Telegram Web Link
(⓮)من أصول عقيدة أهل السنة
🎙በኑረዲን አል-ዓረብ
◎አቂደቱ አህሊ-ሱና◎

     👉ክፍል =⓮

«ሶሀቦችን መውደድ»

🎙በኑረዲን አል-ዓረብ

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍25
➥ንግግር እንምረጥ እባካችሁ⁉️

.....ቃላት ሰው ያጠፋል....

በቃላታችን ቀስት ስንቱ እንደተወጋ፡
ስንቱ እንደታመመ ተጋልጦ ለአደጋ፡
ከሰላም ኑሮው ላይ ስንቱ እንደተናጋ፡

አይገባንም እንጂ ብዙ ግፍ ሰርተናል፡
ማስታመም ስንችል ጨቅጭቀን ገድለናል፡
ዛሬም አልተውነውም ግን ምን ይሻለናል⁉️

ምላስ እንደሆነ ከነገር አይቦዝን፡
በምሰማው ሁሉ አለሁ እኔም ሳዝን፡
ሳስብ ሳሰላስል ስሰፍር ስመዝን፡

ችግርን በተስፋ ጎራደን በጋሻ፡
ሀዘንን በምክር ፅናትን በዋሻ፡
ህመምን በክኒን መርዝን በማርከሻ፡

ስመክት ከርሜ ሰበረኝ ንግግር፡
ሀሜት ጆሮን አልፎ በቅፅበት ሽግግር፡
እስከ ነፍስ ይጓዛል ባይኖረውም እግር፡

....አወ...

እግር ባይኖረውም ሁሉን ነገር ያልፋል፡
ደግሞ እንደ ፈንጅ ነው እያደር ይሰፋል፡
ከተቀጣጠለ ሁሉንም ይጠልፋል፡
እንደ ጂረትም ነው ውስጥ ላይ ይጎርፋል፡
እንጠንቀቅ እንጂ ቃላት ሰው ያጠፋል፡

....ኑረዲን አል-ዓረብ....

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍49
«ክፉ ቃል ክፉ ነው»
ኑረዲን አል-ዓረብ
ለቃላታችን እንጠንቀቅ‼️

«ቃላት ሰው ያጠፋል»

🎙በኑረዲን አል-ዓረብ
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍32
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
Photo
የኦሮሚያ ክልል መጂሊስ ስራውስ⁉️
--------------------------
በእምነታችንና በእምነት ቦታወቻችን ከሚደርሰው በደልና ግፍ በላይ እኛ በዘር ቅርቃር ውስጥ ገብተን አማራ ቢሆን ኖሮ ኦሮሚያ ቢሆን ኖሮ እያልን መሸራኮታችን በኢስላም ዘረኝነት የተወገዘ ከመሆኑም በላይ ለጠላቶቻችን ትልቅ እድል እንደሚፈጥርላቸው አታውቁምን⁉️

.....ዘረኝነት የሚባል ወጥመድ ጠላቶች አዘጋጅተው ሙስሊሙን ከዚህ ወጥመድ ውስጥ ካስገቡት በኋላ ሙስሊሙ በዘረኝነት ልክፍት ተለክፎ መርጦ ባልተፈጠረበት ዘሩ ከሙስሊም ወገኑ ጋር ሲናከስና ሲጠላላ...‼️

እነሱ እንደ ኳስ እየተቀባበሉ አንዴ #በአማራ ሌላ ጊዜ ደግሞ #በኦሮሚያ እያፈራረቁ እቅዳቸውን በሚገባ ይፈፅሙብናል።

ሙስሊሙም ገና የዘረኝነት ወጥመዱ ስላለቀቀው  አማራ ክልል መስጂዱ ሲደፈርና ኢማሜው ሲረሸን ከመስጂዱ መደፈር ከኢማሜው መረ*ሸን ይልቅ ዘሩን አስቀድሞ #ስስልጤ.....#ኦሮሞ...እያለ ያስተባብላል።

ይህን ያስተዋሉት ጠላቶቻችንም ተመቻቸውና ኦሮሚያ ላይም ድንገት ብድግ ብለው መስጂዱን በ➌ ቀን ውስጥ አፍርሱ ምንም አታመጡም አይነት #ትዕዛዝ ይሰጣሉ።

...እውነታቸውን ነው በዘረኝነት ሱስ የተያዘ የእምነቱ መደፈር የማይቆረቁረው ትውልድ ምን ያመጣል⁉️

ባለፉት ጥቂት አመታት መስጅድ ክብሩ ተገፎ በጅምላ የፈረሰበት ክልል ቢኖር #ኦሮሚያ ክልል ዋነኛው ነው።
ከፍተኛ የሙስሊም ቁጥር ባለው በዚህ ክልል መስጂዶችን እንደ ልብ ለማፍረስ ኢምንት ያክል ህዝቡን አላፈሩትም..ለምን⁉️

...የክልሉ መጅሊስ ደግሞ የበለጠ ያሳዝናል። ከጥቂት የተቋሙ አመራሮች ውጭ በተደጋጋሚ ከነሱ በሚሰማው ሽንገላ በመታለል ጠንካራ ተቃውሞ እንኳን እንደ ተቋም ሲያደርግ አይስተዋልም።
....እመኑኝ #ኢስላም አለም ቢዘምትበት አይጠፋም ግን እንደዚህ የምትሽለጠለጡና የምትጉደፈደፉ ሰወች ካላችሁ ነገ አሏህም ፊት ከታሪክም ፊት እንፋረዳችኋለን።

አማራ ክልል በጽንፈኞች ለደረሱ የሙስሊም በደሎች፣ ትግራይ ክልል በአክሱም ተማሪዎች ላይ ለደረሰው እንግልት፣ በጉራጌ ዞን በጉንችሬ በደረሰው የመብት ጥሰት ሁሉ የአካባቢው መጅሊሶች በቻሉት ልክ ጠንክረው ሲታገሉ እንጅ አመራሩ ጋር በመለሳለስ ጉዳዩን ችላ ሲሉ አላስተዋልንም።

ውጤቱ ምንም ይሁን ምን የተቀያየሩ መሪዎች በዚህ ረገድ የሙስሊሙ ህመም ሲጋባባቸው አስተውለናል።

➥የኦሮሚያ መጅሊስ ለሚፈርሱ ቦታዎች ልመና ከሚመስል ተደጋጋሚ ተማጽኖ በዘለለ የክልሉን ሙስሊም መብት ለማስከበር የሄደበት ርቀት ግን #የተልፈሰፈሰ እንጂ ጠንካራ የሚባል አይደለም።

ምን አይነት ሀላፊነት ጫንቃቸው ላይ እንዳለ እንኳን ሳያስተውሉና ሳያስተነትኑት #የዞን_መጂሊስ_አመራሩ ጥቂት ጥረት እንኳን ሳያደርግ ለበላዩ "ከአቅሜ በላይ ነው" የሚል ደብዳቤ ለመጻፍ ሲሮጥና ሲሽቀዳደም ይስተዋላል።

➥የኦሮሚያ ክልል መጅሊስም ቢሆን በተለይ ሸገር ላይ ሲፈርስ ጠብቆ ሌላ ቦታ ትክ ከመቀበል የዘለለ መስጅዱን ላለማስፈረስ ይህ ነው የሚባል ህጋዊ አካሔድ ሲሄድና ሲታገል አይታይም።

ይህ ባለፉት አመታት ያስተዋልነው እውነታ ነው። ይህንን ደካማነት የሚያውቁ በአስተዳደሩ ውስጥ ያሉ መስጅድ ጠሎች እያረፉ እየመጡ ማፍረሳቸውን ቀጥለዋል።

#የኮዬ_ፈጬና #ቱሉዲምቱ አካባቢ ከስፋቱ አንጻር ከፍተኛ የመስጅድ እጥረት ያለበት እንደመሆኑ ተጨማሪ መስጅድ የሚሰጥበት እንጅ ያሉት የሚፈርሱበት ቦታ አልነበረም።

ይህ እየሆነ ያለው የኦሮሚያ ክልል መጂሊስ በሚያሳየው ለዘብተኝነቴና ግደለሽነት ነው።
......ግን ምን ዋጋ አለው፣ እንደፈለጉ ቢያፈርሱ ማን ይጠይቃቸዋል⁉️
ማንስ "ለምን" ብሎ ይታገላቸዋል⁉️

በጣም ያሳፍራል⁉️
እጂግ በጣም ያሳዝናል⁉️

.....ኑረዲን አል_ዓረብ

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍35
በ➌ቀን ውስጥ ይፍረስ የተባለው መስጂድ ይህ ነው

እስኪ ምን ተሰማችሁ
እስከመቼስ ነው በዚህ መልኩ የምንቀጥለው⁉️
👍57
«ለመስጂዳችን ዘብ»

በኦሮሚያ ሁሌ መስጂድን ሲያፈርሱ፡
ከመኖሪያ ቀዬ ሙስሊሞች ሲፈልሱ፡
በጂምላ ስንሞት በኦሮሚያ ክልል፡
ግፍን ስንቋደስ ጠፍቶ የሚያስጠልል፡

...አልበቃቸው ብሎ ያፈረሱት ቦታ፡
ያሁሉ መከራ መስሏቸው ስጦታ፡
አሁንም ድጋሜ ከተዘጋጁልን፡
እስኪ መጂሊሶቹ መግለጫ ያውጡልን⁉️

በአማራ ኢማሜው በመስጂድ ሲረ*ሸን፡
በኢስላም ጥላቻ #ፋኖ ሲረብሸን፡
ውስጣችን ሲታወክ ስቃይ ሲያቀረሸን፡
ግፍ ሞልቶ ፈሶብን እያንገሸገሸን፡
አንድ እንሁን እንጂ ለስንቱ እንሸንሸን⁉️

የሙስሊሞች ብቻ ሲመረጥ ሰፈሩ፡
ዘወትር ከመኖር እየተደፈሩ፡
ምናል ብንሰዋ ቢቀለን አፈሩ፡

ነገ እንዳይጠይቀን ሀያሉ አምላካችን፡
ለመስጂዱ ክብር እንጩህ ሁላችን፡
በታሪክ ገፅ ላይ እንዳንተዛዘብ፡
ሳይፈርስ አለን እንበል ለመስጂዳችን ዘብ፡

.....ኑር....

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍51
ልጆችን ከሳዑድ ወደ ኢትዮ

ከሳዑድ አረቢያ ወደ ኢትዮጲያ ህፃናት ይዞ መግባት ተፈቅዷል።
በሳዑዲ የኢትዮጲያ ኢንባሲ በዛሬው ለት እንዳስተላለፈው ከሆነ የሳዑድ ኢሜግሬሽን ለብዙ ጊዜ አግደውት የነበረውን የህፃናት የጉዞ ክልከላ እንደተነሳና እንደተፈቀደ ገልፀው...ልጆቻቸውን መውሰድ የሚፈልጉ ሰወች ከወዲሁ ቅድመ ሁኔታውን አሟልተው ፕሮሰስ እንድጀምሩ ሲል አብስሯል።

http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍74
➥ እጂግ ጥሩ ጂምር ነው በርቱ እንበርታ

አል-ሒዳያ ኢስላሚክ የዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት

ጆሃንስበርጎች ዝግጁ‼️
==============

....ደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ እና አካባቢው የምትገኙ ወንድም እህቶች በሙሉ

በጉራጌ ዞን ጉመር በታሪካዊ ቦታ እየተገነባ የሚገኘው #አል-ሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ እነሆ ነገ እሮብ October 15 ከመግሪብ በኋላ በጆሃንስበርግ ከተማ #በኢሜጅ_ላይፍ_ስታይል አዳራሽ

ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ እና የዳዕዋ ፕሮግራም ስላለ በጆበርግ እና አካባቢው ነዋሪ የሆናችሁ ወንድም እህቶች በሰዓቱ ተገኝታችሁ  ኩ'ፍርን በዒልም ለመታገል እና ኢስላምን የሚኖር ትውልድ ለመፍጠር በተቋቋመው በዚህ ታላቅ #ኢስላማዊ_ዩኒቨርሲቲ ፕሮጀክት አሻራችሁን እንድታኖሩ ተጋብዛችኋል

በደሉንም ግፉንም ጭቆናውንም ችለን እየጠነከርን መጓዝ በአሏህ እገዛ #አይበገሬነትና አሸናፊነት መለያችን ሆኖ ይቀጥል ዘንድ ሁላችንም በጋራ እንትጋ እላለሁ።
👍34
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
በ➌ቀን ውስጥ ይፍረስ የተባለው መስጂድ ይህ ነው እስኪ ምን ተሰማችሁ እስከመቼስ ነው በዚህ መልኩ የምንቀጥለው⁉️
«ለጊዜው አናፈርስባችሁም ብለዋል‼️

በሶስት ቀናት እናፈርሳለን ካሉ በኋላ
ህዝቡ ቁጣውን ሲገልፅ ለጊዜው ባለበት ይቆይ ማለት አዘናግቶ ለማፍረስ ታቅዷል ማለት ነው ልብ በሉ ⁉️

እንደዚህ አይነት የንቀትና የፌዝ የስላቅና የኩራት ውሳኔስ #ከመንግስት አካል ይጠበቃል ወይ⁉️

«የአመራር እቅዳችሁና የአፈፃፀም ታክቲካችሁ እንደት ነው..እ!?

ግራ ግብት የሚለኝ ነገር «ለጊዜው አናፈርሰውም። ማለት⁉️»
እና ቀን ጠብቃችሁ ማታ በጨለማ ተደብቃችሁ ልታፈርሱት ነው⁉️

የህዝቡ ቁጣና ዝምታ የስሜት ከፍታና ዝቅታ እየተለካ እነርሱ እንዳሻቸው ON/OFF የሚያደርጉን መሆን የለብንም።

አያችሁ ጊዜያዊ ጫጫታ እንደሆነ ተረድተዋል‼️
አስተውሉ ለተወሰነ ቀን ጩኸን ፀጥ እንደምንል ገምተዋል‼️

በመሆኑም እኛ ሙስሊሞች ቋሚና ዘላቂ መፍትሄ እንሻለን ብለን ወጥ አቋም መያዝ አለብን።

እስከ መቼ ድረስ ስለ መስጅድ ፈረሳ፣ ሒጃብና ሶላት እያወራን እንኖራለን⁉️ እስከዛሬ ያፈረሱትንም ይገንቡ፣
ወደፊትም ማፍረሳቸውን ያቁሙ የሚል መርህ ያለውና የፀና አቋም አስቀምጠን እንታገላቸው

«ለጊዜው አናፈርሰውም»
ማለትስ ምን ይሆን በመንግስተኛ ቋንቋ..እንዴ..‼️


ቀልዱን ተውትና ካሁን በኋላ የማይፈርስ መሆኑን ህጋዊ ማረጋገጫ ማግኘት ያስፈልጋል !

ለመሆኑ እስከ ዛሬ ያፈረሳችሁትንስ ምን ሰራችሁበት⁉️

ሸገር በሚባል ከተማ ውስጥ ስንት መስጂድ ነው የፈረሰው ቦታውን ምን ሰራችሁበት⁉️
አልበዛም ወይ⁉️
ለልማት ብላችሁ አፍርሳችሁ ባዶ ሜዳ ያደረጋችሁት እንዲሁም ሌላም ነገር የገነባችሁበት ብዙ ነገሮች አሉ።
ትክክል አይደለም ‼️

ይህ አይነቱ ነገር ሀገር ያፈርሳልና እባካችሁ‼️

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍37
የሸገር ሲቲ

ያለምንም ማሽሞንሞንና ማንቆለጳጰስ እየተፈፀመ ያለው ግፍና መከራ የሙስሊሙን አቅም መፈታተንና ተከታታይ ትንኮሳ ጊዜ እየጠበቀ መስጂድ የማፍረስ ዘመቻ እዚህ ላይ በቃህ ተብሎ ሊያከትም ይገባል።

ከዚህም ባሻገር በምትኩ እስካሁን በማናለብኝነትና በዘግናኝ ሁኔታ ያፈረሳቸውን መስጂዶች በጥራት እንዲገነባ መገደድ አለበት።

ለዚህ ደግሙ ከመጂሊስ አመራሮች የጠነከረ አቋም ከመያዝ ባሻገር የህዝበ-ሙስሊሙ ያላሰለሰ ጥረት ሊኖር ይገባል ባይ ነኝ ።

በታቀደና በተጠና ሴራ ነው መከራ እያየን ያለነው ወገን እንንቃ እሽ⁉️

http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍61
🔻ምዝገባ ላይ ነን🔺

መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዓሪ የቁርኣን ሒፍዝ ማዕከል ለ2018 ዓ.ል  የትምህርት ዘመን በ አዳሪና  በተመላላሽ መርኃግብር  ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ  በምዝገባ ላይ ይገኛል።

የአዳሪ መርኃግብር
ጾታ፡  ለሁለቱም (ለወንድም ለሴትም)
እድሜ: ለወንድ ከ10 - 25 ዓመት
              ለሴት  ከ 10 አመት በላይ

የሚሰጥበት አድራሻ: አንፎ ድልድይ በሚገኘው ዋናው ማዕከል።

የተመላላሽ መርኃግብር፡
ፆታ: ለሁለቱም
እድሜ: ከ 4 አመት በላይ ለሁሉም የእድሜ ክልል 
የሚሰጥበት አድራሻም: በሁሉም ቅርንጫፎች

ለመመዝገብና ለበለጠ መረጃ፡

➡️አንፎ ቅርጫፍ፡
+251913939993 /+251928844757
➡️ቦሌ ቅርንጫፍ፡
+251911119260 /+251930547776

✈️የቴሌግራም አድራሻ
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
👍10
«➏»هدية المسلم الجديد"
🎙አቡ-ፋሩቅ حفظه الله
هدية المسلم الجديد

👉ክፍል=➏

«የመጨረሻው ደርስ ነው።»

🎙በኑረዲን አል-ዓረብ

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍19
ከውስጤ አውጥቼ ልናገር የምፈልገው ብዙ ነገር አለኝ ግን .....I choose to remain silent in my pain so as not to cause more suffering to my humble people.

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍64
ናፍቀኸኝ ነበር⁉️

አባቴን
ምን ላድርግልህ አልኩት⁉️
ልጄ
ድምፅህ አይራቀኝ
እየጠፋህ አታስጨንቀኝ
......አለኝ...አባትነት ...ከባድ ሚዛን ነው።

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍204
«ለአባቴ»

ልጅ የመሆን የክብር ማማ አባ የምልህ ኩራቴ፡
በድቅድቅ ጨለማ መሐል የምትፈነጥቅ መብራቴ፡
በጥም በረሃብ ስቀጣ የምታጠግበኝ ራቴ፡
በቃላት የማትገለፅ ሰንደቄ ውብ ቁጥራቴ፡

አንተ ነህ የኔ ማንነት፤
ድምፅህ ነው ደካማ ጎኔ፡
ልጄ ብለህ ስትጠራኝ፤
እንባ ያቀራል አይኔ፡
አባቴ አንተኮ ማለት፤
ውብ አርማዬ ነህ ለኔ፡

በእልፍ ቦታ ተከፍለህ
በእኔ ሐሣብ የጭንቀት ግዞት፡
ነገዬን ልቦናህ አስልቶ፤
መንፈስህ ኒሻኔን ይዞት፡
መቀመቅ ወርደህ በእሳት፤
ነፍስህን ጠባሳ ወርሶት
አሁንም እንባህ ለእኔ ነው ፥
ችግሬ ሆድክን አብሶት፡

ጋሬጣ አሜኬላዬ፤
በእግሮችህ ተሰንቅረዋል፡
ጫንቃና ብርቱ ክንዶችህ፤
በሸክሜ እጅግ ዝለዋል፡
ዋጋህን በስሌት ተመን፤
አስቤ አልደርስበትም፡
አንድ ነብስ በቂው አይደለም፤
ሦስት አራት አያንስበትም፡

አባቴ....

ለካስ አባት
በእናት አንጀት ላይ
ኮስታራ ገፅ አሣይቶ፡
የጋተውን መራራ ሐሞት፤
በሳቅ ግርዶሹ አቆይቶ፡
በሰው ፊት ጀነን ብሎ፤
ተቆጥቶ ገልምጦ ዝቶ፡
የብቻውን የዕንባ ያፈሳል፤
ለቤተሰብ ለልጅ አብዝቶ፡

አባቴ

ኑሮን በሀይሉ እየገፋ መከራን በክንዱ ትግል፡
ልጅ ለማሳደግ ሲታትር ስቃይን ያለ ግልግል፡
ብቻውን በፅናት ቆሞ የገነባውን ብተሰብ፡
ምን ካሣ ይመጥነዋል ምን ይበቃዋል ቢታሰብ፡

....አባቴ....

አውላላ በረሃ መሐል፤
ለምለም መስክ የምታሳየኝ፡
ጢንጫ ካልኩት ህይወቴ ላይ፡
ወዛም ምንጭ የምታቆየኝ።

የፈገግታ የደስታ ሱሴ፤
የእዳ መዝገቤ ሽረት፡
ድክመቴን የምረሳብህ፤
የህይወት ዘመኔ ጂረት፡
አይኖችህ ሳይከደኑ፤
ትንፋሽህ በርዶ ሳይጠፋ፡
ለልጅህ ዋጋ የከፈልክ፤
በፍፁም እንዳልከፋ፡

አባቴ መርሀባ በለኝ፤
ጉልበትህ ሳይከዳህ በፊት፡
በአስታጠቀከኝ የወኔ ዝናር፤
ሽንፈትን ላድርገው ወንፊት፡
መልካም ያልሁትን ሁሉ፤
ላቅርበው አባቴ አንተ ፊት።

አንተን አዝየህ ልዙር
በየትም እንዳታመልጠኝ፡
አውቃለሁ አይንህን ሳየው
ጀግንነት እንደሚሰጠኝ
የኔ አባት አብሬህ ልሁን፤
በአንድ ቃል ፈቃድክን ስጠኝ⁉️

አሁን ላይ የመድረሴ ምንጭ ፤
ከዚያ ከዚህ መውጣት መግባቴ፡
የውበት የግርማዬ አክሊል፤
መልኬ ነህ ውብ ደም ግባቴ፡
የሁሉን ቦታ የሸፈንክ፤
አንተ ነህ ንጉሴ አባቴ.....፡

ከልጅህ ኑረዲን አል-ዓረብ
እናትም አባትም ለሆንከኝ አሏህ ይጠብቅህ ጋሻዬ

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍100
➥እስኪ በትዝታ በሀር እንዋኝ...!?

ልጅነቴ ትዝ ..ሲለኝ..ትውስታዬ

እዚህ ጋር ደግሞ አማዬ ወጣ ስትል
ደረቅ እንጀራ ወይም ዳቦ ነገር
ቆርሰን የምናጣጥማት ነገርስ...እ...

........የሚገርመኝ ደግሞ ጥፍጥናው በወጥ ስንበላ እንኳን እንደዛ አይጣፍጥም።

«በዛው ልክ እንዳታየን ፍጥነታችን»

እስኪ እንደዚህ ያደገ እጁን ያውጣ‼️

መዋሸት አይቻልም ...እያንዳንድሽን አውቃችኋለሁ...ሁልሽም ሰርቀሻል።

ያኔ በልጅነት ውብ ነበረ ሞሰብ
ሁሉም ቤት የሚገኝ ሁሉም ጋ እሚታሰብ፡
መለያችን ነበር እንደ ህብረተሰብ፡

....ኑር..በትዝታ አለም...
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍232
يا من أفزعكم غلاء الذهب ، هل أفزعكم قرب الأجل؟ الدنيا ممرّ، والآخرة مقرّ ، فاعقلوا قبل أن يُغلق الباب!"
👍25
2025/10/20 07:12:19
Back to Top
HTML Embed Code: