ሚስጥረኛ ብዬ
ሚስጥሬን ብነግርሽ፣
ሚስጥሩ ነው ብለሽ
በሚስጥር ተናገርሽ፤
ያ ሚስጥር በሚስጥር
ሲዞር ሲዞር ውሎ፣
በሚስጥር ነገሩኝ
ሚስጥር ነው ተብሎ።
😂😂😂😂
ሚስጥሬን ብነግርሽ፣
ሚስጥሩ ነው ብለሽ
በሚስጥር ተናገርሽ፤
ያ ሚስጥር በሚስጥር
ሲዞር ሲዞር ውሎ፣
በሚስጥር ነገሩኝ
ሚስጥር ነው ተብሎ።
😂😂😂😂
👍14❤13🥰1
ከክፋት ለመብለጥ
ክፋት ከወደደ ፤
እራሱን ሸሽጎ
በሰው ከፈረደ ፤
ምንም አይባልም
ልቡ እስኪረታ ፤
ሰው መቼም
አይነፃ...
የማይሰራ ሀጥያት
እግዚአብሔር ይፍታ ።...😔
ክፋት ከወደደ ፤
እራሱን ሸሽጎ
በሰው ከፈረደ ፤
ምንም አይባልም
ልቡ እስኪረታ ፤
ሰው መቼም
አይነፃ...
የማይሰራ ሀጥያት
እግዚአብሔር ይፍታ ።...😔
❤6
ሀሳብ ገዳይ..፤
ፍትህ በዳይ...፤
አንደበት ማር ቢቀባበት
ምን ይገኛል ?
እንጀራ እየገዛሁ
እበላለሁ...
ግን መልሶ ይርበኛል ።🤣
ራበኝ ራበኝ ራበኝ 🫠
@dagi1u
ፍትህ በዳይ...፤
አንደበት ማር ቢቀባበት
ምን ይገኛል ?
እንጀራ እየገዛሁ
እበላለሁ...
ግን መልሶ ይርበኛል ።🤣
ራበኝ ራበኝ ራበኝ 🫠
@dagi1u
❤2🥰2
Forwarded from Esuye ከሀጥያተኞች ዋና 1ኛ ጢሞ 1:15
“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18
የክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላቹ እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ አደረሰን አሜን
መስቀልን ስናከብር በጣም ብዙ የመንፈሳዊ ህይወት ጨቅላዎች መስቀሉን ሳይሆን የተሰቀለበትን አክብሩ እንጂ ይሉናል
ልጅ ለእናት ምጥ አስተማረች እንዲሉ የሀገሬው ሰው ለቤተክርስቲያን ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት አዲሷ አይደለም ሰበር ዜናዋ አይደለም ኢየሱስ ጌታ ነው ከማለት አልፋ እንዴት ጌታ እንደሆነ እና ጌትነቱን መስበክ ከጀመረች አመታት አልፈዋታል ምክንያቱም ለአንድ ክርስቲያን ኢየሱስ ጌታ ነው የሚለው ቃል ሳይሆን ጌትነቱን በደምብ ማብራራት ስለሆነ የሚፈልገው ምክንያቱም ክርስቲያን ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነት አምኖ ተቀብሎ ስለሆነ ማለት ነው
ለምሳሌ ያክል አንድን ልጅ ትምህርት ቤት እንዲገባ ከነገርንው ብኋላ እና አስመዘገብንው ትምህርት ነው ማስተማር ያለብን ወይስ ሁሌ ትምህርት ጥሩ ነው ተማር ማለት ነው ያለብን መልሱ ግልፅ ነው ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያንም ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት ብቻ ጥቅም የለውም ቀድሞ ጌታ መሆኑን ያውቃልና ከቻሉ እንዴት ጌታ ሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ማነው ጌትነቱ እንዴት ነው ወ.ዘ.ተ ማስተማር ቤተክርስቲያን ስንዱ እመቤት ናትና ነገር ክርስቶስ ነገር ሥጋዌ ነገር መለኮት .....እያለች ስለ ክርስቶስ በደንብ ዘርዝራ ፈትፍታ ለልጇቿ ታጎርሳለች ወንጌልን ይሄ ነው ክርስቶስን መስበክ
ታድያ ለክርስቶስ ይሄን የሀል አመለካከት ካላቹ ክርስቶስን ትታቹ ለምን እንጨቱን የሚሉ አሉ (ይቅር ይበላቸውና )እኛ እንጨት አንልም ቅዱስ መስቀል ነው የምንለው የክርስቶስ ደም ፈሶበት ቀላል ጥቅም የለሽ የሆነ ነገር አላየንምና
መስቀሉን ሲጀመር ስናከብር እኮ ክርስቶስ ተሰቅሎበታል ብለን ነው የእውቀት አለማወቅ የክፉዎች ክፉ ነው ትል ነበር አያቴ
ባጠቃላይ መስቀልን ምናከብረው
1ኛ ሀይላችን ስለሆነ ነው ጥላትን የምናስበረግግበት ድል የምንነሳበት ስለሆነ 👉👉“
2ኛ የዳንበት ሴጣን ዲያቢሎስ የተቀጠቀጠበት የዘመናት የጥል ግድግዳ የፈረሰበት ስለሆነ ነው
ነገር በሶስት ይፀናል እንዲሉ ልሥልሰው😄
3ኛ በእኛ የነበረውን መርገም በመስቀሉ ስለሆነ ያስወገደልን 👉👉
ስለዚህ በአጭሩ መስቀልን የምናከብረው ጌታ ክርስቶስ ተሰቅሎ ክቡር ደሙን ቅዱስ ስጋውን አፍስሶ ቆርሶ ስለቀደሰው ነው ለእኛም ሀይላችን ነው ለሚጠፉት ግን መኞትን ፌዝነት ነው
መልካም ቀን መልካም በዓል
✍✍ esuye (ከሀጢያተኞች ዋና
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18
የክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላቹ እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳቹ አደረሰን አሜን
መስቀልን ስናከብር በጣም ብዙ የመንፈሳዊ ህይወት ጨቅላዎች መስቀሉን ሳይሆን የተሰቀለበትን አክብሩ እንጂ ይሉናል
ልጅ ለእናት ምጥ አስተማረች እንዲሉ የሀገሬው ሰው ለቤተክርስቲያን ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት አዲሷ አይደለም ሰበር ዜናዋ አይደለም ኢየሱስ ጌታ ነው ከማለት አልፋ እንዴት ጌታ እንደሆነ እና ጌትነቱን መስበክ ከጀመረች አመታት አልፈዋታል ምክንያቱም ለአንድ ክርስቲያን ኢየሱስ ጌታ ነው የሚለው ቃል ሳይሆን ጌትነቱን በደምብ ማብራራት ስለሆነ የሚፈልገው ምክንያቱም ክርስቲያን ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነት አምኖ ተቀብሎ ስለሆነ ማለት ነው
ለምሳሌ ያክል አንድን ልጅ ትምህርት ቤት እንዲገባ ከነገርንው ብኋላ እና አስመዘገብንው ትምህርት ነው ማስተማር ያለብን ወይስ ሁሌ ትምህርት ጥሩ ነው ተማር ማለት ነው ያለብን መልሱ ግልፅ ነው ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያንም ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት ብቻ ጥቅም የለውም ቀድሞ ጌታ መሆኑን ያውቃልና ከቻሉ እንዴት ጌታ ሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ማነው ጌትነቱ እንዴት ነው ወ.ዘ.ተ ማስተማር ቤተክርስቲያን ስንዱ እመቤት ናትና ነገር ክርስቶስ ነገር ሥጋዌ ነገር መለኮት .....እያለች ስለ ክርስቶስ በደንብ ዘርዝራ ፈትፍታ ለልጇቿ ታጎርሳለች ወንጌልን ይሄ ነው ክርስቶስን መስበክ
ታድያ ለክርስቶስ ይሄን የሀል አመለካከት ካላቹ ክርስቶስን ትታቹ ለምን እንጨቱን የሚሉ አሉ (ይቅር ይበላቸውና )እኛ እንጨት አንልም ቅዱስ መስቀል ነው የምንለው የክርስቶስ ደም ፈሶበት ቀላል ጥቅም የለሽ የሆነ ነገር አላየንምና
መስቀሉን ሲጀመር ስናከብር እኮ ክርስቶስ ተሰቅሎበታል ብለን ነው የእውቀት አለማወቅ የክፉዎች ክፉ ነው ትል ነበር አያቴ
ባጠቃላይ መስቀልን ምናከብረው
1ኛ ሀይላችን ስለሆነ ነው ጥላትን የምናስበረግግበት ድል የምንነሳበት ስለሆነ 👉👉“
የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥18
2ኛ የዳንበት ሴጣን ዲያቢሎስ የተቀጠቀጠበት የዘመናት የጥል ግድግዳ የፈረሰበት ስለሆነ ነው
👉👉“ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው።”
— ኤፌሶን 2፥16
ነገር በሶስት ይፀናል እንዲሉ ልሥልሰው😄
3ኛ በእኛ የነበረውን መርገም በመስቀሉ ስለሆነ ያስወገደልን 👉👉
“በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤”
— ቆላስይስ 2፥14
ስለዚህ በአጭሩ መስቀልን የምናከብረው ጌታ ክርስቶስ ተሰቅሎ ክቡር ደሙን ቅዱስ ስጋውን አፍስሶ ቆርሶ ስለቀደሰው ነው ለእኛም ሀይላችን ነው ለሚጠፉት ግን መኞትን ፌዝነት ነው
መልካም ቀን መልካም በዓል
✍✍ esuye (ከሀጢያተኞች ዋና
❤16👍1
ከሀጥያት ሳላመልጥ
ፀሎት ስገዳድፍ ፤
ስሜት ሳገለግል
ከአለም ስጨላልፍ፤
እናት ያለው እግዜር
እናት ያለው አምላክ
እሱ አልተቆጣኝም
ፍፁም ነው የታገሰኝ ፤
በቃኝ የማላውቀው
እኔ ግን ተቆጣሁ
ነውሬ እየበዛ ከሰው ሲያንሰኝ፤
እስቲ እንደው ፍረዱ
እግዜር ምን አረገ፤
እናቱን በሰጠኝ
ንስሀን ባቀና እኔን በታደገ፤ ?
አዳምን በማረ ?
እኔን ጎስቋላውን
ይዞ በትከሻው ፤
ስጋዬ ሲራገፍ
ከአፍር ስመለስ
ግራ ገብ ህይወቴ
የት ይሆን መድረሻው ፤?
ወየውልሽ ነብሴ ለምትዝበቺ ፤
ያልተፈታ ቅኔ ጮኸሽ ለምትፈቺ ፤
ግዜው አይጠብቅም
እንደጉድ ይሄዳል ፤
ሰው በምድር ሳለ
ሲኦልን ይወዳል ?
እንዴት እንዴት ነብሴ ፤
ከስጋ ልጣላ አስታርቂኝ ከራሴ፤
ቀን እየነጎደ ሲቀንስ ሲበዛ፤
ንስሀ እገባለሁ ... ንስሀ እገባለሁ
ጉራዬን ስነዛ ፤
የመዳን ቀን ዛሬ
ሲሆን እያወኩኝ ፤
ሀጥያቴን ስቆጥረው
አሁንም ሳልወጣ
ሀጥያቴ መሀል ነኝ እንደተደበኩኝ ።
@dagi1u
ፀሎት ስገዳድፍ ፤
ስሜት ሳገለግል
ከአለም ስጨላልፍ፤
እናት ያለው እግዜር
እናት ያለው አምላክ
እሱ አልተቆጣኝም
ፍፁም ነው የታገሰኝ ፤
በቃኝ የማላውቀው
እኔ ግን ተቆጣሁ
ነውሬ እየበዛ ከሰው ሲያንሰኝ፤
እስቲ እንደው ፍረዱ
እግዜር ምን አረገ፤
እናቱን በሰጠኝ
ንስሀን ባቀና እኔን በታደገ፤ ?
አዳምን በማረ ?
እኔን ጎስቋላውን
ይዞ በትከሻው ፤
ስጋዬ ሲራገፍ
ከአፍር ስመለስ
ግራ ገብ ህይወቴ
የት ይሆን መድረሻው ፤?
ወየውልሽ ነብሴ ለምትዝበቺ ፤
ያልተፈታ ቅኔ ጮኸሽ ለምትፈቺ ፤
ግዜው አይጠብቅም
እንደጉድ ይሄዳል ፤
ሰው በምድር ሳለ
ሲኦልን ይወዳል ?
እንዴት እንዴት ነብሴ ፤
ከስጋ ልጣላ አስታርቂኝ ከራሴ፤
ቀን እየነጎደ ሲቀንስ ሲበዛ፤
ንስሀ እገባለሁ ... ንስሀ እገባለሁ
ጉራዬን ስነዛ ፤
የመዳን ቀን ዛሬ
ሲሆን እያወኩኝ ፤
ሀጥያቴን ስቆጥረው
አሁንም ሳልወጣ
ሀጥያቴ መሀል ነኝ እንደተደበኩኝ ።
@dagi1u
❤19
ንዴትሽን እወደዋለሁ
እሳት ነው እሳት ይለብሳል፤
ግን እመኚኝ ከዛ በላይ
ናፍቆትሽ እጥፍ ያከሳል፤
ምን አለው አይገናኝም
መስታወት ላይ ቃልን ማራገፍ፤
የስላሴን ልጅ መውደዴን
ፊደል ቆጣጥሮ ማሰለፍ፤
ተፈጥሮ ትንሽ ብትገፋኝ
እንደምንም ቢቻለኝም፤
እወዱሻለሁ ካልኩሽ በቀር
የቀረ ቅኔ የለኝም፤
አቃለሁ ሰነፍ ነኝ እኮ
ከኔ ጋር መሆን ይከብዳል፤
ልቤ ግን እውነት ሀቅ አለው
ከራሱ ሰውን ይወዳል፤
እወድሽ እወድሻለሁ
የሰማ ይሰንጠቅ አለት፤
በአካል እያየሽ ብታውቂኝ
እስቲ ግን ምንነበረበት ?
ተፈጥሮ ትንሽ ብትገፋኝ
እንደምንም ቢቻለኝም፤
እወድሻለሁ ካልኩሽ በቀር
የቀረ ቅኔ የለኝም፤
ሁሌ ነው በቀን በቀኑ
የሚጨምረው ግፊቱ፤
የተሳለበት ይመስል
የፊትሽ ግማሽ ከፊቱ ፤ ፤
እኔ ሳልሆን የሚወድሽ ልቤ ነው የፃፈው
@dagi1u
እሳት ነው እሳት ይለብሳል፤
ግን እመኚኝ ከዛ በላይ
ናፍቆትሽ እጥፍ ያከሳል፤
ምን አለው አይገናኝም
መስታወት ላይ ቃልን ማራገፍ፤
የስላሴን ልጅ መውደዴን
ፊደል ቆጣጥሮ ማሰለፍ፤
ተፈጥሮ ትንሽ ብትገፋኝ
እንደምንም ቢቻለኝም፤
እወዱሻለሁ ካልኩሽ በቀር
የቀረ ቅኔ የለኝም፤
አቃለሁ ሰነፍ ነኝ እኮ
ከኔ ጋር መሆን ይከብዳል፤
ልቤ ግን እውነት ሀቅ አለው
ከራሱ ሰውን ይወዳል፤
እወድሽ እወድሻለሁ
የሰማ ይሰንጠቅ አለት፤
በአካል እያየሽ ብታውቂኝ
እስቲ ግን ምንነበረበት ?
ተፈጥሮ ትንሽ ብትገፋኝ
እንደምንም ቢቻለኝም፤
እወድሻለሁ ካልኩሽ በቀር
የቀረ ቅኔ የለኝም፤
ሁሌ ነው በቀን በቀኑ
የሚጨምረው ግፊቱ፤
የተሳለበት ይመስል
የፊትሽ ግማሽ ከፊቱ ፤ ፤
እኔ ሳልሆን የሚወድሽ ልቤ ነው የፃፈው
@dagi1u
❤13🥰3
🤲🤲🤲🤲🤲አቤቱ🤲🤲🤲🤲🤲
አምላክ በፍቃዱ በአምሳሉ ፈጠረ
ሰውን ባፈጣጠር ውብ አርጎ አከበረ
ጌታ በፍጥረቱ ሊወደስ ሊቀደስ
ከአፈር አበጃጅቶ ሲባርክ ሲያነግስ
ሁሉን ሙሉ አድርጎ አስተካክሎ ቅድሚያ
ልጁን እፍ ብሎ አስገኘው ከትቢያ
የምስጋና ጣዕም የውዳሴን ዜማ
በከንፈሩ ፍሬ አርጎት እንዲስማማ
ከሁሉ አልቆ አከበረው ሰውን
አደለው ሸለመው ጥበብ ማስተዋልን
ሰው ግን...ሰው ግን ረከሰ ቆሸሸ በስራው
ሀጥያት ክፋት ተንኮል ሆኖት መሸሸጊያው
አካሉ እና መልኩ ግሩም ሆኖ ሳለ
በግብሩ መጠልሸት ተዋርዶ ቀለለ
አቤቱ....አምላኬ.....ምንኛ አጥፍተን አሳዝነን ይሆን
የበደል ማርከሻ እስኪታጣ በደልን
ነውራችን ገነነ ድካማችን በዛ
ስጋችን ደቀቀ ነፍሳችን ደንዝዛ
ወደቅን....ከሰርን አንተን አጣን ጌታ
ሀዘን ከቦን ወሮን ሸሸ ከኛ ደስታ
አቤቱ...አምላኬ...ገድለናል ሰርቀናል ዋሽተናል በብርቱ
ስራችን ከርፍቶ ሆኖብናል ከንቱ
ዝሙትን ሰርተናል ስምህን አምተናል
ረክሰናል በሀጥያት ቀለናል ገምተናል
ያልበደልነው በደል ያልነካነው ክፋት
ያልሰራነው ሴራ ያልገለጥነው ትዕቢት
ምንም የለም ከቶ....ሁሉን አዳርሰናል
አንዳችም ሳናስቀር ሀጥያትን ሰርተናል
እናም...እናም...አንተ ቸር ፈጣሪ ሁሉን ቻይ ነህና
ክቡር....ቅዱስ ሀያል ነህና ገናና
አንፃን ከስራችን ማረን በይቅርታ
በንስሀ አጥበህ አርገን የበረታ
✍ብሩክ ተፈራ
አምላክ በፍቃዱ በአምሳሉ ፈጠረ
ሰውን ባፈጣጠር ውብ አርጎ አከበረ
ጌታ በፍጥረቱ ሊወደስ ሊቀደስ
ከአፈር አበጃጅቶ ሲባርክ ሲያነግስ
ሁሉን ሙሉ አድርጎ አስተካክሎ ቅድሚያ
ልጁን እፍ ብሎ አስገኘው ከትቢያ
የምስጋና ጣዕም የውዳሴን ዜማ
በከንፈሩ ፍሬ አርጎት እንዲስማማ
ከሁሉ አልቆ አከበረው ሰውን
አደለው ሸለመው ጥበብ ማስተዋልን
ሰው ግን...ሰው ግን ረከሰ ቆሸሸ በስራው
ሀጥያት ክፋት ተንኮል ሆኖት መሸሸጊያው
አካሉ እና መልኩ ግሩም ሆኖ ሳለ
በግብሩ መጠልሸት ተዋርዶ ቀለለ
አቤቱ....አምላኬ.....ምንኛ አጥፍተን አሳዝነን ይሆን
የበደል ማርከሻ እስኪታጣ በደልን
ነውራችን ገነነ ድካማችን በዛ
ስጋችን ደቀቀ ነፍሳችን ደንዝዛ
ወደቅን....ከሰርን አንተን አጣን ጌታ
ሀዘን ከቦን ወሮን ሸሸ ከኛ ደስታ
አቤቱ...አምላኬ...ገድለናል ሰርቀናል ዋሽተናል በብርቱ
ስራችን ከርፍቶ ሆኖብናል ከንቱ
ዝሙትን ሰርተናል ስምህን አምተናል
ረክሰናል በሀጥያት ቀለናል ገምተናል
ያልበደልነው በደል ያልነካነው ክፋት
ያልሰራነው ሴራ ያልገለጥነው ትዕቢት
ምንም የለም ከቶ....ሁሉን አዳርሰናል
አንዳችም ሳናስቀር ሀጥያትን ሰርተናል
እናም...እናም...አንተ ቸር ፈጣሪ ሁሉን ቻይ ነህና
ክቡር....ቅዱስ ሀያል ነህና ገናና
አንፃን ከስራችን ማረን በይቅርታ
በንስሀ አጥበህ አርገን የበረታ
✍ብሩክ ተፈራ
❤29👍3
የሰወች ህይወት ውስጥ መጥፎ ክምሮችን አትክተት ።
ኢሄን የምልህ አለመክተት ስለምትችል ነው...
የተናደደ ሰው ላይ እሳት አታርከፍክፍበት...
ውሀ ሁንለት በግዱ ይቀዘቅዛል
የተከፋውንም ከልብህ አፅናናው ...
ያለቀሰውን እጅህን ሰደህ ከጉንቾቹ እምባውን
በመዳፍህ አብስለት ...
የተደሰተውንም ደስታው የክፋት ካልሆነ አመፀኛ ምላስህን በገዛ ፍቃድህ ያዝለት ደስ ይበለው..
በወንድምህ ደስታ ተደሰት...
መልካም ማሰብህ ዋጋው ከእግዚአብሔር ስለሆነ
ከባንክ ቤት ወይም ከሰው ኪስ ውስጥ መጠበቅህን ተወው...
እንደ ሰው ኑር....
@dagi1u
ኢሄን የምልህ አለመክተት ስለምትችል ነው...
የተናደደ ሰው ላይ እሳት አታርከፍክፍበት...
ውሀ ሁንለት በግዱ ይቀዘቅዛል
የተከፋውንም ከልብህ አፅናናው ...
ያለቀሰውን እጅህን ሰደህ ከጉንቾቹ እምባውን
በመዳፍህ አብስለት ...
የተደሰተውንም ደስታው የክፋት ካልሆነ አመፀኛ ምላስህን በገዛ ፍቃድህ ያዝለት ደስ ይበለው..
በወንድምህ ደስታ ተደሰት...
መልካም ማሰብህ ዋጋው ከእግዚአብሔር ስለሆነ
ከባንክ ቤት ወይም ከሰው ኪስ ውስጥ መጠበቅህን ተወው...
እንደ ሰው ኑር....
@dagi1u
❤10
አሻግሬ አየሁት
.
.
በግርግር መሐል ጨርቄን ጥዬ ስበር፣
አሻግሬ አየሁት ከቀራንዮ ጫፍ ከጎለጎታ ስር።
መንገዱን በማያዉቅ እልፍ መንገደኛ መንደሩ ታዉኮ፣
አንዱ ካንዱ ሲጋጭ ከሌላኛዉ ተጓዥ ሳይተያይ ታክኮ፣
አላፊ አግዳሚውን ወጪና ወራጁን ቆሜ ስመለከት፣
ደምግባቱን ያጣ የተራቆተ ሰው አየሁኝ በድንገት፣
በደም ረስርሶ በወዝ የረጠበ ቀይ ከለሜዳ፣
በሀሰት ተከሶ ፍርዱን የሚጠብቅ ከጲላጦስ ዘንዳ፣
ይታየኛል አንድ ሰው........
በአይሁድ ሊቀ ካህናት ግራና ቀኙን ተከቦ፣
በህዝብ መካከል የቆመ በእነ ቀያፋ ተዋክቦ፣
ሲንጠበብ ወዙ ሲነሳ ሲወድቅ፣
በጥፊ ሲመቱት እጅጉን ሲሳቀቅ፣
ይታየኛል ንፁህ ሰው......
በቁርጥራጭ ብረት፣
በተሰበረ አጥንት፣
እረፍት በሌለው በወንበዴ ጅራፍ ጀርባውን ተገርፎ፣
አልባስ ተለይቶት እርቃኑን የዋለ ቀሚሱን ተገፎ፣
ስጋዉ ሲቦጫጨቅ፣
ፅሂሙም ሲነጫጭ፣
ቁጥር በማይቆጥረዉ በአይሁድ ግርፋት ቆዳዉ ተገሽልጦ፣
እዡን እያነባ ህማም አይሎበት ፊቱ ተላልጦ፣
በድካም ሲያጣጥር፣
ይታወቀኝ ጀመር፣
ከአይኔ ተንከባሎ ጉንጩን እያራሰ እንባዬ ሲወርድ፣
ላብ እያጠመቀኝ እግሬ ተብረክርኮ ሰዉነቴ ሲርድ፣
አሻግሬ አየሁት.........
በተሳለ ቅንዋት ለአዳም ሲቸነከር፣
በደሙ ቤዛነት ብድራትን ሲቸር፣
በመስቀሉ ካሳ አርአያ ሊሆነን እንባችንን ሊያብስ፣
ለዘላለም ፍቅሩ ለታመነ ቃሉ እስከመሞት ሲደርስ።
✍ኤደን
.
.
በግርግር መሐል ጨርቄን ጥዬ ስበር፣
አሻግሬ አየሁት ከቀራንዮ ጫፍ ከጎለጎታ ስር።
መንገዱን በማያዉቅ እልፍ መንገደኛ መንደሩ ታዉኮ፣
አንዱ ካንዱ ሲጋጭ ከሌላኛዉ ተጓዥ ሳይተያይ ታክኮ፣
አላፊ አግዳሚውን ወጪና ወራጁን ቆሜ ስመለከት፣
ደምግባቱን ያጣ የተራቆተ ሰው አየሁኝ በድንገት፣
በደም ረስርሶ በወዝ የረጠበ ቀይ ከለሜዳ፣
በሀሰት ተከሶ ፍርዱን የሚጠብቅ ከጲላጦስ ዘንዳ፣
ይታየኛል አንድ ሰው........
በአይሁድ ሊቀ ካህናት ግራና ቀኙን ተከቦ፣
በህዝብ መካከል የቆመ በእነ ቀያፋ ተዋክቦ፣
ሲንጠበብ ወዙ ሲነሳ ሲወድቅ፣
በጥፊ ሲመቱት እጅጉን ሲሳቀቅ፣
ይታየኛል ንፁህ ሰው......
በቁርጥራጭ ብረት፣
በተሰበረ አጥንት፣
እረፍት በሌለው በወንበዴ ጅራፍ ጀርባውን ተገርፎ፣
አልባስ ተለይቶት እርቃኑን የዋለ ቀሚሱን ተገፎ፣
ስጋዉ ሲቦጫጨቅ፣
ፅሂሙም ሲነጫጭ፣
ቁጥር በማይቆጥረዉ በአይሁድ ግርፋት ቆዳዉ ተገሽልጦ፣
እዡን እያነባ ህማም አይሎበት ፊቱ ተላልጦ፣
በድካም ሲያጣጥር፣
ይታወቀኝ ጀመር፣
ከአይኔ ተንከባሎ ጉንጩን እያራሰ እንባዬ ሲወርድ፣
ላብ እያጠመቀኝ እግሬ ተብረክርኮ ሰዉነቴ ሲርድ፣
አሻግሬ አየሁት.........
በተሳለ ቅንዋት ለአዳም ሲቸነከር፣
በደሙ ቤዛነት ብድራትን ሲቸር፣
በመስቀሉ ካሳ አርአያ ሊሆነን እንባችንን ሊያብስ፣
ለዘላለም ፍቅሩ ለታመነ ቃሉ እስከመሞት ሲደርስ።
✍ኤደን
❤25
፡ስቃለሁ እንደተመቸኝ፡
እራስን ማጣት ቀለለ
ዘመኔ ቦግ እልም ሆነ፤
አለማወቅ መጋጋጫው
ድድብና እንኳን ዘመነ፤
ከንቱነት መኪና አስገዛ
ደረጃ ነው ሰው ይረገጣል፤
ሁለት ልብ ግራገቡ
ማገር ጠፍቶ የት ይቀመጣል ?
ሰወች ላይ ሰውን ደራርቦ
እሳት ላይ እሳት ለኮሰ፤
ማርያምን ቃል አጣሁ እኮ
ከመሬት ህይወት አነሰ ??😭
አፈር መሆኔን ባውቅም
ግድ የለም ማለት ሰለቸኝ፤
ውስጤ ቢተራመስም
እስቃለሁ እንደተመቸኝ ።
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
እራስን ማጣት ቀለለ
ዘመኔ ቦግ እልም ሆነ፤
አለማወቅ መጋጋጫው
ድድብና እንኳን ዘመነ፤
ከንቱነት መኪና አስገዛ
ደረጃ ነው ሰው ይረገጣል፤
ሁለት ልብ ግራገቡ
ማገር ጠፍቶ የት ይቀመጣል ?
ሰወች ላይ ሰውን ደራርቦ
እሳት ላይ እሳት ለኮሰ፤
ማርያምን ቃል አጣሁ እኮ
ከመሬት ህይወት አነሰ ??😭
አፈር መሆኔን ባውቅም
ግድ የለም ማለት ሰለቸኝ፤
ውስጤ ቢተራመስም
እስቃለሁ እንደተመቸኝ ።
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
❤12🔥1
ማን ይውደደኝ
ዝም አልኳቸው
ሄዱ ጥለውኝ
፡
አያስመስልም ብለውኝ
መግለፄን አወቁ
ገፉኝ ተደበቁ
፡
አርጉልኝ ከማለት
ላድርገው አልኳቸው
፡
ስሜ ከሚጠፋ
ባዶ ልቅር ደስስስ እስከሚላቸው
ንቃ ስጥ ሰጪ ከሆንክ መስጠት
፡
ሁሉም ይለያያል
አንተን መሳይ ካጣህ
ዝም ብለህ ግፋበት ...
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
ዝም አልኳቸው
ሄዱ ጥለውኝ
፡
አያስመስልም ብለውኝ
መግለፄን አወቁ
ገፉኝ ተደበቁ
፡
አርጉልኝ ከማለት
ላድርገው አልኳቸው
፡
ስሜ ከሚጠፋ
ባዶ ልቅር ደስስስ እስከሚላቸው
ንቃ ስጥ ሰጪ ከሆንክ መስጠት
፡
ሁሉም ይለያያል
አንተን መሳይ ካጣህ
ዝም ብለህ ግፋበት ...
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
❤12👍2
ገና ያኔ ድሮሮ
ከሩቅ ዘመን በፊት፣
አማኝ በሞላበት
ፈላስፎችም አሉ ብቻ ትንሽ ጥቂት፤
ታድያ በዛ ዘመን
መሬት ክብ ነበረች
ምጣድ ምትመስል፣
ለጥ ብላ ምትኖር
የማትዞር ማትዋልል፥
ያችኛዋ መሬት
አሁን ከነበረው በጣም ትለያለች፣
ምንም አድሎ የለም
ሁሉን ታበቅላለች፤
ታድያ እነዛ ጥቂት
የሚፈላሰፉ፣
ከንቱ ሀሰበቸውን
በሰው ውስጥ አስፋፉ፤
መሬት ክብ ሳትሆን
ሰማይ የምታክል፣
እንቁላል ነገር ነች
አሎሎ ምትመስል፤
ብለው ማይሆን ወሬ
ምድር ላይ በተኑ፣
ደበራት መሰለኝ
እንደዚ ሲሆኑ፤
አሁን በኛ ዘመን
ትንሽ መረጋጋት ያለ ከመሰላት፣
ለስሟ ነዉ መሰል
ድርቅና ቸነፈር
ጦርነት አይቀራት።
ከሩቅ ዘመን በፊት፣
አማኝ በሞላበት
ፈላስፎችም አሉ ብቻ ትንሽ ጥቂት፤
ታድያ በዛ ዘመን
መሬት ክብ ነበረች
ምጣድ ምትመስል፣
ለጥ ብላ ምትኖር
የማትዞር ማትዋልል፥
ያችኛዋ መሬት
አሁን ከነበረው በጣም ትለያለች፣
ምንም አድሎ የለም
ሁሉን ታበቅላለች፤
ታድያ እነዛ ጥቂት
የሚፈላሰፉ፣
ከንቱ ሀሰበቸውን
በሰው ውስጥ አስፋፉ፤
መሬት ክብ ሳትሆን
ሰማይ የምታክል፣
እንቁላል ነገር ነች
አሎሎ ምትመስል፤
ብለው ማይሆን ወሬ
ምድር ላይ በተኑ፣
ደበራት መሰለኝ
እንደዚ ሲሆኑ፤
አሁን በኛ ዘመን
ትንሽ መረጋጋት ያለ ከመሰላት፣
ለስሟ ነዉ መሰል
ድርቅና ቸነፈር
ጦርነት አይቀራት።
❤18👍4
እኔም እንደ አዳም . . .
በገነት ገዳም
ሁሉ ተሟልቶ ፥ ኑሮ ሲመቻች
አድርጎኝ ታካች
ማለት ሲዳዳኝ "ከፀሐይ በታች..."
የዛኔ መጣች !
መጣች ...
"ንቃ" አለችኝ
ጎኔን እየወጋች ፥ ተፈታተነችኝ
ዝም አልኩኝ በግብሯ
ታገስኳት እንዴትም ፤
ለካ እንደመሳሳቅ ፥ ይጥማል ንዴትም ።
( ምቾት ብቻውን መች ያስደስታል ?
መስኩ ለምለም ነው
አፀዱ ሙሉ
ምግቡ ፥ መጠጡ በገነት ሞልቷል
ምስኪኑ አዳም ግን ትቶት ተኝቷል ።
ሳይጠፋበት ጥፋት ፥ ሳይጎበኘው ሐጥያት
ለካስ ይሰለቻል ፥ መንግስተ - ሰማያት ። )
እሷ ግን በቃ
እግዜር ያስተኛኝ በገነት አልጋ
እንዳልነቃበት ስለሚሰጋ
መሆኑን አውቃ
ህይወት ሰጠችኝ ፥ ምቾቴን ነጥቃ ።
By Habtamu Hadera
በገነት ገዳም
ሁሉ ተሟልቶ ፥ ኑሮ ሲመቻች
አድርጎኝ ታካች
ማለት ሲዳዳኝ "ከፀሐይ በታች..."
የዛኔ መጣች !
መጣች ...
"ንቃ" አለችኝ
ጎኔን እየወጋች ፥ ተፈታተነችኝ
ዝም አልኩኝ በግብሯ
ታገስኳት እንዴትም ፤
ለካ እንደመሳሳቅ ፥ ይጥማል ንዴትም ።
( ምቾት ብቻውን መች ያስደስታል ?
መስኩ ለምለም ነው
አፀዱ ሙሉ
ምግቡ ፥ መጠጡ በገነት ሞልቷል
ምስኪኑ አዳም ግን ትቶት ተኝቷል ።
ሳይጠፋበት ጥፋት ፥ ሳይጎበኘው ሐጥያት
ለካስ ይሰለቻል ፥ መንግስተ - ሰማያት ። )
እሷ ግን በቃ
እግዜር ያስተኛኝ በገነት አልጋ
እንዳልነቃበት ስለሚሰጋ
መሆኑን አውቃ
ህይወት ሰጠችኝ ፥ ምቾቴን ነጥቃ ።
By Habtamu Hadera
❤8
መልስ አጣለሁ
ልቤ ይደነግጣል
እንደ ሰው ለመሳቅ
:
አይኔ ተመልክቷል
አፍቃሪ ሲናናቅ
ከሆነ ጥፋቴ
አጋር መፈለጉ
:
ይሻላል መሰለኝ
ቢቀርብኝ ወጉ
እኔ መከረኛ
ስንቴ ስፈልጋት
:
የሚቆራረጠው
ተስፋዬ አልቆ ነው
ከጨለማ መሀል
የሚደባብሳት
:
ያገኛት ይመስል
ልቤ ሲኮታትን
:
አላገኘም በቃ
አልፏል አመታትን....
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
ልቤ ይደነግጣል
እንደ ሰው ለመሳቅ
:
አይኔ ተመልክቷል
አፍቃሪ ሲናናቅ
ከሆነ ጥፋቴ
አጋር መፈለጉ
:
ይሻላል መሰለኝ
ቢቀርብኝ ወጉ
እኔ መከረኛ
ስንቴ ስፈልጋት
:
የሚቆራረጠው
ተስፋዬ አልቆ ነው
ከጨለማ መሀል
የሚደባብሳት
:
ያገኛት ይመስል
ልቤ ሲኮታትን
:
አላገኘም በቃ
አልፏል አመታትን....
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
❤6
አላውቅም
አላቅም ምን እንደልሽ
ጠፋብኝ ምን እንደሚባል
:
መናፈቅ አለመናፈቅ
መንጠልጠል በጣም ያባባል
ዝም ልበል ላውራ ?
አሟሙተኝ ተብሎ
ማንም አይጠራ
:
ያልገባሽ ያልገባኝ
መስመር ሲዘረጋ
ለኔ እንደጨለመ
ላንቺ ብቻ ነጋ......
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
አላቅም ምን እንደልሽ
ጠፋብኝ ምን እንደሚባል
:
መናፈቅ አለመናፈቅ
መንጠልጠል በጣም ያባባል
ዝም ልበል ላውራ ?
አሟሙተኝ ተብሎ
ማንም አይጠራ
:
ያልገባሽ ያልገባኝ
መስመር ሲዘረጋ
ለኔ እንደጨለመ
ላንቺ ብቻ ነጋ......
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
❤6
Forwarded from Biruk Tefera
በዚህ ምድር ስትኖር
አስብ የሰው ድካም
ማንንም እስከ ጥግ
አትመነው በጣም
ቤተሰብ ጓደኛ
ፍቅረኛ ወዳጄ
አጋር መከታዬ
ብለህ ያልከው ቀኝ እጄ
ሁሉም በየጊዜው
ያልፋል ሆኖ ሽታ
አምላክህን ያዘው
አድርገህ አለኝታ
✍ብሩክ ተፈራ
አስብ የሰው ድካም
ማንንም እስከ ጥግ
አትመነው በጣም
ቤተሰብ ጓደኛ
ፍቅረኛ ወዳጄ
አጋር መከታዬ
ብለህ ያልከው ቀኝ እጄ
ሁሉም በየጊዜው
ያልፋል ሆኖ ሽታ
አምላክህን ያዘው
አድርገህ አለኝታ
✍ብሩክ ተፈራ
❤13
መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒
መልስ አጣለሁ ልቤ ይደነግጣል እንደ ሰው ለመሳቅ : አይኔ ተመልክቷል አፍቃሪ ሲናናቅ ከሆነ ጥፋቴ አጋር መፈለጉ : ይሻላል መሰለኝ ቢቀርብኝ ወጉ እኔ መከረኛ ስንቴ ስፈልጋት : የሚቆራረጠው ተስፋዬ አልቆ ነው…
ቻናሉ መንፈሳዊ ፅሁፎችን የምንጋራበት በመሆኑ መንፈሳዊ ይዘት ያላቸውን ነገሮች ብቻ ብናጋራ።
👍4❤3👏1
ላልችል አልኩኝ
እርግጥ ነው
ንዴት መሀል ስራ አጣሁ
:
ግን አልቆየም
ሀሳቤን ስቆጣው
ማለት የፈለኩትን
ላስረዳሽ ጊዜ ጠላኝ
:
ሄደሽ የለም ማንነቴ
ሳቄን ነው የቀማኝ....
ልልሽ የፈለኩት
እኔ እወድሻለሁ
:
ሁሌም መጨረሻ
ነብስ ትጎዳለች
አፍ በቀባጠረው...
እኔም ልክ እንደዛው
አፌ ሲፈጣጥን
እጣዬን ቀድጄ
:
ምን ይባላል አሁን
እራሴን ጠልቼ
ካንቺ ተዋድጄ ...😁
ማሽላ እያረረ ነው የሚስቀው
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
እርግጥ ነው
ንዴት መሀል ስራ አጣሁ
:
ግን አልቆየም
ሀሳቤን ስቆጣው
ማለት የፈለኩትን
ላስረዳሽ ጊዜ ጠላኝ
:
ሄደሽ የለም ማንነቴ
ሳቄን ነው የቀማኝ....
ልልሽ የፈለኩት
እኔ እወድሻለሁ
:
ሁሌም መጨረሻ
ነብስ ትጎዳለች
አፍ በቀባጠረው...
እኔም ልክ እንደዛው
አፌ ሲፈጣጥን
እጣዬን ቀድጄ
:
ምን ይባላል አሁን
እራሴን ጠልቼ
ካንቺ ተዋድጄ ...😁
ማሽላ እያረረ ነው የሚስቀው
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
ለሳቸው ለማዘን
ሰው መሆኔ ይበቃኛል
:
የፍቅራቸው ሰንሰለቱ
ያስለቅሳል አወ አስሮኛል
"ተመስገን ታቦታችን ገባ"
አሉ "ሀጂ ሙፊታ" በቃላቸው....
እግዜር ያከበረውን
ማክበር ነውና ስራቸው😭
ትልቁ ዋርካ ሲወድቅ
እልፍ ሰው ይበታተናል
:
ከሀሩር የተጠለለ
ከሽሽት ብዛት ይተናል...
ሰው ሰው ለሚሸት አባት
ማን ልሁን እሺ ለማልቀስ ?
:
ክርስቲያን ነኝ ሁሉም ያቃል
ለሳቸው ይሁን ብከሰስ
ሀገሬ ግንዷ ተነካ
አፈር ነው የሰው ልጅ ልብሱ
:
ሀጂ ግን እንዴት ቻሉበት
መሆንን ለወጣት ሱሱ...
አጣኖት አወ አባታችን
በመቃብሮ ቀናንባት
እርሶን ይዛለች እና
ማን መልሽ ማን አውጪ ይበላት😭😭
ሀጂ ሙፍቲ እንድሪስ የኢትዮጲያዊያን ሁሉ አባት ነበሩ 😭😭😭 እግዚአብሔር ነብሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
ሰው መሆኔ ይበቃኛል
:
የፍቅራቸው ሰንሰለቱ
ያስለቅሳል አወ አስሮኛል
"ተመስገን ታቦታችን ገባ"
አሉ "ሀጂ ሙፊታ" በቃላቸው....
እግዜር ያከበረውን
ማክበር ነውና ስራቸው😭
ትልቁ ዋርካ ሲወድቅ
እልፍ ሰው ይበታተናል
:
ከሀሩር የተጠለለ
ከሽሽት ብዛት ይተናል...
ሰው ሰው ለሚሸት አባት
ማን ልሁን እሺ ለማልቀስ ?
:
ክርስቲያን ነኝ ሁሉም ያቃል
ለሳቸው ይሁን ብከሰስ
ሀገሬ ግንዷ ተነካ
አፈር ነው የሰው ልጅ ልብሱ
:
ሀጂ ግን እንዴት ቻሉበት
መሆንን ለወጣት ሱሱ...
አጣኖት አወ አባታችን
በመቃብሮ ቀናንባት
እርሶን ይዛለች እና
ማን መልሽ ማን አውጪ ይበላት😭😭
ሀጂ ሙፍቲ እንድሪስ የኢትዮጲያዊያን ሁሉ አባት ነበሩ 😭😭😭 እግዚአብሔር ነብሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን
✍@dagi1u ግርማዊ ዳግም
❤8👎1