Telegram Web Link
እሁድ 7:30(ረመዳን-7) የሼኽ ሙሐመድ አል-አንሲ ትምህርት ይከታተሉ።
ረመዳን -8 ሰኞ ከቀኑ 7:15 በዩትዩብ ቻናላችን ትምህርቱን ይከታተሉ።

"ዱዓ ስታደርግ..." በሚል ዝግጅት ወደናንተ የቀረበ ሲሆን ዝግጅቱ በረመዳን 7 - 1445ዓ.ሒ በሼኽ ሙሐመድ አል-አንሲ አማካኝነት የሚካሄድ ሲሆን ሰፊ ነጥቦችን ሼኹ ይዳስሳሉ። በዋናነት ስለ ዱዓ ሚስጥራቶች እና እስከዛሬ አስበናቸው የማናቃቸውን ነጥቦችን ከህይወታችን ጋር በማያያዝ የዱዓ ሚስጥራቶችን ያብራርሉናል። ፕሮግራሙን ሼር እና ላይክ እንዲሁም ፔጃችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
http;//youtube.com/@UCf1l3HUhbvYevpMWRDPVhjg
http;//tiktok.com/@islam_mindset

----------------------------------------------------
👍2
👍6
ረመዳን- 12 -1445 ዓ.ሒ

በዚች ህይወት ስትኖር ዋጋ ያላቸውን ነገሮች ስትገዛ በብር ነው። በዱንያ ላይ ብር ነውም ያለው! ነፍስህ ከሰውነትህ ስትለያይ ግን ብር ስራውን አቁሞ በሌላ ይተካል። እርሱም ሀሰና ይባላል።የአኪራ ገንዘብ ነው! ሚዛኑም የሚንቀሳቀሰው በሀሰናት ነው የመጨረሻይቱ ቀን ላይ!ሙዕሚን የሚለየው እዚህ ነጥብ ላይ ነው...ነፍሱ ከሰውነቱ ሳትለየው የዱንያውን ብር ወደ አኪራው ብር(ሀሰናት)ብቻ ለመቀየር ይሰራል። ምን ብሩን ብቻ..ጊዜውንም ጉልበቱንም ወደ ሀሰናት የሚቀይሩ አጋጣሚዎችን ሁሉ ይጠቀምባቸዋል።ሙናፊቆች እና ካሃዲያን ግን ለዚህ በፍፁም አልታደሉም።

www.tg-me.com/@mind_islam
👍3
ረመዳን-15-1445 ዓ.ሒ

ህይወት ትጠቀለላለች...ያውም ሳናስብበት ሳንጨነቅለት..ሳናስተነትነለት! ለዚህም ማሳያ እስካሁን ያሳለፍነውን ዘመናቶች እና ግዜያቶችን ዘወር ብለን መመልከት ብቻ በቂ ነው።ከህይወት ግን የሚያስፈራው ነገር ቢኖር መቼ ከሞት ጋር እንደምንላተም አለማወቃችን ነው። ምክንያቱም ሞት ለመምጣቱ መስፈርት የለውም። ከዚህም አለፍ ስንል ደግሞ አለመዘጋጀታችን እና ዘላለም እንደምንኖር ማስመሰላችን አሰፈሪ ያደርገዋል። ጠንቃቃዎች እንሁን ..ወደ አላህ በቻልነው አቅም እንቃረብ!

@islam_mindset
👍3
ያንተ ማንነት ለነገሮች ቦታ በምትሰጠው ነገር ይወሰናል።ለጊዜውም ቢሆን...!
ለነገሮች ቦታ መስጠት ማለት ደግሞ ውድ የሆነውን ሰዓትህን በምሰጠው ነገር ማሳለፍ ማለት ነው። ምንድን ነው የምታሳልፈው ሰዓትህን ራስህን ጠይቅ...!?

@islam_mindset
ኢድ አል-ፈጥር
ሮብ መሆኑ ተገልጿል።
ረመዳን -30 ሁኗል።አልሀምዱሊላህ!
👍4🥰1
" የረመዳን እንግዳ ነን!?"
ጠይቃችሁ ታውቃላችሁ አስተውላችሁ እንደሆነ ረመዳን ሲገባ መስጂዶች ይጨናነቃሉ።እስከዛሬ የመጀመሪያው ሶፍ ላይ ሲሰግዱ የነበሩ ሰዎች በረመዳን ላይ በረመዳን እንግደኞች ተነጥቀው ሲቸገሩ ይስተዋል ነበር። የሚገርመው ነገር ረመዳን ሳይወጣ እንግዳነታቸውን ጨርሰው በፊት ለነበሩት ሰጋጆች አስረክበው ይወጣሉ። ካላመናችሁ መስድጅ ገብታችሁ አረጋግጡ። ዲንን ዱንያ አድርገን በመያዝ እና የረመዳን እንግዳ አንሁን።ቢያንስ እንኳን ህሊናችንን እንታዘዘው!ራሳችንን እንታዘበው,ባርነታችንን በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ሳንሞት እናረጋግጥ!

(መልዕክቱ የሚጠቅም ነው ብላችሁ ካመናችሁበት ለሌላ ሰው እንዲደርስ ያድርጉ)

www.tg-me.com/mind_islam
#ጀዛኩሙሏህ_ኸይረን
2👍1
የተወዳጁን ኡስታዝ ሼይክ መሐመድ አንሲን ትምህርት በተከታታይ ወደናንተ በአላህ ፈቃድ በዩትዩብ ቻናላችን ይደርሳል። ቻናሉ ለብዙ ሰዎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉት!
እንዲሁም ሰብስክራይብ በማድረግ የቻናሉ ቤተሰብ ይሁኑ።
youtube.com/@islamethiopia
አላህ እኛ ሙስሊሞችን ደረጃ የሚሰጠን በስብስብ ብዛታችን ሳይሆን በዉስጣችን ባለው የተቅዋ ጥንካሬያችን ብቻ ነው።በሚያሳዝን ሁኔታ ግን ይሄንን ዘንግተነዋል።ለዚህም መረጃው እንደ ገለባ በዝተን በመካከላችን ፍሬ መታጣቱ በቂ ነው። አላህ ብቸኛን ሰው ከህዝብ መንጋ ስብስብ እንደሚበልጥ በራሱ ንግግር በሚገባን መልኩ አሰቀምጦልናል።ማስተንተኛ አዕምሮ ካለን! ስለዚህ የራሳችንን ትልቁን የቤት ስራችንን ሳንጨርስ ሌላ ስራዎች አንጀምር።ምክንያቱም እንሰበራለን። ሁላችንም በመጀመሪያ ተቅዋችንን እንመርምር! የሙስሊም ትልቁ አጀንዳ ስብስብን ማጠናከር ሳይሆን ተቅዋን በልብ መጠንከር የሚችልበትን መንገዶችን መስራት እና መዘርጋት ነው። ይህ የዛሬው መልዕክታችን ነው አላህ ከመጥፎ ነገር ሁሉ ይጠብቃችሁ...!
#አሚን..
www.tg-me.com/@mind_islam
#share
#like
#ቤተሰብ_ይሁኑ
👍2
Channel name was changed to «Islamindset- ETHIOPIA»
ኢብኑ ጀዉዚ(አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡-
"ከቅጣት ሁሉ ከባዱ ቅጣት በሐጥያት ላይ መዘዉተር
፤መንፈሳዊነትን መራቅ ፤ ኢማንን መገፈፍ ፤ ከአላህ ጋር የማዉራትን ጥፍጥና አለመታደል ፤ ቁርአንን መርሳትና ኢስቲግፋር ችላ ማለት ነዉ፡፡
ዱንያ ላይ ከቀልብ በሽታ ይልቅ በሰዉነት ላይ የሚደርሰዉ በሽታ ቀላል ነዉ!"ብለዋል
#viral
#foryou
#fb_page
#islamindset
#like
#share
👍4🥰1
2025/10/22 13:48:45
Back to Top
HTML Embed Code: