✟ጭንቀት✟
አባታዊ ምክር
እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው ። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን ሲተረጉመው "ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ይለዋል " የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም ፤ ውጥረት ፤ ወይም ሕመም ማለት ነው ። ጭንቀት ለሕይወታችን ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው ። ስለሆነም የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው ? ስንል #ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን ። በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን ፤ ከሚቀርቡን ፤ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ የምንጠብቀው አለ ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶችሊመጣ ይችላል ። ✞ስለ ሰወች ያለን ተስፈኝነት አለ ። ሌላው ✞ሰዎች ስለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው ።
በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን ይችላል ። ወይም እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል ። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን አድርገን ልንወስድ እንችላለን ። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን ይችላል ።
ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው ።
የቁስ እቃ ፍላጎት እንድንጨነቅ ያደርጋል ። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ አሉታዊ መልስ እንሰጣለን ። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም ሳይሆን ይቀራል ።
✟ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴቤተ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው ። ቁሣዊ ሆነን አልተፈጠርንም ። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው ። መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው ። ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው ። ግፊቱም ፤ ጭንቀቱም ፤ሕመሙና ፤ውጥረቱ ፤በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል ። ከእግዚአብሔር ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም ። ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም አደርጋለሁ ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል ።
✟ ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር ። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ ። እንደገናም ለባርነት ሸጡት ። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት በሐሰት ከሰሰችው ። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ ። በእስር ቤት እያለ ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም ። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና ውስጥ ያመጣዋል ። ሆኖም ግን ዮሴፍ እነዴት ለመፍታት ሞከረ ? ችግሩን እነዴት ተቋቋመው ? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ራሱ ዮሴፍ ነበረ ። አልተለወጠም ።በሁሉም ሁኔታዎች ተመሣሣይ ፤ ማንነት ፤ ፍቅር ፤ እምነት ፤ ነበረው ። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ ። እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ ።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
@menfesawimeker
አባታዊ ምክር
እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው ። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን ሲተረጉመው "ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ይለዋል " የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም ፤ ውጥረት ፤ ወይም ሕመም ማለት ነው ። ጭንቀት ለሕይወታችን ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው ። ስለሆነም የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው ? ስንል #ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን ። በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን ፤ ከሚቀርቡን ፤ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ የምንጠብቀው አለ ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶችሊመጣ ይችላል ። ✞ስለ ሰወች ያለን ተስፈኝነት አለ ። ሌላው ✞ሰዎች ስለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው ።
በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን ይችላል ። ወይም እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል ። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን አድርገን ልንወስድ እንችላለን ። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን ይችላል ።
ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው ።
የቁስ እቃ ፍላጎት እንድንጨነቅ ያደርጋል ። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ አሉታዊ መልስ እንሰጣለን ። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም ሳይሆን ይቀራል ።
✟ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴቤተ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው ። ቁሣዊ ሆነን አልተፈጠርንም ። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው ። መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው ። ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው ። ግፊቱም ፤ ጭንቀቱም ፤ሕመሙና ፤ውጥረቱ ፤በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል ። ከእግዚአብሔር ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም ። ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም አደርጋለሁ ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል ።
✟ ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር ። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ ። እንደገናም ለባርነት ሸጡት ። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት በሐሰት ከሰሰችው ። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ ። በእስር ቤት እያለ ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም ። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና ውስጥ ያመጣዋል ። ሆኖም ግን ዮሴፍ እነዴት ለመፍታት ሞከረ ? ችግሩን እነዴት ተቋቋመው ? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ራሱ ዮሴፍ ነበረ ። አልተለወጠም ።በሁሉም ሁኔታዎች ተመሣሣይ ፤ ማንነት ፤ ፍቅር ፤ እምነት ፤ ነበረው ። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ ። እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ ።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
@menfesawimeker
✝እግዚአብሔር ተስፋ አድርግ
ለመንጋው ሁሉ በጎ እንደሚመኝ እንደ መልካም እረኛ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ በሙሉ ያለምንም ጥርጥር #በዝምታ_ይሠራል ። ይሁን እንጂ ሰዎች በመከራ ውስጥ ሆነው የእግዚአብሔር መልስ ከዘገየባቸው እንደማይሠራ አድርገው ያስባሉ ። እነርሱ እግዚአብሔር አይሠራም ብለው በሚያስብበት ሰዓት ሁሉ እርሱ ግን ለእነርሱ #በጥልቅ_እየሠራ ነው ። ሰዎች ይህንን ስለማይገነዘቡ የእግዚአብሔርን ሥራና የሥራውን ውጤት ፈጥነው ለማየት ይፈልጋሉ ። እነዚህ ሰዎች ግን በእምነታቸው ያመኑትን በዓይናቸው እስኪመለከቱ ድረስ ሊቆዩ ይገባቸዋል ። " እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ ፤ በርታ ልብህም ይጽና ፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ ። " [መዝ 26*14 ] ።
እግዚአብሔርን እንዴት እንጠብቅ?
እግዚአብሔርን የሚጠብቅ ሰው እርሱን በተስፋ ፤ በእምነት ፤ በተሞላ ሙሉ ልብና ያለምንም ድካም ይጠብቀዋል ። ይህ በመሆኑም እንደዚህ ዓይነቱ ሰው እግዚአብሔር በመካከል ገብቶ እንደሚሰራና ሁሉም ነገር ለበጎ እንደሚሆን ያምናል ። " እግዚአብሔር ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን ።" [ ሮሜ 8*28] ። " እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ ፤ ይሮጣሉ አይታክቱም ይሄዳሉ አይደክሙም " [ኢሳ 40*31] ። ኃይላቸው በመከራ የተናወጠባቸው ሁሉ እግዚአብሔርን በተስፋ በመጠባበቅ ኃይላቸውን ያድሳሉ ማለት ነው ። " ጎልማስነትሽን እንደ ንስር ያድሳል " የሚል ቃል ተጽፋል [ መዝ 102*5] ። ስለሆነም ማንም ቢሆን እግዚአብሔር #እምነት በተሞላ ብርቱ ልብና በእርሱ ላይ በመተማመን ይጠብቀዋል ።
ነገር ግን አንድ ሰው እግዚአብሔር እርምጃ እንደሚወስድና እርምጃውም ግልጽና ኃያል እንደሆነ መተማመን አለበት ። ከዚሁ ጋር እርምጃው በተመቻቸ ሰዓት ፍሬያማ በሆነ መንገድ የሚከናወን ነው ። እግዚአብሔር አንድ የሆነ እርምጃ ለመውሰድ ከወደደ ምንም የሚጠባበቀው ሰዓት አይኖርም ። ኢየሱስ ክርስቶስ " ... አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም አላለምን ? /ሐዋ 1*7/ ። አንተ ችግርህን እግዚአብሔር እንደሚያቃልልህ በማመን መቼ ለችግርህ መፍትሔ እንደሚሰጥህ ሳታስብ በእርሱ እጅ ላይ ብቻ ጣለው ። ችግርህን እግዚአብሔር በጊዜው እንደሚያቃልለው መጠባበቅ የአንተ ሥራ አይደለም ።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
@menfesawimeker
ለመንጋው ሁሉ በጎ እንደሚመኝ እንደ መልካም እረኛ እግዚአብሔር ለፍጥረቱ በሙሉ ያለምንም ጥርጥር #በዝምታ_ይሠራል ። ይሁን እንጂ ሰዎች በመከራ ውስጥ ሆነው የእግዚአብሔር መልስ ከዘገየባቸው እንደማይሠራ አድርገው ያስባሉ ። እነርሱ እግዚአብሔር አይሠራም ብለው በሚያስብበት ሰዓት ሁሉ እርሱ ግን ለእነርሱ #በጥልቅ_እየሠራ ነው ። ሰዎች ይህንን ስለማይገነዘቡ የእግዚአብሔርን ሥራና የሥራውን ውጤት ፈጥነው ለማየት ይፈልጋሉ ። እነዚህ ሰዎች ግን በእምነታቸው ያመኑትን በዓይናቸው እስኪመለከቱ ድረስ ሊቆዩ ይገባቸዋል ። " እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ ፤ በርታ ልብህም ይጽና ፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ ። " [መዝ 26*14 ] ።
እግዚአብሔርን እንዴት እንጠብቅ?
እግዚአብሔርን የሚጠብቅ ሰው እርሱን በተስፋ ፤ በእምነት ፤ በተሞላ ሙሉ ልብና ያለምንም ድካም ይጠብቀዋል ። ይህ በመሆኑም እንደዚህ ዓይነቱ ሰው እግዚአብሔር በመካከል ገብቶ እንደሚሰራና ሁሉም ነገር ለበጎ እንደሚሆን ያምናል ። " እግዚአብሔር ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን ።" [ ሮሜ 8*28] ። " እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ ፤ ይሮጣሉ አይታክቱም ይሄዳሉ አይደክሙም " [ኢሳ 40*31] ። ኃይላቸው በመከራ የተናወጠባቸው ሁሉ እግዚአብሔርን በተስፋ በመጠባበቅ ኃይላቸውን ያድሳሉ ማለት ነው ። " ጎልማስነትሽን እንደ ንስር ያድሳል " የሚል ቃል ተጽፋል [ መዝ 102*5] ። ስለሆነም ማንም ቢሆን እግዚአብሔር #እምነት በተሞላ ብርቱ ልብና በእርሱ ላይ በመተማመን ይጠብቀዋል ።
ነገር ግን አንድ ሰው እግዚአብሔር እርምጃ እንደሚወስድና እርምጃውም ግልጽና ኃያል እንደሆነ መተማመን አለበት ። ከዚሁ ጋር እርምጃው በተመቻቸ ሰዓት ፍሬያማ በሆነ መንገድ የሚከናወን ነው ። እግዚአብሔር አንድ የሆነ እርምጃ ለመውሰድ ከወደደ ምንም የሚጠባበቀው ሰዓት አይኖርም ። ኢየሱስ ክርስቶስ " ... አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም አላለምን ? /ሐዋ 1*7/ ። አንተ ችግርህን እግዚአብሔር እንደሚያቃልልህ በማመን መቼ ለችግርህ መፍትሔ እንደሚሰጥህ ሳታስብ በእርሱ እጅ ላይ ብቻ ጣለው ። ችግርህን እግዚአብሔር በጊዜው እንደሚያቃልለው መጠባበቅ የአንተ ሥራ አይደለም ።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
@menfesawimeker
+ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር +
☞ ተወዳጆች ሆይ ጊዜ ሳለልን ድኅነታችንን እንፈጽም፡፡ ጊዜ ሳለልን ለመብራታችን ዘይት የተባለ ምጽዋትን እንያዝ፡፡ ጊዜ ሳለልን መክሊታችንን ለማብዛት እንፍጨርጨር፡፡ በዚህ ዓለም ሳለን ይህን ለማከናወን ልል ዘሊል እና ሐኬተኞች ከኾንን በወዲያኛው ዓለም እልፍ ወትእልፊት ጊዜ ወዮ ብለን ብናለቅስ ብንጮህም እንኳን የሚረዳን የለምና፡፡ ያ ባለ አንድ መክሊት ሠራተኛ አንዲቷን መክሊት ሳይቀንስ ለጌታው ቢያስረክብም ከኩነኔ አላመለጠምና፡፡ አምስቱ ሰነፎች ደናግልም ጌታችንን ለምነውት ነበር፤ በሩን አንኳኩተው ነበር፡፡ ነገር ግን ልመናቸውም ማንኳኳታቸውም ከንቱ ነበር፥ ጥቅም አልባ ነበር፡፡
☞ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ዐውቀን በሀብታችንም፣ በትጋታችንም፣ ለወንድማችን በምናደርገው ማናቸውም ጠቃሚ ነገርም የዓቅማችንን ያህል እንጣር፡፡ መክሊት የተባለው የእያንዳንዱ ሰው በእጁ ያለውና ማድረግ የሚችለው ነገር ማለት ነውና፡፡ ለአንዱ ወንድሙን መጠበቅ ሊኾን ይችላል፥ ለአንዱ በገንዘቡ ደግ ነገር ማድረግ ሊኾን ይችላል፥ ለሌላው ማስተማር ሊኾን ይችላል፥ ለሌላው ደግሞ ይህን በመሰለ ሌላ ነገር ሊኾን ይችላልና ጊዜ ሳለልን በሞተ ሥጋም ሳንወሰድ መክሊታችንን እናብዛ፡፡ አንድ ሰውስ እንኳን መክሊቴ አንዲት ናት አይበል፡፡ የተሰጠችህ መክሊት አንዲት ብትኾንም አንተ ንቁ ከኾንህ ንዑድ ክቡር ከመባል አትከለከልምና፡፡ ምንም ያህል ድኻ ብትኾንም ከዚያች ኹለት ሳንቲም ከሰጠችው ሴት በላይ ድኻ ልትኾን አትችልምና የተሰጠቺኝ ትንሽ ናት አትበለኝ፡፡ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ዮሐንስ በላይ ያልተማርክ ልትኾን አትችልምና እኔኮ አልተማርኩም አትበለኝ፡፡ እነርሱ ምንም ያልተማሩ ቢኾኑም ባሳዩት ትጋት ርስት መንግሥተ ሰማያትን መውረስ ተችሎዋቸዋልና እኔ አይቻለኝም አትበለኝ፡፡
☞ እግዚአብሔር አንደበትን የሰጠን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሔር እግርን የሰጠን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሔር ብርታትን፣ አእምሮን፣ ማሰብን የለገሰን ለዚህ ነው፡፡ እነዚህን ኹሉ የሰጠን ለራሳችን እንድናተርፍባቸውና ለባልጀሮቻችንም እንድንጠቅምባቸው ነውና ኹለት ወይም አምስት መክሊት አልተሰጠኝም አትበለኝ፡፡'
ተርጓሚ፦ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
☞ ተወዳጆች ሆይ ጊዜ ሳለልን ድኅነታችንን እንፈጽም፡፡ ጊዜ ሳለልን ለመብራታችን ዘይት የተባለ ምጽዋትን እንያዝ፡፡ ጊዜ ሳለልን መክሊታችንን ለማብዛት እንፍጨርጨር፡፡ በዚህ ዓለም ሳለን ይህን ለማከናወን ልል ዘሊል እና ሐኬተኞች ከኾንን በወዲያኛው ዓለም እልፍ ወትእልፊት ጊዜ ወዮ ብለን ብናለቅስ ብንጮህም እንኳን የሚረዳን የለምና፡፡ ያ ባለ አንድ መክሊት ሠራተኛ አንዲቷን መክሊት ሳይቀንስ ለጌታው ቢያስረክብም ከኩነኔ አላመለጠምና፡፡ አምስቱ ሰነፎች ደናግልም ጌታችንን ለምነውት ነበር፤ በሩን አንኳኩተው ነበር፡፡ ነገር ግን ልመናቸውም ማንኳኳታቸውም ከንቱ ነበር፥ ጥቅም አልባ ነበር፡፡
☞ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ዐውቀን በሀብታችንም፣ በትጋታችንም፣ ለወንድማችን በምናደርገው ማናቸውም ጠቃሚ ነገርም የዓቅማችንን ያህል እንጣር፡፡ መክሊት የተባለው የእያንዳንዱ ሰው በእጁ ያለውና ማድረግ የሚችለው ነገር ማለት ነውና፡፡ ለአንዱ ወንድሙን መጠበቅ ሊኾን ይችላል፥ ለአንዱ በገንዘቡ ደግ ነገር ማድረግ ሊኾን ይችላል፥ ለሌላው ማስተማር ሊኾን ይችላል፥ ለሌላው ደግሞ ይህን በመሰለ ሌላ ነገር ሊኾን ይችላልና ጊዜ ሳለልን በሞተ ሥጋም ሳንወሰድ መክሊታችንን እናብዛ፡፡ አንድ ሰውስ እንኳን መክሊቴ አንዲት ናት አይበል፡፡ የተሰጠችህ መክሊት አንዲት ብትኾንም አንተ ንቁ ከኾንህ ንዑድ ክቡር ከመባል አትከለከልምና፡፡ ምንም ያህል ድኻ ብትኾንም ከዚያች ኹለት ሳንቲም ከሰጠችው ሴት በላይ ድኻ ልትኾን አትችልምና የተሰጠቺኝ ትንሽ ናት አትበለኝ፡፡ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ዮሐንስ በላይ ያልተማርክ ልትኾን አትችልምና እኔኮ አልተማርኩም አትበለኝ፡፡ እነርሱ ምንም ያልተማሩ ቢኾኑም ባሳዩት ትጋት ርስት መንግሥተ ሰማያትን መውረስ ተችሎዋቸዋልና እኔ አይቻለኝም አትበለኝ፡፡
☞ እግዚአብሔር አንደበትን የሰጠን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሔር እግርን የሰጠን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሔር ብርታትን፣ አእምሮን፣ ማሰብን የለገሰን ለዚህ ነው፡፡ እነዚህን ኹሉ የሰጠን ለራሳችን እንድናተርፍባቸውና ለባልጀሮቻችንም እንድንጠቅምባቸው ነውና ኹለት ወይም አምስት መክሊት አልተሰጠኝም አትበለኝ፡፡'
ተርጓሚ፦ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
+++ ተግሣጽ ለኩሉ +++
አንድ ቀስተኛ ቀስቱን በትክክል ለመወርወር ሲፈልግ በመጀመሪያ ትልቅ ጥንቃቄን ለአቋቋሙ በመውሰድ ከኢላማው ጋር ራሱን ያስተካክላል፡፡ እናንተም እንዲህ ነው መሆን ያለባችሁ የአሳቹን ዲያብሎስን ራስ ለምታት ከሁሉም በፊት ጥሩ ስሜትን ለማግኘት መበርታት ከዚያም የውስጣችንን ቁመና ማስተካከል
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
+++
በክፉ ምኞት እና ሃሳብ ጊዜ ይህንን ወይም ያንን ውሰድልኝ አትበል ይልቁንም ግን እንዲህ ብለህ ጸልይ አቤቱ ጌታ መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ የነፃነት አምላክ መልሼ እንዳልበድል በአንተ ላይ አግዘኝ
አባ ኢሳይያስ ባሕታዊ
+++
ይህ የሆነው በእድል ነው ያም የሆነው በራሱ ጊዜ ነው አትበሉ ከተፈጠረው ሁሉ የተዛባ ወይም የተዘበራረቀ ፣ ትክክል ያልሆነ ፣ ያለ ምክንያት የሆነ ፣ በእድል የሆነ የለም በራስህ ላይ ስንት ፀጉር አለ? አንዲቷንም አምላክ አይረሳም፡፡ ስለዚህ አየህ ምንም ነገር ትንሿም ነገር ከርሱ ፊትና እይታ እንደማያመልጥ? እርሱ ይጠብቅሃል!
ቅዱስ ባስልዮስ ታላቁ
+++
የእግዚአብሔር ፍቅር በራሴ ውስጥ አይሰማኝም ብለህ አትረበሽ ይልቅ ስለ አምላክ ምህረት አስብ እና ራስህንም ከኃጢአት ጠብቅ ከዚያ ልዑል እግዚአብሔር ራሱ ያስተምርሃል
አባ ሲሎዋን አቴናዊ
+++
አንድ ሰው ስለ ኃጢያቱ ንስሐ ቢገባ እና ያንኑ መልሶ ያንኑ ኃጢያት መልሶ ከሰራዉ ከኃጢአቱ መንስኤ እንዳልነፃ ምልክት ነው ፤ ከስሩ ያልተነቀለ ዛፍ ቅርንጫፍ መልሶ እንደሚያበቅል
ቅዱስ ባስልዮስ ታላቁ
+++
በስራችን ሁሉ ፈጣሪ ለምን እንዳደረግነው ያያል ፤ ለርሱ ስንል እንዳረግነው አልያም ለሌላ ፍላጎት እንደ ሆነ እንዳደረግነው
አንድ ቀስተኛ ቀስቱን በትክክል ለመወርወር ሲፈልግ በመጀመሪያ ትልቅ ጥንቃቄን ለአቋቋሙ በመውሰድ ከኢላማው ጋር ራሱን ያስተካክላል፡፡ እናንተም እንዲህ ነው መሆን ያለባችሁ የአሳቹን ዲያብሎስን ራስ ለምታት ከሁሉም በፊት ጥሩ ስሜትን ለማግኘት መበርታት ከዚያም የውስጣችንን ቁመና ማስተካከል
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
+++
በክፉ ምኞት እና ሃሳብ ጊዜ ይህንን ወይም ያንን ውሰድልኝ አትበል ይልቁንም ግን እንዲህ ብለህ ጸልይ አቤቱ ጌታ መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ የነፃነት አምላክ መልሼ እንዳልበድል በአንተ ላይ አግዘኝ
አባ ኢሳይያስ ባሕታዊ
+++
ይህ የሆነው በእድል ነው ያም የሆነው በራሱ ጊዜ ነው አትበሉ ከተፈጠረው ሁሉ የተዛባ ወይም የተዘበራረቀ ፣ ትክክል ያልሆነ ፣ ያለ ምክንያት የሆነ ፣ በእድል የሆነ የለም በራስህ ላይ ስንት ፀጉር አለ? አንዲቷንም አምላክ አይረሳም፡፡ ስለዚህ አየህ ምንም ነገር ትንሿም ነገር ከርሱ ፊትና እይታ እንደማያመልጥ? እርሱ ይጠብቅሃል!
ቅዱስ ባስልዮስ ታላቁ
+++
የእግዚአብሔር ፍቅር በራሴ ውስጥ አይሰማኝም ብለህ አትረበሽ ይልቅ ስለ አምላክ ምህረት አስብ እና ራስህንም ከኃጢአት ጠብቅ ከዚያ ልዑል እግዚአብሔር ራሱ ያስተምርሃል
አባ ሲሎዋን አቴናዊ
+++
አንድ ሰው ስለ ኃጢያቱ ንስሐ ቢገባ እና ያንኑ መልሶ ያንኑ ኃጢያት መልሶ ከሰራዉ ከኃጢአቱ መንስኤ እንዳልነፃ ምልክት ነው ፤ ከስሩ ያልተነቀለ ዛፍ ቅርንጫፍ መልሶ እንደሚያበቅል
ቅዱስ ባስልዮስ ታላቁ
+++
በስራችን ሁሉ ፈጣሪ ለምን እንዳደረግነው ያያል ፤ ለርሱ ስንል እንዳረግነው አልያም ለሌላ ፍላጎት እንደ ሆነ እንዳደረግነው
✝የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል ።
ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ።
"ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር ! እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ።
"ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር ! እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
ሰይጣን ራሳችንን ስንገዛና ከራሳችን ጋር ስንሆን ኃጢአታችንንም ስናስተውል ስለንሰሐም ስናስብ ይፈራል።በዚህ ጊዜ ከእርሱ ማምለጥ ይቻላል።
በእናንተ ሳይፈረድባችሁ አስቀድማችሁ እናንተ በራሳችሁ ላይ ፍረዱ” ቅዱስ መቃርዮስ
እንባህ ከመፍሰስ እንዳይቆም ከወደድህ በጸሎት ጽሙድ ሁን አንድም በተዘክሮ ጽሙድ ሁነህ ኑር።
መከራ መጥቶብህ መከራውን ለማራቅ ከምትጸልየው ጸሎት አስቀድሞ ለሚገባ ንሰሀ ተዘጋጅ።
እኛ ሀጢአታችንን ያስታወስን እንደሆነ እግዚአብሔር ይተዋቸዋል። እኛ ግን ኃጢአታችንን የዘነጋን እንደሆነ እግዚአብሔር ያስታውሰናል”
ቅዱስ እንጦስ
""""""""""""""""""""
በንሰሀ ሕየወት ለመኖር የምንሻ ከሆነ ለወደቅንበት ኃጢአት ምክንያት መደርደርና ለራሳችን ይቅርታን ለመስጠት መሞከር የለብንም።
አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ሥጋችን ምግብ ሲያጣ እንደሚደክም ሁሉ ነፍስም ምግቧን የእግዚአብሔርን ቃል ስታጣ ትደክማለች።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
አንተ ሌሎችን የምትምር ከሆነ እግዚአብሔርም አንተን ይምርሃል። ነገር ግን አንተ እቁጡና ጨካኝ ሆነህ ሳለህ የእጅህን ዋጋ ብታገኝ እንዳታማርር።
አቡነ ሺኖዳ
የዋህ ሰው ሰለ እርሱ ሰዎች ይከላከሉለታል እንጂ እርሱ አይከላከልም።
አቡነ ሺኖዳ
ክርስቲያን በተፈጥሮው የማስተዋል የአርምሞ የጥንቃቄና የሰላም ሰው ነው።
አንተ ካስፈለገህ ሁለት ጊዜ ከተጠየቅህ በመጠኑ ተናገር፣ መልስህም በጥንቃቄ እና በ’እውቀት ባጭሩ የሰዎችን አእምሮ የማያስጨንቅ ይሁን።
እውነትን ከመስማት የበለጠ ለጆሮውች ጌጣጌጥ የላቸውንማ ሴቶች ለምድራዊ ጌጣጌጦች ጆሯቸውን አይብሱ፣ እውነትን ለመስማት የተበሱ ጆሮዎች ቅዱስ ነገርን መለኮታዊ ቃልን ያደምጣሉና።
አንደበትህ በአርምሞ በዝምታ የተመላ ይሁን ልብህን በእርጋታ አአኑረው የሁሉም መጨረሻና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ፣ ለከንቱ ንግግር (ወሬ) ዘገምተኛ እና ሰነፍ ሁን፣ ነገር ግን ቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድህነት የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን።
ማንኛውንም ነገር ለማውቅ የክፋት መርዝ በአምሮህ እንዳይሰራጭ ጉጉት አይደርብህ
የመንፈስ ስጦታዎች ልዩ ልዩ እንደመሆናቸው መጠን እና አንዱ አገልጋይ ሁሉንም ገንዘብ ማድረግ ሰለሚችል በተሰጠው ጸጋ በማመስገን ቢቀመጥ መልካም ነው።
ለመስበክ የተመረጠው ሰባኪ ወንጌልን ለመስበክ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይጠብቅ እንጂ የራሱን አይደለም
ሰነፍ ሰው ሲስቅ ይጮሀል ድምጹንም ከፍ ከፍ ያደርጋል።
የሚስት አክሊሏ ባሏ ነው፣ ፣የባልም ጋብቻው ለሁለቱም የጋብቻቸው አበባም አንድነታቸው ልጆቻቸው ናቸው። ይኸውም በመለኮታዊ አመሰራረት ከስጋ እርሻ የተገኘ ነው ።
ድንቁርና በሃጢአት እንድንወድቅ ስለሚያደርግ እውነትንም በግልጽ የምናይበትን ችሎታን ስለማይሰጥ ጨለማ ነው።
እውቀት ግን የድንቁርናን ጨለማ አስወግዶ እውቀትን ሰለሚያጎናጽፈን ብርሃን ነው።
ልብህን በእርጋታ አኑረው፤የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር (ወሬ) ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን። ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድህነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን ።
ታላቁ ባስልዮስ የቂሳሪያ ሊቀ ጳጳስ።
ትህትና
መድኅን ነው ከሰይጣን አሽክላ ያድንሃል።
/አባ እንጦንስ/
ትህትና
የሰው ዘመድ ነው። / አባ አሞን/
ትህትና
የማይናድ ደልዳላ መሬት ነው። /አባአርሳንዮስ/
ትህትና
ክርስቲያናዊ ምልክት ነው። /አባ መቃርስ/
ትህትና
ከትሩፋት ሁሉ ይበልጣል። /አባ አሞን/
ትህትና
መስቀል ነው። /አባ ታድራ/
ትህትና
የሰው ሁሉ ጋሻ ጦር ነው። /አባ በሐይ/
ትህትና
ግድግዳን የሚያስጌጥ የአፈር ወይዘሮ ነው።/አባ አጋቶን/
ትህትና
የመንግስተ ሰማያት መመላለሻ በር ነው። /አባ ሚልኪ/
ትህትና
ሕፀጽን የሚያስታውቅ መስታወት ነው። /አባጰርዬ/
ትህትና
የነፍሳት ወደብ ነው። /አባ ዮሐንስ/
ትህትና
የወንጌል ትእዘዝ መጀመሪያ ነው። /አባዮሐንስ ሐፂር/
ትህትና
ወደ ንፁሐ ልቡና ሰገነት የሚወጡበት ዕፀሕይወት ናት።/አባመቃርስ/
የእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት
ከሁላችንም ጋር ይሁን
በእናንተ ሳይፈረድባችሁ አስቀድማችሁ እናንተ በራሳችሁ ላይ ፍረዱ” ቅዱስ መቃርዮስ
እንባህ ከመፍሰስ እንዳይቆም ከወደድህ በጸሎት ጽሙድ ሁን አንድም በተዘክሮ ጽሙድ ሁነህ ኑር።
መከራ መጥቶብህ መከራውን ለማራቅ ከምትጸልየው ጸሎት አስቀድሞ ለሚገባ ንሰሀ ተዘጋጅ።
እኛ ሀጢአታችንን ያስታወስን እንደሆነ እግዚአብሔር ይተዋቸዋል። እኛ ግን ኃጢአታችንን የዘነጋን እንደሆነ እግዚአብሔር ያስታውሰናል”
ቅዱስ እንጦስ
""""""""""""""""""""
በንሰሀ ሕየወት ለመኖር የምንሻ ከሆነ ለወደቅንበት ኃጢአት ምክንያት መደርደርና ለራሳችን ይቅርታን ለመስጠት መሞከር የለብንም።
አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ሥጋችን ምግብ ሲያጣ እንደሚደክም ሁሉ ነፍስም ምግቧን የእግዚአብሔርን ቃል ስታጣ ትደክማለች።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
አንተ ሌሎችን የምትምር ከሆነ እግዚአብሔርም አንተን ይምርሃል። ነገር ግን አንተ እቁጡና ጨካኝ ሆነህ ሳለህ የእጅህን ዋጋ ብታገኝ እንዳታማርር።
አቡነ ሺኖዳ
የዋህ ሰው ሰለ እርሱ ሰዎች ይከላከሉለታል እንጂ እርሱ አይከላከልም።
አቡነ ሺኖዳ
ክርስቲያን በተፈጥሮው የማስተዋል የአርምሞ የጥንቃቄና የሰላም ሰው ነው።
አንተ ካስፈለገህ ሁለት ጊዜ ከተጠየቅህ በመጠኑ ተናገር፣ መልስህም በጥንቃቄ እና በ’እውቀት ባጭሩ የሰዎችን አእምሮ የማያስጨንቅ ይሁን።
እውነትን ከመስማት የበለጠ ለጆሮውች ጌጣጌጥ የላቸውንማ ሴቶች ለምድራዊ ጌጣጌጦች ጆሯቸውን አይብሱ፣ እውነትን ለመስማት የተበሱ ጆሮዎች ቅዱስ ነገርን መለኮታዊ ቃልን ያደምጣሉና።
አንደበትህ በአርምሞ በዝምታ የተመላ ይሁን ልብህን በእርጋታ አአኑረው የሁሉም መጨረሻና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ፣ ለከንቱ ንግግር (ወሬ) ዘገምተኛ እና ሰነፍ ሁን፣ ነገር ግን ቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድህነት የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን።
ማንኛውንም ነገር ለማውቅ የክፋት መርዝ በአምሮህ እንዳይሰራጭ ጉጉት አይደርብህ
የመንፈስ ስጦታዎች ልዩ ልዩ እንደመሆናቸው መጠን እና አንዱ አገልጋይ ሁሉንም ገንዘብ ማድረግ ሰለሚችል በተሰጠው ጸጋ በማመስገን ቢቀመጥ መልካም ነው።
ለመስበክ የተመረጠው ሰባኪ ወንጌልን ለመስበክ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይጠብቅ እንጂ የራሱን አይደለም
ሰነፍ ሰው ሲስቅ ይጮሀል ድምጹንም ከፍ ከፍ ያደርጋል።
የሚስት አክሊሏ ባሏ ነው፣ ፣የባልም ጋብቻው ለሁለቱም የጋብቻቸው አበባም አንድነታቸው ልጆቻቸው ናቸው። ይኸውም በመለኮታዊ አመሰራረት ከስጋ እርሻ የተገኘ ነው ።
ድንቁርና በሃጢአት እንድንወድቅ ስለሚያደርግ እውነትንም በግልጽ የምናይበትን ችሎታን ስለማይሰጥ ጨለማ ነው።
እውቀት ግን የድንቁርናን ጨለማ አስወግዶ እውቀትን ሰለሚያጎናጽፈን ብርሃን ነው።
ልብህን በእርጋታ አኑረው፤የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር (ወሬ) ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን። ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድህነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን ።
ታላቁ ባስልዮስ የቂሳሪያ ሊቀ ጳጳስ።
ትህትና
መድኅን ነው ከሰይጣን አሽክላ ያድንሃል።
/አባ እንጦንስ/
ትህትና
የሰው ዘመድ ነው። / አባ አሞን/
ትህትና
የማይናድ ደልዳላ መሬት ነው። /አባአርሳንዮስ/
ትህትና
ክርስቲያናዊ ምልክት ነው። /አባ መቃርስ/
ትህትና
ከትሩፋት ሁሉ ይበልጣል። /አባ አሞን/
ትህትና
መስቀል ነው። /አባ ታድራ/
ትህትና
የሰው ሁሉ ጋሻ ጦር ነው። /አባ በሐይ/
ትህትና
ግድግዳን የሚያስጌጥ የአፈር ወይዘሮ ነው።/አባ አጋቶን/
ትህትና
የመንግስተ ሰማያት መመላለሻ በር ነው። /አባ ሚልኪ/
ትህትና
ሕፀጽን የሚያስታውቅ መስታወት ነው። /አባጰርዬ/
ትህትና
የነፍሳት ወደብ ነው። /አባ ዮሐንስ/
ትህትና
የወንጌል ትእዘዝ መጀመሪያ ነው። /አባዮሐንስ ሐፂር/
ትህትና
ወደ ንፁሐ ልቡና ሰገነት የሚወጡበት ዕፀሕይወት ናት።/አባመቃርስ/
የእግዚአብሔር ቸርነትና ምህረት
ከሁላችንም ጋር ይሁን
ሥጋ ወደም
ዲያብሎስ እጅግ በጣም አብዝቶ ማራቅ የሚፈልገው ከምሥጢራት ሁሉ የበላይ ከሆነው “ከምሥጢረ ቁርባን” ነው፡፡ ምሥጢራት ሁሉ የሚደመደሙት በሥጋ ወደሙ ነው፡፡ መሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ንስሓ፣ ምሥጢረ ተክሊል የሚፈጸሙት በቁርባን ነው፡፡ ይህንን የሚያውቅ የውሸት አባት ዲያብሎስ የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር ከሥጋ ወደሙ ያርቅሃል፡፡ አንተ ግን “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ከቶ አይጠማም” ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን አምናለሁና ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የነሳውን ሥጋና ደም እመገባለሁ በለው፡፡ /ዮሐ6፥35/ የዘላለም ሕይወትን መውረስ እንደምትፈልግም አሳወቀው፡፡ “ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል” /ዮሐ6፥41/ ስለዚህ ለዘላለም በመንግሥተ ሰማያት ለመኖር ከሰማይ የወረደውን እንጀራ እበላለሁ ብለህ ጠላትህን አሳፍረው፡፡ ጠላት ግን በድፍረት እንድትቀርብ ሊፈትንህ ይችላል፡፡ የምትቀበለውን ሥጋና ደም የዕሩቅ ብእሲ ሥጋና ደም ነው ብሎ ሊያታልልህም ይሞክራል፡፡ አንተ ግን አትስማው የምቀበለው ሥጋና ደም በዕለተ አርብ የተቆረሰውና የፈሰሰውን ሥጋና ደም ነው በለው፡፡ ሥጋና ደሙም መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው እንጅ ጠላት እንደሚለው መለኮት የተለየው አይደለም፡፡ ጠላት ውጊያውን አሁንም አያቆምም “ንስሓ ሳትገባ ሳትዘጋጅ ተቀበል” ይልሃል፡፡ እርሱን ከሰማኸው የይሁዳ እጣ ፈንታ አንተ ላይም ይደርሳል፡፡ ሳይዘጋጁ ከኃጢአት ሳይነጹ ቢቀበሉት ግሩም ፍዳን የሚያመጣ የሚባላ እሳት ነው፡፡ ይሁዳ በጸሎተ ሐሙስ ከሌሎች ሐዋርያት ጋር ከቁርባኑ ሥርዓት ተካፋይ ነበረ፡፡ ነገር ግን በልቡ የነበረው ጌታን በ30 ብር የመሸጥ ኃጢአት እንደወጣ እንዲቀር አድርጎታል፡፡ /ማቴ26፥14-29/፣ /ማቴ27÷3-9/ ሥጋና ደሙ ግሩም ፍዳ የሚያመጣ ነው የሚባለው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ በንጽሕና በትሕትና ንስሓ ገብቶ ሊቀበሉት ይገባል፡፡ በዚህ መልኩ ለሚቀበለው የዘላለም ሕይወትን የሚያወርስ ጥበብን የሚገልጽ ምሥጢርን ሁሉ የሚያድል ነው፡፡ ለዚህም ነው ካህኑ በቅዳሴ ሰዓት “ንጹሕ የሆነ ከቁርባኑ ይቀበል ንጹሕ ያልሆነ ግን አይቀበል ለሰይጣንና ለመልእክተኞቹ በተዘጋጀው በመለኮት እሳት እንዳይቃጠል በልቡናው ቂምን የያዘ ልዩ አሳብም ያለበት ቢኖር አይቅረብ እጄን ከአፍአዊ ደም ንጹሕ እንዳደረግሁ እንዲሁም ከሁላችሁ ደም ንጹሕ ነኝ፡፡ ደፍራችሁ ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም ብትቀርቡ ከእርሱ ለመቀበላችሁ መተላለፍ የለብኝም በደላችሁ በራሳችሁ ይመለሳል እንጅ፡፡ በንጽሕና ሆናችሁ ባትቀርቡ እኔ ከበደላችሁ ንጹሕ ነኝ” ብሎ እጁን የሚታጠበው፡፡ ዲያቆኑም ተቀብሎ “ይህን የቄሱን ቃል ያቃለለ ወይም የሳቀና የተነጋገረ ወይም በቤተክርስቲያን በክፋት የቆመ ቢኖር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዳሳዘነው በእርሱም እንደተነሣሣ ይወቅ ይረዳ ስለበረከት ፈንታ መርገምን ስለኃጢአት ሥርየት ፈንታ ገሃነመ እሳትን ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል” ይላል፡፡ ይህ አዋጅ የሚታወጀው ከክርስቶስ ሥጋና ደም ርቀን እንድንቆም ወይም የበይ ተመልካቾች እንድንሆን ተፈልጎ ወይም ለማስፈራራት ተብሎ አይደለም ንስሓ ገብተን፣ የበደልነውን ይቅር ብለን፣ የቀማነውን መልሰን፣ ተዘጋጅተን በንጽህና ሆነን እንድንቀበል ነው እንጅ፡፡ በድፍረት በኃጢአት እንደተጨማለቁ ተዘሎ የሚበላና የሚጠጣ አይደለም ፍዳ መቅሰፍት ያመጣልና፡፡ ጠላት ግን ይህንን አዋጅ እያሳሰበና እንደተመቸው እየተረጎመ “ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የበቃህ አይደለህም” ብሎ ከሥጋ ወደሙ ያርቅሃል፡፡ የአዋጁ ዋና መልእክት ንስሓ ገብታችሁ፣ ከንስሓ አባታችሁ ጋር ጨርሳችሁ ቅረቡ የሚል ነው፡፡ በዚህ ድል ስትነሳው ደግሞ “አንተ ገና ወጣት ነህ ሽማግሌዎች እንኳን ሳይቆርቡ ያንተ ቁርባን ምንድን ነው” ይልሃል፡፡ አንተ ምክሩን አትቀበል “ሽማግሌዎች የራሳቸው ነፍስ ነው ያላችው እኔም እንደዚሁ የራሴ ነፍስ ነው ያለኝ ስለዚህ እነርሱ ስላልቆረቡ እኔ መቁረብ የለብኝም? በወጣትነት ዘመንህ ፈጣሪህን አስብ ተባልኩ እንጅ ሽማግሌዎች የሚሠሩትን እያየህ እንደእነርሱ ሁን አልተባልኩም፡፡ በእርግጥ በጎ ሥራ ሲሠሩ ልመስላቸው ግድ ነው መጥፎ ሲሠሩ ግን ልመስላቸው አልሻም፡፡ እነርሱ የሚቆርቡበት የራሳቸው ጊዜ ሊኖራቸው ይችላል የእኔ ጊዜ ግን ዛሬ ብቻ ነው” ብለህ አሳፍረው፡፡ ይህን ሁሉ ብለህ ስታሸንፈው ደግሞ እንደለመደው ከንቱ ውዳሴን ይጨምርብሃል፡፡ ቆራቢ እንድትባል ብቻ መቁረብን ያለማምድሃል፡፡ ከዚያ በኋላ ልምድ ያደርግብህና ሳትዘጋጅ ንስሓ ሳትገባ በድፍረት መቅረብን ያለማምድሃል፡፡ ስለዚህ በጣም ጥንቃቄ ልታደርግ ያስፈልጋል፡፡ ሥጋና ደሙን ለመቀበል የግድ ንስሓ መግባት ከንስሓ አባት ጋር መወያየትን ይጠይቃል፡፡ የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ስትሻ የዘላለም ቅጣት እንዳይመጣብህ ተጠንቀቅ፡፡
ዲያብሎስ እጅግ በጣም አብዝቶ ማራቅ የሚፈልገው ከምሥጢራት ሁሉ የበላይ ከሆነው “ከምሥጢረ ቁርባን” ነው፡፡ ምሥጢራት ሁሉ የሚደመደሙት በሥጋ ወደሙ ነው፡፡ መሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ንስሓ፣ ምሥጢረ ተክሊል የሚፈጸሙት በቁርባን ነው፡፡ ይህንን የሚያውቅ የውሸት አባት ዲያብሎስ የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር ከሥጋ ወደሙ ያርቅሃል፡፡ አንተ ግን “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ከቶ አይጠማም” ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን አምናለሁና ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የነሳውን ሥጋና ደም እመገባለሁ በለው፡፡ /ዮሐ6፥35/ የዘላለም ሕይወትን መውረስ እንደምትፈልግም አሳወቀው፡፡ “ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል” /ዮሐ6፥41/ ስለዚህ ለዘላለም በመንግሥተ ሰማያት ለመኖር ከሰማይ የወረደውን እንጀራ እበላለሁ ብለህ ጠላትህን አሳፍረው፡፡ ጠላት ግን በድፍረት እንድትቀርብ ሊፈትንህ ይችላል፡፡ የምትቀበለውን ሥጋና ደም የዕሩቅ ብእሲ ሥጋና ደም ነው ብሎ ሊያታልልህም ይሞክራል፡፡ አንተ ግን አትስማው የምቀበለው ሥጋና ደም በዕለተ አርብ የተቆረሰውና የፈሰሰውን ሥጋና ደም ነው በለው፡፡ ሥጋና ደሙም መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው እንጅ ጠላት እንደሚለው መለኮት የተለየው አይደለም፡፡ ጠላት ውጊያውን አሁንም አያቆምም “ንስሓ ሳትገባ ሳትዘጋጅ ተቀበል” ይልሃል፡፡ እርሱን ከሰማኸው የይሁዳ እጣ ፈንታ አንተ ላይም ይደርሳል፡፡ ሳይዘጋጁ ከኃጢአት ሳይነጹ ቢቀበሉት ግሩም ፍዳን የሚያመጣ የሚባላ እሳት ነው፡፡ ይሁዳ በጸሎተ ሐሙስ ከሌሎች ሐዋርያት ጋር ከቁርባኑ ሥርዓት ተካፋይ ነበረ፡፡ ነገር ግን በልቡ የነበረው ጌታን በ30 ብር የመሸጥ ኃጢአት እንደወጣ እንዲቀር አድርጎታል፡፡ /ማቴ26፥14-29/፣ /ማቴ27÷3-9/ ሥጋና ደሙ ግሩም ፍዳ የሚያመጣ ነው የሚባለው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ በንጽሕና በትሕትና ንስሓ ገብቶ ሊቀበሉት ይገባል፡፡ በዚህ መልኩ ለሚቀበለው የዘላለም ሕይወትን የሚያወርስ ጥበብን የሚገልጽ ምሥጢርን ሁሉ የሚያድል ነው፡፡ ለዚህም ነው ካህኑ በቅዳሴ ሰዓት “ንጹሕ የሆነ ከቁርባኑ ይቀበል ንጹሕ ያልሆነ ግን አይቀበል ለሰይጣንና ለመልእክተኞቹ በተዘጋጀው በመለኮት እሳት እንዳይቃጠል በልቡናው ቂምን የያዘ ልዩ አሳብም ያለበት ቢኖር አይቅረብ እጄን ከአፍአዊ ደም ንጹሕ እንዳደረግሁ እንዲሁም ከሁላችሁ ደም ንጹሕ ነኝ፡፡ ደፍራችሁ ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም ብትቀርቡ ከእርሱ ለመቀበላችሁ መተላለፍ የለብኝም በደላችሁ በራሳችሁ ይመለሳል እንጅ፡፡ በንጽሕና ሆናችሁ ባትቀርቡ እኔ ከበደላችሁ ንጹሕ ነኝ” ብሎ እጁን የሚታጠበው፡፡ ዲያቆኑም ተቀብሎ “ይህን የቄሱን ቃል ያቃለለ ወይም የሳቀና የተነጋገረ ወይም በቤተክርስቲያን በክፋት የቆመ ቢኖር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዳሳዘነው በእርሱም እንደተነሣሣ ይወቅ ይረዳ ስለበረከት ፈንታ መርገምን ስለኃጢአት ሥርየት ፈንታ ገሃነመ እሳትን ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል” ይላል፡፡ ይህ አዋጅ የሚታወጀው ከክርስቶስ ሥጋና ደም ርቀን እንድንቆም ወይም የበይ ተመልካቾች እንድንሆን ተፈልጎ ወይም ለማስፈራራት ተብሎ አይደለም ንስሓ ገብተን፣ የበደልነውን ይቅር ብለን፣ የቀማነውን መልሰን፣ ተዘጋጅተን በንጽህና ሆነን እንድንቀበል ነው እንጅ፡፡ በድፍረት በኃጢአት እንደተጨማለቁ ተዘሎ የሚበላና የሚጠጣ አይደለም ፍዳ መቅሰፍት ያመጣልና፡፡ ጠላት ግን ይህንን አዋጅ እያሳሰበና እንደተመቸው እየተረጎመ “ሥጋ ወደሙን ለመቀበል የበቃህ አይደለህም” ብሎ ከሥጋ ወደሙ ያርቅሃል፡፡ የአዋጁ ዋና መልእክት ንስሓ ገብታችሁ፣ ከንስሓ አባታችሁ ጋር ጨርሳችሁ ቅረቡ የሚል ነው፡፡ በዚህ ድል ስትነሳው ደግሞ “አንተ ገና ወጣት ነህ ሽማግሌዎች እንኳን ሳይቆርቡ ያንተ ቁርባን ምንድን ነው” ይልሃል፡፡ አንተ ምክሩን አትቀበል “ሽማግሌዎች የራሳቸው ነፍስ ነው ያላችው እኔም እንደዚሁ የራሴ ነፍስ ነው ያለኝ ስለዚህ እነርሱ ስላልቆረቡ እኔ መቁረብ የለብኝም? በወጣትነት ዘመንህ ፈጣሪህን አስብ ተባልኩ እንጅ ሽማግሌዎች የሚሠሩትን እያየህ እንደእነርሱ ሁን አልተባልኩም፡፡ በእርግጥ በጎ ሥራ ሲሠሩ ልመስላቸው ግድ ነው መጥፎ ሲሠሩ ግን ልመስላቸው አልሻም፡፡ እነርሱ የሚቆርቡበት የራሳቸው ጊዜ ሊኖራቸው ይችላል የእኔ ጊዜ ግን ዛሬ ብቻ ነው” ብለህ አሳፍረው፡፡ ይህን ሁሉ ብለህ ስታሸንፈው ደግሞ እንደለመደው ከንቱ ውዳሴን ይጨምርብሃል፡፡ ቆራቢ እንድትባል ብቻ መቁረብን ያለማምድሃል፡፡ ከዚያ በኋላ ልምድ ያደርግብህና ሳትዘጋጅ ንስሓ ሳትገባ በድፍረት መቅረብን ያለማምድሃል፡፡ ስለዚህ በጣም ጥንቃቄ ልታደርግ ያስፈልጋል፡፡ ሥጋና ደሙን ለመቀበል የግድ ንስሓ መግባት ከንስሓ አባት ጋር መወያየትን ይጠይቃል፡፡ የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ስትሻ የዘላለም ቅጣት እንዳይመጣብህ ተጠንቀቅ፡፡
+ ጥቃቅኑን ቀበሮዎች አጥምዳችኹ ያዙልን+ (መኃ.፪ ፥ ፲፭)
ከጥቃቅኑ ኃጣውእ እንጠበቅ ዘንድ ከማር ይስሐቅ የተገኘ ድርሳን ይኽ ነው፦
"በዐቢያት ኃጣውእ እንዳትሰነካከል ከንዑሳት ኃጣውእ ተከልከል። ንዑሳት የሚላቸውም ማየት መስማት ያለመጠን መብላት መጠጣት ናቸው። . . . መብል መጠጥን ከመውደድኽ የተነሳ ንዑሳት ኃጣውእን ትሰበስባለኽ። ንዑሳት ኃጣውእን ከመውደድኽ የተነሳ ዐበይት ኃጣውእን ሰብስበኽ ትሠራለኽ። ኃጣውእንም ከመውደደኽ የተነሳ ፍዳን ትቀበላለኽ ትሰበስባለኽ። መብል መጠጥ ብናገኝ አፋችንን ከፍተን እግራችንን ዘርግተን ብንበላ ብንጠጣ ሰውነታችንን ወስኖ ገትቶ ማኖር አይቻለንምና" ይላል (፩) ። የሰው ልጅ ካየ ከሰማ ዘንድ ያለ ልክ ከበላ ከጠጣ ዘንድ የክፉ ኅሊናት የፍትወታት እኩያት መናኽሪያ ይኾናልና!
ዳግመኛም ይኼው አባት እንዲኽ ይለናል ፦ "ራሱን ከምክንያተ ኃጢአት ወድዶ ካላራቀ ፣ በግድ ወደ ኃጢአት ይሳባል። . . . ንዑሳት ኃጣውእ ይጎዱኛል የሚል ዐበይት ኃጣውእን ድል ይነሣል። ሳያስቸግረው በመከራ ጊዜ ብርሃን ጸጋን ያገኛል። 'ንዑሳት ኃጣውእ' ይጎዱኛል የሚል ሰውን ፣ ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር ሰኰና ኅሊናውን ይጠብቀዋል።" አለ። በመከራ ጊዜ ኹሉ ረድኤተ - እግዚአብሔር ትመጣለታለች። 'ንዑሳት ኃጣውእ ይጎዱኛል' የማይል ግን በዐበይት ኃጣውእ ድል ይ 'ነሣል። ፍጹም መከራ ይቀበላል" (፪) ይላል።
ዳግመኛም ይኼው አባት እንዲኽ ሲል ያክላል ፦ "ጎበኞችን ንዑሳት ኃጣውእን ተቀብለኽ ታጠፋቸው ዘንድ ፃር ትጋ። ሳያድጉ ሳያብቡ ሳያፈሩ ፈጽመው ሳይሰፉ። ንዑሳት ኃጣውእ ቢታሰቡኽ ኃጣውእን መቃወም ቸል አትበል። እንዲኽ ያልኾነ እንደኾነ ግን የተገዛ ባሯ ገል ደንጊያ አሸክመው እንዲያስኰበዅቡት በፊት በፊታቸው የሚያስኰበዅቡኽ ዐበይት ኃጣውእን ታገኛለኽ። አስቀድሞ ንዑሳት ኃጣውእን የተዋጋ ዐበይት ኃጣውእን ድል ይነሣል።" ይለናል። (፫)
ዲ/ን ዳዊት ሰሎሞን
-------------------
(፩) መጽሐፍተ መነኮሳት (ማር ይስሐቅ ፣ አንቀጽ ፩ (ምዕራፍ. ፬ (ገጽ ፲ ፣ ገጽ ፲፪ ፣ ምዕራፍ ፲፫ (ገጽ ፳፫)
(፪) ዝኒ ከማሁ ፣ አንቀጽ ፪ ፣ ምዕ. ፩ ፣ ገጽ ፳፰ ፣ ገጽ ፴፩
(፫) ዝኒ ከማሁ. አንቀጽ ፪ ፣ ምዕ.፪. ገጽ ፴፪
🔸
ከጥቃቅኑ ኃጣውእ እንጠበቅ ዘንድ ከማር ይስሐቅ የተገኘ ድርሳን ይኽ ነው፦
"በዐቢያት ኃጣውእ እንዳትሰነካከል ከንዑሳት ኃጣውእ ተከልከል። ንዑሳት የሚላቸውም ማየት መስማት ያለመጠን መብላት መጠጣት ናቸው። . . . መብል መጠጥን ከመውደድኽ የተነሳ ንዑሳት ኃጣውእን ትሰበስባለኽ። ንዑሳት ኃጣውእን ከመውደድኽ የተነሳ ዐበይት ኃጣውእን ሰብስበኽ ትሠራለኽ። ኃጣውእንም ከመውደደኽ የተነሳ ፍዳን ትቀበላለኽ ትሰበስባለኽ። መብል መጠጥ ብናገኝ አፋችንን ከፍተን እግራችንን ዘርግተን ብንበላ ብንጠጣ ሰውነታችንን ወስኖ ገትቶ ማኖር አይቻለንምና" ይላል (፩) ። የሰው ልጅ ካየ ከሰማ ዘንድ ያለ ልክ ከበላ ከጠጣ ዘንድ የክፉ ኅሊናት የፍትወታት እኩያት መናኽሪያ ይኾናልና!
ዳግመኛም ይኼው አባት እንዲኽ ይለናል ፦ "ራሱን ከምክንያተ ኃጢአት ወድዶ ካላራቀ ፣ በግድ ወደ ኃጢአት ይሳባል። . . . ንዑሳት ኃጣውእ ይጎዱኛል የሚል ዐበይት ኃጣውእን ድል ይነሣል። ሳያስቸግረው በመከራ ጊዜ ብርሃን ጸጋን ያገኛል። 'ንዑሳት ኃጣውእ' ይጎዱኛል የሚል ሰውን ፣ ስሙ ይክበርና እግዚአብሔር ሰኰና ኅሊናውን ይጠብቀዋል።" አለ። በመከራ ጊዜ ኹሉ ረድኤተ - እግዚአብሔር ትመጣለታለች። 'ንዑሳት ኃጣውእ ይጎዱኛል' የማይል ግን በዐበይት ኃጣውእ ድል ይ 'ነሣል። ፍጹም መከራ ይቀበላል" (፪) ይላል።
ዳግመኛም ይኼው አባት እንዲኽ ሲል ያክላል ፦ "ጎበኞችን ንዑሳት ኃጣውእን ተቀብለኽ ታጠፋቸው ዘንድ ፃር ትጋ። ሳያድጉ ሳያብቡ ሳያፈሩ ፈጽመው ሳይሰፉ። ንዑሳት ኃጣውእ ቢታሰቡኽ ኃጣውእን መቃወም ቸል አትበል። እንዲኽ ያልኾነ እንደኾነ ግን የተገዛ ባሯ ገል ደንጊያ አሸክመው እንዲያስኰበዅቡት በፊት በፊታቸው የሚያስኰበዅቡኽ ዐበይት ኃጣውእን ታገኛለኽ። አስቀድሞ ንዑሳት ኃጣውእን የተዋጋ ዐበይት ኃጣውእን ድል ይነሣል።" ይለናል። (፫)
ዲ/ን ዳዊት ሰሎሞን
-------------------
(፩) መጽሐፍተ መነኮሳት (ማር ይስሐቅ ፣ አንቀጽ ፩ (ምዕራፍ. ፬ (ገጽ ፲ ፣ ገጽ ፲፪ ፣ ምዕራፍ ፲፫ (ገጽ ፳፫)
(፪) ዝኒ ከማሁ ፣ አንቀጽ ፪ ፣ ምዕ. ፩ ፣ ገጽ ፳፰ ፣ ገጽ ፴፩
(፫) ዝኒ ከማሁ. አንቀጽ ፪ ፣ ምዕ.፪. ገጽ ፴፪
🔸
(#ኀጢአቷን_የምትጽፈው1ሴት )
አንዲት ሴት ነበረች ኀጢአቷን የምትጽፍ
ልቧ በኀጢአት የሰከረ ለኀጢአትም ተገዚ የሆነች
ይቸ ሴት የተለያየ ኀጢአት የምሰራ ነት
ትዘሙታለች፣ ትዋሻለች፣ ታማለች፣ ትሰርቃለች፣ ትገድላለች
በአል ትሽራለች፣ ትሰክራለች፣ በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ለብሷ ኀጢአት ነበር። ነገር ግን የምሰረውን ኀጢአቷን ሁሉ አየጻፈች ታስቀምጥ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን የጻፈችው ኀጢአትቷን ብታየው ስንክሳር አክሎ ተመለከተችው
ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚውሉ የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነው።
የዚች ሴትም ኀጢአትም ይህን አክሎ ነበር እንዳየችው ደነገጠችና ኀጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ ለበት ወደ አንጾኪያ ሄደች አባ ባስልዮስን አገኘችው አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው
አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታየው ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኀጢአቷ ብቻ ቀርታ አየቻት። በጣም ከባድ ኀጢአት ነበረች ሊሰሩአት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች
አባቴ ይችሳ አለችው አባ ባስልዮስም ይችን ኀጢአትሽንስ ማስተስረይ የሚችል ልጄ ቅዱስ ኤፍሬም ነው ሂደሽ ለእርሱ ንገሪው አላት።አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኀጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገለጥ የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነው።ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ጭምር ነው። እሷም አባ ባሰስልዮስ እንዳላት ቅዱስ ኤፍሬም ወዳለበት ወደ ሶርያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋቱ እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ ከቅዱ ኤፍሬም ደረሰች።
አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም
ለአባቴ ለአባ ባስለዮስ እንጂ አላት ቅዱስ ኤፍሬም ኀጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት እንጅ ስትመላለስ ኀጢአቷ እንዲቀልላትም ነው። ሂደሽ ለአባ ባስለዮስ ንገሪው እሱ ይደመስስልሻል አላት እሷም አግኝቸው እኮ አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞው በህይወት አታገኝውም ሙቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይዘውት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራሪ የተጻፈው ኀጢአትሽን ከአስከሬኑ ላይ ጣይው አላት እርሷም እሽ ብላ ሄደች የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቀያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሀት እየፈቱት አየች።
የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኀጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስከሬኑ ላይ ጣለችው አስከሬኑም ድምጽ ወጥቶ ኀጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገልጣ ብታይ ተደምስሶላታል። አምላኳን አመሰገነች በደስታ ዘመረች
ከዚህ በኋላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ መኖር ጀመረች።
እንደ ዚች ሴት ኀጢአቱን የሚያስታውስ ማን ነው?
ወደ ካህን ሂዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነው?
ስለኀጢአቱ በረሃ የተንከራተተ ማን ይሆን?
የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም ጨረሻ ያሳምርልን
ኀጢአቷን የደመሰሰ የሁላችንም ኀጢአት ይደምስስልን
አምላኬ ሆይ ያለ ንስሐ አትጥራኝ!
#ለንሰሐ_የሚሆን_ፍሬ_አድርጉ!
የውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ
አንዲት ሴት ነበረች ኀጢአቷን የምትጽፍ
ልቧ በኀጢአት የሰከረ ለኀጢአትም ተገዚ የሆነች
ይቸ ሴት የተለያየ ኀጢአት የምሰራ ነት
ትዘሙታለች፣ ትዋሻለች፣ ታማለች፣ ትሰርቃለች፣ ትገድላለች
በአል ትሽራለች፣ ትሰክራለች፣ በትእቢት የተሞላች ሴት ናት ለብሷ ኀጢአት ነበር። ነገር ግን የምሰረውን ኀጢአቷን ሁሉ አየጻፈች ታስቀምጥ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን የጻፈችው ኀጢአትቷን ብታየው ስንክሳር አክሎ ተመለከተችው
ስንክሳር ማለት በ365 ቀኖች የሚውሉ የቅዱሳን ታሪክ ሰብስቦ የያዘ ትልቅ መጽሐፍ ነው።
የዚች ሴትም ኀጢአትም ይህን አክሎ ነበር እንዳየችው ደነገጠችና ኀጢአቷን ተሸክማ አባት ወደ ለበት ወደ አንጾኪያ ሄደች አባ ባስልዮስን አገኘችው አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው
አባ ባስልዮስም ይፋቅልሽ አላት ገልጣ ብታየው ሁሉ ተፍቆ አንዲት ኀጢአቷ ብቻ ቀርታ አየቻት። በጣም ከባድ ኀጢአት ነበረች ሊሰሩአት የምትከብድ ሊነግሯት የምታሳፍር ነበረች
አባቴ ይችሳ አለችው አባ ባስልዮስም ይችን ኀጢአትሽንስ ማስተስረይ የሚችል ልጄ ቅዱስ ኤፍሬም ነው ሂደሽ ለእርሱ ንገሪው አላት።አባ ባስልዮስ ይሄን ያላት ኀጢአቷን መፋቅ አቅቶት አይደለም የራሱ ክብር ከሚገለጥ የቅዱስ ኤፍሬም ክብር እንዲገለጥ ፈልጎ ነው።ደግሞም ስትመላለስ ንስሐ እንዲሆናት ጭምር ነው። እሷም አባ ባሰስልዮስ እንዳላት ቅዱስ ኤፍሬም ወዳለበት ወደ ሶርያ ሄደች በባዶ እግሯ እንቅፋቱ እየመታት እሾሁ እየወጋት እግሯ ሲደማ ልብሷን ቀዳ እየጠመጠመች ተጉዛ ከቅዱ ኤፍሬም ደረሰች።
አባቴ በዚህ ያለው ኀጢአትሽ ይፋቅልሽ በለኝ አለችው ቅዱስ ኤፍሬም ግን ይሄ ለኔ አይቻለኝም
ለአባቴ ለአባ ባስለዮስ እንጂ አላት ቅዱስ ኤፍሬም ኀጢአቷን መደምሰስ አቅቶት አይደለም በፈሊጥ ቀኖና ሲሰጣት እንጅ ስትመላለስ ኀጢአቷ እንዲቀልላትም ነው። ሂደሽ ለአባ ባስለዮስ ንገሪው እሱ ይደመስስልሻል አላት እሷም አግኝቸው እኮ አይሆንልኝም ብሎ ወደ አንተ ልኮኛል ሳትል እሽ ብላ መንገድ ስትጀምር እንደ ቀድሞው በህይወት አታገኝውም ሙቶ ካህናት ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይዘውት ሲሄዱ ታገኝዋለሽ ሳትጠራሪ የተጻፈው ኀጢአትሽን ከአስከሬኑ ላይ ጣይው አላት እርሷም እሽ ብላ ሄደች የቀኑ ሙቀት የሌሊቱ ብርድ እያሰቀያት ደረሰች ሙቶ ካህናት ፍትሀት እየፈቱት አየች።
የእግዚአብሔር አገልጋይ ባስልዮስ ሆይ የባሪያህን ኀጢአት ደምስስልኝ ብላ ከአስከሬኑ ላይ ጣለችው አስከሬኑም ድምጽ ወጥቶ ኀጢአትሽ ተደምስሶልሻል አላት ገልጣ ብታይ ተደምስሶላታል። አምላኳን አመሰገነች በደስታ ዘመረች
ከዚህ በኋላ ዓለምን ንቃ ገዳም ገብታ መኖር ጀመረች።
እንደ ዚች ሴት ኀጢአቱን የሚያስታውስ ማን ነው?
ወደ ካህን ሂዶ ንስሐ የገባስ ስንቱ ነው?
ስለኀጢአቱ በረሃ የተንከራተተ ማን ይሆን?
የዚችን ሴት መጨረሻ ያሳመረ የሁላችንም ጨረሻ ያሳምርልን
ኀጢአቷን የደመሰሰ የሁላችንም ኀጢአት ይደምስስልን
አምላኬ ሆይ ያለ ንስሐ አትጥራኝ!
#ለንሰሐ_የሚሆን_ፍሬ_አድርጉ!
የውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ
++ሰው እንጂ እግዚአብሔር አልረሳኝም+++
በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ፅኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደኃ ፣የሚበላውን የሚቸገር ረሃብተኛ ፣ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርብ ሆኖ ይታዘብ የነበረው ወዳጁ እንዲህ አለው ‹ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማስገኘት ካልቻለ የመጸለይህ ትርጉም ምንድር ነው? በቃ ፈጣሪህ አልሰማህም ማለት ነው!› ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያሃ ምስኪን ክርስቲያን ግን እንዲህ ሲል መለሰለት ‹እግዚአብሔርማ አልረሳኝም! ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ ነግሮት ነበር፡፡ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን ይህ ሰው ረስቶኛል!!!›
ክርስቲያኖች ለምን አንዳንዶች ከዕለት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፤ አንዳንዶች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ እንጀራ ያጣሉ ? መቼም ‹ለሰው ፊት የማያዳላ› እግዚአብሔር አድልዎ ኖሮበት ነው አትሉም?! (ሐዋ 10፡34)፡፡ይህስ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙት ምንም የሌላቸውን በመርዳት እና በመመገብ በባሕርይው መግቦትን ገንዘብ ያደረገውን አምላክ በጸጋ እንዲመስሉትና በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡
ስለዚህ ‹የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ› ብለን የለመንነው አምላክ ከዕለት እንጀራችን አትርፎ የሚሰጠን ይህን አምላካዊ አደራ እንድንወጣም ስለሚፈልግ እንደሆነ ብንረዳው እንዴት መታደል ነበር!!!
በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ፅኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደኃ ፣የሚበላውን የሚቸገር ረሃብተኛ ፣ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርብ ሆኖ ይታዘብ የነበረው ወዳጁ እንዲህ አለው ‹ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማስገኘት ካልቻለ የመጸለይህ ትርጉም ምንድር ነው? በቃ ፈጣሪህ አልሰማህም ማለት ነው!› ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያሃ ምስኪን ክርስቲያን ግን እንዲህ ሲል መለሰለት ‹እግዚአብሔርማ አልረሳኝም! ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ ነግሮት ነበር፡፡ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን ይህ ሰው ረስቶኛል!!!›
ክርስቲያኖች ለምን አንዳንዶች ከዕለት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፤ አንዳንዶች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ እንጀራ ያጣሉ ? መቼም ‹ለሰው ፊት የማያዳላ› እግዚአብሔር አድልዎ ኖሮበት ነው አትሉም?! (ሐዋ 10፡34)፡፡ይህስ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙት ምንም የሌላቸውን በመርዳት እና በመመገብ በባሕርይው መግቦትን ገንዘብ ያደረገውን አምላክ በጸጋ እንዲመስሉትና በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡
ስለዚህ ‹የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ› ብለን የለመንነው አምላክ ከዕለት እንጀራችን አትርፎ የሚሰጠን ይህን አምላካዊ አደራ እንድንወጣም ስለሚፈልግ እንደሆነ ብንረዳው እንዴት መታደል ነበር!!!
ትህትናን ገንዘብ እናድርግ (አባ ህርያቆስ)
=====================
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ ወራት ( በሥጋ በተገለጠለት ዘመን) ስለ ትህትና ሲያስተምር እንዲህ ብሎዋል። " እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።" (ሉቃ 18፥14)
ይህንን አምላካዊ ቃል ዋቢ በማድረግ ነው ታላቁ አባት አባ ህርያቆስ በቅዳሴ ማርያም መጽሐፉ ላይ '' ትዕቢትና መታጀርን ጌጥ አናድርግ ትዕግሥትን ገንዘብ እናድርግ
'' ሲል የተናገረው።
አባ ዮሐንስ ሐጺርም ስለ ትህትና ሲናገር እንዲህ አለ “ዮሴፍን ማን ሸጠው?” ብሎ ጠየቀ፡፡ ከወንድሞች አንዱም “ወንድሞቹ ሸጡት” ብሎ መለሠለት፡፡
አረጋዊውም (አባ ዮሐንስም) “አይደለም፤ ትሕትናው ነው የሸጠው፡፡ ‘ወንድማቸው ነኝ’ ብሎ በመናገር እንዳይሸጥ ማድረግ ይችል ነበርና፡፡ ነገር ግን ዝምታን ስለመረጠ፤ ራሱን በትሕትናው ሸጠ፡፡ ይኸው የእርሱ ትሕትና ግን በግብጽ አለቃ አደረገው፡፡” በማለት ተናግሯል ።
" እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ፤ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ፤" (ቆላ 3: 13)
ስለዚህ ወድ አንባቢያን ትዕቢት የዲያቢሎስ ስራ ነው! እኛ ደግሞ በጥምቀት ልጅነትን ያገኘን የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ተገንዝበን ራሳችሁን የትህትና ሰው በማድረግ ትዕግስትን ገንዘብ እናድርግ።
" ትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ።"
(መክ 10፥4)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን።
[ ትምህርቱን ለሌሎች ያጋሩ]
=====================
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ ወራት ( በሥጋ በተገለጠለት ዘመን) ስለ ትህትና ሲያስተምር እንዲህ ብሎዋል። " እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።" (ሉቃ 18፥14)
ይህንን አምላካዊ ቃል ዋቢ በማድረግ ነው ታላቁ አባት አባ ህርያቆስ በቅዳሴ ማርያም መጽሐፉ ላይ '' ትዕቢትና መታጀርን ጌጥ አናድርግ ትዕግሥትን ገንዘብ እናድርግ
'' ሲል የተናገረው።
አባ ዮሐንስ ሐጺርም ስለ ትህትና ሲናገር እንዲህ አለ “ዮሴፍን ማን ሸጠው?” ብሎ ጠየቀ፡፡ ከወንድሞች አንዱም “ወንድሞቹ ሸጡት” ብሎ መለሠለት፡፡
አረጋዊውም (አባ ዮሐንስም) “አይደለም፤ ትሕትናው ነው የሸጠው፡፡ ‘ወንድማቸው ነኝ’ ብሎ በመናገር እንዳይሸጥ ማድረግ ይችል ነበርና፡፡ ነገር ግን ዝምታን ስለመረጠ፤ ራሱን በትሕትናው ሸጠ፡፡ ይኸው የእርሱ ትሕትና ግን በግብጽ አለቃ አደረገው፡፡” በማለት ተናግሯል ።
" እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ፤ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ፤" (ቆላ 3: 13)
ስለዚህ ወድ አንባቢያን ትዕቢት የዲያቢሎስ ስራ ነው! እኛ ደግሞ በጥምቀት ልጅነትን ያገኘን የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ተገንዝበን ራሳችሁን የትህትና ሰው በማድረግ ትዕግስትን ገንዘብ እናድርግ።
" ትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና የገዢ ቍጣ የተነሣብህ እንደ ሆነ ስፍራህን አትልቀቅ።"
(መክ 10፥4)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን።
[ ትምህርቱን ለሌሎች ያጋሩ]
ማር ይስሐቅ የተናገረው ሰውነትን የመዝለፍ ሥርዓት
✝ወንድሜ ሰውነትህን ዘወትር ዝለፋት ከሥጋ የምትለዪበት የምታልፊበት ጊዜ ደርሷል በላት ባለሺበት በኋላ ጥለሺው በምትሄጂ ሥራ ዛሬ ለምን ደስ ይልሻል? እሱን በማየት ጥቂት ዘመን ተድላ ደስታ የምታደርጊበት ኋላ ብዙ ዘመን በምታጪው የቀደመ ሥራሽን እወቂ የሠራሺው ሥራ ምን እንደሆነ አስቢ ጽድቅም እንደሆነ ለኃጢአትም እንደሆነ ያለ ዘመንሽን ከማን ጋራ ፈጸምሺው ከጌታ ጋር ነው ወይስ ከሰይጣን ጋር ነው? በትሩፋትሽ ምንን ደስ አስኘሽ ጌታን ነው ወይስ ሰይጣን ነው? በጊዜ ምትሽ ሊዋሐድሽ የሚመጣው ማነው? በመንግሥተ ሰማይ ዐርፈሽ ትኖሪ ዘንድ በሥራሽ ደስ ያለው ማነው ለማን ብለሽ ደከምሽ ለማንስ ብለሽ መከራ ተቀበልሽ ለመንግስተ ሰማይ ብለሽ ነው? ደስ ብሎሽ ታገኚው ዘንድ አኳኋኑስ ምንድር ነው ነፍስሽ ከስጋሽ በተለየች ጊዜ በመንግሥተ ሰማይ ይዋሕድሽ ዘንድ ገንዘብ ያደረግሺው ምንድር ነው ምን ምግባር ነው በማናቸው እርሻ ሊያውሉሽ ተቃጠሩሽ በማመናችው መዓርግ ተቃጠሩሽ በባለ ሠላሳ ነው በባለ ስድሳ ነው ወይ በባለ መቶ ነው ነፍስሽ ከሥጋሽ የምትለይበት ፀሐይ እድሜሽ በገባ ጊዜ ዋጋሽን እሰጥሻለሁ ያለሽ ጌታ ነው ዲያብሎስ ነው?
ነፍሴ ሆይ ሰውነትሽን መርምሪ ዕዳሽ በማናቸው ቦታ እንደሆነ እወቂ መንግስተ ሰማይም እንደሆነ ገሃነምም እንደሆነ እወቂ ለሚያርሱ ሰዎች አሞጭ እሬት የሚያፈራ እርሻሽን ያረስሽ ትሆኚ ማለት በሚሰሩት ሰዎች ፍዳን ማለት የሚያመጣ የኃጢአትን ብትሰሪ እያዘንሽ እየተቆረቆርሽ አልቅሺ ለምኚ።✝
ምንጭ-:
"ዘዘወትር ውዳሴ አምላክ"
✝ወንድሜ ሰውነትህን ዘወትር ዝለፋት ከሥጋ የምትለዪበት የምታልፊበት ጊዜ ደርሷል በላት ባለሺበት በኋላ ጥለሺው በምትሄጂ ሥራ ዛሬ ለምን ደስ ይልሻል? እሱን በማየት ጥቂት ዘመን ተድላ ደስታ የምታደርጊበት ኋላ ብዙ ዘመን በምታጪው የቀደመ ሥራሽን እወቂ የሠራሺው ሥራ ምን እንደሆነ አስቢ ጽድቅም እንደሆነ ለኃጢአትም እንደሆነ ያለ ዘመንሽን ከማን ጋራ ፈጸምሺው ከጌታ ጋር ነው ወይስ ከሰይጣን ጋር ነው? በትሩፋትሽ ምንን ደስ አስኘሽ ጌታን ነው ወይስ ሰይጣን ነው? በጊዜ ምትሽ ሊዋሐድሽ የሚመጣው ማነው? በመንግሥተ ሰማይ ዐርፈሽ ትኖሪ ዘንድ በሥራሽ ደስ ያለው ማነው ለማን ብለሽ ደከምሽ ለማንስ ብለሽ መከራ ተቀበልሽ ለመንግስተ ሰማይ ብለሽ ነው? ደስ ብሎሽ ታገኚው ዘንድ አኳኋኑስ ምንድር ነው ነፍስሽ ከስጋሽ በተለየች ጊዜ በመንግሥተ ሰማይ ይዋሕድሽ ዘንድ ገንዘብ ያደረግሺው ምንድር ነው ምን ምግባር ነው በማናቸው እርሻ ሊያውሉሽ ተቃጠሩሽ በማመናችው መዓርግ ተቃጠሩሽ በባለ ሠላሳ ነው በባለ ስድሳ ነው ወይ በባለ መቶ ነው ነፍስሽ ከሥጋሽ የምትለይበት ፀሐይ እድሜሽ በገባ ጊዜ ዋጋሽን እሰጥሻለሁ ያለሽ ጌታ ነው ዲያብሎስ ነው?
ነፍሴ ሆይ ሰውነትሽን መርምሪ ዕዳሽ በማናቸው ቦታ እንደሆነ እወቂ መንግስተ ሰማይም እንደሆነ ገሃነምም እንደሆነ እወቂ ለሚያርሱ ሰዎች አሞጭ እሬት የሚያፈራ እርሻሽን ያረስሽ ትሆኚ ማለት በሚሰሩት ሰዎች ፍዳን ማለት የሚያመጣ የኃጢአትን ብትሰሪ እያዘንሽ እየተቆረቆርሽ አልቅሺ ለምኚ።✝
ምንጭ-:
"ዘዘወትር ውዳሴ አምላክ"
‹ # መዳንም_በሌላ_በማንም_የለም
‹ # የሉተራዉያን_ስህተት_በሊቃውንት_አስተምህሮ_ሲገለጥ ››
®ራኢይ ፍቅረ ስላሴ
>>> መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም
ከሰማይ በታች ሌላ የለምና›› (ሐዋ 4፡6-12)
ይህንን ኃይለ ቃል የተናገረው በዕድሜ በጸጋና በመንፈሳዊ አገልግሎት በእግዚአብሔር
ቤት ውስጥ የሸመገለው ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ሲሆን መጽንኢ (አጽናኝ)፣
መስተፈስሒ (አስደሳች)፣ መንጽሒ (የሚያነፃ)፣ መስተሰርይ (የሚያስተሰርይ)፣ እና ከሳቲ
(ገላጭ) የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበለ በኋላ በዕለቱ በዙሪያው ተሰብስበው
ለነበሩት ለቤተ አይሁድ በ72 ቋንቋ ወንጌልን በመስበክ 3000 ነፍሳትን አሳመነ፡፡ በዘጠኝ
ሰዓትም ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወደ ቤተመቅደስ ሲሄዱ በቤተመቅደስ በር ላይ
ተቀምጦ ሲለምን የነበረውን አንድ አንካሳ ሰው ወደ እኛ ትኩር ብለህ ተመልከት ብሎ
በናዝሬት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ በማለት ፈወሰው፡
ነገር ግን በነጋው ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን የካህናት አለቆች (ሐናና ቀያፋ) ና የመቅደስ
አዘዦች በምን ኃይል ወይም በማን ስም ይህን አደረጋችሁ? ባሉት ጊዜ ነበር ‹‹እናንተ
በሰቀላችሁት እግዚአብሔርም ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው
ግንበኞች የናቁት የማዕዘን ራስ የሆነው ይህ ድንጋይ ነው መዳንም በሌላ በማንም የለም
እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና›› (ሐዋ 4፡
6-12) በማለት የመለሰላቸው፡፡
በመሆኑም የዚህ ጽሁፍ መሠረታዊ ዓላማ ሉተራውያን ፕሮቴስታንትና ተረፈ አርዮሳውያን
‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› የሚለውን ጥቅስ እንደ መፈክር በመያዝ ዝም ብለን
‹‹ኢየሱስ›› በማለት ብቻ እንድናለን ፕሮሰስ አያስፈልግም በማለት የመዳንን ትርጉም
ባለመረዳት የቅዱሳንን፣ የመላዕክትን የመስቀልን፣ የዕምነትን፣ የፀበልንና ሌሎችን የመዳን
መንገዶችን በመቃወም የስህተት ትምህርት ሲያስተምሩ ይስተዋላሉና፣ ይህ የመናፍቃን
ስህተት በሊቃውንት አስተምህሮ ሲመረመር ምን እንደሚመስል ለተዋህዶ ክርስቲያኖች
ማስተማርና በቂ ግንዛቤ በማስጨበጥ ትውልዱን ከስህተት ትምህርት ከጥርጥር መታደግ
ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ቦታ መዳንን በተመለከተ ያስተምረናል ነገር ግን መዳንን
በተመለከተ የእኛ የአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ ለሁሉም አንድ ዓይነት ቃል ነው
የሚጠቀመው ከዚህም የተነሣ ምስጢርን የማያስተውሉ ሰዎች መጻሕፍትን በትርጉም
ሳይሆን በጥሬ ንባብ ለመረዳት የሚሞክሩ ወገኖች በሁለት መልኩ ሲስቱ እናስተውላለን፡፡
ሀ/ የመጀመሪያዎች መዳንን ጠቅልለው ቅዱሳንንም፣ መላዕክትንም ኢየሱስ ክርስቶስንም
በተመለከተ የተናገረው ቃል አንድ ዓይነት ትርጉም ያለው የሚመስላቸው ናቸው፡፡
ለ/ በሌላው መልኩ ደግሞ መላዕክት ቅዱሳን ያድናሉ ብለን ስንል ኢየሱስ ክርስቶስ
እንደሚያድነው ዓይነት ማዳን ያለ የሚመስላቸው ወገኖችም አሉ፡፡
መዳን የሚለው ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር በሦስት ዓይነት ፍቺ ወይም ትርጉም
አመስጥረን እናየዋለን:-
፩ኛ. የዓለም መድኃኒት የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ
የመጀመሪያውና ዋንኛው እግዚአብሔር አዳምንና ልጆቹን ከወደቁበት ውድቀት አንስቶ
ከጠፉበት ከባዘኑበት መልሶ ወደ ነበሩበት ክብር መመለስ ወይም ለመመለስ ያደረገው ጉዞ
ማዳን ይባላል፡፡ አዳም በዕለተ አርብ ወደ ተፈጠረበት ክብር መመለስ ከባርነት ታድጎ
ከሲኦል ነፃ አውጥቶ አዲስ አድርጎ መሥራቱ ማዳን ነው (2ቆሮ 5፡15)
ከዚህም የተነሣ ነው እግዚአብሔር አዳነን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳነን የባርነታችን ቀንበር
ሰበረ ከእስራታችን ፈታን የምንለው
‹‹ፊል 2፡8-11 በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን ይገልፅልናል
የዘመኑ ፍፃሜ በደረሰ ጊዜ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ
ከድንግል ማርያም ተወልዶ የውርደት ሞት (የመስቀል ሞት) ሞቶ እኛን አዳምና ልጆቹን
እንዴት እንደ አዳነን ነው የሚያስተምረው›› ‹‹በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ
ልክ ከፍ ከፍ አደረገው ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር
ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ
ለእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው›› (ፊልጵ
2፡8-11)
ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለው ስም ከስም ሁሉ የከበረ ስም መሆኑን ሐዋርያው ያስተምረናል
እንዲሁም ፍጥረት ሁሉ ይድንበት ዘንድ የተሰጠው ስም ይህ ስም እንደሆነም አስረግጦ
ይነግረናል፡፡
ሐዋርያው ይህን ያለበት ምክንያት እግዚአብሔር ኤልሻዳይ አዶናይ ኤል፣ አልፋና ኦሜጋ ፣
ፊተኛውና ኋለኛው ፣ ያህዌ የሚለው ስም አያድንም ማለቱ ነው? ይህ አይደለም የቅዱስ
ጳውሎስም ሆነ የሐዋርያት ሃሣብ::
እግዚአብሔር የሚለው ስም የእግዚአብሔርነቱ የአንድነቱ የሦስትነቱ ኅቡዕ ስም ነው
አዶናይ ፣ ኤል ፣ ያህዌ የሚሉት ስሞች ከሥጋዌ በፊት የተሰጡ ስሞች ናቸው ኤልሻዳይ፣
ፊተኛውና ኋለኛው፣ አልፋና ኦሜጋ የሚሉት ስሞች ከሀሊነቱን ሁሉንቻይነቱን ያለ የነበረ ወደ
ፊትም የሚኖር መሆኑን የሚገልጹ ከሥጋዌ በፊት የተሰጡ ስሞች ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ሰው ሆነ በተዋህዶ ከበረ ለማለት የተሰጠው ስም ኢየሱስ የሚለው ነው፣
ከስም ሁሉ በላይ የሆነ ስም ያስባለውም ይህ የተዋህዶ ምስጢር ነው፡፡ኢየሱስ ክርስቶስ
የሚለው ስም ከስም ሁሉ የተለየ ስም ነው፡፡
ሚካኤል ገብርኤል ዑራኤል ብንል የፍጡር ስም ነው ምንም እንኳን የቅዱሳን መልዕክት
ስም ቢሆንም ሌሎችም አበበ፣ ተስፋዬ፣ አልማዝ ….. የተጻውአ መጠሪያ ስም ነው
እግዚአብሔር ስንል የፈጣሪ ብቻ ስም ነው፡፡
ኢየሱስ ስንል ግን ፍጡርና ፈጣሪ በተዋህዶ ያገኙት ስም ነው
የፍጡር ስም ለብቻ ነበረ የፈጣሪም ስም ለብቻ ነበረ ፈጣሪ ከፍጡር ጋር በተዋህዶ
በመክበር ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሲወለድ ግን ኢየሱስ
ክርስቶስ የሚለው ስም ተሰጠው ይህም በመሆኑ ይህ ስም የማይደገም ልዩ ስም ነው
እንደፍጡራን ስም በተለያየ ጊዜ የሚደገም አይደለም፡፡
ኢየሱስ የሚለው ስም ግን ምስጢረ ሥጋዌ ስለማይደገም ሌላ ጊዜ የሚደገም ስም
አይደለም አንዱና ዋንኛውም ምክንያት ይህ ነው ኢየሱስ የሚለው ከስም ሁሉ በላይ የሆነ
ስም ያሰኘው፡፡
ሌላው ምክንያት ሌሎችን ስሞች ግብሩን ተመልክተው የእግዚአብሔርን ድንቅ ስራ
ተመልክተው ሰዎች በዚያ ስም ሲጠሩት በሌላ መልኩ ስምህ ማን ነው ብለው
እነአብርሃም እነሙሴ ‹‹ማን ብየ ልንገራቸው ቢለው ሙሴ›› ፊተኛውና መጨረሻው ሁሉን
ቻይ (ኤልሻዳይ) የሆነው ብለህ ንገራቸው ነው ያለው፡፡
ኢየሱስ የሚለው ስም ግን በመላዕክት ተነግሮ በእናቱ በኩል የወጣ ‹‹ትፀንሻለሽ ወንድ
ልጅ ትወልጃለሽ አሕዛብን በባርነት በትር ይገዛል ድንቅ መካር ኃያል አምላክ ይባላል
ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ›› (ሉቃ1 ፣ ኢሳ 9፡6)
እግዚአብሔር የተባለው በዚህ ዘመን ነው በዚህ ሰዓት ነው ልንለው አንችልም ኢየሱስ
ክርስቶስ የተባለበትን ዘመን የተባለበትን ሰዓትና ቦታ እናውቀዋለን በመሆኑም ኅቡዕ
የነበረው ዘመንና ጊዜያት ዕለትና ቀናት የማይቆጠሩለት ፣ በቦታና በጊዜ የማይወሰን ተወስኖ
ተወልዶ ኢየሱስ ስለተባለ ይህ ስም ልዩ ስም ነው እንድንበት ዘንድ የተሰጠ ስም ሲልም
ቃላቶቹን ኢየሱስ የሚለውን ብቻ ሳይሆን ይህንን የማዳንን ምስጢር የሚወክል ስም
የዳንበት ስም የተፈወስንበት ስም ስለሆነ ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ስም አንድን ግብር
ይወክላልና ኢየሱስ ክርስቶስ ተብሎ
‹ # የሉተራዉያን_ስህተት_በሊቃውንት_አስተምህሮ_ሲገለጥ ››
®ራኢይ ፍቅረ ስላሴ
>>> መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም
ከሰማይ በታች ሌላ የለምና›› (ሐዋ 4፡6-12)
ይህንን ኃይለ ቃል የተናገረው በዕድሜ በጸጋና በመንፈሳዊ አገልግሎት በእግዚአብሔር
ቤት ውስጥ የሸመገለው ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ሲሆን መጽንኢ (አጽናኝ)፣
መስተፈስሒ (አስደሳች)፣ መንጽሒ (የሚያነፃ)፣ መስተሰርይ (የሚያስተሰርይ)፣ እና ከሳቲ
(ገላጭ) የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበለ በኋላ በዕለቱ በዙሪያው ተሰብስበው
ለነበሩት ለቤተ አይሁድ በ72 ቋንቋ ወንጌልን በመስበክ 3000 ነፍሳትን አሳመነ፡፡ በዘጠኝ
ሰዓትም ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወደ ቤተመቅደስ ሲሄዱ በቤተመቅደስ በር ላይ
ተቀምጦ ሲለምን የነበረውን አንድ አንካሳ ሰው ወደ እኛ ትኩር ብለህ ተመልከት ብሎ
በናዝሬት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ በማለት ፈወሰው፡
ነገር ግን በነጋው ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን የካህናት አለቆች (ሐናና ቀያፋ) ና የመቅደስ
አዘዦች በምን ኃይል ወይም በማን ስም ይህን አደረጋችሁ? ባሉት ጊዜ ነበር ‹‹እናንተ
በሰቀላችሁት እግዚአብሔርም ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው
ግንበኞች የናቁት የማዕዘን ራስ የሆነው ይህ ድንጋይ ነው መዳንም በሌላ በማንም የለም
እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና›› (ሐዋ 4፡
6-12) በማለት የመለሰላቸው፡፡
በመሆኑም የዚህ ጽሁፍ መሠረታዊ ዓላማ ሉተራውያን ፕሮቴስታንትና ተረፈ አርዮሳውያን
‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› የሚለውን ጥቅስ እንደ መፈክር በመያዝ ዝም ብለን
‹‹ኢየሱስ›› በማለት ብቻ እንድናለን ፕሮሰስ አያስፈልግም በማለት የመዳንን ትርጉም
ባለመረዳት የቅዱሳንን፣ የመላዕክትን የመስቀልን፣ የዕምነትን፣ የፀበልንና ሌሎችን የመዳን
መንገዶችን በመቃወም የስህተት ትምህርት ሲያስተምሩ ይስተዋላሉና፣ ይህ የመናፍቃን
ስህተት በሊቃውንት አስተምህሮ ሲመረመር ምን እንደሚመስል ለተዋህዶ ክርስቲያኖች
ማስተማርና በቂ ግንዛቤ በማስጨበጥ ትውልዱን ከስህተት ትምህርት ከጥርጥር መታደግ
ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ቦታ መዳንን በተመለከተ ያስተምረናል ነገር ግን መዳንን
በተመለከተ የእኛ የአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ ለሁሉም አንድ ዓይነት ቃል ነው
የሚጠቀመው ከዚህም የተነሣ ምስጢርን የማያስተውሉ ሰዎች መጻሕፍትን በትርጉም
ሳይሆን በጥሬ ንባብ ለመረዳት የሚሞክሩ ወገኖች በሁለት መልኩ ሲስቱ እናስተውላለን፡፡
ሀ/ የመጀመሪያዎች መዳንን ጠቅልለው ቅዱሳንንም፣ መላዕክትንም ኢየሱስ ክርስቶስንም
በተመለከተ የተናገረው ቃል አንድ ዓይነት ትርጉም ያለው የሚመስላቸው ናቸው፡፡
ለ/ በሌላው መልኩ ደግሞ መላዕክት ቅዱሳን ያድናሉ ብለን ስንል ኢየሱስ ክርስቶስ
እንደሚያድነው ዓይነት ማዳን ያለ የሚመስላቸው ወገኖችም አሉ፡፡
መዳን የሚለው ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር በሦስት ዓይነት ፍቺ ወይም ትርጉም
አመስጥረን እናየዋለን:-
፩ኛ. የዓለም መድኃኒት የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ
የመጀመሪያውና ዋንኛው እግዚአብሔር አዳምንና ልጆቹን ከወደቁበት ውድቀት አንስቶ
ከጠፉበት ከባዘኑበት መልሶ ወደ ነበሩበት ክብር መመለስ ወይም ለመመለስ ያደረገው ጉዞ
ማዳን ይባላል፡፡ አዳም በዕለተ አርብ ወደ ተፈጠረበት ክብር መመለስ ከባርነት ታድጎ
ከሲኦል ነፃ አውጥቶ አዲስ አድርጎ መሥራቱ ማዳን ነው (2ቆሮ 5፡15)
ከዚህም የተነሣ ነው እግዚአብሔር አዳነን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳነን የባርነታችን ቀንበር
ሰበረ ከእስራታችን ፈታን የምንለው
‹‹ፊል 2፡8-11 በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን ይገልፅልናል
የዘመኑ ፍፃሜ በደረሰ ጊዜ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ
ከድንግል ማርያም ተወልዶ የውርደት ሞት (የመስቀል ሞት) ሞቶ እኛን አዳምና ልጆቹን
እንዴት እንደ አዳነን ነው የሚያስተምረው›› ‹‹በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ
ልክ ከፍ ከፍ አደረገው ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው ይህም በሰማይና በምድር
ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ መላስም ሁሉ
ለእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው›› (ፊልጵ
2፡8-11)
ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለው ስም ከስም ሁሉ የከበረ ስም መሆኑን ሐዋርያው ያስተምረናል
እንዲሁም ፍጥረት ሁሉ ይድንበት ዘንድ የተሰጠው ስም ይህ ስም እንደሆነም አስረግጦ
ይነግረናል፡፡
ሐዋርያው ይህን ያለበት ምክንያት እግዚአብሔር ኤልሻዳይ አዶናይ ኤል፣ አልፋና ኦሜጋ ፣
ፊተኛውና ኋለኛው ፣ ያህዌ የሚለው ስም አያድንም ማለቱ ነው? ይህ አይደለም የቅዱስ
ጳውሎስም ሆነ የሐዋርያት ሃሣብ::
እግዚአብሔር የሚለው ስም የእግዚአብሔርነቱ የአንድነቱ የሦስትነቱ ኅቡዕ ስም ነው
አዶናይ ፣ ኤል ፣ ያህዌ የሚሉት ስሞች ከሥጋዌ በፊት የተሰጡ ስሞች ናቸው ኤልሻዳይ፣
ፊተኛውና ኋለኛው፣ አልፋና ኦሜጋ የሚሉት ስሞች ከሀሊነቱን ሁሉንቻይነቱን ያለ የነበረ ወደ
ፊትም የሚኖር መሆኑን የሚገልጹ ከሥጋዌ በፊት የተሰጡ ስሞች ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ሰው ሆነ በተዋህዶ ከበረ ለማለት የተሰጠው ስም ኢየሱስ የሚለው ነው፣
ከስም ሁሉ በላይ የሆነ ስም ያስባለውም ይህ የተዋህዶ ምስጢር ነው፡፡ኢየሱስ ክርስቶስ
የሚለው ስም ከስም ሁሉ የተለየ ስም ነው፡፡
ሚካኤል ገብርኤል ዑራኤል ብንል የፍጡር ስም ነው ምንም እንኳን የቅዱሳን መልዕክት
ስም ቢሆንም ሌሎችም አበበ፣ ተስፋዬ፣ አልማዝ ….. የተጻውአ መጠሪያ ስም ነው
እግዚአብሔር ስንል የፈጣሪ ብቻ ስም ነው፡፡
ኢየሱስ ስንል ግን ፍጡርና ፈጣሪ በተዋህዶ ያገኙት ስም ነው
የፍጡር ስም ለብቻ ነበረ የፈጣሪም ስም ለብቻ ነበረ ፈጣሪ ከፍጡር ጋር በተዋህዶ
በመክበር ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሲወለድ ግን ኢየሱስ
ክርስቶስ የሚለው ስም ተሰጠው ይህም በመሆኑ ይህ ስም የማይደገም ልዩ ስም ነው
እንደፍጡራን ስም በተለያየ ጊዜ የሚደገም አይደለም፡፡
ኢየሱስ የሚለው ስም ግን ምስጢረ ሥጋዌ ስለማይደገም ሌላ ጊዜ የሚደገም ስም
አይደለም አንዱና ዋንኛውም ምክንያት ይህ ነው ኢየሱስ የሚለው ከስም ሁሉ በላይ የሆነ
ስም ያሰኘው፡፡
ሌላው ምክንያት ሌሎችን ስሞች ግብሩን ተመልክተው የእግዚአብሔርን ድንቅ ስራ
ተመልክተው ሰዎች በዚያ ስም ሲጠሩት በሌላ መልኩ ስምህ ማን ነው ብለው
እነአብርሃም እነሙሴ ‹‹ማን ብየ ልንገራቸው ቢለው ሙሴ›› ፊተኛውና መጨረሻው ሁሉን
ቻይ (ኤልሻዳይ) የሆነው ብለህ ንገራቸው ነው ያለው፡፡
ኢየሱስ የሚለው ስም ግን በመላዕክት ተነግሮ በእናቱ በኩል የወጣ ‹‹ትፀንሻለሽ ወንድ
ልጅ ትወልጃለሽ አሕዛብን በባርነት በትር ይገዛል ድንቅ መካር ኃያል አምላክ ይባላል
ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ›› (ሉቃ1 ፣ ኢሳ 9፡6)
እግዚአብሔር የተባለው በዚህ ዘመን ነው በዚህ ሰዓት ነው ልንለው አንችልም ኢየሱስ
ክርስቶስ የተባለበትን ዘመን የተባለበትን ሰዓትና ቦታ እናውቀዋለን በመሆኑም ኅቡዕ
የነበረው ዘመንና ጊዜያት ዕለትና ቀናት የማይቆጠሩለት ፣ በቦታና በጊዜ የማይወሰን ተወስኖ
ተወልዶ ኢየሱስ ስለተባለ ይህ ስም ልዩ ስም ነው እንድንበት ዘንድ የተሰጠ ስም ሲልም
ቃላቶቹን ኢየሱስ የሚለውን ብቻ ሳይሆን ይህንን የማዳንን ምስጢር የሚወክል ስም
የዳንበት ስም የተፈወስንበት ስም ስለሆነ ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ስም አንድን ግብር
ይወክላልና ኢየሱስ ክርስቶስ ተብሎ
ስም ሲወጣለት ምስጢረ ሥጋዌን ምስጢረ
ተዋህዶን፣ ሥጋዌን ለመግለጽ ነው፣ ስለዚህም ለመዳን የተሰጠን ምስጢር ምስጢረ
ተዋህዶ ነው፣ ምስጢረ ተዋህዶ ባይፈጸም ድህነት የለም፣ ለዚህ ነው ስሙ ልዩ ስም ነው፣
አጋንንት ሲሰሙት የሚንቀጠቀጡለት ስም የሆነው አጋንንት የሚፈሯት ተዋሕዶን ነው፣
ዲያብሎስ ድል የተነሣው በምስጢረ ተዋህዶ በምስጢረ ሥጋዌ ነውና፡፡
ምስጢረ ስላሴ ለእኛ ሳይገለጥ ኅቡዕ ይሁን እንጂ በፊትም ነበረ፣ ሌሎችም ምስጢራት
ከምስጢረ ሥጋዌ በኋላ የመጡ ናቸው ከምስጢር ሁሉ የሚበልጠው አስደናቂው ምስጢር
ምስጢረ ሥጋዌ ነው፣ ለምን ቢባል አምላክ ሰው የሆነበት ልዩና ረቂቅ ምስጢር ስለሆነ ነው
ለዚህም ነው ሊቃውንት እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው
የሆነበት በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ የተወለደበት ምስጢር ይበልጣል ያሉት፡፡
‹‹መቼም እግዚአብሔርን ያየው አንድስኳ የለም በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ ተረከው
እንጂ›› ዩሐ 1፡18 እንዳለ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እግዚአብሔርን አየነው ዳሰስነው
ነካነው ብለን የምንናገርበት ምስጢር ይህ የሥጋዌ ምስጢር ነው፡፡ እግዚአብሔርን ማንም
አላየውም ነገር ግን በምስጢረ ስጋዌ የእኛን ሥጋ ለብሶ በማርያም ሥጋ ተዳሰሰ ታየ
ሲናገር ተሰማ አፉን ከፍቶ ሲያስተምር ታየ ይህንን ነው ማዳን የሚሉት ቅዱሳት መጻሕፍት
ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ ነው፣ አዳነን፣ እግዚአብሔር አዳነን ማለት ይህ ነው ይህ
የእግዚአብሔር ማዳን የሚተካ ነገር አይደለም ሌላ ፍጡር የሚጋራው ማዳን አይደለም
እግዚአብሔር በከሐሊነቱ በእግዚአብሔርነቱ የሚያደርገው ብቻ ነው ለምን አዳምን ከሲኦል
ግዛት ነፃ ማውጣት እንደገና በአዲስ ተፈጥሮ በሥጋ ተፈጥሮ መስራት የእግዚአብሔር ብቻ
ገንዘብ ስለሆነ፣ የተዘጋውን ገነት መክፈት የእግዚአብሔር ብቻ ገንዘቡ ስለሆነ ይህ ማዳን
የማይተካ ነው በቅዱሳን መላዕክት በቅዱሳን ጻድቃን በድንግል ማርያም ሊደረግ የማይቻል
ማዳን ነው ይህ ማዳን ደግሞ በዓለም ላይ በዘመናት መካከል የተደረገ ማዳን ነው
በቀራኒዮ አደባባይ ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ ያደረገው ማዳን ነው፡፡
ሌላው ማዳን ሁሉ ከዚህ የሚገኝ በረከት ነው፣ ይህ የመጀመሪያው ማዳን ነው የቅዱሳን
ማዳን፣ በጸበል መዳን በእምነት መዳን፣ በቅዱሳት መጻሕፍት ተሻሽቶ ተሳልሞ መዳን፣
በመስቀል መዳን የምንላቸው ሁሉ በዚህ መዳን ምክነያት የተገኙ ናቸው ይህን ማዳን
ኢየሱስ ክርስቶስ ያድናል ብለን ቅዱሳን መላዕክት ያድናሉ ስንል ልዩነት አለው ይህንን
አውቀን ነው እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንናገረው ሉተራውያን ወይም መናፍቃኑ እንደሚሉት
ጠቅልለን አይደለም የምንናገረው፣ ምን ማለታችን እንደሆነ አውቀን ተረድተን ነው
የምንመሰክረው፡፡
ለምሣሌ (በመዝ 33፡7) ላይ ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል
ያድናቸውማል›› የኢየሱስ ክርስቶስን ያድናል ያለው መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ሥፍራ ደግሞ
ቅዱሳን መላዕክት ያድናሉ ይላል፣ ይህ ማለት መላዕክት አዳምን ከሲኦል አውጥተው ወደ
ገነት ይመልሱታል ማለት አይደለም ይህን ማድረግ ለፍጥረታት ስላልተቻለ ነቢዩ ዳዊትም
ሆነ ነቢዩ ኢሳይያስ እጅህን፣ ቀኝህን ከአርያም ላክ አድነንም ሰማዮችን ቀደህ ውረድ (መዝ
143፡5-7 ፣ ኢሳ 64፡1) በማለት ተናግረዋል፡፡
አዳምን ከወደቀበት የሚያነሣ ወደ ጥንት ክብሩ የሚመልስ አልተገኘም ነበርና
እግዚአብሔር ቀኙን ማዳኑን ጥበቡን አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ላከው አዳምን
ለማዳን አበው የእንሰሳት በመስዋዕት፣ ነቢያት በጽድቃቸውና በለቅሶ በጸሎት እንዲያውም
ደማቸውን በማፍሰስ አጥንታቸውን በመከስከስ ሞክረዋል ግን ስላልቻሉ እንዲህ ነው
ያሉት ‹‹ጽድቃችን እንደ መርገም ጨርቅ ነው፣ በደላችን እንደ ነፋስ አፍገምግሞ
ወስዶናል›› ኢሳ 64፡5 ምክንያቱም የሰው ልጅ መዳን ወደ ጥንተ ተፈጥሮ መመለስ
በእነዚህ ቅዱሳን በአብርሃም፣ በይስሐቅ፣ በያዕቆብ በሰሎሞን በዳዊት በነቢያቱ የሚሆን
አልነበረም የሚከፈል ካሣ ይጠይቅ ነበረ ስለዚህም ነው ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ
ራሱ ሊቀ ካህን፣ ራሱ በግ፣ ራሱ እግዚአብሔር ሆኖ፣ በአንድ ጊዜ ሦስቱንም ሆኖ
መስዋዕት ሰውቶ፣ መስዋዕት ተቀብሎ፣ ራሱ ደግሞ መስዋዕት ሆኖ ድኅነትን ፈጸመልን፡፡
ይህንን ማዳን ማንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን የተለየ ማዳን ነው የኦሪቱም ሊቀ ካህናት የሐዲሱም ሊቀ ካህናት
ሦስት ነገር ይፈልጋሉ ክህነት ይፈልጋሉ፣ መስዋዕት ይፈልጋሉ፣ መስዋዕትን የሚቀበላቸውም
ይፈልጋሉ፡፡ በሐዲስ ኪዳን በቤተመቅደስ ካህኑ በክህነቱ፣ መስዋዕቱን ኅብስቱንና ወይኑን
ያቀርባል፣ መስዋዕቱን የሚቀበል እግዚአብሔር ነው እርሱ ካህን ነው፣ መስዋዕቱ በግ ነው
መስዋዕቱን የሚቀበል እግዚአብሔር ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ልዩ ካህን ነው (ዕብ 8፡2) ምክንያቱም
ሊቀ ካህናቱ ሁሉ ሦስት ነገሮች (መስዋዕት፣ ክህነት፣ መስዋዕት ተቀባይ) ሲፈልጉ እርሱ
ግን አላስፈለገውም፡፡
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንደመሰከረ ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር››
የእግዚአብሔር በግ የተባለ መስዋዕቱ ራሱ ነው ፣ ሊቀ ካህን ነው መስዋዕቱን አቀረበ፣
እግዚአብሔር ነው መስዋዕቱን ተቀበለ (2ቆሮ 5፡16-21) ይህንን ነው የኢየሱስ ክርስቶስ
ማዳን በፍጡር ሊደረግ የማይችል ድህነት የምንለው
ነገር ግን አይሁድ ፈሪሳውያን ሰዱቃውያን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት፣ የአብ
የባሕርይ ልጁ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መድኅኒት (አዳኝ) እንደሆነ አያምኑም ነበረና
ይሰናከሉበት ነበረና የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ደጋግመው በመጥራት ከማስተማራቸው
ባሻገር ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› በማለት የተናገሩት፡፡ ‹‹ሰው ደግሞ የሰውን ልጅ
የእግዚአብሔርን ልጅ የአብ የባሕርይ ልጅ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ
ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የተካከለ ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ የከበረ እንደሆነ ካላመነ
አይድንምና››
‹‹ዮሐ 20፡31 ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ታምኑ ዘንድ
አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፏል››
መጥምቀ ዮሐንስም ‹‹እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ
መስክሬአለሁ›› ዮሐ 1፡34 ነው ያለው ይህ ነው ምስክርነቱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ
መድኀኒት አዳኝ ፈዋሽ እንደሆነ የአብ የባሕርይ ልጅ እንደሆነ መመስከር፣ ምክንያቱም
አይሁድ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካከለ ብለው ሊገድሉት ይፈልጉት ነበረና (ዮሐ 5፡
18) ስለዚህም መዳን በሌላ በማንም የለም በደላችን የተደመሰሰው፣ መርገማችን
የተሻረው ፣ አዳምና ልጆቹ ወደ ቀደመ ክብራችን የተመለስነው በኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን
ነው፡፡
፪ኛ. የመላዕክት ማዳን፣ የቅዱሳን ማዳን፣ የመስቀል ማዳን የፀበል ማዳን ፣ በመስቀልና
በእምነት በቅዱሳት መጻሕፍት በመተሻሸት መዳን የምንለው ነው::
ሀ/ የመላዕክት ማዳን
ከላይ ከፍ ብለን እንደጠቀስነው የመላዕክትን ማዳን በተመለከተ ቅዱስ ዳዊት
‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል›› (መዝ 33፡7)
ይላል መላዕክት ያድናሉ ብለን ስንል ምን ማለታችን ነው ብለን ብንጠይቅና ብንጠየቅ
የመላዕክት ማዳን የጸጋ ነው፡፡
በአጠቃላይ የመላዕክት ማዳን የምንለው ሦስት ነገሮችን ነው፡-
ጥበቃቸውን (መላዕክት በመጠበቅ ያድናሉ ይታደጋሉ)
‹‹በመንገድህ ሁሉ ይጠብቅህ ዘንድ መላዕክቱን ስለ አንተ ታዟል›› መዝ 90፡11 ‹‹ከክፉ
ነገር ሁሉ ያዳነኝ እርሱ እንዚህን ብላቴናዎች ይባርክ›› (ዘፍ 48፡16)
ተዋህዶን፣ ሥጋዌን ለመግለጽ ነው፣ ስለዚህም ለመዳን የተሰጠን ምስጢር ምስጢረ
ተዋህዶ ነው፣ ምስጢረ ተዋህዶ ባይፈጸም ድህነት የለም፣ ለዚህ ነው ስሙ ልዩ ስም ነው፣
አጋንንት ሲሰሙት የሚንቀጠቀጡለት ስም የሆነው አጋንንት የሚፈሯት ተዋሕዶን ነው፣
ዲያብሎስ ድል የተነሣው በምስጢረ ተዋህዶ በምስጢረ ሥጋዌ ነውና፡፡
ምስጢረ ስላሴ ለእኛ ሳይገለጥ ኅቡዕ ይሁን እንጂ በፊትም ነበረ፣ ሌሎችም ምስጢራት
ከምስጢረ ሥጋዌ በኋላ የመጡ ናቸው ከምስጢር ሁሉ የሚበልጠው አስደናቂው ምስጢር
ምስጢረ ሥጋዌ ነው፣ ለምን ቢባል አምላክ ሰው የሆነበት ልዩና ረቂቅ ምስጢር ስለሆነ ነው
ለዚህም ነው ሊቃውንት እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው
የሆነበት በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ የተወለደበት ምስጢር ይበልጣል ያሉት፡፡
‹‹መቼም እግዚአብሔርን ያየው አንድስኳ የለም በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ ተረከው
እንጂ›› ዩሐ 1፡18 እንዳለ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እግዚአብሔርን አየነው ዳሰስነው
ነካነው ብለን የምንናገርበት ምስጢር ይህ የሥጋዌ ምስጢር ነው፡፡ እግዚአብሔርን ማንም
አላየውም ነገር ግን በምስጢረ ስጋዌ የእኛን ሥጋ ለብሶ በማርያም ሥጋ ተዳሰሰ ታየ
ሲናገር ተሰማ አፉን ከፍቶ ሲያስተምር ታየ ይህንን ነው ማዳን የሚሉት ቅዱሳት መጻሕፍት
ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ ነው፣ አዳነን፣ እግዚአብሔር አዳነን ማለት ይህ ነው ይህ
የእግዚአብሔር ማዳን የሚተካ ነገር አይደለም ሌላ ፍጡር የሚጋራው ማዳን አይደለም
እግዚአብሔር በከሐሊነቱ በእግዚአብሔርነቱ የሚያደርገው ብቻ ነው ለምን አዳምን ከሲኦል
ግዛት ነፃ ማውጣት እንደገና በአዲስ ተፈጥሮ በሥጋ ተፈጥሮ መስራት የእግዚአብሔር ብቻ
ገንዘብ ስለሆነ፣ የተዘጋውን ገነት መክፈት የእግዚአብሔር ብቻ ገንዘቡ ስለሆነ ይህ ማዳን
የማይተካ ነው በቅዱሳን መላዕክት በቅዱሳን ጻድቃን በድንግል ማርያም ሊደረግ የማይቻል
ማዳን ነው ይህ ማዳን ደግሞ በዓለም ላይ በዘመናት መካከል የተደረገ ማዳን ነው
በቀራኒዮ አደባባይ ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ ያደረገው ማዳን ነው፡፡
ሌላው ማዳን ሁሉ ከዚህ የሚገኝ በረከት ነው፣ ይህ የመጀመሪያው ማዳን ነው የቅዱሳን
ማዳን፣ በጸበል መዳን በእምነት መዳን፣ በቅዱሳት መጻሕፍት ተሻሽቶ ተሳልሞ መዳን፣
በመስቀል መዳን የምንላቸው ሁሉ በዚህ መዳን ምክነያት የተገኙ ናቸው ይህን ማዳን
ኢየሱስ ክርስቶስ ያድናል ብለን ቅዱሳን መላዕክት ያድናሉ ስንል ልዩነት አለው ይህንን
አውቀን ነው እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንናገረው ሉተራውያን ወይም መናፍቃኑ እንደሚሉት
ጠቅልለን አይደለም የምንናገረው፣ ምን ማለታችን እንደሆነ አውቀን ተረድተን ነው
የምንመሰክረው፡፡
ለምሣሌ (በመዝ 33፡7) ላይ ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ዙሪያ ይሰፍራል
ያድናቸውማል›› የኢየሱስ ክርስቶስን ያድናል ያለው መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ሥፍራ ደግሞ
ቅዱሳን መላዕክት ያድናሉ ይላል፣ ይህ ማለት መላዕክት አዳምን ከሲኦል አውጥተው ወደ
ገነት ይመልሱታል ማለት አይደለም ይህን ማድረግ ለፍጥረታት ስላልተቻለ ነቢዩ ዳዊትም
ሆነ ነቢዩ ኢሳይያስ እጅህን፣ ቀኝህን ከአርያም ላክ አድነንም ሰማዮችን ቀደህ ውረድ (መዝ
143፡5-7 ፣ ኢሳ 64፡1) በማለት ተናግረዋል፡፡
አዳምን ከወደቀበት የሚያነሣ ወደ ጥንት ክብሩ የሚመልስ አልተገኘም ነበርና
እግዚአብሔር ቀኙን ማዳኑን ጥበቡን አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ላከው አዳምን
ለማዳን አበው የእንሰሳት በመስዋዕት፣ ነቢያት በጽድቃቸውና በለቅሶ በጸሎት እንዲያውም
ደማቸውን በማፍሰስ አጥንታቸውን በመከስከስ ሞክረዋል ግን ስላልቻሉ እንዲህ ነው
ያሉት ‹‹ጽድቃችን እንደ መርገም ጨርቅ ነው፣ በደላችን እንደ ነፋስ አፍገምግሞ
ወስዶናል›› ኢሳ 64፡5 ምክንያቱም የሰው ልጅ መዳን ወደ ጥንተ ተፈጥሮ መመለስ
በእነዚህ ቅዱሳን በአብርሃም፣ በይስሐቅ፣ በያዕቆብ በሰሎሞን በዳዊት በነቢያቱ የሚሆን
አልነበረም የሚከፈል ካሣ ይጠይቅ ነበረ ስለዚህም ነው ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ
ራሱ ሊቀ ካህን፣ ራሱ በግ፣ ራሱ እግዚአብሔር ሆኖ፣ በአንድ ጊዜ ሦስቱንም ሆኖ
መስዋዕት ሰውቶ፣ መስዋዕት ተቀብሎ፣ ራሱ ደግሞ መስዋዕት ሆኖ ድኅነትን ፈጸመልን፡፡
ይህንን ማዳን ማንም ሊያደርገው አይችልም፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን የተለየ ማዳን ነው የኦሪቱም ሊቀ ካህናት የሐዲሱም ሊቀ ካህናት
ሦስት ነገር ይፈልጋሉ ክህነት ይፈልጋሉ፣ መስዋዕት ይፈልጋሉ፣ መስዋዕትን የሚቀበላቸውም
ይፈልጋሉ፡፡ በሐዲስ ኪዳን በቤተመቅደስ ካህኑ በክህነቱ፣ መስዋዕቱን ኅብስቱንና ወይኑን
ያቀርባል፣ መስዋዕቱን የሚቀበል እግዚአብሔር ነው እርሱ ካህን ነው፣ መስዋዕቱ በግ ነው
መስዋዕቱን የሚቀበል እግዚአብሔር ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ልዩ ካህን ነው (ዕብ 8፡2) ምክንያቱም
ሊቀ ካህናቱ ሁሉ ሦስት ነገሮች (መስዋዕት፣ ክህነት፣ መስዋዕት ተቀባይ) ሲፈልጉ እርሱ
ግን አላስፈለገውም፡፡
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንደመሰከረ ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር››
የእግዚአብሔር በግ የተባለ መስዋዕቱ ራሱ ነው ፣ ሊቀ ካህን ነው መስዋዕቱን አቀረበ፣
እግዚአብሔር ነው መስዋዕቱን ተቀበለ (2ቆሮ 5፡16-21) ይህንን ነው የኢየሱስ ክርስቶስ
ማዳን በፍጡር ሊደረግ የማይችል ድህነት የምንለው
ነገር ግን አይሁድ ፈሪሳውያን ሰዱቃውያን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት፣ የአብ
የባሕርይ ልጁ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መድኅኒት (አዳኝ) እንደሆነ አያምኑም ነበረና
ይሰናከሉበት ነበረና የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ደጋግመው በመጥራት ከማስተማራቸው
ባሻገር ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› በማለት የተናገሩት፡፡ ‹‹ሰው ደግሞ የሰውን ልጅ
የእግዚአብሔርን ልጅ የአብ የባሕርይ ልጅ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ
ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የተካከለ ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ የከበረ እንደሆነ ካላመነ
አይድንምና››
‹‹ዮሐ 20፡31 ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ታምኑ ዘንድ
አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፏል››
መጥምቀ ዮሐንስም ‹‹እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ
መስክሬአለሁ›› ዮሐ 1፡34 ነው ያለው ይህ ነው ምስክርነቱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ
መድኀኒት አዳኝ ፈዋሽ እንደሆነ የአብ የባሕርይ ልጅ እንደሆነ መመስከር፣ ምክንያቱም
አይሁድ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካከለ ብለው ሊገድሉት ይፈልጉት ነበረና (ዮሐ 5፡
18) ስለዚህም መዳን በሌላ በማንም የለም በደላችን የተደመሰሰው፣ መርገማችን
የተሻረው ፣ አዳምና ልጆቹ ወደ ቀደመ ክብራችን የተመለስነው በኢየሱስ ክርስቶስ ማዳን
ነው፡፡
፪ኛ. የመላዕክት ማዳን፣ የቅዱሳን ማዳን፣ የመስቀል ማዳን የፀበል ማዳን ፣ በመስቀልና
በእምነት በቅዱሳት መጻሕፍት በመተሻሸት መዳን የምንለው ነው::
ሀ/ የመላዕክት ማዳን
ከላይ ከፍ ብለን እንደጠቀስነው የመላዕክትን ማዳን በተመለከተ ቅዱስ ዳዊት
‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል›› (መዝ 33፡7)
ይላል መላዕክት ያድናሉ ብለን ስንል ምን ማለታችን ነው ብለን ብንጠይቅና ብንጠየቅ
የመላዕክት ማዳን የጸጋ ነው፡፡
በአጠቃላይ የመላዕክት ማዳን የምንለው ሦስት ነገሮችን ነው፡-
ጥበቃቸውን (መላዕክት በመጠበቅ ያድናሉ ይታደጋሉ)
‹‹በመንገድህ ሁሉ ይጠብቅህ ዘንድ መላዕክቱን ስለ አንተ ታዟል›› መዝ 90፡11 ‹‹ከክፉ
ነገር ሁሉ ያዳነኝ እርሱ እንዚህን ብላቴናዎች ይባርክ›› (ዘፍ 48፡16)
እግዚአብሔር ልጆቹ ይገስጻል።
#እግዚአብሔር_አምላክ_ልጆቹ_ይገስጻል_ጠላቶች_ግን_ይቀጣል።
እርሱ ለተወዳጁ ልጆቹ " የቀደመ ፍቅራችሁን ትታችኋል" በማለት ያለውን ጣፋጭ ግዜ ያስታውሳቸዋል። ወደ ቀደመውና ውደሚያውቀው ነገር ግን አሁን ወደ ቀነሰበት ወይም ወደ ጠፋበት ወደ መጀመርያው ፍቅሩ መመለስ የሚችለውን ሰው ይገስጸዋል። አብዛኛውን ጊዜ የሚገስጸው ሰው ግን ፍቅሩ የቀነሰበት ሰው ነው።
#እግዚአብሔር ይህን ፍቅር ይጠብቀዋል፡ትኩረትም ይሰጠዋል፡ምክንያቱም እርሱ ከምንም ነገር በላይ ልብን ይፈልጋልና። እርሱ ተራ ተግባራትን አይፈልግም። እርሱ ልባቸው ከእርሱ ርቆ ወደ እርሱ የሚጸልዩትን ሰዎች ይገስጻቸዋል። ስለሆነም እንዲህ ይላቸዋል ፡-" ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፥ . . ." ማቴ15፡8።
#እግዚአብሔር_የተዉት_ልጆቹን_ወይም_እርሱን_የሚያውቁትን_ሰዎች_ይገስጻችዋል።
ስለሆነም በነብዩ ኢሳይያስ የትንቢት መጽሓፍ ውስጥ እንዲህ ብሏቸዋል፡- " . . . ሰማያት ስሙ ምድርም አድምጪ ፥ ልጆችሽን ወለድሁ አሳደግሁም እነርሱም ዐመጹብኝ።"ኢሳ1፡2።
እርሱ የተንከባከበው የወይን ቦታውን ገስጾታል፥ስለዚህ ቦታው ሲናገርም እንዲህ ብሏል፡- "ለወይኔ ያላደርግሁለት፥ከዚህ ሌላ አደርግለት ዘንድ የሚገባኝ ምንድር ነው? ወይንን ያፈራል ብዬ ስተማመን ስለ ምን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ?"ኢሳ 5፡4።
#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
(ፍቅር ከሚል መጽሓፋቸውበአያሌው ዘኢየሱስ የተተረጎመ ) ተጽሓፈ በእግዚአብሔር ፍቅር ነው።
#እግዚአብሔር_አምላክ_ልጆቹ_ይገስጻል_ጠላቶች_ግን_ይቀጣል።
እርሱ ለተወዳጁ ልጆቹ " የቀደመ ፍቅራችሁን ትታችኋል" በማለት ያለውን ጣፋጭ ግዜ ያስታውሳቸዋል። ወደ ቀደመውና ውደሚያውቀው ነገር ግን አሁን ወደ ቀነሰበት ወይም ወደ ጠፋበት ወደ መጀመርያው ፍቅሩ መመለስ የሚችለውን ሰው ይገስጸዋል። አብዛኛውን ጊዜ የሚገስጸው ሰው ግን ፍቅሩ የቀነሰበት ሰው ነው።
#እግዚአብሔር ይህን ፍቅር ይጠብቀዋል፡ትኩረትም ይሰጠዋል፡ምክንያቱም እርሱ ከምንም ነገር በላይ ልብን ይፈልጋልና። እርሱ ተራ ተግባራትን አይፈልግም። እርሱ ልባቸው ከእርሱ ርቆ ወደ እርሱ የሚጸልዩትን ሰዎች ይገስጻቸዋል። ስለሆነም እንዲህ ይላቸዋል ፡-" ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ፥ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፥ . . ." ማቴ15፡8።
#እግዚአብሔር_የተዉት_ልጆቹን_ወይም_እርሱን_የሚያውቁትን_ሰዎች_ይገስጻችዋል።
ስለሆነም በነብዩ ኢሳይያስ የትንቢት መጽሓፍ ውስጥ እንዲህ ብሏቸዋል፡- " . . . ሰማያት ስሙ ምድርም አድምጪ ፥ ልጆችሽን ወለድሁ አሳደግሁም እነርሱም ዐመጹብኝ።"ኢሳ1፡2።
እርሱ የተንከባከበው የወይን ቦታውን ገስጾታል፥ስለዚህ ቦታው ሲናገርም እንዲህ ብሏል፡- "ለወይኔ ያላደርግሁለት፥ከዚህ ሌላ አደርግለት ዘንድ የሚገባኝ ምንድር ነው? ወይንን ያፈራል ብዬ ስተማመን ስለ ምን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ?"ኢሳ 5፡4።
#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
(ፍቅር ከሚል መጽሓፋቸውበአያሌው ዘኢየሱስ የተተረጎመ ) ተጽሓፈ በእግዚአብሔር ፍቅር ነው።
+++ የመነኩሴው ፈሊጥ +++
መጾም ያቃተውን ሰው ጹም፣ መመጽወት የተሳነውን መጽውት፣ መራመድ የማይችለውን ሩጥ የሚሉ መካሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ መራመድ የማይችል እንዴት መሮጥ እንዳለበት ከማሳየት ይልቅ ቀንበር ማክበድ ጠባያችን ሆኗል፡፡ ይህ የሚያሳየው ቃሉ እንጂ ተግባሩ የተለየን መሆኑን ነው፡፡ በተግባር መግለጥ ብንችል ኖሮ፣ ማገዝ ቢያቅተን እናሯሩጠውና ሰውነቱ ሞቆ ተጋድሎ ሲጀምር እናፈገፍግ ነበር፡፡ እኛ ግን ልምድ የሌለውን ሁሉ ተሸከም ማለት ይቀለናል፡፡ ከባለ ግመሉ ከአባ ቆሪር ምክር ለመመጽወት የሄደ ክርስቲያን ግመሉ ከሚችለው በላይ ስለጫነው አንተ አቅም አጥተህ ምክር ለመቀበል መጥተህ ሳለ ግመሉን ካለ አቅሙ ለምን ጫንከው ተብሏል፡፡
ከዐቅማቸው በላይ ተሸክመው የከበዳቸውን ሰዎች በማገዝ ሸክሙ ሳይከብዳቸው፣ ከክርስቲያናዊ ተጋድሎ ሳያፈገፍጉ በእምነት እንዲኖሩ ማገዝ ከዘመናችን የሃይማኖት ሰዎች የሚጠበቅ መሆኑን ለማስታወስ የአባ ዳንኤልን ፈሊጥ በአብነት እጠቅሰዋለሁ፡፡ አንድ አባ ዳንኤል የሚባል መነኩሴ ነበር፡፡ የደከመ ባገኝ አግዛለሁ እያለ በጨረቃ ከበዓቱ ወጥቶ ገዳማውያን በሚገኙበት በረሓ ይዞር ነበር፡፡
በአንድ ወቅት የማትሠራው ኃጢአት ያልነበር፣ ከጽድቅ ተግባር የማትተዋወቅ ሴት አገኘ፡፡ አባ ዳንኤልም ሴቲቱን ወደ ሴቶች ገዳም ወስዶ ልብላ ካለች ትብላ፣ ልተኛ ካለች ትተኛ፣ የፈቀደችውን ሁሉ ታድርግ፣ የገዳሙ ሕግ አይፈቅድም በማለት ቀንበር አንዳታከብዱባት ብሎ ለእመምኔቷ አስረክቧት ሔደ፡፡ እመምኔቷም እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ ሴቲቱ በፈለገች ጊዜ ትበላለች፣ ስትፈልግ ትተኛለች፡፡ ያሰኛትን ታደርጋለች፡፡ ግን ደስታ የላትም፤ አብረዋት የሚኖሩት መነኮሳት ቤተ ክርስቲያን አድረው፣ በሥራ ተጠምደው ሲኖሩ ተመለከተች፡፡ እሷ በልታ ይርባታል፡፡ እነሱ ሳይበሉ አይራቡም፣ እሷ ተኝታ ይደክማታል፣ እነሱ ቆመው ውለው፣ ቆመው አድረው ድካም አያውቁም፡፡ ቀስ በቀስ መገረም፣ ከዚያም በሕይወታቸው መቅናት ጀመረች፡፡
ምግብ ሲያቀርቡላት እስከ ሦስት ሰዓት ልቆይ ማለት ጸሎት አድርጋ መብላት ተለማመደች፡፡ ቆየችና እስከ ስድስት ልቆይ አለቻቸው ከዚያም እስከ ዘጠኝ፣ ከዚያም በ24 ሰዓት አንድ ጊዜ መመገብ ጀመረች፡፡ ከዚያም ከሳምንት አንድ ቀን ብቻ መቅመስ በመጨረሻም በዓቷን ዘግታ በሦስት ሳምንትም፣ በወርም በሕይወት ለመቆየት ያህል መቅመስ ደረሰች እንዲህ ድክመታችን ታግሠው ለክብር የሚያበቁን ባለ ፈሊጥ መምህራን ማግኘት ለዚህ ዘመን እንዛዝላ ተሸካሚ ከዕንቊ የበለጠ ስጦታ ነው እላለሁ፡፡
መጾም ያቃተውን ሰው ጹም፣ መመጽወት የተሳነውን መጽውት፣ መራመድ የማይችለውን ሩጥ የሚሉ መካሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ መራመድ የማይችል እንዴት መሮጥ እንዳለበት ከማሳየት ይልቅ ቀንበር ማክበድ ጠባያችን ሆኗል፡፡ ይህ የሚያሳየው ቃሉ እንጂ ተግባሩ የተለየን መሆኑን ነው፡፡ በተግባር መግለጥ ብንችል ኖሮ፣ ማገዝ ቢያቅተን እናሯሩጠውና ሰውነቱ ሞቆ ተጋድሎ ሲጀምር እናፈገፍግ ነበር፡፡ እኛ ግን ልምድ የሌለውን ሁሉ ተሸከም ማለት ይቀለናል፡፡ ከባለ ግመሉ ከአባ ቆሪር ምክር ለመመጽወት የሄደ ክርስቲያን ግመሉ ከሚችለው በላይ ስለጫነው አንተ አቅም አጥተህ ምክር ለመቀበል መጥተህ ሳለ ግመሉን ካለ አቅሙ ለምን ጫንከው ተብሏል፡፡
ከዐቅማቸው በላይ ተሸክመው የከበዳቸውን ሰዎች በማገዝ ሸክሙ ሳይከብዳቸው፣ ከክርስቲያናዊ ተጋድሎ ሳያፈገፍጉ በእምነት እንዲኖሩ ማገዝ ከዘመናችን የሃይማኖት ሰዎች የሚጠበቅ መሆኑን ለማስታወስ የአባ ዳንኤልን ፈሊጥ በአብነት እጠቅሰዋለሁ፡፡ አንድ አባ ዳንኤል የሚባል መነኩሴ ነበር፡፡ የደከመ ባገኝ አግዛለሁ እያለ በጨረቃ ከበዓቱ ወጥቶ ገዳማውያን በሚገኙበት በረሓ ይዞር ነበር፡፡
በአንድ ወቅት የማትሠራው ኃጢአት ያልነበር፣ ከጽድቅ ተግባር የማትተዋወቅ ሴት አገኘ፡፡ አባ ዳንኤልም ሴቲቱን ወደ ሴቶች ገዳም ወስዶ ልብላ ካለች ትብላ፣ ልተኛ ካለች ትተኛ፣ የፈቀደችውን ሁሉ ታድርግ፣ የገዳሙ ሕግ አይፈቅድም በማለት ቀንበር አንዳታከብዱባት ብሎ ለእመምኔቷ አስረክቧት ሔደ፡፡ እመምኔቷም እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ ሴቲቱ በፈለገች ጊዜ ትበላለች፣ ስትፈልግ ትተኛለች፡፡ ያሰኛትን ታደርጋለች፡፡ ግን ደስታ የላትም፤ አብረዋት የሚኖሩት መነኮሳት ቤተ ክርስቲያን አድረው፣ በሥራ ተጠምደው ሲኖሩ ተመለከተች፡፡ እሷ በልታ ይርባታል፡፡ እነሱ ሳይበሉ አይራቡም፣ እሷ ተኝታ ይደክማታል፣ እነሱ ቆመው ውለው፣ ቆመው አድረው ድካም አያውቁም፡፡ ቀስ በቀስ መገረም፣ ከዚያም በሕይወታቸው መቅናት ጀመረች፡፡
ምግብ ሲያቀርቡላት እስከ ሦስት ሰዓት ልቆይ ማለት ጸሎት አድርጋ መብላት ተለማመደች፡፡ ቆየችና እስከ ስድስት ልቆይ አለቻቸው ከዚያም እስከ ዘጠኝ፣ ከዚያም በ24 ሰዓት አንድ ጊዜ መመገብ ጀመረች፡፡ ከዚያም ከሳምንት አንድ ቀን ብቻ መቅመስ በመጨረሻም በዓቷን ዘግታ በሦስት ሳምንትም፣ በወርም በሕይወት ለመቆየት ያህል መቅመስ ደረሰች እንዲህ ድክመታችን ታግሠው ለክብር የሚያበቁን ባለ ፈሊጥ መምህራን ማግኘት ለዚህ ዘመን እንዛዝላ ተሸካሚ ከዕንቊ የበለጠ ስጦታ ነው እላለሁ፡፡
+++ አንድ "ግዩር" እንዲኽ ይመክራል +++
(መጋቤ ወብሉይ ወሐዲስ ቀሲስ አባ ገብረኪዳን ግርማ እንደጻፉት)
ስለ እግዚአብሔር ብለን ሰውን እንውደድ እንጅ ስለ ሰው ብለን እግዚአብሔርን መውደድ አይገባንም ። በእግዚአብሔር ፊት ሰውን መውደድህን ይገለጥልህ እንጅ በሰው ፊት የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመምሰል ብለህ የምትኖ ር አትሁን ። ለሰዎች ብለህ እንደወደድከው ለሰዎች ብለህ ልትጠላው ትችላለህ እና።
......
የእግዚአብሔር ሰው መሆን ማለት እግዚአብሔርን መመገብ እንጅ እግዚአብሔርን ማወቅ አይደለም ። ለመዳን ብለህ እወቅ እንጅ በእውቀትህ የምትድን አይምሰልህ ። የማታውቀውን የምታውቀው ልትኖረው እንጅ እውቀቱ በክርስቶስ ቀኝ ሊያቆምህ አይምሰልህ ። በጎ ነገርን ያወቅሃት ዕለት ብቻ ደስ አይበልህ ፥ የሠራሃት ዕለት እንጅ ፥ በመሥራትህም አትመካ አልፈጸምካትምና ። ከእግዚአብሔር ያወቅሃትን መልካም ነገር ወዲያው ሥራት ፥ እየሠራሃት ያለችህን መልካም ነገር አትልቀቃት ። እየኖርክ ተማር እንጅ እየተማርክ ብቻ ዘመንህን እንዳትፈጽም ተጠንንቀቅ ። ያለ ዕውቀት ብትኖር ከፍርድ የምታመልጥ አይደለምና መቼም ቢሆን ከቤተክርስቲያን ጉባዔያት አትታጣ ፥ በማወቅህ ፍርድ አይቀርልህምና ያወቅኸውን ፈጥነህ ሥራ ።
.....
ቤተክርስቲያንን በኹለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን በትምህርት ዕወቃት ፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን በኑሮ ዕወቃት ። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን ፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ ። በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ ። እሊህም ፦ ኪዳን ማስደረስ ፥ ማስቀደስ ና ንስሐ ገብቶ መቁረብ ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው ። ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ ።
.....
በሕይወትህ ኹሉ ቤተክርስቲያናዊ ኹን ! ብቻየን ለፋሁበት ብለህ ገንዘብህን ብቻህን አትጨርሰው ። ከምታገኘው ሁሉ ለመድኀኔዓለም ድርሻ አስቀምጥ ። የለመነህን ሰው አትመርምረው ቢቻልህ ስጠው ባይቻልህ እዘንለት እንጅ ። ለስንፍናህ ሁሉ ምክንያት አታብጅለት ። መልካሙን ነገርም ዛሬ ሥራው ፥ ክፉውን ነገርም ዛሬ ተናዘዘው ። እያንዳንዱ የጊዜ ሽርፍራፊ የገነትና የሲዖል ሰው ለመሆንህ ዋጋ እንዳለው እወቅ ። ይቆየን መልካም የሆነ እግዚአብሔር ለመልካም የሚሳብ መልካምን የሚያደርግ በመልካሞ የሚጸና በጎ ሕሊና ይስጠን!
አባ ገብረኪዳን
ሰኔ ፲፯ - ፳፻፲፪ ዓም
----------------
ማሳሰቢያ፦ "ግዩር" የሚለው ቃል "መጻተኛ ፣ ስደተኛ..." የሚል ትርጒም አለው። ነገር ግን አባታችን በምን አገባብ እንደተጠቀሙት እርሳቸውን መጠየቅ ሳያሻ አይቀርም
(መጋቤ ወብሉይ ወሐዲስ ቀሲስ አባ ገብረኪዳን ግርማ እንደጻፉት)
ስለ እግዚአብሔር ብለን ሰውን እንውደድ እንጅ ስለ ሰው ብለን እግዚአብሔርን መውደድ አይገባንም ። በእግዚአብሔር ፊት ሰውን መውደድህን ይገለጥልህ እንጅ በሰው ፊት የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመምሰል ብለህ የምትኖ ር አትሁን ። ለሰዎች ብለህ እንደወደድከው ለሰዎች ብለህ ልትጠላው ትችላለህ እና።
......
የእግዚአብሔር ሰው መሆን ማለት እግዚአብሔርን መመገብ እንጅ እግዚአብሔርን ማወቅ አይደለም ። ለመዳን ብለህ እወቅ እንጅ በእውቀትህ የምትድን አይምሰልህ ። የማታውቀውን የምታውቀው ልትኖረው እንጅ እውቀቱ በክርስቶስ ቀኝ ሊያቆምህ አይምሰልህ ። በጎ ነገርን ያወቅሃት ዕለት ብቻ ደስ አይበልህ ፥ የሠራሃት ዕለት እንጅ ፥ በመሥራትህም አትመካ አልፈጸምካትምና ። ከእግዚአብሔር ያወቅሃትን መልካም ነገር ወዲያው ሥራት ፥ እየሠራሃት ያለችህን መልካም ነገር አትልቀቃት ። እየኖርክ ተማር እንጅ እየተማርክ ብቻ ዘመንህን እንዳትፈጽም ተጠንንቀቅ ። ያለ ዕውቀት ብትኖር ከፍርድ የምታመልጥ አይደለምና መቼም ቢሆን ከቤተክርስቲያን ጉባዔያት አትታጣ ፥ በማወቅህ ፍርድ አይቀርልህምና ያወቅኸውን ፈጥነህ ሥራ ።
.....
ቤተክርስቲያንን በኹለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን በትምህርት ዕወቃት ፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን በኑሮ ዕወቃት ። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን ፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ ። በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ ። እሊህም ፦ ኪዳን ማስደረስ ፥ ማስቀደስ ና ንስሐ ገብቶ መቁረብ ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው ። ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ ።
.....
በሕይወትህ ኹሉ ቤተክርስቲያናዊ ኹን ! ብቻየን ለፋሁበት ብለህ ገንዘብህን ብቻህን አትጨርሰው ። ከምታገኘው ሁሉ ለመድኀኔዓለም ድርሻ አስቀምጥ ። የለመነህን ሰው አትመርምረው ቢቻልህ ስጠው ባይቻልህ እዘንለት እንጅ ። ለስንፍናህ ሁሉ ምክንያት አታብጅለት ። መልካሙን ነገርም ዛሬ ሥራው ፥ ክፉውን ነገርም ዛሬ ተናዘዘው ። እያንዳንዱ የጊዜ ሽርፍራፊ የገነትና የሲዖል ሰው ለመሆንህ ዋጋ እንዳለው እወቅ ። ይቆየን መልካም የሆነ እግዚአብሔር ለመልካም የሚሳብ መልካምን የሚያደርግ በመልካሞ የሚጸና በጎ ሕሊና ይስጠን!
አባ ገብረኪዳን
ሰኔ ፲፯ - ፳፻፲፪ ዓም
----------------
ማሳሰቢያ፦ "ግዩር" የሚለው ቃል "መጻተኛ ፣ ስደተኛ..." የሚል ትርጒም አለው። ነገር ግን አባታችን በምን አገባብ እንደተጠቀሙት እርሳቸውን መጠየቅ ሳያሻ አይቀርም
*ምክረ አጋንንት*
በቅዱስ አቡነ ዮሴፍ ዘላስታ
ልጹም ትላለህ ፤ ተው አትጹም ይልሃል!አንተም ትተወዋለህ።
ልመጽውት ትላለህ ፤ ተው አትመጽውት ይልሃል። አንተም ትተወዋለህ።
ንስሐ ልግባ ትላለህ ፤ ትንሽ ቆይ ይልሃል። አንተም ያለንስሐ ትሞታለህ።
ልቁረብ ትላለህ ፤ ገና ነህ ትንሽ ቆይ ይልሃል። አንተም ሳትቆርብ ትሞታለህ
ላስቀድስ ትላለህ ፤ ተው ትንሽ ተኛ ይልሃል። አንተም ሳትሄድ ታረፍዳለህ።
ጸበል ልግባ ትላለህ ፤ ጤነኛ ነህ ይልሃል። ገዳም ልባረክ ልሂድ ትላለህ ፤ ተው ስራን
ስራ ይልሃል፡፡ አንተም ሳትሄድ ስትቆጭ ትኖራለህ።
አስራት በኩራት ልስጥ ትላለህ ፤ ተው አትስጥ የለህም ይልሃል። አንተም
ትተወዋለህ።
በአንድ ልወሰን ትላለህ ፤ ተው ቆንጆዎቹ ያልፉሃል ይልሃል። አንተም በዝሙት
ትወድቃለህ።
# በመጨረሻም_የተወሰነልህ_ግዜ_ያልቃል ። ነፍስህን አጋንንት እንደ ኳስ እየተቀባበሉ
ይወስዷታል።
# ልጠጣ ስትል ፤ ጠጣ ይልሃል። ያሰክርሃል።
# ልዝፈን ስትል ፤ዝፈን ይልሃል። ያስጨፍርሃል!
# ልስረቅ ስትል ስረቅ ይልሃል። ያሰርቅሃል!
# ልጣለው ስትል ተጣላ ይልሃል። ያጣላሃል።
# ልዋሽ ስትል ዋሽ ይልሃል። ያስዋሽሃል! ስጋዊ ተድላን ይሰጥሃል። ይመችሃል፡ስጋህ ወፍሮ
፣ ቀልቶ ፣ ወዝቶ በጓደኞችህ ‹ ተመቸህ እኮ ! › ያስብልሃል። አንተም ደስ ይልሃል! በዛው
ትገፋበታለህ።
# ሃሳብህ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ቀርቶ ወደ ጅምናዝየም ቤት መሔድ
ይሆናል።
# ሃሳብህ ሁሉ የተመጣጠኑ ምግቦችን መመገብ ይሆናል። ሃሳብህ ሁሉ ሳውና ባዝ ፣
ስቲም ቤት ፣ማሳጅ ቤት ሂደህ መታሸት እና መዝናናት ይሆናል።
# እግርህ ሁሉ ወደ ሲኒማ ቤት ፣ ወደ ናይት ክለብ ቤት ፣ ወደ ሆቴል ቤት ፣ ወደ
ግሮሰሪ ቤት ፣ ወደ ሱፐር ማርኬት ፣ ወደ ምናምን ቦታ ይሆናል።
በእነዚህ ሁሉ ስጋህ ሲመቸው
ቁሞ መጸለይ ይደክምሃል።
መስገድ ያቅትሃል።
መጾም ይከብድሃል።
ቤተክርስቲያን ለመሄድ ይጨልምሃል።
ስጋህ በአጋንንት መረብ ይጠመዳል።
ደም ብዝት አስይዞ ሴት ያዝልሃል።
ደም ብዛት አሲይዞሽ ወንድ ያዝልሻል።
የነርቭ በሽታ አስይዞ መቆምና መሄድ ያስቅትሃል።
ስኳር በሽታ አሲይዞ ከጾም ይከለክልሃል።
ጨጓራ በሽታ አስይዞ ጾምን ይከለክልሃል።
# ምላስህ እግዚአብሔርን ማመስገንን ሳይሆን ዘወትር ስለ በሽታህ እንድትዘምር
ያደርጋታል።
# በጣም ብዙዎች ሃብት ሞልቷቸው በሽተኛ ያደርጋቸዋል። ገና ከጥዋቱ እነዚህ ሰዎች
የእግዚአብሔርን መንገድ ተከትለው ቢሄዶ ኖሮ ፤ እንደ አብርሃም ፣እንደ ይስሐቅ እና እንደ
ያዕቆብ በምድር ሃብታም እንደ ሆኑ ሁሉ በሰማይም እንደ ቅዱሳኑ የገነት ባለቤት በሆኑ
ነበር።
# ሰይጣን ክፉ ነው! ሃብታሙን በሽተኛ ፣ ድሃውን ደግሞ ጤነኛ አድርጎ አምላክን ወቃሽ
ያደርገዋል።እንዲህ እንዲህ እያለ የመሰናበቻ ጊዜ ይደርሳል። በኃጢአት የዳበረው ስጋችን
አፈር ነውና በቅጽበት እሬሳ ተብሎ ወደ አፈር ይገባል። ነፍስ ግን እያዘነችና እየተፀፀተች
ወደ ሲዖል ትወረወራለች።
# የምናያቸው ቆንጆ ሴቶች ፣ የምናያቸው ቆንጆ ወንዶች ፣ የምናየው የልኳንዳ ስጋ ፣
የምናየው መጠጥና ምግብ ሁሉ ያምረናል። ስጋችን ያሸንፈናል፥ ነፍሳችን ትሸነፋለች።
ለገነት ተፈጥረን ለሲዖል እንሆናለን።ሁላችንም ወደ እግዚያብሄር ተመልሰን ንሰሀ እንግባ።።
በቅዱስ አቡነ ዮሴፍ ዘላስታ
ልጹም ትላለህ ፤ ተው አትጹም ይልሃል!አንተም ትተወዋለህ።
ልመጽውት ትላለህ ፤ ተው አትመጽውት ይልሃል። አንተም ትተወዋለህ።
ንስሐ ልግባ ትላለህ ፤ ትንሽ ቆይ ይልሃል። አንተም ያለንስሐ ትሞታለህ።
ልቁረብ ትላለህ ፤ ገና ነህ ትንሽ ቆይ ይልሃል። አንተም ሳትቆርብ ትሞታለህ
ላስቀድስ ትላለህ ፤ ተው ትንሽ ተኛ ይልሃል። አንተም ሳትሄድ ታረፍዳለህ።
ጸበል ልግባ ትላለህ ፤ ጤነኛ ነህ ይልሃል። ገዳም ልባረክ ልሂድ ትላለህ ፤ ተው ስራን
ስራ ይልሃል፡፡ አንተም ሳትሄድ ስትቆጭ ትኖራለህ።
አስራት በኩራት ልስጥ ትላለህ ፤ ተው አትስጥ የለህም ይልሃል። አንተም
ትተወዋለህ።
በአንድ ልወሰን ትላለህ ፤ ተው ቆንጆዎቹ ያልፉሃል ይልሃል። አንተም በዝሙት
ትወድቃለህ።
# በመጨረሻም_የተወሰነልህ_ግዜ_ያልቃል ። ነፍስህን አጋንንት እንደ ኳስ እየተቀባበሉ
ይወስዷታል።
# ልጠጣ ስትል ፤ ጠጣ ይልሃል። ያሰክርሃል።
# ልዝፈን ስትል ፤ዝፈን ይልሃል። ያስጨፍርሃል!
# ልስረቅ ስትል ስረቅ ይልሃል። ያሰርቅሃል!
# ልጣለው ስትል ተጣላ ይልሃል። ያጣላሃል።
# ልዋሽ ስትል ዋሽ ይልሃል። ያስዋሽሃል! ስጋዊ ተድላን ይሰጥሃል። ይመችሃል፡ስጋህ ወፍሮ
፣ ቀልቶ ፣ ወዝቶ በጓደኞችህ ‹ ተመቸህ እኮ ! › ያስብልሃል። አንተም ደስ ይልሃል! በዛው
ትገፋበታለህ።
# ሃሳብህ ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ቀርቶ ወደ ጅምናዝየም ቤት መሔድ
ይሆናል።
# ሃሳብህ ሁሉ የተመጣጠኑ ምግቦችን መመገብ ይሆናል። ሃሳብህ ሁሉ ሳውና ባዝ ፣
ስቲም ቤት ፣ማሳጅ ቤት ሂደህ መታሸት እና መዝናናት ይሆናል።
# እግርህ ሁሉ ወደ ሲኒማ ቤት ፣ ወደ ናይት ክለብ ቤት ፣ ወደ ሆቴል ቤት ፣ ወደ
ግሮሰሪ ቤት ፣ ወደ ሱፐር ማርኬት ፣ ወደ ምናምን ቦታ ይሆናል።
በእነዚህ ሁሉ ስጋህ ሲመቸው
ቁሞ መጸለይ ይደክምሃል።
መስገድ ያቅትሃል።
መጾም ይከብድሃል።
ቤተክርስቲያን ለመሄድ ይጨልምሃል።
ስጋህ በአጋንንት መረብ ይጠመዳል።
ደም ብዝት አስይዞ ሴት ያዝልሃል።
ደም ብዛት አሲይዞሽ ወንድ ያዝልሻል።
የነርቭ በሽታ አስይዞ መቆምና መሄድ ያስቅትሃል።
ስኳር በሽታ አሲይዞ ከጾም ይከለክልሃል።
ጨጓራ በሽታ አስይዞ ጾምን ይከለክልሃል።
# ምላስህ እግዚአብሔርን ማመስገንን ሳይሆን ዘወትር ስለ በሽታህ እንድትዘምር
ያደርጋታል።
# በጣም ብዙዎች ሃብት ሞልቷቸው በሽተኛ ያደርጋቸዋል። ገና ከጥዋቱ እነዚህ ሰዎች
የእግዚአብሔርን መንገድ ተከትለው ቢሄዶ ኖሮ ፤ እንደ አብርሃም ፣እንደ ይስሐቅ እና እንደ
ያዕቆብ በምድር ሃብታም እንደ ሆኑ ሁሉ በሰማይም እንደ ቅዱሳኑ የገነት ባለቤት በሆኑ
ነበር።
# ሰይጣን ክፉ ነው! ሃብታሙን በሽተኛ ፣ ድሃውን ደግሞ ጤነኛ አድርጎ አምላክን ወቃሽ
ያደርገዋል።እንዲህ እንዲህ እያለ የመሰናበቻ ጊዜ ይደርሳል። በኃጢአት የዳበረው ስጋችን
አፈር ነውና በቅጽበት እሬሳ ተብሎ ወደ አፈር ይገባል። ነፍስ ግን እያዘነችና እየተፀፀተች
ወደ ሲዖል ትወረወራለች።
# የምናያቸው ቆንጆ ሴቶች ፣ የምናያቸው ቆንጆ ወንዶች ፣ የምናየው የልኳንዳ ስጋ ፣
የምናየው መጠጥና ምግብ ሁሉ ያምረናል። ስጋችን ያሸንፈናል፥ ነፍሳችን ትሸነፋለች።
ለገነት ተፈጥረን ለሲዖል እንሆናለን።ሁላችንም ወደ እግዚያብሄር ተመልሰን ንሰሀ እንግባ።።
በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