣ ተስፋ መቁረጥ እየተሰማቸው የሚመጡ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን ጠቁመዋል።

ይሁንና የአዕምሮ ህመም የሚፈልገው ዜጋ ቁጥር እየጨመረ የመምጣቱን ያህል በመንግስት የተሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ መሆኑንም አማካሪዋ ጠቁመዋል።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በጉዳዩ ዙሪያ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በኢትዮጵያ በጦርነቱ እና በሌሎች የማህበራዊ ቀውሶች ምክንያት የስነ ልቦና ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ከአዕምሮ ህመም ጋር ተያይዞ ህክምናውን ለሚፈልጉ ዜጎች የሚውሉ መድሃኒት እጥረቶች ነበሩ የሚሉት ሚኒስትሯ አሁን ላይ ከአቅራቢዎች ጋር በተሰራው ስራ ችግሩ በመቃለል ላይ መሆኑንም አክለዋል።

የአዕምሮ ህመም በቀላሉ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ በሁሉም ሆስፒታሎች የስነ ልቦና ባለሙያ ለማሟላት እየተሞከረ መሆኑን አክለዋል።

በአጠቃላይ ግን በሚሹ የጦርነት እና ግጭት አካባቢዎች በልዩ መልኩ ባለሙያ እየተደራጀ ነው የተባለ ሲሆን በሌሎች መደበኛ እንቅስቃሴዎች ባሉባቸው አካባቢዎች ደግሞ ስለ አዕምሮ ህመም ምንነት፣ ህክምናው እና ሌሎች ተያያዥ አገልግሎቶች ቀስ በቀስ እንዲሟሉ ይደረጋሉም ተብሏል።

በዓለማችን ከአጠቃላይ ህዝብ ቁጥር ውስጥ 970 ሚሊዮን ያህሉ የአዕምሮ ህመምተኞች ሲሆን በየዓመቱም ስምንት ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ በዚሁ ህመም ምክንያት ህይወታቸውን ያጣሉ።

በየዓመቱ ህይወታቸው ከሚያልፉ አጠቃላይ ዜጎች ውስጥም 14 በመቶ ያህሉ የአዕምሮ ህመምተኞች እንደሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት ከአምስት ወራት በፊት ያወጣው ሪፖርት ያስረዳል።

Via: Alain Amharic

@melkam_enaseb
ግራ የተጋቡበት ጉዳይ አለ?

በሚጨነቁበት በማንኛውም ስነ ልቦናዊ ጉዳዮች ላይ ባለሙያዎቻችን ከፍቅርና ትህትና ጋር ደስተኛ ሆነው ህይወትዎን እንዲመሩ ይረዷቹሀል።

ወደ ስነ ልቦና ምክክር አገልግሎት የሚመጡ ሰዎች ደስተኛ፣ ስኬታማና ከፍተኛ ችግር የመፍታት አቅም ይኖራቸዋል።

የሚጨነቁበት ማንኛውም ስነልቦናዊ ጉዳይ መፍትሔ አለው፣ ያማክሩን!

አድራሻችን: ጀሞ ሚካኤል ቤ/ክ አጠገብ ንብ ባንክ ያለበት ህንጻ 4ኛ ፎቅ።

ስልክ: 0967678832
       +251940594855

ራዕያችን ሁለንተናዊ ስኬት ያለው ትውልድ ተፈጥሮ ማየት ነው።

(ፍካት የሥነ ልቦና ማማከር አግልግሎት)

@melkam_enaseb
መሰረት ክንፈ ካሳተመችው ''የጥቁር እናት ነኝ'' ከተሰኘው መጽሐፍ የተገኘውን ገቢ ለተለያዩ የኦቲዝም ማዕከላት እንዲሁም ለችግሩ ተጠቂ ድጋፍ ለሚሹ ቤተሰቦች አድርሳለች።

እናመሰግናለን መሲ!

@melkam_enaseb
⬆️ Training announcement!

Certificate course on applied counseling techniques and skills.

For further details and registration, use the link below! ⬇️

https://tinyurl.com/56tktzcj

(Aha Psychological Services)

@melkam_enaseb
ያሳዝኑኛል!

ባርኮት የ5 አመት ልጅ ነው። እናትና አባቱ በየቀኑ ይጣላሉ። ጭቅጭቃቸው ስለሚያስጨንቀው ቀኑ ሲመሽ መረበሽ ይጀምራል። አባቱ እናቱን ሲመታት የሚሰማውን ሐዘን መቋቋም ያቅተዋል። አቅም ኖሮት እናቱን መታደግ አለመቻሉ ያሳዝነዋል። በኮልታፋ አንደበቱ እናቱን "እማዬ ሳድግ አባዬን እመታልሻለው" ይላታል። ጓደኛው አቤል ዘወትር እሁድ ከእናቱና አባቱ ጋር ቤተ ክርስቲያን ሲሄድ እሱ ለዚህ ነገር ለምን እንዳልታደለ ግራ ይገባዋል። ከጓደኞቹ ጋር ሲጫወት በራስ መተማመን የለውም።

ባርኮት ሲያድግ ምን አይነት ስብዕና ይኖረው ይሆን? ችግሮች በመወያየት መፍታት ይችል ይሆን? ጥሩ ትዳር ይመሰርት ይሆን? አላውቅም። ይሄ ታሪክ የባርኮትና የብዙ ልጆች ኑሮ ነው።

- በስነ ልቦና ሳያድጉ ልጅ በወለዱ ሐላፊነት በጎደላቸው ወላጆች ግጭት ምክንያት በጭንቀት ውስጥ የሚኖሩ ልጆች ያሳዝኑኛል።

- በቤተሰቦቻቸው ግጭት ምክንያት በልባቸው እሪታን የሚያሰሙ አድማጭ ግን የሌላቸው ህጻናት ያሳዝኑኛል።

- ትልቅ አቅም ያላቸው ነገር ግን በቤተሰቦቻቸው ግጭት ምክንያት ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ የሚያድጉ ህጻናት ያሳዝኑኛል።

ወላጆች ልጆች በእናንተ በኩል መጡ እንጂ ፈጣሪ በአደራ እንደሰጣቹ አስታውሱ። ልጆቻቹ ጤናማ ስነ ልቦና ይዘው እንዲያድጉ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ።

ኤርሚያስ ኪሮስ (Counseling Psychologist)

@melkam_enaseb
NARCOLEPSY

(በዶ/ር ኢየሩሳሌም ጌቱ)

ናርኮሌፕሲ (Narcolepsy) የመተኛትና የመንቃት ዑደቶችን የሚቆጣጠረው የአእምሮ ክፍል መዛባት ሲሆን በዚህም የተጠቁ ሰዎች ቀናቸውን በመተኛት ያሳልፍሉ፡፡

ናርኮሌፕሲ የቀን ስራ ላይ በጣም ተፅዕኖ ያሳድራል። ሰዋች ያለፍቃዳቸው ወይም ሳያስቡት እንቅልፍ ይወስዳቸዋል ይህም እየበሉ፣ እያወሩ ወይም መኪና እያሽከረከሩ ሊሆን ይችላል።

ብዙውን ጊዜ ምልክቱ በልጅነት የሚጀምር ሲሆን በማንኛውም የእድሜ ክልል ላይ ሊጀምር ይችላል። ወንዶችንም ሆነ ሴቶችንም በእኩል መጠን ያጠቃል።

መንስኤዎች፦

ኖርኮሌፕስ ብዙ መንስኤዎች ሲኖሩት አብዛኛውን ጊዜ የሚከሰተው በሰውነት ውስጥ የሚገኙ ሀይፓክሪቲን (hypocretin) የሚባል የኬሚካል መጠን ማነስ ነው። ይህ ኬሚካልም ለመንቃት የሚያስችል እና የእንቅልፍ መንቃት ዑደትን የሚያስተካክል ነው።

ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ መንስኤ ባይኖረውም በህክምና በተደረገ ጥናት እንደሚገልፅው ኖርኮሌፕሲ የሀይፓክሬቲን ኬሚካል እጥረትን የሚያመጡ ብዙ ምክንያቶች ውጤት ነው።

ዋነኛ ምክንያቶች ተብለው የሚጠቀሱት:-

- ሀይፓክሪቲን (hypocretin) የሚያመነጩት የአእምሮ ህዋሶች መሞት (loss of Brain cells): ይህም አብዛኛውን ጊዜ የሚከሰተው (Autoimmune Disorder) የሰውነት በሽታ መከላከያ ሲስተም እክል ሲገጥመው ነው።

- ተመሳሳይ ታሪክ በቤተሰብ መኖር

- የአንጎል መጎዳት: የተሽከርካሪ ወይም የመመታት አደጋ መኖር (Brain injuries)

@melkam_enaseb
በመኝታ ሰዓት እነኚህን ያስወግዱ!

በመኝታ ሰዓት ስማርት ስልኮችን፣ ኮምፒውተሮችን፣ ታብሌቶችን እና ቲቪዎችን መጠቀም ለአእምሯችን ጤና የበለጠ አደገኛ የሚሆኑበት ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ።

በመጀመሪያ: የእኛ ዲጂታል መሳሪያ ብዙውን ጊዜ የጭንቀት እና የሚያነቃ የይዘት ምንጭ ናቸው። ዜና ስንመለከት ወይም ከመተኛታችን በፊት በሰዎች ላይ በማህበራዊ ድህረ ገጽ ስንበሳጭ ጭንቀትን ሊጨምር ይችላል ይህም ጥሩ እንቅልፍ እንዳንተኛ ያደርገናል (በኋላም የአዕምሮ ስራን ይጎዳል)።

በሁለተኛ ደረጃ: አንዳንድ ተመራማሪዎች በዲጂታል መሳሪያዎቻችን የሚወጣው ሰማያዊ መብራት ሜላቶኒን የእንቅልፍ ሆርሞንን ማምረት ይጎዳል ብለው ያምናሉ።

ከመተኛቶ በፊት ዲጂታል መሳሪያዎችን መጠቀም በጥልቅ እንቅልፍ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው ታይቷል።

መልካም ምሽት!

@melkam_enaseb
#CME_Webinar_YetenaWeg & #EMA

You are invited to join a webinar.

Topic: Psychosomatic Disorders.

Presenter: Dr. Biniyam Worku

🗓  Jan 29th 2023 (This Sunday)

  5:00 PM - 7:00 PM (Ethiopian Time)

Register Via the link below:

https://us02web.zoom.us/webinar/register/WN_1wWMVjOeSwm6ueva191B6g

After registering, you will receive a confirmation email about joining the webinar.

@melkam_enaseb
2025/07/09 20:05:22
Back to Top
HTML Embed Code: