Telegram Web Link
ጀግናዬ

ለጉዞ ስትዘጋጅ ከቤት ወጥቶ ከማያውቅ ሰው ምክር አትቀበል እሽ⁉️

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍72
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
👉ፍፁማዊነት‼️

«ፌፁም ቄስ ፍፁም ሸህ»

መጀመሪያ ሀሳቡን በደንብ ተረዱት እሽ

http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍78
㈀ ㈀㄀ⴀ 㜀ⴀ 㐀开 㜀✀㄀㐀✀㌀㠀✀
匀甀瀀攀爀 嘀漀椀挀攀 刀攀挀漀爀搀攀爀
👉ኢብኑ ተይምያን ለምን ይጠሉታል⁉️

የጥመት ሰወች በአንድ ድምፅ
ኢብኑ ተይምያን የሚጠሉት ለምንድን ነው!?


#ክርስቲያኖች
#አይሁዶች
#መላሒዳወች
#ሱፍዮች
#ጀህምዮች
#አሻኢራወች_የሚያከፍሩት

እነዚህ ሁሉ ጠማሞች #ኢብኑ_ተይምያን የሚጠሉት በፈተና ጊዜ ታግሶ ሀቅ ላይ ስለቆመና ለሁላቸውም የጥመት መንገድ አጥጋቢ መልስ ስለሰጣቸው ነው።

አሏህ ይዘንላቸው ታላቅ የኢስላም ጠበቃ፡
በጥበብ የተካኑ በእውቀትም የነቃ፡
ታጋይ ነበር ለውሒድ ሱና፡
ለነፍሱ እማይሳሳ ጀግና፡

አሏህ በጀነት ይሰብስበን አሚን

https://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
https://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍67
ሐውልት ⁉️

ኸረ አቦ እባካችሁ ግፍ አታሳዩብን፡
ያልተቋጨ ገና ብዙ ጉድ አለብን፡
የቀብሩ ይበቃል ሀውልቱ ይቅርብን፡

.....ኸረ ተው ...!!

ተመልከት ይህን ጉድ አስተውል ቆረጣ፡
ተይዟል በዛ ቤት ዲዛይን መረጣ፡
ይበርዳል ያልነው ጉድ እየባሰ መጣ‼️

.....ያ አሏህ....

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍105
በጣም አስቸኳይ ማስታወቂያ‼️
አደራም ጭምር

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ በሚከተሉት መስፈርቶች ኡስታዝ መቅጠር ይፈልጋል።
1.በዐቂዳውም በመንሐጁም በሰለፎች አካሂያድ የሆነ
2.ስለመንሐጅ መርሆዎች እና ፊርቃዎች ጠንቅቆ የሚያውቅ
3.ጥሩ ስነ ምግባር ያለው ተማሪዎችን መያዝ የሚችል ታጋሽ
4.ከዘረኝነት የፀዳ

ደመወዝ በስምምነት
ፆታ፡ወንድ
ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርቶች የሚያሟላ ኡስታዝ በሚከተሉት የተማሪ ተወካይ እና ኮሚቴ ስልኮች በመደወል ማናገር ይችላሉ።

🔏ስልክ
🖌️ 0918742346
ዐብዱረሽድ ሙሐመድ (የጀመዐው ዋና ተወካይ)
🖌️0911962099  ዶ/ር ሙደሲር(ዋና ኮሚቴ)

https://www.tg-me.com/WSU_Muslim1SelefyStudents
👍30
....አክሱም....!?

«ምቀኝነትና ጥላቻ በዚህ ልክ...»

