Telegram Web Link
የሴቶች፣ህጻናት እና ወጣቶች ሚኒስትሯ ፊልሰን አብዱላሂ የስራ መልቀቂያ አስገቡ።

በዕድሜ ትንሿ የካቢኔ አባል ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መልቀቂያ ማስገባታቸውን በተለያዩ የማህበረሰብ ገጾቻቸው አስታውቀዋል።

ሚኒስትሯ በሰው ሃይል እና በጀት እጦት እምብዛም ይሰራ ያልነበረውን መስሪያ ቤት የመምራቱን ሃላፊነት መረከቡ ለውድቀት እንደመመቻቸት ሆኖ ነው የተሰማኝ ሲሉ በገለጹበትና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጻፍኩ ባሉት ደብዳቤያቸው በችግሮች መካከልም ቢሆን የተቋሙን የ10 ዓመታት እቅድ ከማዘጋጀት ጀምሮ ባለፈው አንድ ዓመት ትልቅ ጥረትን ስናደርግ እንደነበር በኩራት ለመናገር እችላለሁ ብለዋል፡፡

በማንኛውም የስራ ጫና እና ውጥረት ውስጥ ሆነን መቼ እንስራ እና መቼ እንልቀቅ በሚል የሚያጋጥሙ ልዩነቶችን እንደሚቀበሉ ተስፋ አደርጋለሁ ሲሉም ነው ፊልሰን በደብዳቤያቸው ያሰፈሩት፡፡

ስነ ምግባሬን የተመለከተ ማንኛውም ሁኔታ ከእምነት እና እሴቶቼ የተቃረነ ነው ያሉም ሲሆን ይህን አሳልፎ መስጠት ለራሴ እና ለዜጎች ያለኝን እምነት መጣስ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ለህሊናዬ በሚከብዱ ባሏቸው ግላዊ ምክንያቶች ምክንያት የመልቀቂያ ደብዳቤውን መጻፋቸውንም አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቋሙን እንዲመሩ ለሰጧቸው እድልም አመስግነዋል፡፡

ወ/ሮ ፊልሰን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አቅራቢነት መጋቢት 3/2012 ዓ.ም የሴቶች፣ህጻናት እና ወጣቶች ሚኒስትር ሆነው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሾማቸው የሚታወስ ነው፡፡
Via al ain
@nidatube
ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ኢንስታግራም በአለም ዙርያ ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸውን ተራኪንግ ድረ ገጾች አስታውቀዋል።

ችግሩ ምን እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም።
Via al ain

@nidatube @nidatubebot
የፓኪስታን የኒኩሌር አባት አብዱልቃድር ከሃን ህወታቸው አለፈ

አብዱልቀድር ከሃን ፓኪስታን የኒኩሌር የጦር መሳሪያን የታጠቀች የመጀመሪያዋ እስላማዊ ሀገር ማድረግ የቻሉ ናቸው

አብዱልቀድር ከሃን በህመም ምክንያት በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የፓኪስታን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ የሆነው ቢቲቪ ዘግቧል።

ፓኪስታናዊው የኒኩሌር ተመራማሪ አብዱልቀድር ከሃን የሀገሪቱ ብሄራዊ ጀግና ተደርገው ነው በበርካቶች የሀገሪቱ ዜጎች ዘንድ የሚታዩት።

ምንያቱ ደግሞ አብዱልቀድር ከሃን ፓኪስታን የኒኩሌር የጦር መሳሪያን የታጠቀች የመጀመሪያዋ እስላማዊ ሀገር እንድትሆን ማድረግ በመቻላቸው ነው ተብሏል።

አብዱልቀድር ከሃን የፓኪስታን የመጀመሪያው የኒኩሌር ማብላያ ጣቢያ በኢስላማባድ አቅራቢያ እንዲተከል ማድረግ የቻሉ ሲሆን፤ እንደ አውሮፓውያኑ በ1998 ሀገሪቱ የመጀመሪያውን የኒኩሌር የጦር መሳሪያ ሙከራ እንድታደርግም አስችለዋል።

Via alain
የጁምአ ቀን
~~~~

ነብዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ)እንዲህ ብለዋል ፡ አርብ(ጁመዓ) ቀን፡ ገላውን ታጥቦ መላ ሰውነቱን አፀዳድቶ ፡ቅባትና ሽቶ ከተቀባ በሗላ ጁመአ ለመስገድ ቀደም ብሎ ወደ መስጊድ ፡በመሔድ ሌሎች ሰዎችን ሳይገፋና ሳይረብሺ በፀጥታ ቦታውን ለሚይዝ ፡ከዚያም የቻለውን ያህል (ነፍል) ከሰገደ በሗላ በፀጥታ ኹጥባን(የኢማሙን ንግግር )ለሚያዳምጥ ሰው ከዚያ ጁመዓ ጀምሮ እስከሚቀጥለው ጁመአ ድረስ በመካከል ያለው ሐጢያቱን አላህ ይተውለታል፡፡ ነብዩ{ሰ,ዐ,ወ} ስለ ጁምአ ቀን ታላቅነት ሲናገሩ የጁምአ ቀን የቀኖች ሁሉ ኑጉስ ነው እነዚህ አምስት ነገሮች በጁምአ ቀን ተከስተዋል ብለዋል። እነሱም
1, አላህ አደምን የፈጠረው በጁመአ ቀን ነው፣
2, አደም ከጀነት የወጡት በጁምአ ቀን ነው፣
3, አደም የሞተውም በጁመአ ቀን ነው፣ 4, ቂያማ የምትቆመውም በጁመአ ቀን ነው፣
5, በጁምአ ቀን የሆነች ሠአት አለች።አንድ የአላህ ባሪያ የጠየቀውን ነገር ይሠጠዋል፣ያቺን ሠአት ካገኛት ሀራም ነገር እስካልሆነ ድረስ አላህ ይቀበለዋል። በሌላ የሀድስ ዘገባ አንድ ሰው ታጥቦ ያለውን ጥሩ ልብስ ለብሶ ሽቶ ተቀብቶ ወደ መስጂድ ሄዶ ማንንም አዛ ሳያደርግ ኢማሙ ቁጥባ ሲያደርጉ ዝም ብሎ ከሠማ ጁማአውን ከሰገደ አላህ ካለፈው ጁምአ እሥከ አሁኑ ጁምአ ያለውን ወንጀሉን ያብስለታል። በሌላ የሀድስ ዘገባ የጁምአ እለት በመጀመሪያ ሠአት ወደ መስጅድ የገባ ግመል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ የቀንድ ከብት ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ በግ/ፍየል ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ ዶሮ ሰደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታል። ከዚህም አርፍዶ የመጣ እንቁላል ሠደቃ እንዳደረገ ይፃፍለታላ። ኢማሙ ሚንበር ላይ ሲወጡ የሚመዘግቡት መላኢኮች የኢማሙን ኹጥባ ለመስማት መስጂድ ይገባሉ። የአላህ መላእክተኛ(ሰ,ዐ,ወ) እንድህ ብለዋል፦

የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላወትን ማውረድ አብዙ፣ማንኛውም ሠው የጁምአ ቀን በእኔ ላይ ሠላዋት አያወርድም ሠላዋቱ ቢቀርብልኝ እንጅ።

{አልባኒ ሶሂህ ብለውታል} ‌"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ። መሸጥንም ተዉ፡፡ ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነወ።" ‌ "ሶለቲቱም በተፈጸመች ጊዜ በምድር ላይ ተበተኑ። ከአላህም ችሮታ ፈልጉ፡፡ አላህንም በብዙ አውሱ፡፡ ልትድኑ ይከጀላልና፡፡" ((62:9_10)

የጁመአ ቀን ሱናወች ~~~~~~~~~
~ገላን መታጠብ
~ ጥሩ ልብስ መልበስ
~ሽቶ መቀባት ለወንዶች
~ ሲዋክ
~ ማልዶ በግዜ ወደ መስጅድ መሄድ
~ ሱረቱል ካፍን መቅራት ዱአ ማብዛት ~ በረሱል (ሰ፣ዐ፣ወ) ላይ ሰለዋት ማውረድ።

‌ اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد ال

لَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ

https://www.tg-me.com/joinchat-QoR5qFfHQ7j_IRrI
አሜሪካ፤ ህወሓት ወደ ደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች መቃረቡን እንዲገታ ጥሪ አቀረበች

ተኩስ ለማቆም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ድርድር ይጀመርም ነው ዋሽንግተን ያለችው

የጦርነቱ መዛመት እጅግ አሳስቦኛል ያለችው አሜሪካ ህወሓት፤ ከአማራ እና አፋር ክልሎች እንዲወጣ በድጋሚ ጥሪ አቀረበች።

ህወሓት ወደ ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መቃረቡን እንዲገታም ጥሪ ያቀረበችው አሜሪካ ከባድ መሳሪያዎችን ወደ ከተሞች እንዳይተኩስ አሳስባለች።
መንግስት በመቀሌና በሌሎች የትግራይ አካባቢዎች የፈፀማቸውን የአየር ድብደባዎች በጽኑ መቃወሜ ይታወስልኝ ያለችው ዋሽንግተን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ ሁሉም አካላት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ድርድር መጀመር አለባቸው ብላለች።
Vi al ain

@nidatube
የህወሓት ታጣቂዎች በንፋስ መውጫ ከተማ በ9 ቀናት ውስጥ 71 ሴቶችን አስገድደው ደፍረዋል - አምነስቲ

ወንጀሎቹ የተፈጸሙት በህጻናት ፊት መሆኑንም ድርጅቱ ገልጿል

ሴቶቹ የተደረፈሩት የህወሓት ታጣቂዎች በከተማዋ በቆዩባቸው ዘጠኝ ቀናት ውስጥ ነው

የህወሓት ታጣቂዎች በንፋስ መውጫ ከተማ 71 ሴቶችን አስገድደው መድፈራቸው ተገለጸ፡፡

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተቋም አምኒስቲ ኢንተርናሽናል የህወሓት ታጣቂዎች በወረራ በያዟቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች ያደረሱትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አስመልክቶ ያጠናቀረውን ሪፖርት አውጥቷል፡፡

ተቋሙ በሪፖርቱ እንደገለጸው የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ንፋስ መውጫ ከተማ ከነሀሴ 6 ቀን እስከ 15 ቀን 2013 ዓ.ም በከተማዋ በቆዩባቸው ዘጠኝ ቀናት ውስጥ የተለያ ጥቃቶችን ፈጽሟል፡፡

ታጣቂዎቹ ከፈጸሟቸው ወንጀሎች መካከል በቡድን ሴቶችን መድፈር፣ ንብረት ማውደም፣ መዝረፍ እና አጸያፊ ስድቦችን በንጹሃን ላይ መፈጸማቸውን ድርጅቱ በሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

ስለተፈጸመባቸው የቡድን አስገድዶ መደፈር አስመልክቶ በአምኒስቲ ኢንተርናሽናል ቃለመጠይቅ ከተደረገላቸው ሴቶች መካከል አንዷ ገበያነሽ የተባለች የከተማው ነዋሪ ናት፡፡

ምግብ በመሸጥ እንደምትተዳደር የገለጸችው የ30 ዓመቷ ገበያነሽ "የሆነብኝን መናገር ቀላል አይደለም። ለሶስት ሆነው ደፈሩኝ። የደፈሩኝ ልጆቼ እያለቀሱ ነው። ትልቁ ልጄ 10 ታናሹ ደሞ 9 ዓመቱ ነው። ሁለቱም ወታደሮቹ ሲደፍሩኝ እያዩ ያለቅሱ ነበር። ከደፈሩኝ በኃላ እየሰደቡኝ ሽሮና በርበሬ ወሰዱ። በጥፊ መቱኝ። በፊቴ መሳሪያቸውን እያቀባበሉ እንደሚገድሉኝ አስፈራሩኝ" ስትል ተናግራለች፡፡

ሌላኛዋ በህወሓት ታጣቂዎች በቡድን የተደፈረችው የ28 ዓመቷ ሀመልማል ስትሆን እንጀራ በመሸጥ ሕይወቷን የምትመራ የከተማው ነዋሪ ናት።

"የ10 ዓመትና የ2 ዓመት ልጆች አሉኝ። ወታደሮቹ ልጆቼን እንዳይገድሉብኝ ፈርቼ ነበር። ልጆቼን አትግደሉብኝ እኔን እንደፈለጋችሁ አድርጉ አልኳቸው። ትንሿ ተኝታ ነበር። ትልቋ ግን እያየች ደፈሩኝ። ምን እንዳየች ለመናገር አቅሙ የለኝም" ስትል በህወሃት ታጣቂዎቹ የደረሰባትን ተናግራለች፡፡

ታጣቂዎቹ የህክምና ተቋማትን ማውደማቸውን የገለጸው ይህ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋም በተለይም ተገደው የተደፈሩ ሴቶች ህክምና እንዳያገኙ መደረጉንም አስታውቋል፡፡

ድርጅቱ ቃለመጠይቅ ካደረጋቸው 16 ሴቶች መካከል 14ቱ በህወሓት ታጣቂዎች በቡድን መደፈራቸውን ተናግረዋል፡፡

አምነስቲ አክሎም በንፋስ መውጫ ከተማ በአጠቃላይ 70 ሴቶች በታጣቂዎቹ መደፈራቸውን ከከተማው ሴቶች እና ህጻናት ጽህፈት ቤት መስማቱንም በሪፖርቱ አካቷል፡፡

የተቋሙ ዋና ጸሃፊ አግኔስ ካላማርድ በማጠቃለያ ሪፖርቱ ላይ በሰጡት አስተያየት “የህወሓት ታጣቂዎች በንፋስ መውጫ ከተማ የጦር ወንጀል መፈጸሙን ከተጎጂዎች ያገኘነው መረጃ ያስረዳል” ብለዋል፡፡

የቡድኑ ታጣቂዎች አሁንም በአማራ እና አፋር ክልሎች ጥቃቱን ቀጥለዋል ያሉት ዋና ጸሃፊው እየፈጸሟቸው ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንዲያቆሙ ጠይቀዋል፡፡

Via al ain

@nidatube
የጋዳፊ ልጅ በሊቢያ ለፕሬዚዳንትነት ሊወዳደር ነው ተባለ
ጋዳፊ በኔቶ መራሹ ጦር በ2011 ከስልጣን መወገዳቸውና መገደላቸው ይታወሳል

የቀድሞ የሊቢያ መሪ ሙዓማር ጋዳፊ ልጅ ሰይፍ አል እስላም ጋዳፊ በቀጣይ ወር በሀገሪቱ በሚካሄደው ምርጫ እንደሚሳተፍ ተገለጸ፡፡

የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽኑ ባለስልጣን እንደገለጹት ታህሳስ 24 ቀን በሊቢያ በሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ በመሆን ከተመዘገቡት መካከል የቀድሞ የሊቢያ መሪ ሙአማር ጋዳፊ ልጅ ሰይፍ አል እስላም ጋዳፊ አንዱ ነው፡፡
ሰይፍ አል እስላም ጋዳፊ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ሆኖ መመዝገቡ አሁን ላይ መረጋገጡን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የ 49 ዓመቱ የጋዳፊ ልጅ ዛሬ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በምትገኘው ሴብሃ ከተማ ለፕሬዝዳንትንት ለመወዳደር ዕጩ ሆኖ ሲፈርም ታይቷል ነው የተባለው፡፡
የሊቢያው የቀድሞ መሪ ሙአመር አል ጋዳፊ ልጅ ሰይፍ አል እስላም ጋዳፊ እ.ኤ.አ በ 2011 አባቱ በኔቶ መራሹ ተልዕኮ ከመገደላቸው በፊት ሁነኛ የሀገሪቱ ሰው እንደነበር ይገለጻል፡፡

አል ዐይን

@nidatube
የጦርነቱ መዘዝና ቀጣይ እጣ ፈንታችን

ጦርነቱን የፈለጉት፣ በውጤቱም አትራፊ የሚሆኑ አካላት መኖራቸው የማያጠራጥር ሀቅ ነው። በሌላ በኩል የጦርነቱ ውጤት ምንም ይሁን ምን የሚከስሩ ህዝቦች አሉ። ከነዚህ ቀዳሚው የወሎ ህዝብ ነው። የጦርነቱ አብዘሀኛው የወጪ ደረሰኝ የተቆረጠው ምንም ትርፍ በማያገኘው የወሎ ህዝብ ሰም ነው። በዚህም የህይወት፣ የንብረትና የሰነ ልቦና ኪሳራ ከፍሏል፣ እየከፈለ ይገኛል።

ጦርነቱ በወሎ ህዝብ ላይ ያደረሰውን ኪሳራ ለመረዳት አራት የሚሆኑ ጥናቶችን መመለከት አጋዥ ይሆናል: —

1) የአማራ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ጦርነቱ በመሰረተ ልማት ላይ ያደረሰውን ጉዳት በጥናት አቅርቧል። በጥቅሉ ከ300 ቢሊየን ብር በላይ ግምት ያለው መሰረተ ልማት ወድሟል። ት/ቤቶች፣ ጤና ተቋማት፣ መንገዶች፣ የህዝብ መገልገያዎች ወድመዋል። ይህ ወጪ የህዝቡን የንብረት ኪሳራ ሳይጨምር ነው። የወሎ ህዝብ ወታደሩን ሲቀልብ፣ ነጋዴ ለህልውና ዘመቻ አዋጣ እየተባለ ከየትኛውም አካባቢ በላይ አዋጥቷል። እነዚህ ወጪዎች ሲደመሩ ኪሳራው የከፋ ነው።

2) ሌላኛው ጥናት በሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን የተዘጋጀው ሲሆን ከንፁሀን ሞት፣ መደፈርና መፈናቀል ጋር የተያያዘ ነው። ባለው ምቹ ያልሆነ ተጨባጭ ውስጥ በተደረገው ጥናት በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሀን ህይወታቸውን ተነጥቀዋል፣ በሚሊየኖች ተፈናቅለዋል፣ በመቶ ሺዎች ረሀብ አፋፍ ላይ ናቸው። ገና ካሁኑ በመድሀኒት እጦት ሰለሚሞቱ ወገኖቻችን እየሰማን ነው። የሰነ ልቦና ጉዳቱ በጥናቶች መዳሰስ የሚችልና የሚለካ አይደለም። ምናልባትም ትውልድ ተሻጋሪ ሊሆን ይችላል። የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በመላው ሀገሪቱ ሲከናወን የወሎ ተማሪዎች ጢሻ ለጢሻ እየተንከራተቱ ነበር። የሌሎች አካባቢ ተማሪዎች ወደ ት/ቤት የወሎ ተማሪዎች ወደ ሰደተኛ ካምፖች ተመዋል። የዚህ ሂደት ውጤት ዘመን ተሻጋሪ ነው። ሁኔታዎች በዚሁ ከቀጠሉ ደግሞ ሞት፣ መፈናቀሉና የሰነ ልቦና ጉዳቱ ይከፋል።

3) የፎርቹን ጋዜጣ ለንባብ ያበቃው ሪፖርት በአካባቢው የደረሰውን የእህልና ሰብል ውድመት ይገልፃል። በሪፖርቱ መሰረት 8 ሚሊየን ኩንታል ገደማ እህል በጦርነቱ ምክኒያት በወሎ ብቻ ተከስሯል። ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ የሰብል ኪሳራው ከዚህ ሊከፋ እንደሚችል ሪፖርቱ ይጠቅሳል። በአካባቢው ከባድ ርሀብ ሊከሰት እየተቃረበ ለመሆኑ ከዚህ በላይ አመላካች የለም።

4) የክልሉ አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚሽን ያወጣው አጠቃላይ ክልላዊ ሪፖርት የሰብዐዊና ቁሳዊ ውድመቱ እጅግ የከፋ መሆኑን የሚያመላክት ነው። The reporter በእንግሊዝኛ ዘገባው የክልሉን ፕላን ኮሚሽን ዘገባ ጠቅሶ ባወጣው ሀተታ "ክልሉን ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት ለመመለስ ከሰላሳ እሰከ አርባ" አመት ይፈጃል ሲል አሰነብቧል። በዚሁ ዘገባ ላይ የግብርና ምርት ኪሳራው ብቻ ከ260 ቢሊየን ብር በላይ እንደሆነ የክልሉ ፕላን ኮሚሽን ገልፀዋል።

ለህዝባችን የተሻለው ቢሆናል የቱ ነው?

ጦርነቱን በተመለከት አራት ቢሆናሎች (scenarios) ፊት ለፊታችን ተደቅኗል።

→ አንደኛው ቢሆናል መንግሰት መልሶ ማጥቃት በማድረግ ጦርነቱን ያሸንፋል የሚል ነው። ይህ የቢሆናል ግምት እውን ቢሆን እንኳ በወሎ ህዝብ ላይ የሚያደርሰው ሰብዐዊና ቁሳዊ ቀውስ የትየለሌ ነው። ጦርነቱ ወደ ሙሉ ወሎ በመሰፋፋቱ ህዝቡ hostage የሆነበት ተጨባጭ ተፈጥሯል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ የሚደረግ መልሶ ማጥቃት የሚኖረው Collateral damage ለማሰብ የሚከብድ ነው። በተጨማሪ በአጭር ጊዜ የመሳካት እድሉ አነሰተኛ መሆኑ ከጦርነት የተረፈውን ህዝብ ርሀብ የሚጨርስበት እድል ይፈጥራል።

→ ሁለተኛው የቢሆናል ግምት የህወሀት ሀይሎችና ሌሎች አጋሮቻቸው ጦርነቱ ያሸንፋሉ የሚል ነው። ይህ ቢሆናልም በአጭር ጊዜ የሚሆን ባለመሆኑ ከላይ የተጠቀሰው የህዝቡ መራብን ቀጣይና የተባበሰ ያደርገዋል።

→ ሶስተኛው የቢሆናል መላምት ጦርነቱ የተራዘመና አሸናፊ የሌለው ይሆናል የሚል ነው። ይህ ቢሆናል ዋነኛ የጦርነት ቀጠና ለሆነው ወሎ ተጨማሪ ሞት፣ መፈናቀልና የንብረት መወደም የሚያሰከትል ብሎም እየተባባሰ የመጣውን የረሀብ አደጋን የሚያፋጥን ነው።

→ አራተኛው የቢሆናል መላምት ጦርነቱ ቁሞ ድርድር ይደረጋል የሚል ነው። ይህ የመሆን እድሉ እጅግ አነሰተኛው መላምት ነው። ሁለቱም አካል ለድርድር የሚያሰቀምጧቸው መሰፈርትና አጀንዳ የተራራቀ ነው። ቢሆንም ግን በአንድም ይሁን በሌላ ምክኒያት ወደ ድርድር ከመጡ ቢያንሰ በጊዜያዊነት የረሀብ አደጋ የተደቀነባቸውን ወገኖች መታደገ የሚያስችል አማራጭ ነው። ድርድሩ ይሳካም አይሳካም ጅምሩ ብቻ የሰብዐዊ እርዳታ የሚደርሰበትን ኮሪደር (Humanitarian Coridor) ሰለሚያሰገኝ በምግብና መድሀኒት እጦት ወደ ሞት እየቀረቡ ያሉ ዜጎችን ህይወት ይታደጋል።

ከነዚህ አራት ቢሆናሎች የመጀመሪያዎቹ ሶስቱ ለወርና ሁለት ወር እንኳ ከቀጠሉ ከጥይት የተረፉ ብዙ ወዳጆቻችንን በምግብና መድሀኒት እጦት ያሳጡናል። በርግጥ ለወሎ ህዝብ በዚ ሰዐት ማን መጣ ማን ሄደ ከሚለው በላይ ህልውናውን የሚያቆይበት ዳቦ ማግኘት ያሳሰበዋል። ይህ በአሰቸኳይ ሊሳካ የሚችለው አንድም የሰብዐዊ እርዳታ ኮሪደር ሲመቻች {መንግሰት ወደ ኮምቦልቻ የሰብዐዊ እርዳታ በረራዎችን እፈቅዳለው ቢልም ያሰቀመጠው ግልፅ ጊዜ የለም} አልያም ጦርነቱ በድርድር የሚያልቅበት መንገድ ሲኖር ብቻ ነው።

በርግጥ ይህ ሀሳብ ለብዙዎች ሊጎረብጥ ይችላል። ይህን እረዳዋለሁ። ከስሜታዊነት ወጥተን፣ ከራሳችን ቁጭትና የበቀል ስሜት ይልቅ የህዝባችንን ህልውና ስናሰቀድም ግን ለወሎ ህዝብ ካሉት መጥፎ አማራጮች አነሰተኛው መጥፎ የጦርነቱ በድርድር መጠናቀቅ ነው። ለወራት ጦርነት ጎስመን ለህዝባችን መከራ፣ መንከራተትና ውርደትን እንጂ የፈጠርንለት አንዳች ነገር የለም።

Ye Emmu Lij - የእሙ ልጅ
@nidatube @nidatubebot
ምዝገባ ተጀመረ!
~~~~~~~~~~
ወዶ ዘማች የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተምሳሌታዊ ወጣትን የማፍራት ተልእኮውን ለማሳካት ለአንድ አመት የተለያዩ ወጣት ተኮር ዝግጅቶችን ለማህበረሰባችን አድርሷል፡፡ በአዲሱም ምእራፍ የፕሮግራሙን ማእቀፍ በማስፋት በርካታ ዘርፎች ላይ የሚሰራ የወጣት ፕሮጀክት እንዲሆን ታሳቢ በማድረግ ቋሚ አባላት የሚፈሩበት አንደኛ ዙር ምዝገባ ጀምሯል፡፡ በመሆኑም የእንቅስቃሴው አካል መሆን የሚፈልጉና የፕሮጀክቱን እሴቶች የሚጠብቁ ሁሉ ከታች ባለው ሊንክ መመዝገብ የሚችሉበት ልዩ እድል ተመቻችቷል፡፡ ምዝገባውን በአግባቡ ያካሄዱና (ኢንተርቪውን ጨምሮ) የተለያዩ የማጣሪያ እርከኖችን ያለፉ ውስን ወጣቶች የፕሮጀክቱ ሙሉ አባል ይሆናሉ፡፡

ከታች ያሉትን ሊንኮችን በመጫን መመዝገብ ይቻላል!

ሙሉ ስም
እድሜ
የትምህርት ደረጃ
አባል ለመሆን የፈለጉበት ምክንያት
ልዩ ተሰጥኦ
የአባልነት ግዴታ ለመወጣት ያለዎት ዝግጁነት
አድራሻ (ስልክ ቁጥርና የመኖሪያ አድራሻ)

በቴሌግራም www.tg-me.com/Temsaletawi_Wetat ላይ በውስጥ መስመር መረጃዎችን መላክ፤ አልያም በጉግል ፎርም መሙላት ይቻላል፡፡

https://forms.gle/q2xAXxKWSasjnpiE7
ቻይና በ2030 አሜሪካን በመብለጥ የዓለም ቁጥር አንድ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት እንደምትሆን ተተነበየ።
በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት የዓለም ቁጥር አንድ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ቻይና እንደምትሆን የምጣኔ ሀብት አማካሪ ድርጅቶች አስታወቁ።

አሁን ላይ የዓለም ሁለተኛዋ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት ቻይና በአውሮፓውያኑ 2030 ቁጥር አንድ በመሆን አሜሪካን ልትበልጥ እንደምትችልም ነው የተተነበየው።

የቻይና ኢኮኖሚ በመንግስት ኢንቨስትመንት ላይ ፣በትላልቅ የቴክኖሎጂ ላማትና በሀገር ውስጥ ፍጆታ ላይ ትኩረት በማድረግ የአሜሪካን ቦታ እንደሚረከብም ነው በስፋት እየተገመተ ያለው።

ከብሪታኒያው የኢኮኖሚና ቢዝነስ ምርምር ማዕከል ትንቢያ በተጨማሪም የብድር ኢንሹራንስ ኩባንያ የሆነው ኢዩለር ሄርሜስም ተመሳሳይ ትንቢያ ሰርቷል ተብሏል።

የቤጅንግ እና የዋሸንግተን የንግድ እሰጥ አገባ እና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በማምረቻ ኢንዱስትሪዎች ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩ ተገልጿል።

በአውሮፓውያኑ 2020 የቻይና ጠቅላላ ኢኮኖሚ 15 ነጥብ 92 ትሪሊየን ዶላር እንደሆነ አይ ኤችኤስ የተባለ ኩባንያ ጠቅሷል። በቀጣዩ ዓመት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ18 ቢሊዮን እንደደረሰም ነው የተነገረው።የአሜሪካ ጠቅላላ ኢኮኖሚ ደግሞ 23 ትሪሊዮን ዶላር መሆኑም ተገልጿል።

የቤጅንግ እና የዋሸንግተን ፉክክር ኢኮኖሚያዊ ቢመስልም አሁን አሁን ግን ወታደራዊ መልክ እየያዘ መምጣቱም እየተነገረ ነው። ሀገራቱ አሁን ላይ በምጣኔ ሀብት ቅራኔ ውስጥ መግባታቸው በስፋት እየተወራ ሲሆን መሪዎቹ በጉዳዩ ላይ መወያየታቸው ይታወሳል።

አል ዐይን
ራፍያ አርሻድ
ሙስሊም ሴቶች በቤተሰብ ተፅዕኖ እንጂ በፍላጎታቸው አይደለም ሂጃብ የሚያደርጉት የሚለው የአንዳንድ ማህበረሰብ ህሳቤ የተሳሳተ ነው

እኔ እስኮላር ሺፕ ተመዝግቤ ቃለ መጠይቅ በማደርግበት ቀን ቤተሰቦቼ እንዲህ ነበር ያሉኝ

" በእንግሊዝ የተማሪዎች ምልማላ ቦርድ ለመመረጥ ሂጃብሽ ተፅዕኖ ይፈጥርብሻል በመሆኑም ሂጃብሽን አስቀምጠሽ ምዕራባውያን ሴት መስለሽ ለኢንተርቪው ቅረቢ በአስገዳጅ ሁኔታ ሂጃብሽን በማውለቅሽ ፈጣሪ አያዝንብሽም ነበር ያሉኝ

በሂጃቤ ምክንያት ዕድሉን የማጣው ከሆነ አላዝንም
አለማዊ ምቾቴን ለማስተካከል አኼራዬን አላበላሽም በማለት ሂጃቤን እንዳጠለቅኩ ነበር ወደ ቃለ ምልልስ የሄድኩት

ኢንተርቪውን አለፍኩ ይኸው ከ17 አመታት በኃላ በእንግሊዝ ብቸኛዋ ሂጃብ ለባሽ ሙስሊም የፌደራል ዳኛ በመሆን ተመረጥኩ " ነበር ያለችው

Via bilal zeyad

@nidatube
ሩሲያ ጸረ ኑክሌር ኃይሏ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዘች

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጸረ ኑክሌር ኃይላቸው በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዙ፡፡

ፑቲን ከገቡበት የዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ ከምዕራባዊ ሃገራት ጋር ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ነው ጦሩ በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንዲሆን ያዘዙት፡፡

ዛሬ እሁድ ከከፍተኛ ባለስልጣናቶቻቸው ጋር በነበራቸው ውይይት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል የሆኑ ሃገራት ጠንከር ያለ መግለጫ እያወጡ መሆኑንና ማዕቀቦችን እየጣሉ በመሆኑ ጸረ ኑክሌር ኃይሉ በተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን አዘዋል፡፡

ፑቲን ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ማዕቀብን ጨምሮ ሌሎች እርምጃዎችን በሚወስዱና ጣልቃ በሚገቡ ሃገራት ላይ ጠንከር ያለ የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስዱ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል፡፡

አል ዐይን

@nidatube
Congratulation 🎉🎉🎉
هنيأ لكم
እንኳን ደስ ያለን ፣ እንኳን ደስ ያለዎ

ሼይኻችን ዶ/ር ሙሐመድ ሐሚዲን አብዱሰመድ በታሪክ ምርምርና ጥናት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በከፍተኛ ማዕረግ በማጠናቀቃቸው እንኳን ደስ አለዎ ለማለት እወዳለው

ሼይኽ መሐመድ ሀሚዲን ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትልቅ ተስፋ የሚጣልባቸው ታላቅ አሊም ናቸው::

ለሃገራቸውን ሙስሊሞች ኢስላማዊ እውቀት እንዲስፋፋ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን እየተቀዛቀዘ የመጣውን የቂርዓት ክፍተት ለመሙላት የዳዕዋ ቲቪን በመመስረት ለመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም በየቤቱ ኢስላማዊ ትምህርቶችን በቋሚነት እንዲከታተል ማድረግ ችለዋል::

ከዚህ በበለጠም የኡለሞቻችን በሞት እና በተለያዩ ችግሮች መመናመን አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በመረዳት ተተኪ አሊሞችን እና ዱዓቶችን ለማፍራት ትልቅ ኢስላማዊ ተቋም ለመገንባት ታላቅ ፕሮጀክት ነድፈው ወደ ተግባር በመግባት ለኡማው ከሚያስብ ታላቅ አሊም የሚጠበቅ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ::

ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል ታላላቅ ስራዎችን በእድሜያቸው ለመስራት እየለፉ የሚገኙ እኚህን የመሰሉ ታላቅ አሊም በውስጣችን መገኘታቸው ለሁላችንም ትልቅ እድል ሲሆን በእውቀታቸው ከመጠቀም በተጨማሪ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተጨንቀው ለማሳካት እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፕሮጀክቶቻቸውን ማገዝ ከሁላችን ይጠበቃል::

ሼይኻችን ዶ/ር መሐመድ ሀሚዲን የዶክትሬት ድግሪያቸውን በስኬት በማጠናቀቃቸው በድጋሚ እንኳም ደስ አለዎት እያልኩኝ አላህ ረጅም እድሜ ከጤና ጋር እንዲለግሶት ፣ኡማውም ከእርሶ ብዙ የሚጠቀም ያድርገው ዘንድ መልካም ዱዓዬ ነው

@nidatube
በየመን አንድ ዐይን ያለው ህፃን ተወለደ
ህጻኑ በምድር ላይ በህይወት መቆየት የቻለው ለ7 ሰዓታት ብቻ ነው

አለማችን ብዙ ለማመን የሚከብዱ አስደናቂ ነገሮችን እያስተናገደች ሲሆን፤ ከሁለት ቀናት በፊትም በየመን የተፈጠረው አዲስ ክስተት በርካቶችን እያነጋገረ ነው።

ክስተቱ የተፈጠረው በየመኗ አል-በይዳ ግዛት በምግተኘው የራዳአ ከተማ ሲሆን፤ በተከማዋም በሚገኝ ሆስፒታል አንድ ዐይን ያለው ህፃን መወለዱ ተሰምቷል።

በአል-ሂላል እስፔሻላይዝድ ሜዲካል ሆስፒታል የህክምና ምንጮች እንደገለፁት፤ ህጻኑ ከሁለት ቀናት የተወለደ ሲሆን፤ ከተወለደ ብዙም ሳይቆይ ህይወቱ ማለፉን ጠቁመዋል።

ህፃኑ ወደ ማሞቂያ ክፍል ከተወሰደ ከሰባት ሰዓታት በኋላ ህይወቱ ማለፉን የሆስፒታሉ ምንጮች አስታውቀዋል።

አል ዐይን

@nidatube
ዝነኛው አሊ ቢራ ከእንግዲህ ወደ ዘፈን አልመለስም ፊቴን ወደአላህ አዙሪያለሁ አለ። አላህ ይቀበልህ

"ዳግም ሁለተኛ ወደ ዘፈን አልመለስ አላህ ተውበቴን ይቀበለኝ" ብሏል አሊ ቢራ

አልሀምዱሊላህ ፣ዱኣ አድርጉለት

@nidatube
ለመሸፋፈን ብንለፋ አልሸፈን ያለን ነውር ዛሬም ራሱን ገልጧል

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! የሞቱትን ለጀነት፣ ለቆሰሉት ፈጣን ፈውስ፣ ንብረታቸውን ላጡ የተሻለ ካሳ ከአላህ እማፀናለሁ

መተባበርና መተዛዘን በሚጠበቅባቸው ግዚያትና ቦታዎች ማጥቃት ቀላል የሆነላቸው ድንገተኛ ክስተት ሆኖ አይደለም

በቀላሉ ሊቆም የሚችልን ችግር እንደሰደድ እሳት ያስፋፉት ከአቅም በላይ ሆኖ አይደለም፣

በመቃብር ስፍራ ላይ ያስጀመሩትን ጥቃት ወደመኖሪያ ቤት፣ የንግድ ማእከላትና መሳጂዶች ያዛመቱት ድንገት ከጃቸው ወጥቶ አይደለም

ትንሽ መስለው ሰፊውን ህዝብ የሚያውኩት ክፋታቸው በቁጥራቸው ብቻ የሚገለፅ ሆኖ አይደለም

ብዙዎቹ ነገሮች ሁሌ ለመስጠት እንደምንሞክረው ቀና መላምት፣ ለህዝቦች አብሮነት እንደምንለፋው አልሳካ ያሉት ለመሸፋፈን የምንጥረው ነውር ራሱን ደግሞ ደጋግሞ እየገለጠ ነው።

ይህንን ነውር የጎንደር ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ሊጠየፈው ይገባል። ከውስጡ የበቀሉ የነውረኛ ሥብስቦችን ነቅሎ ለመጣል የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ቢከፍል ለጎንደር ህዝብ የቆየ ሰላማዊነትና ለነገዋ ጎንደር እፎይታ እጅግ የሚገባ አንገብጋቢ ስራ ነው። የአካባቢው ባለስልጣናትና የክልሉ መንግስት አካባቢውን እና ክልሉን እረፍት የለሽ ሁከት ውስጥ እየከተቱ ክልሉን የነውረኞች መሸሸጊያ እንደሆነ የሚሰሩትን ሳያቃልል እና ምንም ምክንያት ሳይደረድር ሊያስቆምና ሊቀጣ ይገባል። አመራሩ የሚወስደው የማያዳግም እርምጃ ለሰላሙ ብቻ ሳይሆን ነውረኞች በአመራሩ ውስጥ ሰርገው አለመግባታቸውን ማስተማመኛ የሚሰጥ ነው።

ነውረኞች የመጨረሻ ግባቸው የህዝባችን ቋንቋ እና ምግባር በነሱ ደረጃ ወርዶ የነሱ ህግ ገዢ እንዲሆን ነው የሚሹት። ትንሽ ቢሆኑም በነውራቸው ብዙውን ሊበክሉ እንደሚችሉ በማመን ወደሜዳቸው ነው ሊጠሩን የሚመኙት፣ እረፍታቸው የሚመነጨው አለመረጋጋት በመፍጠር ስለሆነ ከሰከነ መንፈሳዊነትና ከተረጋጋ አውድ እንድንወጣ ነው የሚለፉት

ለነርሱ የምንደረድረው የይሆናል ምክንያት አልቆብን ግልፁን መናገር ብንጀምርም ያስነሱትን የነውር መንገድ በጎንደርም ሆነ በተቀረው አካባቢ እንዲሰፍን ግን ፈፅሞ አንፈቅድላቸውም። የተቀረውን አካባቢ ሰላም እንዲጠበቅ እየሰራን እነርሱን ነቅሎ ለመጣል ከጎንደር ህዝብና የሀገር ሽማግሌዎች፣ ከአካባቢው አመራሮች፣ ከክልሉና ከፌዴራል መንግስት ጋር በትብብር እንሰራለን። እንደምናሸንፋቸውም ሙሉ እምነት አለን!

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ
ሚያዝያ 18/2014
በጎንደር ሙሰሊም ላይ ያነጣጠረ ግደያ የሁለት ሃይማኖቶች ግጭት ለማስመሰል የምትጋጋጡ ሚዲያዎች ተቆጠቡ ፣ ጥቃቱ ሙሰሊም ላይ ብቻ የተደረገ የአንድ ወገን ጥቃት ነው።

share ...share...share
🚩 የጎንደር አሥተዳደር መስጊድ ላይ ድራማ መሥራትን መርጧል!
—————————
.ኢስሀቅ እሸቱ

የጎንደር አሥተዳደር በታጠቁ አሸባሪዎች ደሙ ሲፈስ፣ አጥንቱ ሲከሰከስ የቆየውን የጎንደር ሙስሊም ከለላ በመስጠት ፈንታ ድራማ ይሠራበት ጀምሯል። ጌሾ ሠፈር አቅራቢያ የሚገኘውና በ3 አቅጣጫ በጥይት ሲደበደብ የከረመው መስጊድ ላይ አዲስ ❝ጂሐዳዊ ሐረካት❞ መሰል ድራማ መሥራትን መርጧል።
.
በትናንትናው ዕለት በመስጊዱ ጀርባ ባሉ ቤቶች በኩል ገጀራዎችን እና መሣሪያዎችን ከውጭ በማስገባት ❝መስጊድ ውስጥ ተገኘ❞ በሚል የሐሰት ዶኩመንተሪ ሲቀርጹ መዋላቸውን ማወቅ ተችሏል። ለድማራው ግብዓት እንዲሆንም የሃይማኖት አባቶችን በማምጣት ❝ሙስሊሙ ጥፋቱን አምኖ ቤተ ክርስትያንን ይቅርታ ይጠይቅና ሠላም ይውረድ ይህንን ካደረጋችሁ የዒድ ሶላት እንድትሰግዱ ይፈቀድላችኋል❞ የሚል እጅግ አሳፋሪ ጥያቄ አቅርበዋል።
.
መንግሥት ❝በቁጥጥር ሥር ውለዋል❞ ካላቸው 380 ሰዎች አብዛኛዎቹ ሙስሊሞች መሆናቸውንም ማወቅ የተቻለ ሲሆን ልክ በሞጣው ጥቃት እንዳደረጉት ሙስሊሙን ራሱ ተጠያቂ ለማድረጎ ቆርጠው እየሠሩ ይገኛሉ።
.
ይህንን ተበዳይን በዳይ አስመስሎ የማቅረብ ነውረኛ ፕሮፓጋንዳ መከላከል የምንችለው እኛው ነን! ሁላችንም ኢ-ሰብዓዊውን በደል በማጋለጥ ከተበዳይ ጎን እንቁም! ሐሽታጎቹን ተጠቅመን እንጻፍ! በዝምታ የምናሣልፋት እያንዳንዷ ሰከንድ በጎንደር ሙስሊሞች አንገት ሸምቀቆው እንዲጠብቅ እንደምታደርግ አንዘንጋ! ሼር በማድረግና በራሳችን በመጻፍ እንረባረብ!
.
#የጎንደርጭፍጨፋ #GondarMassacre #ደባርቅ #ሙስሊምጠልነት #ፋኖ
2024/05/14 14:07:17
Back to Top
HTML Embed Code: