"የጉባኤቤትቆይታችሁስኬት የሚለካውባገኛችሁት ዕውቀት ብቻ ሳይሆን በምትሰማሩበት መንፈሳዊ አገልግሎት የድካምና የመሰልቸት መንፈስ ሳይሰማችሁ ቃለ እግዚአብሔር ለተጠማውና በጠረፍ ላለው ሕዝባችሁ በመድረስ ወደ ቅድስና ሕይወት ስትመሩ ነው" ያሉት ደግሞ በማኅበረ ቅዱሳን የቤ/ን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ት/ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ዲ/ን ደረጀ ጋረደው እንደሆኑ ተመላክቷል።
ዳይሬክተሩ ጨምረው እንደተናገሩት በዚህ ዓመት ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተመረጡ 169 የአብነት ት/ቤቶች፣ ለ229 መምህራንና 2000 የአብነት ደቀ መዛሙርት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ዕቅድ ይዞ ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ለዛሬዎቹ ተመራቂዎች ለሕክምና ፣ለትምህርት፣ ለቀለብና ለመሳሰሉት ድጋፍ አድራጊዎችን በማስተባበር 842,650.00 ብር ወጪ በማድረግ እንዲማሩ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
የሚዛን ተፈሪ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ር ጥላሁን ታደሰ በበኩላቸው የአገልጋይ ካህናት እጥረትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ብዙ ፈተናዎች ቢኖሩም ዛሬ ለአራት ወራት ያስተማርናቸው አገልጋይ ካህናትን በማስመረቃችን ደስ ብሎናል ብለዋል።
በሸካ ፣ ቤንቺ ሸኮ እና ምዕ/ ኦሞ ሀገረ ስብከት 197 አብያተ ክርስቲያናት መካከል 5ቱ ገዳማት ሲሆኑ በአገልጋይ እጥረት ምክንያት አንድ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ የተዘጋ፣ 25ቱ አብያተ ክርስቲያናት በአመት የሚቀደስባቸው፣ 5ቱ ወርሐዊ በዓላትን በመጠበቅ የሚቀደስባቸው፣ ከ100 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሰንበት ት/ቤት የሌላቸውና ሰርክ ጉባኤ የማይሰጥባቸው እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
መሠረታዊ የክህነት ት/ት የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶች የተማሩትና ለምርቃት የበቁት ደቀ መዛሙርቱ በአካባቢያቸው ቋንቋ በማስተማር እና የክህነት አገልግሎቱን በመስጠት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዳይሬክተሩ ጨምረው እንደተናገሩት በዚህ ዓመት ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተመረጡ 169 የአብነት ት/ቤቶች፣ ለ229 መምህራንና 2000 የአብነት ደቀ መዛሙርት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ዕቅድ ይዞ ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ለዛሬዎቹ ተመራቂዎች ለሕክምና ፣ለትምህርት፣ ለቀለብና ለመሳሰሉት ድጋፍ አድራጊዎችን በማስተባበር 842,650.00 ብር ወጪ በማድረግ እንዲማሩ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
የሚዛን ተፈሪ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ር ጥላሁን ታደሰ በበኩላቸው የአገልጋይ ካህናት እጥረትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ብዙ ፈተናዎች ቢኖሩም ዛሬ ለአራት ወራት ያስተማርናቸው አገልጋይ ካህናትን በማስመረቃችን ደስ ብሎናል ብለዋል።
በሸካ ፣ ቤንቺ ሸኮ እና ምዕ/ ኦሞ ሀገረ ስብከት 197 አብያተ ክርስቲያናት መካከል 5ቱ ገዳማት ሲሆኑ በአገልጋይ እጥረት ምክንያት አንድ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ የተዘጋ፣ 25ቱ አብያተ ክርስቲያናት በአመት የሚቀደስባቸው፣ 5ቱ ወርሐዊ በዓላትን በመጠበቅ የሚቀደስባቸው፣ ከ100 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሰንበት ት/ቤት የሌላቸውና ሰርክ ጉባኤ የማይሰጥባቸው እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
መሠረታዊ የክህነት ት/ት የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶች የተማሩትና ለምርቃት የበቁት ደቀ መዛሙርቱ በአካባቢያቸው ቋንቋ በማስተማር እና የክህነት አገልግሎቱን በመስጠት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ማኅበረ ቅዱሳን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው በመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የመልሶ ማቋቋሚያ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ
ባለፈው ዓመት ሐምሌ አጋማሽ በጎፋ ዞን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በቦታው በመገኘት የአልባሳትና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፍ ማድረጊያ ቦታ የተገኙት የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ እና የወረዳው አስተዳደር ተወካይ አቶ ዓለምነህ ነጋሽ ፣የገዜ ጎፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ ዲያቆን ፍጹም መሪነህ እና ሌሎች አባላትም ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል።
የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ እና የወረዳው አስተዳደር ተወካይ አቶ ዓለምነህ ነጋሽ እንደገለጸት በሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በማኅበረሰባችን ላይ የደረሰውን ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት በማድረግ ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ያሉ ወገኖች ድጋፋቸውን እያደረጉ በመሆኑ ህዝባችን እየተጽናኑ ይገኛል ብለዋል።
ማኅበረ ቅዱሳን ችግሩ ባጋጠመበት ባለፈው ዓመትም፣ ነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በቦታው በመገኘት 1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት የቤት መሥሪያ ቆርቆሮና ለተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ግብዓቶችን ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ድጋፉ የተደረገው ማኅበረ ወልድ ዘሰሜን አሜሪካ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን ለዚሁ ድጋፍ በጠቅላላው ከ700 ሺህ ብር በላይ ወጭ መሆኑ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ሐምሌ አጋማሽ በጎፋ ዞን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በቦታው በመገኘት የአልባሳትና የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፍ ማድረጊያ ቦታ የተገኙት የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ እና የወረዳው አስተዳደር ተወካይ አቶ ዓለምነህ ነጋሽ ፣የገዜ ጎፋ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ተወካይ ዲያቆን ፍጹም መሪነህ እና ሌሎች አባላትም ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል።
የገዜ ጎፋ ወረዳ ዋና አፈ-ጉባኤ እና የወረዳው አስተዳደር ተወካይ አቶ ዓለምነህ ነጋሽ እንደገለጸት በሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በማኅበረሰባችን ላይ የደረሰውን ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት በማድረግ ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ ያሉ ወገኖች ድጋፋቸውን እያደረጉ በመሆኑ ህዝባችን እየተጽናኑ ይገኛል ብለዋል።
ማኅበረ ቅዱሳን ችግሩ ባጋጠመበት ባለፈው ዓመትም፣ ነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በቦታው በመገኘት 1.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት የቤት መሥሪያ ቆርቆሮና ለተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ግብዓቶችን ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ድጋፉ የተደረገው ማኅበረ ወልድ ዘሰሜን አሜሪካ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን ለዚሁ ድጋፍ በጠቅላላው ከ700 ሺህ ብር በላይ ወጭ መሆኑ ተገልጿል።
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ባለፉት 7 ወራት ብቻ በመጠለያዎች ጣቢያዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች፣ በድርቅና መሰል ማኅበራዊ ቀውስ ለተጎዱ ወገኖች፣ ለገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ከ10 በላይ የሚሆኑ ተመሳሳይ ማኅበራዊ ድጋፎችን አድርጓል። በቀጣይ ጊዜም መሰል የነፍስ አድን ድጋፎችን ለማድረስ በሚደረገው የሰብአዊነት ሥራ ምእመናን የተለመደ ድጋፍ እንድታደርጉልን ማኅበሩ ጥሪውን ያቀርባል።
ድጋፍ ለማድረግ፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በጎ ፈንድ ሚ፡- https://gofund.me/f4c1b82e
6. በወገን ፈንድ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ድጋፍ ለማድረግ፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በጎ ፈንድ ሚ፡- https://gofund.me/f4c1b82e
6. በወገን ፈንድ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
gofundme.com
Donate to ኑ! የክቡራን ወገኖቻችንን ሕይወት እናትርፍ !!!, organized by Mahibere Kidusan
ኑ! የክቡራን ወገኖቻችንን ሕይወት እናትርፍ !!!
+++
ማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት 6 ዓመታት በሀገራችን ኢትዮጵያ እያጋጠመ ባለው ማኅ… Mahibere Kidusan needs your support for ኑ! የክቡራን ወገኖቻችንን ሕይወት እናትርፍ !!!
+++
ማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት 6 ዓመታት በሀገራችን ኢትዮጵያ እያጋጠመ ባለው ማኅ… Mahibere Kidusan needs your support for ኑ! የክቡራን ወገኖቻችንን ሕይወት እናትርፍ !!!
የማኅበረ ቅዱሳን ላሊበላ ወረዳ ማእከል የጤና ቡድን ለተከዜ ኃይላ ለጥበብ ወምእራፈ ቅዱሳን አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ አንድነት ገዳም ገዳማውያን ነጻ የሕክምና አገልግሎት ሰጠ
ሰኔ ፲፱/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ኦርቶዶክሳዊያን ሙያተኞች በሙያቸው ተገቢውን አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ይችሉ ዘንድ በሁሉም ማእከላት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል የማድረግ ሥራዎችን እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
በዚሁ መሠረት በማኅበረ ቅዱሳን ላሊበላ ወረዳ ማእከል ሙያ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች አገልግሎት ክፍል የጤና ባለሙያዎች ኅብረት በላስታ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ለሚገኘው ለተከዜ ኃይላ ለጥበብ ወምእራፈ ቅዱሳን አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ አንድነት ገዳም 46 መናንያን ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠቱን የጤና ባለሙያዎች ኅብረት አስተባባሪው ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ ሲሳይ ገልጸዋል።
ወቅቱ ወረሽኝ የሚበዛበት በመሆኑ የሕክምና አገልግሎቱን መስጠት አስፈልጓል ያሉት ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ በሙያችን ገዳማውያንን በማገልገላችን የእኛም ነፍስ ታክማለች፤ በቀጣይም አገሎግሎቱን ለማስፋት የዳሰሳ ጥናት በመሥራት ወደ ሌሎች ገዳማት ለመድረስ እንሠራለን ብለዋል።
ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ አክለውም ለሥራቸው መሳካት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉትን አካላት አመስግነው ለቀጣይ መሰል ተግባራትም በጎ አድራጊዎች፣ አጋርና ባለድርሻ አካላት መድኃኒትና መሰል ድጋፎችን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የገዳሙ መጋቢ አባ ገብረ ጻድቅ ከፍያለ በበኩላቸው "የገዳሙን ሕግና ሥርዓት በጠበቀ እንዲሁም የመናንያኑን መንፈሳዊ ሕይወት ባከበረ መልኩ ይህ አገልግሎት መሰጠቱ እንዳስደሰታቸው ገልጸው የሕክምና አገልግሎቱ በተጠናከረ መንገድ ቀጣይነት እንዲኖረው" አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሰኔ ፲፱/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ኦርቶዶክሳዊያን ሙያተኞች በሙያቸው ተገቢውን አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ይችሉ ዘንድ በሁሉም ማእከላት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል የማድረግ ሥራዎችን እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
በዚሁ መሠረት በማኅበረ ቅዱሳን ላሊበላ ወረዳ ማእከል ሙያ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች አገልግሎት ክፍል የጤና ባለሙያዎች ኅብረት በላስታ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ለሚገኘው ለተከዜ ኃይላ ለጥበብ ወምእራፈ ቅዱሳን አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስ አንድነት ገዳም 46 መናንያን ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠቱን የጤና ባለሙያዎች ኅብረት አስተባባሪው ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ ሲሳይ ገልጸዋል።
ወቅቱ ወረሽኝ የሚበዛበት በመሆኑ የሕክምና አገልግሎቱን መስጠት አስፈልጓል ያሉት ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ በሙያችን ገዳማውያንን በማገልገላችን የእኛም ነፍስ ታክማለች፤ በቀጣይም አገሎግሎቱን ለማስፋት የዳሰሳ ጥናት በመሥራት ወደ ሌሎች ገዳማት ለመድረስ እንሠራለን ብለዋል።
ዲ/ን ዶ/ር ፈንታ አክለውም ለሥራቸው መሳካት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉትን አካላት አመስግነው ለቀጣይ መሰል ተግባራትም በጎ አድራጊዎች፣ አጋርና ባለድርሻ አካላት መድኃኒትና መሰል ድጋፎችን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የገዳሙ መጋቢ አባ ገብረ ጻድቅ ከፍያለ በበኩላቸው "የገዳሙን ሕግና ሥርዓት በጠበቀ እንዲሁም የመናንያኑን መንፈሳዊ ሕይወት ባከበረ መልኩ ይህ አገልግሎት መሰጠቱ እንዳስደሰታቸው ገልጸው የሕክምና አገልግሎቱ በተጠናከረ መንገድ ቀጣይነት እንዲኖረው" አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ለሕክምናው የወጣው ወጭ በገንዘብ ሲተመን 51,050.90 ብር እንደሚሆንና የላስታ ወረዳ ጤና ጽ/ቤትና ሌሎች በጎ አድራጊዎች ባደረጉት ድጋፍ የተሸፈነ መሆኑ ተገልጿል።
በሕክምና አገልግሎቱ 3 ሐኪሞች፣ 3 ነርሶች፣ 2 የላብራቶሪ ባለሙያዎች እንዲሁም 1 ፋርማሲ በአጠቃላይ 9 የጤና ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን የተገኘው መረጃ ያመልክታል።
በሕክምና አገልግሎቱ 3 ሐኪሞች፣ 3 ነርሶች፣ 2 የላብራቶሪ ባለሙያዎች እንዲሁም 1 ፋርማሲ በአጠቃላይ 9 የጤና ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን የተገኘው መረጃ ያመልክታል።
በሽሬ ከተማ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች 1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነባቸው የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ መደረጉ ተገለጸ፡፡
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሀገራችን እያጋጠሙ ያሉ ሰፊ ማኅበራዊ ቀውሶች በማኅበረሰብ ክፍሎች፣ በገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ላይ እያስከተሉት ያለውን ችግር ለማቅለል ፣ ባለፉት 7 ተከታታይ ዓመታት ሁለገብ ማኅበራዊ ድጋፎችን በመላ ሀገራችን እያደረገ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህ መሠረት በሰሜን ኢትዮጵያ ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስ፣ ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በትግራይ ሽሬ እንደ ሥላሴ ከተማና ዙሪያው በሚገኙ 18 ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ከ35,000 በላይ ተፈናቃዮች በከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
ማኅበሩም በመላ ሀገሪቱ እንደሚያደርገው ሁሉ ሰኔ 19 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በመጠለያ ጣቢያዎች በመገኘት 1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት 100 ኩንታል የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፉም ከ500 የሚልቁ ወገኖች ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን በዚህ የድጋፍ ርክክብ ወቅትም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ልዑካን፣ የማኅበረ ቅዱሳን ሰሜን ምሥራቅና ሽረ ማእከል ተወካዮች እንዲሁም የመንግሥት አካላት በመገኘት ድጋፉን ለተጎጅዎች አስረክበዋል።
በተጨማሪም በችግሩ ለተጎዱ በአካባቢው ለሚገኙ ከ10 ለሚልቁ ገዳማት ድጋፎች የተደረጉ ሲሆን በተመሳሳይ ከወራት በፊት በአክሱም ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፎች መደረጋቸው ይታወሳል።
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሀገራችን እያጋጠሙ ያሉ ሰፊ ማኅበራዊ ቀውሶች በማኅበረሰብ ክፍሎች፣ በገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ላይ እያስከተሉት ያለውን ችግር ለማቅለል ፣ ባለፉት 7 ተከታታይ ዓመታት ሁለገብ ማኅበራዊ ድጋፎችን በመላ ሀገራችን እያደረገ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህ መሠረት በሰሜን ኢትዮጵያ ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስ፣ ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በትግራይ ሽሬ እንደ ሥላሴ ከተማና ዙሪያው በሚገኙ 18 ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ከ35,000 በላይ ተፈናቃዮች በከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
ማኅበሩም በመላ ሀገሪቱ እንደሚያደርገው ሁሉ ሰኔ 19 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በመጠለያ ጣቢያዎች በመገኘት 1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት 100 ኩንታል የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አድርጓል።
በድጋፉም ከ500 የሚልቁ ወገኖች ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን በዚህ የድጋፍ ርክክብ ወቅትም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ልዑካን፣ የማኅበረ ቅዱሳን ሰሜን ምሥራቅና ሽረ ማእከል ተወካዮች እንዲሁም የመንግሥት አካላት በመገኘት ድጋፉን ለተጎጅዎች አስረክበዋል።
በተጨማሪም በችግሩ ለተጎዱ በአካባቢው ለሚገኙ ከ10 ለሚልቁ ገዳማት ድጋፎች የተደረጉ ሲሆን በተመሳሳይ ከወራት በፊት በአክሱም ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ድጋፎች መደረጋቸው ይታወሳል።