ክርስቲያኖች የእምነታቸው መገለጫ ትዝ የሚላቸው ሙስሊሞች ለምን ብለው ጥያቄ ሲያነሱ #ሙስሊሞችን ከመጥላትና ከምቀኝነት የተነሳ እንጂ ለሀይማኖታቸው አስበው አይደለም።

«ይህ አይነቱ ምቀኝነት ደግሞ እምነታችሁን ጥያቄ ውስጥ ከመክተትና ተከታያችሁ እንድጠረጥራችሁ ከማድረግ የዘለለ ጥቅም የለውም።

ይህ አይነቱ ፉክክር ምቀኝነትና የሙስሊም ጥላቻ ራሳችሁን #ክርስቲያኖቹን ነው ትዝብት ላይ የሚጥለው እና እየታሰበበት።

የአክሱም ተማሪዎች ላነሱት የሒጃብ የመብት ጥያቄ የሚመለከተው አካል መልስ ከመስጠት ይልቅ ክርስቲያን ተማሪዎች ነጠለ በማስለበስ የሀይማኖት ተቃርኖ ሊያስመስለው እየታገለ ነው።

ሙስሊም ተማሪዎች ኃይማኖታቸው ያዘዛቸውን የመብት ጥያቄ ከማንሳት የዘለለ ሌላውን አካል አጀንዳ ያደረገ የፉክክር ትግል አልጀመሩም።

ይህ አካሔድ ባለፉት አመታት ሁሉ መሠል ጥያቄ ሲነሳ ጥያቄውን ላለመመለስ በአስተዳደር ሰዎች ይፈጠር የነበረ ደካማ #ቁማር ነው። ከዚህ በፊት በጉንችሬ ተሞክሮ አላዛለቀም፣ አሁን ደግሞ አክሱም ላይ ጀምረውታል። ከመነሻውም ሳይለብሱት የነበረውን ልብስ ዛሬ ሌላውን ለማስከልከል መልበስም በመሠረቱ ለኃይማኖት ያለን ቀናኢነት የሚያሳይ አይደለም።

ተማሪዎቹ በዘላቂነት ነጠላውን የመልበስ ፍላጎቱ ካላቸው እስካሁን መዘግየትም አልነበረባቸውም። አሁንም ቢሆን ከቀናት ፉክክር በዘለለ ታግለው ቢያሳኩትና እድሜ ልካቸውን ቢለብሱት መብታቸው ነው። ሒጃብ ሲጠየቅ ነጠላው ትዝ የሚላቸው ከሆነ ግን ነጠላውን ከተራ ፉክክር የዘለለ ልባቸው ላይ ቦታ ያልሰጡት ልብስ መሆኑን በተግባራቸው መስክረዋል ማለት ነው..!

.....ኑረዲን
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍59
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
«ማነው ግን ተክፊሩ»

የኢስላምን ጠላት #የአይሁዶች ወዳጅ ፡
የክርስቲያን ታማኝ ሙስሊሙን አሳዳጅ፡
የሁሉም ጥመቶች ንፁህ ቃል አቀባይ፡
የሽርክ ሙሒቦች ሐቅን አስተባባይ፡

መጁሳውን ሳይቀር ወደው የተጠጉ፡
ሙስሊሙን ነጥለው በውስጥ የሚወጉ፡
መረጃ ሲሰጡ የሚበረግጉ፡
አህባሽ እንደዚህ ነው በቃ ተረጋጉ፡

እስኪ ተመልከቱ ይህንን ዘመቻ፡
ክፋትና በደል የግ*ድያ ዛቻ፡
ከአህባሽ ነው የወጣው ግፍና ጥላቻ፡

ለነሱ ሀላል ነው ዘወትር ጫት መቃም፡
የተውሒድ ሰወች ግን ኒካሁም አይበቃም!?

ግፍ እየፈረዱ ወጥተው ከመስመሩ፡
ከሀዲያን ጋር ሆነው ሴራ እየቀመሩ፡
እስኪ ይፈተሹ እስኪ ይመርመሩ!?

ማነው እንደነሱ ጥላቻ ያወጀ፡
ማን አለ እንደ አህባሾች ሐቅን የፈረጀ፡
ማነው ሙስሊሞችን ደፍሮ ያከፈረው!?
ማነው ያለ ደሊል ግፍ የተናገረው⁉️
👍65
የዛ ሰፈር ሰወች
እስኪ የእውነት ሙስሊሙን የምትወዱ ከሆነና እንደምትሉት ለሙስሊሞች ፍቅር ክብር ካላችሁ አክሱም ላይ ሒጃብ ተከልክሏል፣
መስጅድም የለም፣
ይባስ ብለው #አክሱምን ለቃችሁ ውጡ እየተባሉ እየተሳደዱና እየታደኑ ነው።

… እስኪ የምትሉት እውነት ከሆነ ይህን ነገር ተማክራችሁ ተወያይታችሁ ፍቀዱና ውደታችሁን በተግባር አሳዩን እኛም እንመናችሁ..እ⁉️

ነው ወይንስ የአክሱም ሙስሊሞችም «#ውሃብያ» ተብለው ተፈርጀዋል⁉️

ሁሉም ሙስሊም ይህንን ነገር ባገኘበት ቦታ ሊጠይቃቸው ይገባል
👍68
"ወሃBያ ተከትሎ መስገድ አይቻልም፣ ያረ ^ዱት ስጋ አይብበላም፣ ኒካሕ የላቸውም"

#ማነው_ተKፊሩ?
#ክፍል_2
~
ሰሞኑን ኢኽዋንና አሕ ^ ባሽ በሰለፊያ ደዕዋ ላይ የጋራ ዘመቻ እንደከፈቱ እያየን ነው። በቀዳሚነት እያራገቡት ያለው ነጥብ ተKፊሪዮች ናቸው የሚል ነው። ሙስሊሞችን በጅምላ ከኢስላም በማውጣት ላይ የተሰማራው ማን እንደሆነ በተከታታይ በማስረጃ አቀርባለሁ። ክፍል አንድን አሳልፌያለሁ።

በዚህኛው ክፍል ያቀረብኩት መረጃ የአሕ ^ ባሹን ዑመር ይማምን ንግግር ነው። በቅድሚያ አንድ ነጥብ ላስቀድም። አላህ ከፍጡራን በላይ ነው የሚለው እምነት በቁርኣንም፣ በሐዲሥም የተረጋገጠ የሰለፎች ኢጅማዕ ያለበት ጉዳይ ነው። በዚህ ላይ ተደጋጋሚ መረጃዎችን ያቀረብኩ ቢሆንም ለቅምሻ ያክል ብቻ ጠቆም ላድርግ፦

1. ታላቁ ዓሊም ዐብዱላህ ብኑል ሙባረክ (181 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-

فَإِنَّ أَهْلَ الْإِثْبَاتِ مِنْ أَهْلِ السُّنَّةِ يُجْمِعُونَ ... وَأَنَّ اللَّهَ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ

“የአላህን መገለጫዎች የሚያፀድቁት የሱና ሰዎች … አላህ ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ኢጅማዕ አድርገዋል።” [አልኢባና፣ ኢብኑ በጧህ፡ ቁ. 694]

2. አቡ ዙርዐ አራዚይ (264 ሂ.) እና ሓቲም አራዚይ (277 ሂ.) የአህሉ ሱናን ዐቂዳ ሲተነትኑ እንዲህ ብለዋል፡-

أَدْرَكْنَا الْعُلَمَاءَ فِي جَمِيعِ الْأَمْصَارِ حِجَازًا وَعِرَاقًا وَشَامًا وَيَمَنًا فَكَانَ مِنْ مَذْهَبِهِمُ: … وَأَنَّ اللَّهَ عَزَّ وَجَلَّ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ كَمَا وَصَفَ نَفْسَهُ فِي كِتَابِهِ , وَعَلَى لِسَانِ رَسُولِهِ ﷺ بِلَا كَيْفٍ

“በሁሉም ሃገራት - በሒጃዝ፣ በዒራቅ፣ በሻም፣ በየመን፣… ያሉ ዑለማዎችን አግኝተናል። ከመዝሀባቸው ውስጥ … አላህ - ዐዘ ወጀል - እራሱን በቁርኣኑ፣ እንዲሁም በመልእክተኛው ﷺ አንደበት እንደተገለፀው - ያለ እንዴት - ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ማመን ነው። [ላለካኢ፡ ቁ. 321]

3. ታላቁ ኢማም ኢብኑ ቁተይባህ (276 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-

وَالْأُمَمُ كُلُّهَا - عَرَبِيُّهَا وَعَجَمِيُّهَا - تَقُولُ: إِنَّ اللَّهَ تَعَالَى فِي السَّمَاءِ مَا تُرِكَتْ عَلَى فِطَرِهَا وَلَمْ تُنْقَلْ عَنْ ذَلِكَ بِالتَّعْلِيمِ

“ህዝቦች በሙሉ ዐረቡም ሌላውም አላህ በሰማይ ነው ይላሉ። በተፈጥሯቸው ላይ እስከተተውና ከዚህ ላይ በስብከት እስካልተወሰዱ ድረስ።” [ተእዊሉ ሙኽተሊፊል ሐዲሥ፡ 395]


በዚህ ላይ ያሉ የሰለፎች ንግግሮች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ድምፁን ያያያዝኩት ዑመር ይማም የተባለው አሕ ^ባሽስ ምን ይላል?

አላህን ከፍጡራን በላይ ከዐርሹ በላይ ነው የሚሉ ሙስሊሞችን በሙሉ ከኢስላም ያስወጣል። ሙስሊሞች አይደሉም፣ እነሱን በሶላት ተከትሎ መስገድ አይቻልም፣ ያረ ^ዱት ስጋ አይብበላም፣ ኒካሕም የላቸውም ይላል። ይሄ የሱ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው የአሕ ^ባሽ ቡድን አቋም ነው። ዛሬ ያሉ ሙስሊሞችን ከተራው ህዝብ አልፈው እስከ ዑለማእ ከእስልምና ያስወጣሉ። ለሐጅ እና ለዑምራ ወደ ሳዑዲ ሲሄዱ ኢማሞቹ ሙስሊሞች አይደሉም በሚል አብረው አይሰግዱም።

እንደ ዑመር ይማም ሃይማኖት አላህ ከዐርሹ በላይ ነው በማለት ከሶሐቦች ጀምሮ ያለፉ የጥንት ሰለፎች በሙሉ ሙስሊሞች አይደሉም ማለት ነው። እንግዲህ ተመልከቱ! ከዚህ በላይ ተKፊነት ኖሮ አይናቸውን በጨው አጥበው ሌሎችን በተK ፊርነት እየከሰሱ ነው። በሺርክ እየጨፈሩ ሌሎችን ከኢስላም ሲያስወጡ ማየት ስላቅ ነው መቼም። እኮ ማነው ተKፊሩ ?

በደንብ "ሼር" እያደረጋችሁ ባረከላሁ ፊኩም።

=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
👍37
👉ማነው ተክፊሩ⁉️
🎙በኑረዲን አል-አረብ
👉ማነው ተክፊሩ⁉️

ፀሀፊ👉 ዑስታዝ ኢብኑ ሙነወር
አቅራቢ 👉ኑረዲን አል-ዓረቢ

ሸር በማድረግ አሰራጩት
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍47
ቻናሏን ብናሳድጋትስ...እ.
..አትጠቅመንም ይመስላችኋል..⁉️

የሱና ቤት አይጠብምና ሌሎችን እየጋበዝን ተሸጋሽገን ጠጋጠጋ ብለን ተቃቅፈን እንደግ....እ

ብናሳድጋት ለብዙ ነገር ትጠቅመን እንደሆነ ብዬ ነው «መቸም የሚዲያ ተፅኖ ይገባችኋል..ጮሌ ናችሁ...እና...

www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍143
عاجل..
ትክክለኛ ሰው ከትክክለኛ ቦታ ላይ

አሏሁ አክበር
አሏሁ አክበር
‏أمر ملكي:

‏بناءً على ما عرضه ولي العهد.

‏يُعين فضيلة الشيخ الدكتور صالح بن فوزان بن عبدالله الفوزان مفتيًا عامًا للمملكة العربية السعودية ورئيسًا لهيئة كبار العلماء ورئيسًا عامًا للرئاسة العامة للبحوث العلمية والإفتاء بمرتبة الوزير

‏ ታዋቂው ሸይኽ ዶ / ር ሳሊህ ቢን ፋውዛን ቢን አብዱላህ አል ፋውዛን ሀፊዞሁሏህ

የሳውዲ አረቢያ ግዛት ታላቅ ሙፍቲ ፣ የከፍተኛ ምሁራን ምክር ቤት ሊቀመንበር እና የጄኔራል የሳይንሳዊ ምርምር ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

አሏህ እድሜያቸውን ያርዝምልን አሚን

http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍135
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
👉ለምን ፈራን...⁉️

የሙፍቲን መቃብር ለምን እንደፈራን፡
ከዚህ ዘግናኝ ድርጊት ቀድመን እንደጠራን፡

.....ለምን እንደሆነ አስተውላችኋል...!?
....የሽርክ ክብደቱ በርግጥ ገብቷችኋል..!?

የሽርክን አደጋ ግፉን ስለቀራን፡
የምናየው ነገር በጣም ነው ያስፈራን?!

ኮልፌ ገብተው ለፈድሉ ምንጣፍ አንጥፈውና ጫት ይዘው ከገቡ፤ ለሐጂ ዑመር ደግሞ ቀብራቸውን ለብቻ ሲያገኙት ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ መገመት ቀላል ነው። ወሏሁ-ል-ሙስተዓን!
👍68
👉አይዟችሁ አሏህ ከኛ ጋር ነው።

አብሽር የሱናው ሰው
------------------

አህባሽ ምንም ቢጮህ
ኢኽዋን ምን ቢንጫጫ፡
ሱፍይ ምን ቢፎክር
ምን ቢሰጥ መግለጫ፡
ተብሊግ ምን ቢዞረን፤
ቢቀርብም ለምርጫ፡
ቀላል ስለማይሆን፤
መረጃ እንደ በርጫ፡

የሐቅ ሰወችን አይችሉም መጋፈጥ፡
ካልሆነ በስተቀር ወድቆ ለመፈጥፈጥ፡
የሱና ሰው ጉዞው ደምቋል በመረጃ፡
የተድበሰበሰ የለም መጋረጃ፡
አህባሽ ግን በጫት ነው የሚያወጣው ሀጃ!

ሐጃው እንድወጣ የጫት ቀርጥ ይቅማል፡
መቃብር ያመልካል ሽርክን ይፈፅማል፡
በየደረሰበት ቢዲዓን ይለቅማል፡
እንደዚህም ሆኖ ይሰግዳል ይፆማል⁉️
አስተውሎ ላየው እጂጉን ይገርማል‼️

የሱና ሰወች ግን ቁርዓን ነው ዳኛቸው፡
የነብዩ ፈለግ ሐዲስ ነው መሪያቸው፡
የሶሀባ አረዳድ ይህ ነው ቀኖናቸው፡
ለሌላው ቲወሪ ጉዳይም የላቸው፡

.....ታዲያ...

በጌታ ቃል ኪዳን ፍፁም የታዘዘ፡
በአዳዲስ ፈጠራ ሐቁን ያልበረዘ፡
ማን ያሸንፈዋል አሏህን የያዘ ?⁉️

አትፍራ ሴራውን ማንም ይጠንስሰው፡
አንተ ሐቅን ስበክ ቢዲዓን አፍርሰው፡
አሏህ ከኛ ጋር ነው አብሽር የሱና ሰው፡

አሏሁ አክበር

«ከወንጀላችንም ቢሆን ሰለፍይ ያደረገን ጌታ ምስጋና ይገባው ወላሒ...እህህህህ ረፍቱኮ»

.....በኑረዲን አል-ዓረብ



http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
http://www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍88
Forwarded from Fuad Mohammed
أعز الله السعودية بلاد يعز فيها أهل السنة ويذل فيها أهل البدع وأبقاها ذخرا للإسلام والمسلمين
👍16
(❷)نواقض الإسلام
🎙አቡ-ፋሩቅ حفظه الله
ነዋቂዱል-ኢስላም

ክፍል =❷

👉ከአሏህ ውጭ አምልኮ እና አማላጆችን መጣራት ያለው መዘዝ

🎙በአቡ-ፋሩቅ
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
www.tg-me.com/nuredinal_arebi
👍6
2025/10/23 03:04:07
Back to Top
HTML Embed Code: