Telegram Web Link
7 የመስቀሉ ቃላት
👉 በግጥም 👈
➊ኛ ➪ ኤሎሄ ኤሎሄ
ዘጠኝ ሰአትም ሲሆን
ክርስቶስ በመስቀል ላይ ጮሀ
ኤሎሄ ኤሎሄ ለማ ሰበቅታኒ
ብሎ በከፍታ ድምፅ ጮሀ
አምላኬ አምላኬ
አባቴ የኔማ መጮሄ
ለጠላቴ መዳን
ሆንኩላቸው አዲስ ኪዳን
ኤሎሄ ኤሎሄ እላለው
ስለ ምንስ ተውከኝ
ስለ ሁሉ ስላም ሁሉ መዳን
በመስቀል ተሰቀልኩኝ
ብሎ አሰምቶ ጮሀ
ከመስቀል ስር ያሉት
ክርስቶስ ያለውን ሰሙት
ይሄስ ኤልያስን ይጠራል አሉት
ሌሎቹን ያድናል ይፈዉሳል
እስኪ እራሱን ያድን
ከመስቀል ላይ ይውረድ
ያን ግዜ አይተን እናምንበታለን
ብለው ተዘባበቱበት
እየነቀነቁ አንገታቸውን

❷ኛ ➪ አባት ሆይ የሚደርጉትን አያቁምና ይቅር በላቸው
አባት ሆይ ሚያደርጉትን
አያቁም እና ይቅር በላቸው
እንደ እነርሱ አይተ
ፍርድን አትፍረድባቸው
እንደ ቸርነት ይሁን
አይሁን እንደ በደላቸው
እንደ ፍቃዳቸው እንደ እነርሱ
አትመልከት እንደ ስራቸው
እኔ ልጅህ ልሙት
እኔ ቤዛ ልሁን ስለ ሂወታቸው
ጨርቅ ልብሴን ተካፈሉት
እርስ በእርስ ዕጣ ተጣጥለው

❸ኛ ➬ዛሬ ከኔ ጋር በገነት ትሆናል
ተዘከረነ እግዚኦ
በውሰተ መንግስትከ
እየሱስ ሆይ በመንግስት
ስትመጣ አስበኝ አለው
በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴው
እውነት እውነት እልሃለው
ዘጠና ዘጠኙን የተውኩት
ስለ ጠፋው ስለ አንዱ ነው
እውነት እውነት እልሃለው
እኔ የተሰቀልኩት ስለ ሃጣን ነው
እውነት አንተስ ታድለሃል
በመንግስት አስበኝ ያልከው
ዛሬ ከኔ ጋር በገነት ትሆናለ
አዳምንም ትቀድማለ አለው

❹ኛ ➪አባት ሆይ ነብሴን በእጅ አደራ እሰጣለው
አባት ሆይ አባት ሆይ
ነብሴን በእጅ አደራ እሰጣለው
ስለ ሃጢያተኞት ስለ ሃጣን ስራ
ቤዛ ሆንኩኝ ተቀበልኩኝ መከራ
አባት ሆይ ነብሴን ተቀበላት
ስለ ሚገድሉኝ በደለኞች
እኔ ሄያው ልጅ ልሙት

❺ኛ ➪አንቺ ሴት እነሆ ልጅሽ
አንቺ ሴት እነሆ ልጅሽ
ዮሃንስ ወዳቼ እነኋት እናትክ
ለአንተ ሰጠው አደረ እናቴን
ይዘሃት ሂድ ወደ ቤትክ
አታልቅሺ ዝም በይ እናቴ
ዮሃንስ ወዳጄ ይሆንሻል ምትክ
እናቴ ዙፋኔ በጅግር ያሳደክሽኝ
ወደ ዮሃንስ ቤት ግቢ
እኔስ ለአለም ቤዛ ሆንኩኝ
እናንተ የተዋህዶ ልጆች
እነዋት እናቴ እናታቹ
አደረ ሰጠዋቹ እናቴን
ይሄው ውሰዷት ወደየቤታቹ

❻ኛ ➬ ተጠማሁ
ተጠማሁ ተጠማሁ አለ
እየሱስ በመስቀል ተሰቅሎ ሳለ
ሆምጣጤ መራራ ሰጡት
የባህርን ጌታ ውሃን ነፈጉት
መራራውን ሆምጣጤ ተቀብሎ
እርሱ አልቻልም ለነጠጣት
በጣም መራራ ነው
ክፉ ጉሮሮን የሚልጥ

❼ ኛ ➪ተፈፀመ
ተፈፀመ አዎ ሁሉም ተፈፀመ
በናዝሬቱ እየሱስ
ሁሉም እንደ ታለም
ነብያት እንደ ተናገሩለት
ሁሉም በእርሱ ተፈፀመ
እስከ መስቀሉ ሞት
እስከ መስቀሉ ሞት
እስከ መስቀሉ ሞት፡፡

👉ተፃፈ ሃብታሙ አበራ
22👍14
√ በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ ባዕድ ቃላት
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ ዐማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡

ኪርያላይሶን፡- ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬኤሌይሶን» ነው፡፡
«ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬኤሌይሶን» መባል አለበት፡፡ ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡
«ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይሄውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በዐማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
ናይናን፡- የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ ፣ማረን» ማለት ነው፡፡
እብኖዲ፡- የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡
«እብኖዲናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው፡፡
ታኦስ፡- የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ ፣አምላክ» ማለትነው፡፡
«ታኦስናይናን» ማለትም  «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
ማስያስ፡- የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
ትስቡጣ፡- «ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው፡፡

አምንስቲቲ = አስበን፤ 
ሙኪርያ = አቤቱ ጌታ ሆይ፤ 
አንቲ ፋሲልያሱ = በመንግሥትህ፤
ሙአግያ = ቅዱስ፤ 
ሙዳሱጣ = ቸር ጌታ ማለት ነው፡፡

አምነስቲ ቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ
Em-nees the-tee mo-ki-riey enti vasilia so፡- የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ - አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡

አምንስቲ ቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ
Em-nees the-tee mo-a-geh-e enti vasilia so፡- የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው።

አምንስቲ ቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ
Em-nees the-tee mo-zess-pota enti vasilia so፡- የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡

√ ሥርዓተ ሕማማት
በሐዋርያት ቀኖና እንዲህ ይላል «ይልቁንም በእነዚህ በስድስቱ ቀኖች መጾም የሚችል ቢኖር ሁለት ሁለት ቀን ይጹም፡፡ የማይችል ግን አንድ አንድ ቀን ይጹም፡፡ ሌሎችን ቀኖች እስከ ዘጠኝ ሰዓት ይጹሙ፤ እችላለሁ የሚል ግን ፀሐይ እስኪገባ ይጹም፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ተሰብስባችሁ መጻሕፍተ ኦሪትን እና መጻሕፍተ ነቢያትን፣ የዳዊትንም መዝሙር እያነበባችሁ በምስጋና በጸሎት ዶሮ እስከሚጮህ ድረስ የሌሊቱን ሰዓት ጠብቁ፡፡

አንድ ምእመን የታመመ ቢሆን ወይም ክርስቲያን በሌለበት አገር ሆኖ ሳያውቅ የሕማማት ሰሞን ቢያልፍበት ወይንም በደዌ ውስጥ ሆኖ ቢቀርበት ከበዓለ ሃምሳ በኋላ ሰውነቱን በማድከምም ደስታን ያድርግ፡፡ ባለመፍራት እንዳይጠፋ ውስጣዊ ሰውነቱን ይመርምር፡፡ ጾምን ከመፍታታቸው በፊት ገላቸውን ይታጠቡ፤ ሁሉም መብራት የሚያበሩ ይሁኑ፡፡ የቻለ ዓርብ እና ቅዳሜ ኹለት ቀን ይጹም፤ ሁለት ቀን መጾም የማይችል በሽተኛ ቢሆን ግን ቀዳም ሥዑርን ይጹም፡፡ የኀዘን ቀን ስለሆነች፡፡ እንጀራ እና ጨውም አይቅመስ፡፡»

√ የሰሙነ ሕማማት ሥርዓት በፍትሐ ነገሥት

• ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15 
ቊጥር 578:- በነዚህ በስድስቱ ቀኖች (በሰሙነ ሕማማት) ከቂጣ ከጨው ከውኃ ብቻ በቀር አይብሉባቸው፡፡ በነዚህ ቀኖች ከወይን ከሥጋ ተለዩ የኀዘን ቀኖች ናቸውና የደስታ ቀኖች አይደሉም፡፡ ዓርብንና ቅዳሜን ግን ኹለቱንም በአንድነት ጹሟቸው፡፡ የሚችል እስከ ሌሊቱ ዶሮ ጩኸት ጊዜ ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው ሰውየውም ኹለቱን ቀኖች በአንድነት መጾም ባይቻለው ግን የቅዳሜን ጾም ይጹም፡፡
ቊጥር 590:- ካህን ሰሙነ ሕማማትን ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል አስቀድሞ ቢያውል ይሻር፡፡ ከሕማማት ቀጥላ ከምትሆን ከቅዳሜ ስዑር በቀር እሑድንና ቅዳሜን የጾመ ካህን ቢኖር ይሻር፡፡
ቊጥር፡ 593:- ከካህናት ወገን ማንም ቢሆን በአርባ ጾም በዓርብና በረቡዕም ጾም ወይን መጠጣት አይገባውም ወደ መዋት (ውሽባ ቤት) አይግባ፡፡ በዐቢይ ጾም ወራት ሰው ከሚስቱ ጋር አይተኛ፡፡
ቊጥር 597 :- ሴቶችም ጌጣቸውን ይተው፡፡ ሁሉም ለእያንዳንዱ በአርባ ጾምና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይገባዋል ድኅነታችንና የኃጢአታችን ሥርየት በእነርሱ ነውና፡፡ ይኸውም ሥራ አንዱስ እንኳ በአርባ ጾም ወራት በምንጣፍ ፈጽሞ እንዳይገናኝ ከጋብቻ ሕግ የወጣ ነው፡፡ ክብርት በምትሆን በሕማማት ወራት ይህችን ኃጢአት የሚሠራት ሰው ወዮለት፡፡ በአርባ ጾም በተድላ በደስታ ፈቃዳችንን ካደረግን ትንሣኤውን ባየን ጊዜ ተድላ ደስታችን ወዴት አለ?
ቊጥር 599:- በተባሕትዎ በትሕትና አርባ ቀን ጾምን ይጹሙ፡፡ ከጥሉላት መከልከል ይገባል፡፡ አያግቡም፡፡
ቊጥር 600:- በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሣት ክህነት መስጠት ለሞቱ ሰዎች መጸለ ይአይገባም፡፡ በእነዚህም ቀኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፈጽሞ ማገልገል ይገባል እንጅ፡፡ በሰሙነ ሕማማት ስለሚሞቱት ሰዎች የሙታን ግንዘትና የሐዋርያት ሥራ ወንጌላት የሙታን ፍትሐት በሆሣዕና በዓል ቀን ይነበብ እንጅ፡፡
ቊጥር 601:- በጸሎተ ኀሙስ ጸሎተ ተአምኆ እግዚአ ሕያዋን የቡራኬ ጸሎት አይባልም (አይጸለይም)፡፡ ቅዳሜ ግን እግዚአ ሕያዋን ይባላል ፍትሐት ይፈታል፡፡ ከመሳለም በቀር ጸሎተ ዕጣንም ይጸለያል፡፡ በዕለተ እሑድ ግን ዘት ማድረግ በፋሲካ ቀንም ማልቀስ አይገባም፡፡ ዳግመኛም በውስጧ በአርባ ጾም ከተድላ ከደስታ ወገን ምንም ማድረግ አይገባም፡፡ መጋባት ክህነት መስጠት ክርስትና ማንሣት ከሹመትም ወገን ስለሚሞቱት ከመጸለይ በቀር ምንም ማድረግ አይገባም፡፡ ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና ይደረግለታል፡፡

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም ኅብረት በክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት ያለ ጥርጥር በፍጹም ልባችን ከምናምን ምእመናን ጋር ይኹን! [፪ኛቆሮ.፲፫፥፲፬]፡፡
9👍5
#ታነባ_ነበር

በእርግዝናዋ
ስንት ያየችበት፣
የወለደችው
በከብቶች በረት፣
እየተላካት
እየታዘዘ፣
ዉሀ እየቀዳ
ሸክም እያገዘ፣

ያሳደገችው
በምድረ በዳ፣
የምትሳሳለት
የልጇ ቆዳ፣
ከግርፊያ ብዛት
ተነጫጭቶ አልቆ፣
ስጋውን አልፎ
አጥንቱ ዘልቆ፣
ርቆት ደምግባት
ተገፎ ልብሱ፣
መስቀል ላይ ሲጮህ
ስቶጣ ነብሱ፣
እያየች ማርያም
ሁሉንም ነገር፣
በታላቅ ስቃይ
ታነባ ነበር።

#ኤዶምገነት_ፃፈችው
10👍8🥰3🔥1
( የወጉት )
=============

ያኔ ....
አይሁድ በጭካኔ
ክንድህን ወጥረው
ለፍቅርህ ብድራት ለውለታህ ዋጋ
አምስት ችንካር ቆጥረው
ያለ ርህራሄ
በመስቀሉ አግድም
እጅህን ሲዘረጉት
አላወቁት እንጂ ...
ባንተ መዳፍ በኩል
እልፍ ልቦችን ነው በምስማር የወጉት !!
👍107🥰5
አሻግሬ አየሁት
.
.
በግርግር መሐል ጨርቄን ጥዬ ስበር፣
አሻግሬ አየሁት ከቀራንዮ ጫፍ ከጎለጎታ ስር።

መንገዱን በማያዉቅ እልፍ መንገደኛ መንደሩ ታዉኮ፣
አንዱ ካንዱ ሲጋጭ ከሌላኛዉ ተጓዥ ሳይተያይ ታክኮ፣

አላፊ አግዳሚውን ወጪና ወራጁን ቆሜ ስመለከት፣
ደምግባቱን ያጣ የተራቆተ ሰው አየሁኝ በድንገት፣

በደም ረስርሶ በወዝ የረጠበ ቀይ ከለሜዳ፣
በሀሰት ተከሶ ፍርዱን የሚጠብቅ ከጲላጦስ ዘንዳ፣

ይታየኛል አንድ ሰው........

በአይሁድ ሊቀ ካህናት ግራና ቀኙን ተከቦ፣
በህዝብ መካከል የቆመ በእነ ቀያፋ ተዋክቦ፣

ሲንጠበብ ወዙ ሲነሳ ሲወድቅ፣
በጥፊ ሲመቱት እጅጉን ሲሳቀቅ፣

ይታየኛል ንፁህ ሰው......

በቁርጥራጭ ብረት፣
በተሰበረ አጥንት፣

እረፍት በሌለው በወንበዴ ጅራፍ ጀርባውን ተገርፎ፣
አልባስ ተለይቶት እርቃኑን የዋለ ቀሚሱን ተገፎ፣

ስጋዉ ሲቦጫጨቅ፣
ፅሂሙም ሲነጫጭ፣

ቁጥር በማይቆጥረዉ በአይሁድ ግርፋት ቆዳዉ ተገሽልጦ፣
እዡን እያነባ ህማም አይሎበት ፊቱ ተላልጦ፣

በድካም ሲያጣጥር፣
ይታወቀኝ ጀመር፣

ከአይኔ ተንከባሎ ጉንጩን እያራሰ እንባዬ ሲወርድ፣
ላብ እያጠመቀኝ እግሬ ተብረክርኮ ሰዉነቴ ሲርድ፣

አሻግሬ አየሁት.........

በተሳለ ቅንዋት ለአዳም ሲቸነከር፣
በደሙ ቤዛነት ብድራትን ሲቸር፣

በመስቀሉ ካሳ አርአያ ሊሆነን እንባችንን ሊያብስ፣
ለዘላለም ፍቅሩ ለታመነ ቃሉ እስከመሞት ሲደርስ።

በኤደን ታደሰ እንደተፃፈ
🥰20👍1812👎1
አንዳድ ጊዜ ብቻችሁን ሁኑ!

በመጀመሪያ ለብቻ በመሆንና በብቸኝነት መካከል ልዩነቱን እንወቅ፡፡ 

ለብቻ መሆን ማለት አንድ ተግባርና ልምምድ ነው፡፡ በራስ ፈቃድና ሆን ተብሎ ከሰዎች ገለል ያለ ቦታና ጊዜ መርጦ ከራስ ጋር ማሳለፍ ማለት ነው፡፡ ለብቻ ለመሆን የግድ በአካልም ሆነ በማሕበራዊ ሚዲያ ከሰዎች ለየት ማለትን ይጠይቃል፡፡

ብቸኛ መሆን ማለት ተግባር ሳይሆን ስሜት ነው፡፡ ይህ ስሜት የሚመጣው በእኛ ፈቃድ ሳይሆን በውስጣችን ካለው የምልከታና የስነ-ልቦና ቀውስ ነው፡፡ ብቸኝነት ስሜት እንዲሰማን የግድ ከሰው በመለየት ብቻችንን መሆን የለብንም፡፡ በሰዎች መካከል እየኖርን እንኳን ይህ ስሜት ሊያጠቃን ይችላል፡፡

•  ከእለት እለት ከሰዎች ጋር የምታሳልፉ ከሆነና አንድም ቀን ለብቻችሁ የምታሳልፉበት ጊዜ ከሌላችሁ . . .

•  ሁል ጊዜ ከሰው ጋር ካልሆናችሁ የሚጨንቃችሁ ከሆነ . . .

•  በአካል ከሰዎች ጋር ካልሆናችሁ የግድ ሶሻል ሚዲያ ላይ የምታሳልፉ ከሆነ . . .

•  ብቻችሁን ስትሆኑ የብቸኝነት ስሜት የሚያጠቃችሁ ከሆነ፡፡

ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ስሜቶች እንዳለባችሁ የምታስቡ ከሆነ ብቻችሁን የመሆን ልምምድ እንደሌላችሁና የለብቸኝነት ስሜት ተጋላጭ እንደሆናችሁ አሳባቂ ሁኔታ ነው፡፡

ለብቻችሁ ከራሳችሁ ጋር ጊዜን ማሳለፍ ለብዙ ነገር ይጠቅማችኋል፡፡

•  ከሰዎች አመለካከት አጉል ተጽእኖ ነጻ በሆነ መልኩ ውስጠ-ህሊናችሁን እንድታደምጡ፣

•  ተረጋግቶ ስለወደፊት ለማቀድ፣

•  ከሰዎች ጋር ያላችሁን ግንኙነት ለማመዛዘን፣

•  ምቾት የማይሰጡ ስሜቶች የፈጠሩባችሁን ሁኔታዎች ለይቶ በማወቅ ለማስተካከል

እና ለመሳሰሉት ስኬታማ ልምምዶች ይጠቅማችኋል፡፡  

ለመጨረሻ ጊዜ ለብቻችሁ ያሳለፋችሁት መቼ ነው?

በየስንት ጊዜው ለብቻችሁ የመሆን ልምምድ አላችሁ?

ይህንን ልምምድ ዛሬውኑ ለመጀመር ብትወስኑ ምን ይመስላችኋል ?

እስኪ ኮመንት ላይ መልሳቹን ጻፉ😅
  
  
  
👍319👎1
Find your happiness in your own world.
👍4
--አቤቱ--
------------
ደግ ሰው አለቀ፤
ሁሉ ክንድህ ስር ወደቀ።
ልጆችህ ተጨንቀናል፤
ከእግርህ በታች ወድቀናል።
እምነታችን አልፀና፤
ማእበል በረታና።
አለም መአት ወረደባት፤
መርከባችንን ምጥ ያዛት።
አቤቱ....
በደቃቃ ደዌ፥ ትውልድ ረገፈ፤
አንም አልተገኘ ፥መከራን ያለፈ።
ጌታ ካላቆምከው፥ በቃችሁ ካላልከን፤
በሰማይ በምድር፥ ረዳት ማን አለን።
የቤትህ ግርግዳ፥ በሳት የተሰራ፤
ይበቃሻል በላት፥ ያለምን መከራ።
መፍረስ የሌለብህ፥ የመድሀኒት ደጃፍ።
አንተ ትችላለህ፥ መከራን ማሳለፍ፤
እማማ ኢትዮጵያ፥ ይቺ ቅድስት ሀገር፤
እናቴ ኢትዮጵያ፥ ይቺ ታላቅ ሀገር።
በዘመናት ችግር፥ ትከሻዋ ጎብጧል፤
በሸክሟ ጽናት፥ ጀርባዋ ተልጧል፤
አትችልም ጌታዬ፥ እናቴ ደክማለች።
ቀና ካላረካት፥ ጎብጣ ትቀራለች፤
አትችልም ሀገሬ፥ መከራ በቅቷታል።
ችግር በየአይነቱ፥
ጦርነት ባይነቱ፥ ተፈራርቆባታል።
አትችልም ጌታዬ፥ እናቴ ደክማለች፤
ይበቃል ካላልካት፥ ጎብጣ ትቀራለች።
አንድ ጻድቅ ጠፍቶ፥ ከቶም በምድሪቱ፤
ከፈርኦን መከራ፥ ጨከነ መአቱ።
ቸነፈር ፀናብን፥ ቀባሪ እስኪጠፋ፤
ዋኔ ዋኔ ሆኗል፥ የእንባችን ተስፋ።
ክንድህን የቻለ፥ የምድር ሀይል የለም፤
ሀያል ነህ ዘላለም ጌታ መድሀኔአለም።
አንድም ሶስትም ፥ሆነህ አለምን የገዛህ፤
ዛሬም ለዘላለም፥ የምትኖር አንተ ነህ።
የመጻጉን አልጋ፥ በራሱ ያሸከምክ፤
የጣቢታን ትንፋሽ፥ በቃልህ የመለስክ።
በልብሶችህ ቁጨት፥ የደም ምንጭ ያደረክ፤
በምራቅህ ስለህ አይን፥ የፈጠርክ አምላክ።
ታምራትህ ብዙ፥ ፍቅርህ ለዘላለም፤
ምረትህን ስጠን፥ ጌታ መድሀኔ አለም።
++++++++++++++++++++
34👍9🥰2
#ElmestoAgya #እልመስጦአግያ #Share

——ዳግም ትንሳኤ——

በተዘጉ ደጆች፣ ገባ አምላካችን፤
ሰላም ለናንተ ይሁን፣ አለን ሰላማችን፡፡
ቶማስ ሆይ አስገባ፣ ጣትህን በጎኑ፤
እጅግ ብፁዓን ናቸው፣ ሳያዩ የሚያምኑ።
14👍10🥰3👏1
Guys ዛሬ አንድ ምርጥ ቻናል ልጋብዛቹህ ሁላቹም ይህን ቻናል እየገባቹ join አድርጉ እና ትወዱታላቹህ

https://www.tg-me.com/Apostolic_Answers
👍64
♡ ሁሉም ያልፋል ♡
✞ የመዝሙር ግጥሞች ✞
♡ ሁሉም ያልፋል ♡

ሁሉም ያልፋል እግዚአብሔር ያሳልፋል /2/
ልጆቹን መቼ ይረሳል

ብርሃን ይመጣል ጨለመው ተገፎ
ደስታ ይሆናል መከራው አልፎ
የምስራች ቃል ይሞላል በአፋችን
ሀዘናችን ጠፍቶ ይፈካል ፊታችን/2/

በትር ነው ምርኩዝ ነው እሱን ላመኑበት
ባህር ውቅያኖሱን ከፍለው የሚያልፉበት
በእሳት መካከል በግፍ ለተጣሉ
ውሃ እየሆናቸው በድል ይወጣሉ /2/

ማስተዋል ጥሩ ነው ትዕዛዛቱን ማክበር
ያኖራል በሕይወት በሰማይ በምድር
የማያልፍ ቀን የለም ታሪክ የማይሆን
በአምላክ አንድ ቀን ነው አንድ ሺ ዘመን /2/

ይቅርታ እንዲሰጠን በደልን ሳይቆጥር
ማረን እንበለው ስለሆነ ፍቅር
ነገ ቀን ሲመጣ ብርሀኑ ሲያበራ
ፊታችን እንዳይዞር ወደ ክፉ ስራ /2/
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
12👍12
መንፈሳዊ ኪነ-ጥበብ💒 pinned «Guys ዛሬ አንድ ምርጥ ቻናል ልጋብዛቹህ ሁላቹም ይህን ቻናል እየገባቹ join አድርጉ እና ትወዱታላቹህ https://www.tg-me.com/Apostolic_Answers»
#ኧረ_አልሆንልኝም_አለ

/ድንቅ የንስሐ መነባንብ/

ኧር አልሆንልኝም አለ መንፈሴ አልገዛም አለ፤
የጭንቅ አማላጅቱ አንድ ብትዪኝ ምን አለ?

ጸሎት ምህላ አቃተኝ መንፈሴ ለንሰሐ ሸፈተ፤
መንጸፈ ደይን ወደቅኩኝ ነፍሴ በኃጢአት ሸፈተ።
እምቢ አለኝ ፆም ጸሎት እምቢኝ አለኝ ንስሐ፤
ስጋ መንፈሴ ኮብልሎ እየዋኘ ከዓለም ውሃ።

ኧር አንድ በይኝ እመቤቴ ወለላይቱ ተማለጂኝ፤
ጨርሶ ዓለም ሳይነጥቀኝ ከወደኩበት አንሺኝ።

ነጭ ነጠላ አጣፍቼ ከቤተ መቅደስ ስወጣ፤
መጽሐፍ ቅዱስ ዘርግቼ ለስብከት መድረክ ስወጣ፤
ልብሰ ተክህኖ ለብሼ ንፍቅ ገባሬ ሰናይ ስሆን፤
ጥቅስ በቃሌ ስደረድር ለዜማ ቅኔ ስቀኝ፤
አካሌ እዚህ ሆኖ መንፈሴ እየሸፈተ፤
ነፍሴን በኃጢአት ገንዞ ስጋዬ ነፍሴን ጎተተ።

ኧር አንድ በይኝ እመብርሃን ወለላይቱ ተማለጂኝ፤
ጨርሶ ዓለም ሳይነጥቀኝ ከወደኩበት አንሺኝ።

ማለዳ ኪዳን አድርሼ ቅዳሴ ጸሎት ጨርሼ፤
ከቤተክርስቲያን ወጥቼ ወደ ስጋ ገቢያ ተመልሼ፤
በኃጢአት ባህር ስዋኝ የግፍ ዳንኪራ ስረግጥ እውላለሁ፤
የልጅነት ፀጋዬን አውጥቼ ብኩርናዬን እሸጣለሁ።
እዚህ መልአክ መስዬ ላዬ በቅድስና በርቶ፤
ውጪ ከክፋት ከፍቼ ኃጢአት በጽድቄ ተተክቶ፤

በሀሜት የሰው ስጋ ስበላ በወንድሜ ሸር ስሸርብ፤
ስዋሽ ስቀጥፍ ውዬ ስሰርቅ ሳሽሟጥጥ ስሳደብ፤
ነጠላ ስለብስ ግን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ስገባ፤
ሰዓሊለነ ቅድስት ስል ያለ ንስሐ እንባ፤
የመውደቂያዬ ጉድጓድ ጥልቀቱ ወሰን ዳርቻ የለውም፤
እዝነ ህሊናዬ ለዓለም እንጂ ለጽድቅ ቦታ የለውም፤

መሃረነ ክርስቶስ እንዳልል ተዘከረነ ፈጣሪዬ፤
ኃጢአት በደሌ አፈነኝ በሀፍረት ነደደ ህሊናዬ፤
ምን ብዬ ልጥራው ጌታዬን ተዘከረነ ብዬ።
ስለእኔ መገረፉን የመስቀሉን ፍቅር አቃልዬ፤
እንዴት ማረኝ ልበለው ስለ ስጋ ጣዕም ተቃጥዬ።

ምን ብዬ ልጥራው ጌታዬን?

ዓይኔን ወደ ፀፍፀፈ ሰማይ ወደ ሥላሴ መንበር፤
አንስቼ ማየት አቃተኝ ማረኝ ብዬ ለመናገር።
ለሰው ጻድቅ መስዬ የኃጢአት ጎተራ ሆኛለሁ፤
እንዴት አባቴ ቀና ብዬ መንበረ ጸባኦትን አያለሁ።
እባክሽን እናቴ ወለላይቱ ተማለጂኝ፤
እንደቃና ዘገሊላ ባዶ ማድጋዬን ሙዪልኝ።
ከፊቱ እንዳላፍር ከአማኑኤል ጋር አስታርቂኝ፤
ለተጠማ ውሻ እንዳዘንሽ ለመጻተኛው እዘኚልኝ።

አንቺ የትሁታን ትሁት ርህሪይተ ልብ እናቴ፤
ከልጅሽ ከኢየሱስ አማልጂኝ እዘኚ ለእኔም እመቤቴ።
አንቺ ውዳሴሽ የነፍስ ስንቅ ስምሽ ከማር የጣፈጠ፤
በላኤሰብዕ በእፍኝ ውሃ በምልጃሽ ከሞት ያመለጠ።

አንቺ መላእክት የሚጎበኙሽ የካህናት አለቆች ምስጋናቸው፤
በመወሰን የማይወሰን እሳተ መለኮትን የቻልሽው።
አንቺ ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋ የሆንሺው፤
ዛሬም ለእኔም ተስፋ ሁኚኝ ለነፍሴ ስለነፍሴ ተዋሺው።

እንጂ እኔማ አልቻልኩም የልቤ ንጽህና ጠፍቷል፤
ለጸሎት እንኳን ስቆም ልቤ ለሁለት ተከፍሏል፡፡

ኧረ አልሆንልኝም አለ መንፈሴ አልገዛም አለ፡፡
የጭንቅ አማላጂቱ አንድ ብትዪኝ ምን አለ?
እምቢ አለኝ ፆም ጸሎት እምቢኝ አለኝ ንስሐ፤
ስጋ መንፈሴ ኮብልሎ እየዋኘ ከዓለም ውሃ።

የልቤን መወላወል የነፍሴን ድካም አበርቺ፤
በአማላጅነትሽ ስር ነኝ እና ከልጅሽ አስታርቂኝ አንቺ።
ለሰው ዓይን ባይገለጥም ሰውሬ የሰራሁት ኃጢአት፤
አምላክን አሳዝኖታል የምኖርበት ሕይወት፤
ይኸው የምናገረው አይሰምር የወረወረኩት አይመታም፤
ስጋዬ አልተቀደሰ ገበታዬ በረከት የለውም፤
ዕውቀት ምርምር አይዘልቀኝም ህሊናዬ ፍሬ አይቋጥር፤
ዝርው ሆኖብኝ ቀርቶ የነፍስ የስጋዬ ምስጢር።

ይኸው የማወራው ለሰው አይጥም ፍቅር ከእኔ ቤት ርቋል፤
መቆም መቀመጤ አያምርም ሰው በስራዬ ይማረራል፤

የኃጢአት ምንዳዬ ይኸው የኃጢአት ደሞዜ ይኸው ስቃዬ ውስጤን በልቶታል፤
ለአንድነት የተናገርኩት ዛሬም ጉባኤ ይበትናል።

እና አዛኝቱ ታረቂኝ ከልጅሽ ከአማኑኤል አማልጂኝ፤
ከሰው የሸሸግኩት ኃጢአት ጨርሶ በልቶ ሳይውጠኝ።
የበላኤሰብዕ እመቤት እባክሽን ተማለጂኝ፤
አንቺ ሕይወቴን ዳብሺው ነፍሴ ዕረፍት እንድታገኝ።

ኧረ አልሆንልኝም አለ መንፈሴ አልገዛም አለ፤
የጭንቅ አማላጅቱ አንድ ብትዪኝ ምን አለ?

መልካም ቀን
👍3428👎3🔥3
እመቤታችን በአንቺ ምልጃ
@ney_ney_emye_maryam
#እመቤታችን_በአንቺ_ምልጃ (በማየ ቃና)

እመቤታችን በአንቺ ምልጃ (2)
ድንግል ማርያም በአንቺ ምልጃ (2)
መድኃኔዓለም ተአምር ሠራ በማየ ቃና(2)

ለጌታችን ተአምር >>> በማየ ቃና
ተመርጣ ታድላ >>> በማየ ቃና
መጀመሪያ ኾነች >>> በማየ ቃና
ቃና ዘገሊላ >>> በማየ ቃና

ቃናን ሊያደርጋት የተአምሩ ቀዳሚ ስፍራ
የድንግልም ክብር ተገለጠ የምልጃ ሥራ

አዝ ---------------

ታውቋት ስላለችው >>> በማየ ቃና
ወይንኬ አልቦሙ >>> በማየ ቃና
ውኃ ወይን ሲሆን >>> በማየ ቃና
ኹሉ ዓዩ ሰሙ >>> በማየ ቃና

ቃናን ሊያደርጋት የተአምሩ ቀዳሚ ስፍራ
የድንግልም ክብር ተገለጠ የምልጃ ሥራ

አዝ -------------

አሳላፊዎቹ >>> በማየ ቃና
ግራ ቢገባቸው >>> በማየ ቃና
የድንግል ማርያም ልጅ >>> በማየ ቃና
ከጭንቅ አወጣቸው >>> በማየ ቃና

ቃናን ሊያደርጋት የተአምሩ ቀዳሚ ስፍራ
የድንግልም ክብር ተገለጠ የምልጃ ሥራ

አዝ --------------

እኛም እናምናለን >>> በማየ ቃና
በርሷ ትንብልና >>> በማየ ቃና
ስለ ቃልኪዳኗ >>> በማየ ቃና
ሁሉ እንደሚቀና >>> በማየ ቃና

ቃናን ሊያደርጋት የተአምሩ ቀዳሚ ስፍራ
የድንግልም ክብር ተገለጠ የምልጃ ሥራ


መዝሙር: ቀሲስ እስክንድር ወ/ማርያም

Guys ሰሞኑን ለማግባት ያሰባቹት አልያም ሚንዜ የሆናቹ ካላቹ እቺን መዝሙር ሸምድዷት ትጠቅማቹሀለች😂😂😂
መልካም ምሽት
36👍13🥰7
ሰላም👋 እንዴት አመሻቹህ

ውድ የዚህ ቻናል ብተሰቦች የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን የመዝሙር lyrics የተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎችን በዚ ቻናል በየጊዜው post በማድረግ ሌሎችን ማስተማር የምትፈልጉ ካላችሁ admin ይሰጣቹሀል ከዚህ በታች ባለው username አናግሩኝ
👇👇👇👇👇
@abrex_1
👍65
አረገ በክብር
የሰማያት ጌታ ፥ አለምን የሰራ
ጨለማን አርቆ ፥ ብርሀንን ያበራ
ቀድሞ በትንሳኤው ፥ ታይቶ እንደነበረ
እነሆ በሞገስ ፥ በስብሀት አረገ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ተምሳሌት ሊሆነን ፥ መንግስቱን ሊያወርሰን
ስፍራን አዘጋጅቶ ፥ ወደርሱ ሊወስደን
አረገ በክብር ፥ ሀያል ንጉስ ጌታ
ይገባል ምስጋና ፥ በሆታ በእልልታ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የማዳኑን ስራ ፥ ለእኛ እንደገለጠ
በፍርዱ ዘፋን ላይ ፥   በላይ ተቀመጠ
ወደ ሰማይ ወጣ ፥ ከሰማይ የመጣው
በአባቱ ቀኝ ሆኖ ፥ አለሙን ሊገዛው
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
እንደ በፊት ላይሞት ፥ ላይታይ ተገርፎ
ፍፁም በሚያስፈራ ፥ ግርማን ተጎናፅፎ
እልፉን መላዕክቱን ፥ ዙሪያው በመሰብሰብ
ለመምጣት ዳግመኛ ፥ ያ ጊዜ ሲቃረብ
አረገ በክብር ፥ ሀያል ንጉስ ጌታ
ይገባል ምሰጋና ፥ በሆታ በእልልታ

ብሩክ ተፈራ
38👏8👍6🥰1
የእግዚአብሔር ጥበቃ !

ትላንትና ማታ ቤተክርስትያን ቁጭ ብለን አባትና ልጅ አጠገባችን መጥተዉ ገና ቁጭ እንዳሉ ልጅ አባቷ እቅፍ ዉስጥ ሆና “አባዬ ወክ እንዉጣ” እያለች ታስቸግራለች

አባት ማስቸገሯን መቀጠሏ ስለረበሸዉ እዛዉ አካባቢ እንድትንቀሳቀስ ይለቃታል ልጅ ገና ከመለቀቋ ፊት ለፊቷ ወዳገኘችው መንገድ ሩጫዋን ቀጠለች

ይሄንን ያየ አባት ልጁ ሳታየዉ ከኃላዋ ይከተላት ጀመረ እንዳትወድቅበት ሊይዛት ፣ እንዳትጠፋ ሊጠብቃት ፣ ፍላጐቷን ሳይነፍጋት እንድትራመድ ፈቅዶ እያደረግኩልሽ ነዉ ሳይል በሚችለዉ ሁሉ አለላት

በጣም ርቃ ባይደርስባት እንኳን ፊት ለፊቷ ያሉትን ሰዎች ያዙልኝ ይላል እንጂ ተስፋ ቆርጦ አይተዋትም

ታድያ የፈጠረን ለእኛ ሲል ራሱን መስዋዕት ያደረገልን የሰማዩ አባታችን እማ እንዴት እየጠበቀን ይሆን ?

እንኳን አደረሳችሁ !

ስላልተዉከን ተመስገን 🙏
43👍2
ያ_ውሻ ...


ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር  ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሃ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ  ?

መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔
43👍4
2025/10/25 17:31:05
Back to Top
HTML Embed Code: