ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
+ ተራ የማይደርሰው ተጠማቂ +
"ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ፦ ልትድን ትወዳለህን? አለው ሰውዬውም፦ ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል፡ ብሎ መለሰለት" ዮሐ.5:5-7
ይህንን ጥያቄና መልስ ሳይ በሽተኛውን ማናገር ያምረኝና እንዲህ በል ይለኛል :-
አንተ በሽተኛ ግድ የለህም የተጠየቅከውን መልስ:: እመነኝ ጠያቂህ ተራ ጠያቂ አይደለም::
የሚጠይቅህ ሲያደርቁህ እንደኖሩት አሰልቺ ጠያቂዎች አይደለም:: ጥያቄውም የሌሎችን ሰዎች ዓይነት ጥያቄ አይደለም:: ከፊትህ የቆመው የመጠመቂያውን ውኃ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሞላውን ውኃ የፈጠረ ነው::
"ወደ መጠመቂያው የሚያኖረኝ ሰው የለኝም" አልክን? የተጠየቅከውን መልስ እንጂ!
ወደ መጠመቂያው መግባት ትወድዳለህን? ብሎ ማን ጠየቀህ? ተው እንጂ! የጠየቀህ ማን እንደሆነ ባታውቅ እንኩዋን ጥያቄውን በደንብ ስማ::
ሰው የለኝም አትበለው : ስለመጠመቂያው ወረፋ አትንገረው : ስንት ሰው ቀድሞህ እንደዳነ አትቁጠርለት:: የጠየቀህ ግልፅ ጥያቄ ነው::
ልትድን ትወዳለህን?
እግዚአብሔር ፊት ስለ ችግርህ ክብደት ለምን ታወራለህ? ምን እንደሌለህማ እሱም ያውቃል:: አዎን እድን ዘንድ በለው:: ችግርህን ትተህ የምትፈልገውን ንገረው:: የችግርህ መወሳሰብና ሥር መስደድ ለእሱ የሚከብድ አይደለምና መዳን እንደምትሻ ብቻ በእምነት ንገረው የሚል ተግሣፅ በበሽተኛው በኩል ወደ እኛ ደረሰ::
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
መጻጉዕ (በሽተኛው) ቤተ ሳይዳ ከመጣ 38 ዓመት ሆነው:: ዳዊትና ሰሎሞን 40 40 ዓመት ነግሠው እንኳን ብዙ የምሬት ቅኔ ተቀኝተዋል:: ይህ ሰው አልጋ ላይ ሆኖ አርባ ዓመት ሊሞላው ሲል ምንኛ ተንገሽግሾ ይሆን?
ልብ በሉ ጌታችን በቤተልሔም ሲወለድ ይህ በሽተኛ በአልጋው ላይ ነበረ:: እረኞች ከብዙ መላእክት ጋር ሲዘምሩ እሱ የአንድን መልአክ መውረድና ውኃውን ማናወጥ እየጠበቀ ስድስተኛ ዓመቱን ደፍኖ ነበር:: ጌታችን የሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ደርሶ ወደ መጠመቂያው ሥፍራ ሲመጣም ይህ ሰው አልጋው ላይ ነው:: መጠመቂያዋን 38 ዓመት በተስፋ ሲጠብቅ ቆይቶ ሳይጠመቅባት ቀረ::
ጌታ ሆይ የማይደርሰኝን ወረፋ ከመጠበቅ አድነኝ:: እንድፈወስበት ባልፈቀድክበት ሥፍራ ዕድሜዬን እንዳልጨርስ ጠብቀኝ::
ወደ ሐዲስ ኪዳንዋ ቤተ ሳይዳ ወደ ቤተክርስቲያን ከመጣሁ ብዙ ዘመን አስቆጠርኩኝ:: ግን እስካሁንም ድረስ ከኃጢአት አልጋ ላይ አልወረድሁም:: መነሣት እፈልጋለሁ ግን አቃተኝ:: ልቤ እንጂ እግሬ ጸንቶ መቆም አልቻለም::
ፈረቃ የሌለብህን የሕይወት ውኃ አንተን ሊጠጡ ሲመጡ በዓይኔ እየተቀበልኩ ብዙዎች ጠጥተውህ ሲድኑ በዓይኔ እየሸኘሁ አልጋዬ ላይ ቀረሁ::
እኔ እንደተኛሁ ስንቱ ቀድሞኝ እንደዳነ ባየህልኝ:: ከእኔ በኁዋላ መጥተውስ ከእኔ በፊት ስንቶች ዳኑ?
ስንቱ ከኃጢአት አልጋ በንስሓ ተነሥቶ ያንተን ሥጋና ደም ተቀብሎ ተፈወሰ?
የቤተ ሳይዳው ሐኪም ሆይ ወደ አንጋፋው በሽተኛህ ወደ ጽኑዕ ሕመምተኛህ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ይሆን? ያን ሕመምተኛ "ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበረ" አውቀህ ያናገርከው ሆይ እኔን የምታናግረኝ መቼ ይሆን? እኔስ ብዙ ዘመን እንደሆነኝ አታውቅምን? ሰው የለኝም : ልብ የለኝም : ኃይል የለኝም : አቅም የለኝም ብዬ ብሶቴን የምነግርህ መቼ ይሆን?
"ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ" ዮሐ.5:8-9
አንተ ተነሥ ብለኸው የማይነሣ ማን ነው? እንኳንስ ከአልጋ ከመቃብርም ተነሥ ያልከው ይነሣ የለምን?
ግዴለህም እኔንም ተነሥ በለኝ:: ተነሥ ኃይልን ልበስ ያልከኝ እንደሆነ እንኳንስ "ሸክሜም ቀሊል ነው" ያልከው አንተ ያዘዝከኝ የራሴን ሸክም ቀርቶ የወንድሜን ሸክምም ተሸክሜ የአንተን ሕግ እፈጽማለሁ:: (ገላ. 6:2)
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
"ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ... ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ፡ አለው" ይላል::
በሽተኛው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ እንደሔደ ሳነብ አንድ ነገር ልቤን አስጨነቀው:: ይህ ሰውዬ 38 ዓመት ሙሉ የኖረው በቤተ ሳይዳ ነው:: ክርስቶስ ድንገት ፈውሶት ሒድ ሲለው እሺ ብሎ ከዚያ መጠመቂያ ሥፍራ ከወጣ በኁዋላ ወዴት ሔደ?
የሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛው ሆይ እውነት ወዴት ሔድህ? ከመጠመቂያው መውጣትህን ሰምተን አድንቀናል:: ከዚያስ ወዴት ሔድክ? ዙሪያ ገባው አልተለወጠብህም? መንገድስ አልጠፋብህም?
ወደ ዘመዶች ቤት ሔድክ እንዳልል "ሰው የለኝም" ስትል ሰምቼሃለሁ::
አልጋህንስ የት አደረስካት? መቼም ሰባብረህ እንደማትጥላት የታወቀ ነው:: አልጋ ለታመመ ብቻ ሳይሆን ለጤነኛም ያስፈልጋልና አራት እግር እያላት ጥላህ ያልሔደችውን ዘመድህን መቼም በክብር ማስቀመጥህ አይቀርም::
ለማንኛውም እዚያው ምዕራፍ ላይ ኢየሱስ ይህንን በሽተኛ ዳግም በመቅደስ አገኘው ይላል:: ዮሐ. 5:14 ጌታ ከመጠመቂያ ቦታ አድኖ ያስነሣውን ሰው በመቅደስ ቆሞ አገኘው:: ይህ በሽተኛ እግሩ ሲጸናለት የሔደው ወደ ፈጣሪ ደጅ መሆኑ ያስመሰግነዋል::
ጌታ በመጠጥ ቤት ቢያገኘው ኖሮ ያሳዝን ነበር:: እግርህን ያጸናሁልህ ለዚህ ነው ወይ ብሎ ባዘነበት ነበር:: አሁን ግን ያዳነው ጌታ በመቅደስ አግኝቶት "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" አለው::
ይህንን የምታነብ ወንድሜ ሆይ ክርስቶስ አንተንስ አላዳነህም? "ኸረ እኔ ሽባ ሆኜ አላውቅም:: ማንም እኔን ከአልጋ አላስነሣኝም ትለኝ እንደሆን እመነኝ ክርስቶስ እንደ አንተ ያዳነውስ የለም:: እርሱ እኔና አንተን ተነሡ ብሎ ያስነሣን ከ38 ሳይሆን ከዘላለም የሲኦልና የኃጢአት አልጋ ነው::
እኛን የፈወሰን አልጋችንን አሸክሞ ሳይሆን እሱ ራሱ እኛን ከነአልጋችን ተሸክሞን ነው:: ካላመንከኝ ነቢዩ ኢሳይያስን ጠይቀው "እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ" ሲልህ ትሰማዋለህ:: ኢሳ. 53:12 የእኛን በደል ተሸክሞ ጀርባው ምን ያህል እንደ ቆሰለ ባየህ:: ይህንስ ጀርባዬን ታያለህ የተባለውን ሙሴን ብትጠይቀው ሳይሻል አይቀርም::
ያዳነህ አምላክ አንተንስ የት ነው የሚያገኝህ? እንደዚህ ሰውዬ መቅደስ ያገኝህ ይሆን?
የትም ቢያገኝህ ግን ቃሉ አንድ ነው "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" ከሠላሳ ስምንት ዓመት የአልጋ ቁራኝነት የሚብስ ምን ሊመጣ ነው? ካልክስ እሱን ከማየት ይሠውረኝ ብትል ይሻልሃል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 10 2014 ዓ.ም.
ባሕር ዳር ኢትዮጵያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
"ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ፦ ልትድን ትወዳለህን? አለው ሰውዬውም፦ ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል፡ ብሎ መለሰለት" ዮሐ.5:5-7
ይህንን ጥያቄና መልስ ሳይ በሽተኛውን ማናገር ያምረኝና እንዲህ በል ይለኛል :-
አንተ በሽተኛ ግድ የለህም የተጠየቅከውን መልስ:: እመነኝ ጠያቂህ ተራ ጠያቂ አይደለም::
የሚጠይቅህ ሲያደርቁህ እንደኖሩት አሰልቺ ጠያቂዎች አይደለም:: ጥያቄውም የሌሎችን ሰዎች ዓይነት ጥያቄ አይደለም:: ከፊትህ የቆመው የመጠመቂያውን ውኃ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሞላውን ውኃ የፈጠረ ነው::
"ወደ መጠመቂያው የሚያኖረኝ ሰው የለኝም" አልክን? የተጠየቅከውን መልስ እንጂ!
ወደ መጠመቂያው መግባት ትወድዳለህን? ብሎ ማን ጠየቀህ? ተው እንጂ! የጠየቀህ ማን እንደሆነ ባታውቅ እንኩዋን ጥያቄውን በደንብ ስማ::
ሰው የለኝም አትበለው : ስለመጠመቂያው ወረፋ አትንገረው : ስንት ሰው ቀድሞህ እንደዳነ አትቁጠርለት:: የጠየቀህ ግልፅ ጥያቄ ነው::
ልትድን ትወዳለህን?
እግዚአብሔር ፊት ስለ ችግርህ ክብደት ለምን ታወራለህ? ምን እንደሌለህማ እሱም ያውቃል:: አዎን እድን ዘንድ በለው:: ችግርህን ትተህ የምትፈልገውን ንገረው:: የችግርህ መወሳሰብና ሥር መስደድ ለእሱ የሚከብድ አይደለምና መዳን እንደምትሻ ብቻ በእምነት ንገረው የሚል ተግሣፅ በበሽተኛው በኩል ወደ እኛ ደረሰ::
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
መጻጉዕ (በሽተኛው) ቤተ ሳይዳ ከመጣ 38 ዓመት ሆነው:: ዳዊትና ሰሎሞን 40 40 ዓመት ነግሠው እንኳን ብዙ የምሬት ቅኔ ተቀኝተዋል:: ይህ ሰው አልጋ ላይ ሆኖ አርባ ዓመት ሊሞላው ሲል ምንኛ ተንገሽግሾ ይሆን?
ልብ በሉ ጌታችን በቤተልሔም ሲወለድ ይህ በሽተኛ በአልጋው ላይ ነበረ:: እረኞች ከብዙ መላእክት ጋር ሲዘምሩ እሱ የአንድን መልአክ መውረድና ውኃውን ማናወጥ እየጠበቀ ስድስተኛ ዓመቱን ደፍኖ ነበር:: ጌታችን የሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ደርሶ ወደ መጠመቂያው ሥፍራ ሲመጣም ይህ ሰው አልጋው ላይ ነው:: መጠመቂያዋን 38 ዓመት በተስፋ ሲጠብቅ ቆይቶ ሳይጠመቅባት ቀረ::
ጌታ ሆይ የማይደርሰኝን ወረፋ ከመጠበቅ አድነኝ:: እንድፈወስበት ባልፈቀድክበት ሥፍራ ዕድሜዬን እንዳልጨርስ ጠብቀኝ::
ወደ ሐዲስ ኪዳንዋ ቤተ ሳይዳ ወደ ቤተክርስቲያን ከመጣሁ ብዙ ዘመን አስቆጠርኩኝ:: ግን እስካሁንም ድረስ ከኃጢአት አልጋ ላይ አልወረድሁም:: መነሣት እፈልጋለሁ ግን አቃተኝ:: ልቤ እንጂ እግሬ ጸንቶ መቆም አልቻለም::
ፈረቃ የሌለብህን የሕይወት ውኃ አንተን ሊጠጡ ሲመጡ በዓይኔ እየተቀበልኩ ብዙዎች ጠጥተውህ ሲድኑ በዓይኔ እየሸኘሁ አልጋዬ ላይ ቀረሁ::
እኔ እንደተኛሁ ስንቱ ቀድሞኝ እንደዳነ ባየህልኝ:: ከእኔ በኁዋላ መጥተውስ ከእኔ በፊት ስንቶች ዳኑ?
ስንቱ ከኃጢአት አልጋ በንስሓ ተነሥቶ ያንተን ሥጋና ደም ተቀብሎ ተፈወሰ?
የቤተ ሳይዳው ሐኪም ሆይ ወደ አንጋፋው በሽተኛህ ወደ ጽኑዕ ሕመምተኛህ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ይሆን? ያን ሕመምተኛ "ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበረ" አውቀህ ያናገርከው ሆይ እኔን የምታናግረኝ መቼ ይሆን? እኔስ ብዙ ዘመን እንደሆነኝ አታውቅምን? ሰው የለኝም : ልብ የለኝም : ኃይል የለኝም : አቅም የለኝም ብዬ ብሶቴን የምነግርህ መቼ ይሆን?
"ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ" ዮሐ.5:8-9
አንተ ተነሥ ብለኸው የማይነሣ ማን ነው? እንኳንስ ከአልጋ ከመቃብርም ተነሥ ያልከው ይነሣ የለምን?
ግዴለህም እኔንም ተነሥ በለኝ:: ተነሥ ኃይልን ልበስ ያልከኝ እንደሆነ እንኳንስ "ሸክሜም ቀሊል ነው" ያልከው አንተ ያዘዝከኝ የራሴን ሸክም ቀርቶ የወንድሜን ሸክምም ተሸክሜ የአንተን ሕግ እፈጽማለሁ:: (ገላ. 6:2)
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
"ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ... ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ፡ አለው" ይላል::
በሽተኛው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ እንደሔደ ሳነብ አንድ ነገር ልቤን አስጨነቀው:: ይህ ሰውዬ 38 ዓመት ሙሉ የኖረው በቤተ ሳይዳ ነው:: ክርስቶስ ድንገት ፈውሶት ሒድ ሲለው እሺ ብሎ ከዚያ መጠመቂያ ሥፍራ ከወጣ በኁዋላ ወዴት ሔደ?
የሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛው ሆይ እውነት ወዴት ሔድህ? ከመጠመቂያው መውጣትህን ሰምተን አድንቀናል:: ከዚያስ ወዴት ሔድክ? ዙሪያ ገባው አልተለወጠብህም? መንገድስ አልጠፋብህም?
ወደ ዘመዶች ቤት ሔድክ እንዳልል "ሰው የለኝም" ስትል ሰምቼሃለሁ::
አልጋህንስ የት አደረስካት? መቼም ሰባብረህ እንደማትጥላት የታወቀ ነው:: አልጋ ለታመመ ብቻ ሳይሆን ለጤነኛም ያስፈልጋልና አራት እግር እያላት ጥላህ ያልሔደችውን ዘመድህን መቼም በክብር ማስቀመጥህ አይቀርም::
ለማንኛውም እዚያው ምዕራፍ ላይ ኢየሱስ ይህንን በሽተኛ ዳግም በመቅደስ አገኘው ይላል:: ዮሐ. 5:14 ጌታ ከመጠመቂያ ቦታ አድኖ ያስነሣውን ሰው በመቅደስ ቆሞ አገኘው:: ይህ በሽተኛ እግሩ ሲጸናለት የሔደው ወደ ፈጣሪ ደጅ መሆኑ ያስመሰግነዋል::
ጌታ በመጠጥ ቤት ቢያገኘው ኖሮ ያሳዝን ነበር:: እግርህን ያጸናሁልህ ለዚህ ነው ወይ ብሎ ባዘነበት ነበር:: አሁን ግን ያዳነው ጌታ በመቅደስ አግኝቶት "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" አለው::
ይህንን የምታነብ ወንድሜ ሆይ ክርስቶስ አንተንስ አላዳነህም? "ኸረ እኔ ሽባ ሆኜ አላውቅም:: ማንም እኔን ከአልጋ አላስነሣኝም ትለኝ እንደሆን እመነኝ ክርስቶስ እንደ አንተ ያዳነውስ የለም:: እርሱ እኔና አንተን ተነሡ ብሎ ያስነሣን ከ38 ሳይሆን ከዘላለም የሲኦልና የኃጢአት አልጋ ነው::
እኛን የፈወሰን አልጋችንን አሸክሞ ሳይሆን እሱ ራሱ እኛን ከነአልጋችን ተሸክሞን ነው:: ካላመንከኝ ነቢዩ ኢሳይያስን ጠይቀው "እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ" ሲልህ ትሰማዋለህ:: ኢሳ. 53:12 የእኛን በደል ተሸክሞ ጀርባው ምን ያህል እንደ ቆሰለ ባየህ:: ይህንስ ጀርባዬን ታያለህ የተባለውን ሙሴን ብትጠይቀው ሳይሻል አይቀርም::
ያዳነህ አምላክ አንተንስ የት ነው የሚያገኝህ? እንደዚህ ሰውዬ መቅደስ ያገኝህ ይሆን?
የትም ቢያገኝህ ግን ቃሉ አንድ ነው "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" ከሠላሳ ስምንት ዓመት የአልጋ ቁራኝነት የሚብስ ምን ሊመጣ ነው? ካልክስ እሱን ከማየት ይሠውረኝ ብትል ይሻልሃል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 10 2014 ዓ.ም.
ባሕር ዳር ኢትዮጵያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
+ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ +
"የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው::
በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ?
ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል"
"የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው::
በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ?
ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል"
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
"ዘሐይወ ኢያእመረ ዘአሕየዎ …የዳነው ያዳነውን አላወቀውም" (ዮሐ. ፭፥፲፫)
የነፍሳችንን ማሠሪያ እንዲፈታና ዓለሙን ከተያዘት የኃጢአት በሽታ እንዲያድን ለቤዛነት፤ እንዲሁም የመልካምና የበጎ ምግባራት ሁሉ አብነት ሆኖ በሥራና በቃል እንዲያስተምር ለአርአያነትም ወዳለንባት ምድር በሥጋ ቅድስት ድንግል ማርያም የወረደው እግዚአ ለሰንበት ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአራተኛው የአቢይ ጾም ሳምንት በመፃጉዕ እሑድ በ"ቤተሳይዳ" የፈጸመውን ተአምራት ቤተክርስቲያናችን ታሰባለች። በዕለቱም በዮሐንስ ወንጌል አምስተኛው ምዕራፍ የተቀመጠው ታሪክ በልዩ ልዩ ኅብረ ምሥጢር ተሰናስሎ በሊቃውንቱ ይነገራል።
መፃጉዕ ተብሎ የደረሰበት ድካመ ሥጋ ጽናት ከሕመም ከበሽታ ከደዌም በላይ መገለጫው የሆነ ሰው ለ፴፰ ዓመት በአልጋው ላይ ሆኖ ምሕረትን ሲጠባበቅባት የኖረባት ስፍራን "ቤተ ሳይዳ" ይላታል።
በቅዱስ መጽሐፍ የሥፍራዎችን ስያሜ ስንመረምር በይሁዳና በገሊላ ለሚገኙ ሁለት የተለያዩ ግዛቶች በተመሳሳይ አገባብ "ቤተ ሳይዳ" የሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸው እናገኛለን:: በሁለቱ አውራጃዎች (ይሁዳና በገሊላ) ሥር "ቤተ ሳይዳ" በሚል የተጠቀሱት ሥፍራዎች በትርጉም ፊደላቱ ያለአገባብ መሰደር ከወለዱት የሞክሼነት ስህተት (Metathetical Corruption) የተገኘ ክፍተት እንጂ ቦታዎቹስ በጥንታዊቷ የእስራኤል ግዛት ከመገኘታቸው ውጪ ምንም የሚያገናኛቸው መልክአ ምድራዊ ኩነት የለም "ጲላጦስ ጰንጤናዊ መልአከ ይሁዳ ወሄሮድስ ንጉሠ ገሊላ" (ሉቃ· ፫፥፩) እንዲል የግዛቶቹ አገረ ገዢዎችም እንዲሁ ለየቅል ነበሩ:: አገባቡን አካቶ ለመረዳት እንዲያመች የሁለቱንም መካናት ከተማና መንደር ለይቶ ማወቁ ተገቢ ነው::
🍁 በይሁዳ ግዛት ከሚገኙና እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ገቢረ ተአምራቱን ከፈጸመባቸው ሥፍራዎች ፦ ቤተሳይዳ(Bethesda) ፣ ቢታኒያ ፣ ቤተልሔም ፣ ቤተፋጌ ፣ ኢያሪኮ ፣ ጌቴሰማኒ ፣ ሊቶስጥሮስ(ገበታ) ፣ ኤማሁስ፣ ቀራንዮ(ጎልጎታ) ፣ ኢየሩሳሌም እና የደብረዘይት ተራራ የሚጠቀሱ ሲሆን፤
🍁 በገሊላ አውራጃ ደግሞ ፦ ቤተሳይዳ(Bethsaida) ፣ ሄኖን ፣ ቃና፣ ቅፍርናሆም፣ ኮራዚ፣ ጌንሳሬጥ፣ ደብረታቦር፣ ናይን እና የገሊላ ባህር ተገልጸው እናገኛልን::
እነዚህኑ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳና "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ አካባቢያዊ መገኛ ለይተው የሚያመለክቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም በይሁዳ ኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ ያለችዋን "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት" (ዮሐ ·፭፥፪) ብሎ የገለጠበትንና በገሊላ ስለምትገኘዋ ደግሞ "ወሖሩ እሙንቱሂ ኀበ ፊልጶስ ዘቤተ ሳይዳ ዘገሊላ" (ዮሐ ፲፪፥፳፩) የሚለው ማየት ይቻላል::
በሌላ መልኩ አንዳንዶች ደግሞ በሁለቱም ሥፍራዎች ክርስቶስ አምላካችን ለፈውስ ሥራ ያገኛቸውን ሰዎች አይተው ተመሳሳይ ቦታ ሲመስላቸው ይታያል ይህም "መጻጉዕ" እና "ዕውር" የነበሩትን ማዳኑ ነው:: ይኸውም "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት …በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት። (ዮሐ ·፭፥፪) የተባለውና "ወበጽሑ ቤተ ሳይዳ ወአምጽኡ ኀቤሁ ዕውረ ወአስተብቁዕዎ ይግስሶ … ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ። ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት።" (ማር· ፰፥፳፪) የሚለው ነው::
🔑 "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ (Bethsaida) በትርጉም "የማጥመጃ ቤት" የሚል ፍቺ ያለው በተለይ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ አሳ አጥማጆቹ ወንድማማቾችና ቅዱስ ፊልጶስ የነበሩባት መንደር ናት " ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።" (ዮሐ·፩፡፵፭) እንዲል።
፨ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ (Bethesda or Bethchasday) የመጠመቂያ ሥፍራ ስትሆን በግሪኩ ቤተ ዛታ ( Βηθζαθά) ወይም ቅልንብትራ (κολυμβήθρα) እንዲሁም በእብራይስጡና በአረማይኩ "ቤተ`ስዳ" (Beth hesda ( בית חסד /חסדא )) በማለት "ከማጥመጃ ቤት" ለይቶ "ቤተ ሣሕል / የምሕረት ቤት" የሚል ትርጉም ያለው መጠመቂያና መላለሻ መንገድ መሆንዋን ያመለክተናል። የግእዙ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ለዚህ በመጨነቅ የቦታውን ስያሜ ከእብራይስጡ "የአንድዮሽ ትርጉም" ስያሜ (ቤተ ሳይዳ) ጋር በግሪኩ ያለውንም መጠሪያ ጭምር አካቶ ቅልንብትራ ( κολυμβήθρα / kolumbethra) ሲል እናገኘዋለን::
ቤተ ሳይዳ ዘይሁዳ ባለ አምስት በር መመላለሻ አምስት ዓይነት ድውያን ፈውስን ከማየ ጥምቀቱ ሲጠባበቁ የሚኖሩባት በአምስተኛው የዮሐንስ ወንጌል ተጽፎ ያለ የጌታችን ማዳን የተገለጠባት ሥፍራ ናት። "እስመ ኦሪት መንፈቀ ፍጻሜ ወኅዳጠ መክፈልት" እንዲላት መልአከ እግዚአብሔር ለቀድሶተ ማይ ወርዶ ውኃውን ሲያናውጥ ቀድሞ የገባ የሚነጻባት በዕለቱ ከአንድ በቀር ለሌላው ፈውስ የማይደገምባት ቦታ ናት ይህችው "ቤተ ሳይዳ" ።
ታዲያ ከእነዚህ መካከል ነበር ይህን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል የድኅነት ተስፈኛ ሆኖ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ "መፈውስ ወማሕየዊ" ጌታችን ቀርቦ አዎን እንዲለው እያወቀ ብወዳችሁ አላዋቂ የሆነ የእናንተን ሥጋ ተዋሕጄ መጣሁላችሁ ሲለን ("አኮ ኢያእሚሮ ኅቡአተ አላ ከመ የሀብ መካነ ለጥንተ ትስብዕቱ ዘኢየአምር ኅቡአተ" እንዲል) ያንን በሽተኛ "ትፈቅድኑ ትሕየው? … ባድንህ ፈቃድህ ነውን?" አለው። የሚገርመው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራውያን መልእክቱ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፪ ላይ "የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።" ብሎ የመሰከረለት ጌታችን ፈውስን በመጠባበቅ ከመዳን ውጪ ሌላ ዓላማ ያልነበረውን ይህን ሰው ዓይቶ ፈቃዱን እያወቀ ግን ፍቀድልኝና ላድንህ አለው። " ሰው በከንቱ ወራቱ ቍጥርና እንደ ጥላ በሚያሳልፈው ዘመኑ በሕይወቱ ሳለ ለሰው የሚሻለውን የሚያውቅ ማነው? "(መክ ፮፥፲፪) እንዲል የሚያስፈልገንን ሳንነግረው የሚያውቅ የሚሰጠንም ከእርሱ ከፈጣሪው ውጪ በእውነት ማን አለ? መፃጉዕ ግን ኋላ የሚክድ ነውና "በሰንበት ላይ ያመጸ ፣ ራሱን ከአብ የሚያስተካክል ፣ ቤተመቅደሱን አፍርሱት ያለ መች አድነኝ ብየው ሳልፈቅድለት ያዳነኝና አልጋ ያሸከመኝ ነውኮ" ብሎ በዕለተ ዓርብ የሚከስበትን ሲያሳጣውና ለኋላ ጥፋቱ የገዛ ኅሊናው እንዲቀጣው ፈቃዱን ጠየቀው። "አልብየ ሰብእ" ሰው የሌለኝ ሆኖ እንጂ ያንንማ ማን ይጠላል በሚል ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ድኅነትን ፈቅዶ ገለጠ። እስከ ሁከተ ማይ ሳያቆየው "ተንሥእ ንሣእ ዓራተከ ወሑር … ተንስና አልጋህን አንስተህ ሂድ" አለው ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ ዘመን የተሸከመች ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ።
የነፍሳችንን ማሠሪያ እንዲፈታና ዓለሙን ከተያዘት የኃጢአት በሽታ እንዲያድን ለቤዛነት፤ እንዲሁም የመልካምና የበጎ ምግባራት ሁሉ አብነት ሆኖ በሥራና በቃል እንዲያስተምር ለአርአያነትም ወዳለንባት ምድር በሥጋ ቅድስት ድንግል ማርያም የወረደው እግዚአ ለሰንበት ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአራተኛው የአቢይ ጾም ሳምንት በመፃጉዕ እሑድ በ"ቤተሳይዳ" የፈጸመውን ተአምራት ቤተክርስቲያናችን ታሰባለች። በዕለቱም በዮሐንስ ወንጌል አምስተኛው ምዕራፍ የተቀመጠው ታሪክ በልዩ ልዩ ኅብረ ምሥጢር ተሰናስሎ በሊቃውንቱ ይነገራል።
መፃጉዕ ተብሎ የደረሰበት ድካመ ሥጋ ጽናት ከሕመም ከበሽታ ከደዌም በላይ መገለጫው የሆነ ሰው ለ፴፰ ዓመት በአልጋው ላይ ሆኖ ምሕረትን ሲጠባበቅባት የኖረባት ስፍራን "ቤተ ሳይዳ" ይላታል።
በቅዱስ መጽሐፍ የሥፍራዎችን ስያሜ ስንመረምር በይሁዳና በገሊላ ለሚገኙ ሁለት የተለያዩ ግዛቶች በተመሳሳይ አገባብ "ቤተ ሳይዳ" የሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸው እናገኛለን:: በሁለቱ አውራጃዎች (ይሁዳና በገሊላ) ሥር "ቤተ ሳይዳ" በሚል የተጠቀሱት ሥፍራዎች በትርጉም ፊደላቱ ያለአገባብ መሰደር ከወለዱት የሞክሼነት ስህተት (Metathetical Corruption) የተገኘ ክፍተት እንጂ ቦታዎቹስ በጥንታዊቷ የእስራኤል ግዛት ከመገኘታቸው ውጪ ምንም የሚያገናኛቸው መልክአ ምድራዊ ኩነት የለም "ጲላጦስ ጰንጤናዊ መልአከ ይሁዳ ወሄሮድስ ንጉሠ ገሊላ" (ሉቃ· ፫፥፩) እንዲል የግዛቶቹ አገረ ገዢዎችም እንዲሁ ለየቅል ነበሩ:: አገባቡን አካቶ ለመረዳት እንዲያመች የሁለቱንም መካናት ከተማና መንደር ለይቶ ማወቁ ተገቢ ነው::
🍁 በይሁዳ ግዛት ከሚገኙና እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ገቢረ ተአምራቱን ከፈጸመባቸው ሥፍራዎች ፦ ቤተሳይዳ(Bethesda) ፣ ቢታኒያ ፣ ቤተልሔም ፣ ቤተፋጌ ፣ ኢያሪኮ ፣ ጌቴሰማኒ ፣ ሊቶስጥሮስ(ገበታ) ፣ ኤማሁስ፣ ቀራንዮ(ጎልጎታ) ፣ ኢየሩሳሌም እና የደብረዘይት ተራራ የሚጠቀሱ ሲሆን፤
🍁 በገሊላ አውራጃ ደግሞ ፦ ቤተሳይዳ(Bethsaida) ፣ ሄኖን ፣ ቃና፣ ቅፍርናሆም፣ ኮራዚ፣ ጌንሳሬጥ፣ ደብረታቦር፣ ናይን እና የገሊላ ባህር ተገልጸው እናገኛልን::
እነዚህኑ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳና "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ አካባቢያዊ መገኛ ለይተው የሚያመለክቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም በይሁዳ ኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ ያለችዋን "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት" (ዮሐ ·፭፥፪) ብሎ የገለጠበትንና በገሊላ ስለምትገኘዋ ደግሞ "ወሖሩ እሙንቱሂ ኀበ ፊልጶስ ዘቤተ ሳይዳ ዘገሊላ" (ዮሐ ፲፪፥፳፩) የሚለው ማየት ይቻላል::
በሌላ መልኩ አንዳንዶች ደግሞ በሁለቱም ሥፍራዎች ክርስቶስ አምላካችን ለፈውስ ሥራ ያገኛቸውን ሰዎች አይተው ተመሳሳይ ቦታ ሲመስላቸው ይታያል ይህም "መጻጉዕ" እና "ዕውር" የነበሩትን ማዳኑ ነው:: ይኸውም "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት …በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት። (ዮሐ ·፭፥፪) የተባለውና "ወበጽሑ ቤተ ሳይዳ ወአምጽኡ ኀቤሁ ዕውረ ወአስተብቁዕዎ ይግስሶ … ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ። ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት።" (ማር· ፰፥፳፪) የሚለው ነው::
🔑 "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ (Bethsaida) በትርጉም "የማጥመጃ ቤት" የሚል ፍቺ ያለው በተለይ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ አሳ አጥማጆቹ ወንድማማቾችና ቅዱስ ፊልጶስ የነበሩባት መንደር ናት " ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።" (ዮሐ·፩፡፵፭) እንዲል።
፨ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ (Bethesda or Bethchasday) የመጠመቂያ ሥፍራ ስትሆን በግሪኩ ቤተ ዛታ ( Βηθζαθά) ወይም ቅልንብትራ (κολυμβήθρα) እንዲሁም በእብራይስጡና በአረማይኩ "ቤተ`ስዳ" (Beth hesda ( בית חסד /חסדא )) በማለት "ከማጥመጃ ቤት" ለይቶ "ቤተ ሣሕል / የምሕረት ቤት" የሚል ትርጉም ያለው መጠመቂያና መላለሻ መንገድ መሆንዋን ያመለክተናል። የግእዙ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ለዚህ በመጨነቅ የቦታውን ስያሜ ከእብራይስጡ "የአንድዮሽ ትርጉም" ስያሜ (ቤተ ሳይዳ) ጋር በግሪኩ ያለውንም መጠሪያ ጭምር አካቶ ቅልንብትራ ( κολυμβήθρα / kolumbethra) ሲል እናገኘዋለን::
ቤተ ሳይዳ ዘይሁዳ ባለ አምስት በር መመላለሻ አምስት ዓይነት ድውያን ፈውስን ከማየ ጥምቀቱ ሲጠባበቁ የሚኖሩባት በአምስተኛው የዮሐንስ ወንጌል ተጽፎ ያለ የጌታችን ማዳን የተገለጠባት ሥፍራ ናት። "እስመ ኦሪት መንፈቀ ፍጻሜ ወኅዳጠ መክፈልት" እንዲላት መልአከ እግዚአብሔር ለቀድሶተ ማይ ወርዶ ውኃውን ሲያናውጥ ቀድሞ የገባ የሚነጻባት በዕለቱ ከአንድ በቀር ለሌላው ፈውስ የማይደገምባት ቦታ ናት ይህችው "ቤተ ሳይዳ" ።
ታዲያ ከእነዚህ መካከል ነበር ይህን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል የድኅነት ተስፈኛ ሆኖ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ "መፈውስ ወማሕየዊ" ጌታችን ቀርቦ አዎን እንዲለው እያወቀ ብወዳችሁ አላዋቂ የሆነ የእናንተን ሥጋ ተዋሕጄ መጣሁላችሁ ሲለን ("አኮ ኢያእሚሮ ኅቡአተ አላ ከመ የሀብ መካነ ለጥንተ ትስብዕቱ ዘኢየአምር ኅቡአተ" እንዲል) ያንን በሽተኛ "ትፈቅድኑ ትሕየው? … ባድንህ ፈቃድህ ነውን?" አለው። የሚገርመው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራውያን መልእክቱ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፪ ላይ "የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።" ብሎ የመሰከረለት ጌታችን ፈውስን በመጠባበቅ ከመዳን ውጪ ሌላ ዓላማ ያልነበረውን ይህን ሰው ዓይቶ ፈቃዱን እያወቀ ግን ፍቀድልኝና ላድንህ አለው። " ሰው በከንቱ ወራቱ ቍጥርና እንደ ጥላ በሚያሳልፈው ዘመኑ በሕይወቱ ሳለ ለሰው የሚሻለውን የሚያውቅ ማነው? "(መክ ፮፥፲፪) እንዲል የሚያስፈልገንን ሳንነግረው የሚያውቅ የሚሰጠንም ከእርሱ ከፈጣሪው ውጪ በእውነት ማን አለ? መፃጉዕ ግን ኋላ የሚክድ ነውና "በሰንበት ላይ ያመጸ ፣ ራሱን ከአብ የሚያስተካክል ፣ ቤተመቅደሱን አፍርሱት ያለ መች አድነኝ ብየው ሳልፈቅድለት ያዳነኝና አልጋ ያሸከመኝ ነውኮ" ብሎ በዕለተ ዓርብ የሚከስበትን ሲያሳጣውና ለኋላ ጥፋቱ የገዛ ኅሊናው እንዲቀጣው ፈቃዱን ጠየቀው። "አልብየ ሰብእ" ሰው የሌለኝ ሆኖ እንጂ ያንንማ ማን ይጠላል በሚል ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ድኅነትን ፈቅዶ ገለጠ። እስከ ሁከተ ማይ ሳያቆየው "ተንሥእ ንሣእ ዓራተከ ወሑር … ተንስና አልጋህን አንስተህ ሂድ" አለው ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ ዘመን የተሸከመች ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ።
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
ይህች "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ ምሣሌቷ ብዙ ኅብር ያለው ነው። ለአብነትም ያህል ምሳሌ፦
፩· ውኃው የቤተ አይሁድ ምሳሌ አምስት መመላለሻ የሕግጋተ ኦሪት የአምስቱ መፃሕፍተ ሙሴ በነዚያ ታጥረው ለመኖራቸው። ቀድሞ የገባባት አንዱ እንዲድን እነሱም አንድነት ቤተ እስራኤል ተሰኝተው ለመኖራቸው ምሳሌ ነው።
፪· በሌላ አገባብ
፠ በዚያ ውኀውን ለማወክ የወረደው መልአክ = ቀሳውስት(ካህናት) "ለቀድሶተ ማየ ጥምቀት" የመውረዳቸው ምሳሌ ነው።
፠ የመጠመቂያ ውኀው = የማየ ጥምቀት ምሳሌ ሲሆን
፠ በቤተ ሳይዳ ያለው አምስቱ እርከን(መመላለሻ) =የአምስቱ አእማደ ምስጢር በዚያ ሊያምኑ ያሉ ተስፈኞችና ያመኑባትም ልጅነትን ያገኙባታልና።
፠ አምስቱ ዓይነት ድውያንም የአምስቱ ጾታ ምዕመናን ከነ ፈተናቸው የተመሳጠረበት ምሳሌ ነው (አእሩግ=በፍቅረ ነዋቅይ....ወራዙት=በዝሙት.... አንስት=በትውዝፍት በምንዝር ጌጥ....ካህናት=በትእቢት አእምሯችን ረቂቅ መዓረጋችን ምጡቅ እያሉ... መነኮሳት=በስስት ምግብን በሹት ጊዜ ባያገኙት ይልቁንም አጽንኦ በአት እየፈቱ በአንሰሐስሖ ዘበከንቱ ይፈትናቸዋል) ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
፫· ለአዲስ ኪዳን ድኅነተ ነፍስ ምስጢራዊ ምሳሌ አገባብም አለው፤
፠ ቤተሳይዳ የበጎች በር በመባልዋ እና በኦሪቱ በጎች ወደ ቤተ መቅደስ ወጥተው ለመስዋዕት ከመቅረባቸው አስቀድሞ የሚታጠቡበት ውኀ ያለበት በመሆኑ ለበአዲስ ኪዳንም የመንፈስ ቅዱስ ልጅነት የሚገኝባትን ወደ አማናዊ መስዋዕት ቅዱስ ቁርባን የምታደርስ የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ
፠ አምስቱን መመላለሻየምታደርስ ደግሞ ወደ ፍፃሜ ሕግ ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ እግዚአብሔር አልፎም ፍጽምት ወደሆነች ወደ ሕግጋተ ወንጌልም የምታደርስ የአምስቱ ብኄረ ኦሪት መፃሕፍተ ሙሴ ምሳሌ ያደርጋቸዋል።
፠ ለሁከተ ማይ የወረደው መልአክ የሰማዩ አቃቤ ሥራይ የክርስቶስ ምሳሌ ነው
፠ ከአንድ ብቻ በቀር ሕሙም በአንድ ዕለት አለመዳኑ በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥላ ሥር አምነው ያሉ ምዕመናንና ምዕመናት ብቻ ድኅነተ ነፍስ እናዳላቸው ያሳያል።
፠ የውኀው መናወጽ የሰቃልያነ ክርስቶስ "ሁከተ አይሁድ" ምሳሌ ጥንቱን "ስቅሎ ስቅሎ " የሚለው ያ ቁጣ የዕለተ ዓርብ መድኃኒት መገኛ ነውና።
እስኪ ደግሞ በማጠቃለያው ወደ መፃጉዕ ታሪክ እንመለስና ጥቂት ፍሬ ነገር ለሕይወታችን እንስማ።
ቀድሞ በ
ዛሬም
ከደዌው :ከማጣቱ :ከችግሩ: ከሥጋ ኑሮ ጉድለቱ ዳግመኛ ለመታረቅ እንደ መፃጉዕ አምላኩን ያልረሳ ማነው?
ተአምራቱን አይቶ ቃሉን ሰምቶ አምላኩን ያስታወሰስ ማነው " ቃሉን ያይና ይሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ምክር የቆመ ማን ነውና? ቃሉንስ ያደመጠ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር. ፳፫፥፲፰) ማንም። ጌታችን ባስተማረው ማሕየዊ ቃሉ ላይ እንኳ ሳይቀር ያመጹትን አይሁድ እስኪ ተመልከቱ " ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።" ሉቃ ፲፮፥፲፬ እኛንም ቢሆን ከአዳም እስራት ነፃ ያደረገንን አምላክ ውለታ ዘንግተን በቃሉ የምናፌዝ ሁላችንን ወደ ልባችን እንድንመለስ ነቢዩ እንዲህ ሲል ይመክረናል "እስራት እንዳይጸናባችሁ አታፊዙ " ( ኢሳ· ፳፰፥፳፪ ) ይመክረናል።
በፍፃሜ ሕይወቱ በአውደ ምኩናን የሀሰት ክስ የቀረበበትን ይህን የእውነትና የሕይወት ጌታ ቀድሞ ወደ መጠመቂያው እንኳ ለመቅረብ አቅም ያልነበረው ዛሬ ግን አልጋ ለመሸከም በበቃውና ያለ ተረፈ ደዌ በጸናው ኃይሉ የጌታውን ጉንጮች በጥፊ የመምታት ጉልበትና ድፍረት አገኘ። "ዘተሰብሐ ውስተ ገጸ ሙሴ በትስብእቱ ተጸፍአ ገጾ ወተቀስፈ ዘባኖ በእንቲአነ ከመ ይፈጽም ስምዓ ነቢይ ዘይብል መጠውኩ ዘባንየ ለመቅሰፍት ወመላትሕየ ለጽፍአት… በገጹ ነፀብራቅ የሙሴን ፊት ያበራ እርሱ በነቢዩ ጀርባዬን ለግርፋት ጉንጮቼንም ለጽፍአት ሰጠሁ ተብሎ የተነገረውን ለመፈጸም ለእኛ ሲል ፊቱን በጥፊ ተመታ ጀርባውንም ተገረፈ "እንዲል (ሰይፈ ሥላሴ)
አምላከ ምሕረት እግዚአ ለሰንበት ቀድሞ "ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ … ከዚህ የጠናው "ስለ ደዌ ሥጋ ፈንታ ደዌ ነፍስ" እንዳያገኝህ ሁለተኛ እንዳትበድል" (ቁ ፲፬) ያለውን ዘንግቶ ደዌ ዘኃጢአትን ጠርቶ ተወዳጃት፤ በዕለተ ዓርብ የጌታውን ጉንጮች የጸፉች እጁም ደርቃ
"መፃጉዕ ይትዐረቅ ምስለ ብእሲት ደዌሁ
ሠላሳ አዝማነ እስመ ነበረት ምስሌሁ"
☞ መፃጉዕ ከሚስቱ ከደዌው ይታረቅ
ሠላሳ ዓመት አብራው ኖራለች ሳትርቅ
አብረው አያሌ ዓመታት የኖሩ ባልና ሚስት ሲፋቱ ተነፋፍቀው መለያየቱ እምቢኝ እንደሚላቸውና እንደሚታረቁ ሁሉ ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ተብሎ ሳለ ጌታውን ጸፍቶ መፃጉዕም ዳግመኛ ወደ ፴፰ ዓመት "የአልጋ ወዳጁ" ደዌ መመለሱን የቅኔው ምስጢር ያስተምረናል።
እንግዲህ እኛም በኃጢአት ከሚመጣ ደዌ ተጠብቀን በአባታዊ ምሕረቱ የሚጠብቀንን ቸሩ አምላካችንን እያመሰገንን በቤቱ እንድንጸና መፃጉዕን "ተነሳ" እንዳለው እኛንም ከወደቅንበት ዓራተ ዝንጋኤ፣ ዓራተ ኃጢአት በንስሃ እንዲያነሳንና ዳግም ከመበደልም እንዲጠብቀን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን። አሜን
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ☞ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ·ም· በጣልያን ሮም የተፃፈ
፩· ውኃው የቤተ አይሁድ ምሳሌ አምስት መመላለሻ የሕግጋተ ኦሪት የአምስቱ መፃሕፍተ ሙሴ በነዚያ ታጥረው ለመኖራቸው። ቀድሞ የገባባት አንዱ እንዲድን እነሱም አንድነት ቤተ እስራኤል ተሰኝተው ለመኖራቸው ምሳሌ ነው።
፪· በሌላ አገባብ
፠ በዚያ ውኀውን ለማወክ የወረደው መልአክ = ቀሳውስት(ካህናት) "ለቀድሶተ ማየ ጥምቀት" የመውረዳቸው ምሳሌ ነው።
፠ የመጠመቂያ ውኀው = የማየ ጥምቀት ምሳሌ ሲሆን
፠ በቤተ ሳይዳ ያለው አምስቱ እርከን(መመላለሻ) =የአምስቱ አእማደ ምስጢር በዚያ ሊያምኑ ያሉ ተስፈኞችና ያመኑባትም ልጅነትን ያገኙባታልና።
፠ አምስቱ ዓይነት ድውያንም የአምስቱ ጾታ ምዕመናን ከነ ፈተናቸው የተመሳጠረበት ምሳሌ ነው (አእሩግ=በፍቅረ ነዋቅይ....ወራዙት=በዝሙት.... አንስት=በትውዝፍት በምንዝር ጌጥ....ካህናት=በትእቢት አእምሯችን ረቂቅ መዓረጋችን ምጡቅ እያሉ... መነኮሳት=በስስት ምግብን በሹት ጊዜ ባያገኙት ይልቁንም አጽንኦ በአት እየፈቱ በአንሰሐስሖ ዘበከንቱ ይፈትናቸዋል) ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
፫· ለአዲስ ኪዳን ድኅነተ ነፍስ ምስጢራዊ ምሳሌ አገባብም አለው፤
፠ ቤተሳይዳ የበጎች በር በመባልዋ እና በኦሪቱ በጎች ወደ ቤተ መቅደስ ወጥተው ለመስዋዕት ከመቅረባቸው አስቀድሞ የሚታጠቡበት ውኀ ያለበት በመሆኑ ለበአዲስ ኪዳንም የመንፈስ ቅዱስ ልጅነት የሚገኝባትን ወደ አማናዊ መስዋዕት ቅዱስ ቁርባን የምታደርስ የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ
፠ አምስቱን መመላለሻየምታደርስ ደግሞ ወደ ፍፃሜ ሕግ ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ እግዚአብሔር አልፎም ፍጽምት ወደሆነች ወደ ሕግጋተ ወንጌልም የምታደርስ የአምስቱ ብኄረ ኦሪት መፃሕፍተ ሙሴ ምሳሌ ያደርጋቸዋል።
፠ ለሁከተ ማይ የወረደው መልአክ የሰማዩ አቃቤ ሥራይ የክርስቶስ ምሳሌ ነው
፠ ከአንድ ብቻ በቀር ሕሙም በአንድ ዕለት አለመዳኑ በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥላ ሥር አምነው ያሉ ምዕመናንና ምዕመናት ብቻ ድኅነተ ነፍስ እናዳላቸው ያሳያል።
፠ የውኀው መናወጽ የሰቃልያነ ክርስቶስ "ሁከተ አይሁድ" ምሳሌ ጥንቱን "ስቅሎ ስቅሎ " የሚለው ያ ቁጣ የዕለተ ዓርብ መድኃኒት መገኛ ነውና።
እስኪ ደግሞ በማጠቃለያው ወደ መፃጉዕ ታሪክ እንመለስና ጥቂት ፍሬ ነገር ለሕይወታችን እንስማ።
ቀድሞ በ
ቤተ ሳይዳ
እያለ የነበረበትን ያንን ሁሉ ጭንቅ ኋላ በሊቶስጥሮስ የፍርድ ገበታ ቆሞ በረሳ ጊዜ " ታዲያ ቢያድነኝ በከንቱ መች ሆነና የገዛ አልጋዬን ትቼለት የመጣሁ ለመዳኔ ዋጋ የከፈልኩበት አይደለምን?" እንኳ እንዳይል ያለ ተረፈ ደዌ አንስቶት ያለህን ይዘህ ሂድ እኔ ከአንተ አንዳች አልሻም ባሰኘ ቃል ሸኝቶታል። ግን ታዲያ ይህ ምስኪን መፃጉዕ "ሰው የለኝም" ብሎ የደረሰለትን ሰው ረሳ ማን እንደሆነ እንኳ አላወቀም። ወንጌላዊውም "ዘሐይወ ኢያእመረ ዘአሕየዎ …የዳነውኋላ የተፈወሰው ያዳነውን አላወቀውም" ( ዮሐ.፭፥፲፫) ይለዋል። ያዳነው ማን እንደሆነ ሲጠየቅ ለምሥጋና ያይደለ ለክስ ነበር ስሙን የፈለገው። በኑሮው የማንነቱ መገለጫ "ከሚጣፍጠውም ምግቤ ሆዱን ሞላ፥ እኔንም ጣለኝ።" ተብሎ ለናቡከደነፆር በነቢዩ እንደተነገረ ያለ ነው (ኤር.፶፩፥፴፬ ) በአገራችንም ካለው ብሂለ አበው "ታሞ የተነሳ ፈጣሪውን ረሳ" የሚለው እንደነዚህ ያሉትን በሚገባ ለመግለጽ የተነገረ ነው። ሊቀ ነቢያት ሙሴን በዘዳግም ፲ ቁጥር ፳፩ ላይ እንዲህ ይላል "ዓይኖችህ ያዩትን እነዚህን ታላላቆች የሚያስፈሩትንም ነገሮች ያደረገልህ እርሱ ክብርህ ነው፥ እርሱም አምላክህ ነው።" ነገር ግን ይህን ሁሉ ያደረገውን አምላክ ብዙዎች የነበሩ "ህዝበ እስራኤል" ረስተው አሳዝነውት በምድረበዳ በከንቱ ወድቀው ቀሩ ..... ዛሬም
ከደዌው :ከማጣቱ :ከችግሩ: ከሥጋ ኑሮ ጉድለቱ ዳግመኛ ለመታረቅ እንደ መፃጉዕ አምላኩን ያልረሳ ማነው?
ተአምራቱን አይቶ ቃሉን ሰምቶ አምላኩን ያስታወሰስ ማነው " ቃሉን ያይና ይሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ምክር የቆመ ማን ነውና? ቃሉንስ ያደመጠ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር. ፳፫፥፲፰) ማንም። ጌታችን ባስተማረው ማሕየዊ ቃሉ ላይ እንኳ ሳይቀር ያመጹትን አይሁድ እስኪ ተመልከቱ " ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።" ሉቃ ፲፮፥፲፬ እኛንም ቢሆን ከአዳም እስራት ነፃ ያደረገንን አምላክ ውለታ ዘንግተን በቃሉ የምናፌዝ ሁላችንን ወደ ልባችን እንድንመለስ ነቢዩ እንዲህ ሲል ይመክረናል "እስራት እንዳይጸናባችሁ አታፊዙ " ( ኢሳ· ፳፰፥፳፪ ) ይመክረናል።
በፍፃሜ ሕይወቱ በአውደ ምኩናን የሀሰት ክስ የቀረበበትን ይህን የእውነትና የሕይወት ጌታ ቀድሞ ወደ መጠመቂያው እንኳ ለመቅረብ አቅም ያልነበረው ዛሬ ግን አልጋ ለመሸከም በበቃውና ያለ ተረፈ ደዌ በጸናው ኃይሉ የጌታውን ጉንጮች በጥፊ የመምታት ጉልበትና ድፍረት አገኘ። "ዘተሰብሐ ውስተ ገጸ ሙሴ በትስብእቱ ተጸፍአ ገጾ ወተቀስፈ ዘባኖ በእንቲአነ ከመ ይፈጽም ስምዓ ነቢይ ዘይብል መጠውኩ ዘባንየ ለመቅሰፍት ወመላትሕየ ለጽፍአት… በገጹ ነፀብራቅ የሙሴን ፊት ያበራ እርሱ በነቢዩ ጀርባዬን ለግርፋት ጉንጮቼንም ለጽፍአት ሰጠሁ ተብሎ የተነገረውን ለመፈጸም ለእኛ ሲል ፊቱን በጥፊ ተመታ ጀርባውንም ተገረፈ "እንዲል (ሰይፈ ሥላሴ)
አምላከ ምሕረት እግዚአ ለሰንበት ቀድሞ "ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ … ከዚህ የጠናው "ስለ ደዌ ሥጋ ፈንታ ደዌ ነፍስ" እንዳያገኝህ ሁለተኛ እንዳትበድል" (ቁ ፲፬) ያለውን ዘንግቶ ደዌ ዘኃጢአትን ጠርቶ ተወዳጃት፤ በዕለተ ዓርብ የጌታውን ጉንጮች የጸፉች እጁም ደርቃ
ሰላ
ቀርታለች አንዱ ሊቅ ይህን አልሰማ ባይ መፃጉዕ እና ይቅር ባይ አምላኩን እያደነቀ በጉባዔ ቃናው ይህን ተናገረ "መፃጉዕ ይትዐረቅ ምስለ ብእሲት ደዌሁ
ሠላሳ አዝማነ እስመ ነበረት ምስሌሁ"
☞ መፃጉዕ ከሚስቱ ከደዌው ይታረቅ
ሠላሳ ዓመት አብራው ኖራለች ሳትርቅ
አብረው አያሌ ዓመታት የኖሩ ባልና ሚስት ሲፋቱ ተነፋፍቀው መለያየቱ እምቢኝ እንደሚላቸውና እንደሚታረቁ ሁሉ ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ተብሎ ሳለ ጌታውን ጸፍቶ መፃጉዕም ዳግመኛ ወደ ፴፰ ዓመት "የአልጋ ወዳጁ" ደዌ መመለሱን የቅኔው ምስጢር ያስተምረናል።
እንግዲህ እኛም በኃጢአት ከሚመጣ ደዌ ተጠብቀን በአባታዊ ምሕረቱ የሚጠብቀንን ቸሩ አምላካችንን እያመሰገንን በቤቱ እንድንጸና መፃጉዕን "ተነሳ" እንዳለው እኛንም ከወደቅንበት ዓራተ ዝንጋኤ፣ ዓራተ ኃጢአት በንስሃ እንዲያነሳንና ዳግም ከመበደልም እንዲጠብቀን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን። አሜን
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ☞ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ·ም· በጣልያን ሮም የተፃፈ
╔✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╗
❀…#ሥራሽ_ያውጣሽ! …❀
╚✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╝
† ከዚህም በኋላ ተርቢኖስን ሚስትህ የነበርኩ ዕሌኒ እኔ ነኝ አንተ ግን በብረት ሣጥን አድርገህ ወደ ባሕር ስትጥለኝ ዐመፅን ክፋትን የምትሠሪ አንቺ ክፉ ሴት #ሥራሽ_ያውጣሽ [ይከተልሽ]
☞ ሥራሽ መልካም ከሆነ ያድንሽ ክፉ ከሆነ ግን ያጥፋሽ ብለህ ተናገርከኝ ይህንንም እያልክ ከጥልቅ ባሕር ውስጥ ጣልከኝ። ለእኔ ግን ንጹሕ የሆነ ሥራዬ በጎ እውነተኛ ሃይማኖቴ ተከትሎኝ ክብር ይግባውና ፈጣሪዬና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ብዛት አሁን ከአለሁበት ደረጃ ላይ አደረሰኝ አለችው።
† ወእምድኅረዝ ትቤሎ ለተርቢኖስ አነ ይእቲ ዕሌኒ ብእሲትከ አንተሰ እንዘ ትገድፈኒ ውስተ ባሕር ገቢረከ በሣፁን ነበብከኒ እንዘ ትብል ኦ ብእሲት እኪት ገባሪተ ዐመፃ ወእከይ #ዝ_ግብርኪ_ለይትሉኪ ወለእመ ኮነ ሠናየ ያሕዩኪ ወለእመሰ ኮነ እኩየ ያህጕልኪ።
☞ ወዘንተ ቃለ እንዘ ትብል ወገርከኒ ውስተ ባሕር ዕሙቅ። ወሊተሰ ዘተለወኒ ግብርየ ንጹሕ ወምግባርየ ሠናይ ወሃይማኖትየ እሙን አብጽሐኒ ኀበ ዝንቱ ኀበ ሀሎኩ ቦቱ በብዝኀ ኂሩቱ አምላኪየ ወእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት።
[ድርሳነ መስቀል]
"ወይመጽእ ዳግመ በስብሐት ወበዐቢይ ክብር ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ ወይፈድዮ ለኵሉ በከመ ምግባሩ ⇨ ዳግመኛም ፡ በሕያዋንና ፡ በሙታን ፡ ይፈርድ ፡ ዘንድ ፡ በታላቅ ፡ ክብርና ፡ ጌትነት ፡ ይመጣልና ፣ ፡ ለሁሉም ፡ እንደእየ ፡ ሥራው ፡ ይከፍለዋል"
[መጽሐፈ ዲድስቅልያ 30:33]
https://youtu.be/a5Aula5LEqA
❀…#ሥራሽ_ያውጣሽ! …❀
╚✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╝
† ከዚህም በኋላ ተርቢኖስን ሚስትህ የነበርኩ ዕሌኒ እኔ ነኝ አንተ ግን በብረት ሣጥን አድርገህ ወደ ባሕር ስትጥለኝ ዐመፅን ክፋትን የምትሠሪ አንቺ ክፉ ሴት #ሥራሽ_ያውጣሽ [ይከተልሽ]
☞ ሥራሽ መልካም ከሆነ ያድንሽ ክፉ ከሆነ ግን ያጥፋሽ ብለህ ተናገርከኝ ይህንንም እያልክ ከጥልቅ ባሕር ውስጥ ጣልከኝ። ለእኔ ግን ንጹሕ የሆነ ሥራዬ በጎ እውነተኛ ሃይማኖቴ ተከትሎኝ ክብር ይግባውና ፈጣሪዬና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ብዛት አሁን ከአለሁበት ደረጃ ላይ አደረሰኝ አለችው።
† ወእምድኅረዝ ትቤሎ ለተርቢኖስ አነ ይእቲ ዕሌኒ ብእሲትከ አንተሰ እንዘ ትገድፈኒ ውስተ ባሕር ገቢረከ በሣፁን ነበብከኒ እንዘ ትብል ኦ ብእሲት እኪት ገባሪተ ዐመፃ ወእከይ #ዝ_ግብርኪ_ለይትሉኪ ወለእመ ኮነ ሠናየ ያሕዩኪ ወለእመሰ ኮነ እኩየ ያህጕልኪ።
☞ ወዘንተ ቃለ እንዘ ትብል ወገርከኒ ውስተ ባሕር ዕሙቅ። ወሊተሰ ዘተለወኒ ግብርየ ንጹሕ ወምግባርየ ሠናይ ወሃይማኖትየ እሙን አብጽሐኒ ኀበ ዝንቱ ኀበ ሀሎኩ ቦቱ በብዝኀ ኂሩቱ አምላኪየ ወእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት።
[ድርሳነ መስቀል]
"ወይመጽእ ዳግመ በስብሐት ወበዐቢይ ክብር ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ ወይፈድዮ ለኵሉ በከመ ምግባሩ ⇨ ዳግመኛም ፡ በሕያዋንና ፡ በሙታን ፡ ይፈርድ ፡ ዘንድ ፡ በታላቅ ፡ ክብርና ፡ ጌትነት ፡ ይመጣልና ፣ ፡ ለሁሉም ፡ እንደእየ ፡ ሥራው ፡ ይከፍለዋል"
[መጽሐፈ ዲድስቅልያ 30:33]
https://youtu.be/a5Aula5LEqA
YouTube
ስራሽ ያውጣሽ + ዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን::
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_...
እግዚአብሔር…
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_...
እግዚአብሔር…
የደብረ ዘይትን ሳምንት ለውይይት!
ሳምንቱን ለተከታታይ ፬ቱ ቀናት እንደ ሥሉስ ቅዱስ መልካም ፈቃድ በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ ጥያቄዎች በተከታዮቹ ፬ት ሰንበትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመምህራንና ከመጻሕፍት ያገኘኋቸውን ጥቂት ሐሳቦች በዝርዝር ሐተታ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።
እስከዛው ግን የሚሰማችሁን ሐሳብና ጥያቄ ብታሰፍሩ ለመማማር እድሉን እንደሚያሰፋልን እምነቴ ነው።
፩] ታቦተ ሰንበት
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይዝ» … መባሉ ስለምን ነው?
⚀ ሰኞ መጋቢት ፲፩ በሠርክ የሚመለስ
፪] ሰንበትና ስግደት
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
⚁ ማክሰኞ መጋቢት ፲፪ በሠርክ የሚመለስ
፫] ዕለተ ሰንበት
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ የሚመለስ
፬] ተግባረ ሰንበት
☞ የሰንበት ዕረፍት ፣ የሰንበት መብራት ፣ የሰንበት ውኃ … የሚሉት ትውፊቶች በሐዲስ ኪዳን እንዴት ይታያሉ?
⚃ ሐሙስ መጋቢት ፲፬
ምናልባት ተጨማሪ ማየት የሚገባን የሰንበት ጉዳይ ካለ ⚄ ዓርብ መጋቢት ፲፭ ከማጠቃለያ ጋር የምንመለስ ይሆናል!
ኦርቶዶክስ መልስ ናት! ኦርቶዶክሳዊ መልስ አለው።
ሳምንቱን ለተከታታይ ፬ቱ ቀናት እንደ ሥሉስ ቅዱስ መልካም ፈቃድ በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ ጥያቄዎች በተከታዮቹ ፬ት ሰንበትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመምህራንና ከመጻሕፍት ያገኘኋቸውን ጥቂት ሐሳቦች በዝርዝር ሐተታ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።
እስከዛው ግን የሚሰማችሁን ሐሳብና ጥያቄ ብታሰፍሩ ለመማማር እድሉን እንደሚያሰፋልን እምነቴ ነው።
፩] ታቦተ ሰንበት
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይዝ» … መባሉ ስለምን ነው?
⚀ ሰኞ መጋቢት ፲፩ በሠርክ የሚመለስ
፪] ሰንበትና ስግደት
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
⚁ ማክሰኞ መጋቢት ፲፪ በሠርክ የሚመለስ
፫] ዕለተ ሰንበት
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ የሚመለስ
፬] ተግባረ ሰንበት
☞ የሰንበት ዕረፍት ፣ የሰንበት መብራት ፣ የሰንበት ውኃ … የሚሉት ትውፊቶች በሐዲስ ኪዳን እንዴት ይታያሉ?
⚃ ሐሙስ መጋቢት ፲፬
ምናልባት ተጨማሪ ማየት የሚገባን የሰንበት ጉዳይ ካለ ⚄ ዓርብ መጋቢት ፲፭ ከማጠቃለያ ጋር የምንመለስ ይሆናል!
ኦርቶዶክስ መልስ ናት! ኦርቶዶክሳዊ መልስ አለው።
ክፍል ፩] ታቦተ ሰንበት
━━━━✦✿✦━━━━
በዓለ ደብረ ዘይት እኩለ ጾም ነው፤ የጌታችን ምጽኣቱ ዓለም በተፈጠረበት ዕለት በዕለተ ሰንበት መሆኑን ቅድስት ቤተክርስቲያን ታምናለች ታስተምራለችም! ቸሩ ጌታችን "በሰንበት ኢይኩን ጉያክሙ ⇨ ስደታችሁ በሰንበት አይሁን" ብሎ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰብስቦ በዕለተ ሰንበት አሕማላት (የለመለሙ ዕፀዋት) ካሉበት ቦታ ከ"ዐጸደ ሐምል" ተራራ ዐጸደ ዘይትም ወደበዛበት ሥፍራ አስጠግቶ ነገረ ምጽአቱን ያስተማረበት መታሰቢያ በዓለ ደብረ ዘይት ይባላል። ቀኑ ለኹዳዴ እኩለ ፆም ነው!
ባለቅኔው
"ተዝካሮ ግበሩ ባሕታውያን ደቂቁ፤
ለምውት ጾም እስመ ደብረ ዘይት መንፈቁ።" እንዳለ።
ገባሬ ሕይወት እግዚአ ለሰንበት ራሱ ጌታችን የቀደሳትና ከፍ ከፍ ያደረጋት ዕለት በመሆኗ "ቀደሳ ወአልዓላ" እያልን በእርሷ ደስ ብሎን ስናከብራትና ስናገናት እንውላለን።
በእርግጥ ጊዜው የእግዚአብሔርን በዓላት ከምድር ላይ እንሻር የሚሉ የበዙበት ዘመን መሆኑን ስናይ የዳዊት ትንቢት እያነሳን የትንቢቱ መፈጸሚያ በሆኑት እንደነቃለን።
“አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር አሉ።” ☞ 【መዝ ፸፬፥፰ 】
በዓለም ታሪክ እ.አ.አ. ከ1536 በፊት «በካቶሊካዊት» ቤተ እምነት በዐመት ውስጥ 95 የሚሆኑ የ«ቤተክርስቲያኗ» በዓላትና 52 ሰንበታት ይከሩ እንደነበር፤ ነገር ግን ከ1536 አንስቶ በተሃድሷውያኑ ጫና በዓላቱን ወደ 27 አውርደዋቸዋል።
ኋላ ላይ የተነሱት ከካተሊካዊ ባህል ፕሮቴስታንቱን እናነፃለን የሚሉ ወገኖች (The Puritans) በዓላቶችን በሙሉ (ገናና ፋሲካን ሳይቀር) በመሻር ዝክረ ዕለታትን ከሁለት ወገን ይከፍላሉ፦
① ችግር ጉዳትና አደጋ ከላይ የወረደ ቁጣ ተብለው የሚዘከሩባቸው ቀናት «ዕለታተ ፆም» ( Days of Fasting) ሲባሉ
② ልዩ በረከት ከአምላክ የሚሰጡባቸው ቀናት ዕለታተ ባርኮ/የምስጋና ቀናት (Days of Thanksgiving) ብለዋቸዋል።
【James W. Baker የተጻፈው "Thanksgiving: The Biography of an American Holiday" 】
ዛሬም የእኛዋን ቤተክርስቲያን አውቀው ይሁን ሳያውቁ በዚህ ወጀብ የሚንጧትን አበልጻጊዎች አስታግሶ ፣ ከመፍቀሬ ሁከት ሰይጣን ሰውሮ ፣ በመፍቀርያነ ምሕረት መላእክቱ ከልሎ ፈተናውን ሁሉ ያሻግርልን።
ወደዛሬው የመጀመሪያ ቀን ጉዳያችን እንለፍ፤ ትናንት በተሠጠው ጥቆማ መሠረት [https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=6005958766119252&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz]
ታቦተ ሰንበትን የሚመለከቱ ጥቂት ሐሳቦች እናሳለን። መነሻ ጥያቄው እንዲህ የሚል ነው
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይት» … መባሉ ስለምን ነው?
ቀድመን የሚከተለውን ጥያቄ እናንሳ
▶ ጽላት/ታቦት ለማን ይቀረጻል (በማን ይሰየማል) ?
በአጭር መልስ በስማቸው ጽላት የሚቀረጽላቸው ፣ መቅደስ የሚታነጽላቸው ፣ ጠበል የሚፈልቅና የሚሰየምላቸው ፣ ድርሳን ገድል መልክእ የሚጻፍ የሚደረስላቸው ቅዱሳን ናቸው።
▶ ቅዱሳንስ የምንለው ማንን ነው?
የኔታ ሐረገወይን አገዘ (ሊቀ ጠበብት) ነገረ ቅዱሳንን ሲያስረዱ ቅድስና የባህሪ ገንዘቡ የሆነ አምላክነትና ፈጣሪነትን ከማንም ያልተቀበለ ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ይሁንና ግን ከባህሪ ቅድስና በታች ያሉ በሥጦታ ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ቅዱሳንም አሉ ፤ እነዚህም ቅዱሳን/ቅዱሳት ዘበጸጋ ይባላሉ።
ለዚህ የጸጋ ቅድስና ምክንያቶች (ምንጮች) ደግሞ በጥቅሉ ሦስት ናቸው።
★ በመጽናት ቅዱሳን የምንላቸው አሉ ፦ ቅዱሳን መላእክት
★ በመመረጥ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ እመቤታችን፣ ንዋያት [ታቦት፣ መስቀል፣ መካናት/መቅደስ፣ ሥዕላት ፣ ንዋያተ ቅድሳት … ] ፣ ዕለታት ፣ መጻሕፍት፣ በጸሎት የከበሩ ቅብዓት [ቅብዓ ሜሮን ፣ ቅብዕ ቅዱስ፣ ቅብዓ ቀንዲል… ]
★ በተጋድሎ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ በቅድስናው ማዕረግ ከፍ ያሉ መስተጋድላን ጻድቃን ጽኑዓን …
መጽሐፍ ‘ሰብእ ይቄድሶ ለመካን ፤ ወመካን ይቄድሶ ለሰብእ’ ይላል፤ ደግሞም ቅዱሳን የረገጡትን ቦታ ብቻ ሳይሆን ገቢረ ተዓምራት የፈጸሙባቸውን ዕለታት ጭምር ቅዱስ ያሰኛሉ።
" ኀበ ቅዱሳን ይከውን ቅዱሰ ⇨ ከቅዱሳን ጋር የሚውል ቅዱስ ይኾናልና" 【ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፻፳፮】
ሰንበት ቅድስት ዕለት ናት። በእርግጥ በገዳማትና በአንድአንድ "ሊቃውንት" አንደበት የሰንበት ታቦት የሚባል የለም "እግዚኣ ለሰንበት" እንጂ ሲሉ ይደመጣል።
በአገባቡ «እግዚኣ ሰንበትና እግዚአ ለሰንበት» የሚሉት መልእክታት ፍቺና ምሥጢራቸው ለየቅል ነው።
እስኪ ደግመን አንድ ጥያቄ እናንሳ
▶ ለዕለታትና ለንዋያት ታቦት ይቀረጻል ወይ?
መልሱ፦ አዎ።
አስረጅ ፦ በእመቤታችን ስም ጽላት/ታቦት እንደሚቀረጽ ሁላችን እናውቃለን ፤ የዕረፍቷን መታሰቢያ መነሻ አድርጎ በ፳፩ ክብረ በዓሉ የሚታሰብ ሲሆን ሌሎቹን ታቦተ ልደታ ፣ ታቦተ በዓታ … እያሉ ለቀናቱ መታሰቢያ በመስጠት ዕለታት ይዘከሩባቸዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በቅዱስ መስቀሉ ስም ጽላት/ታቦት ተቀርጾ መቅደስ ታንጾ ድርሳን ተደርሶ መልክእ ተጽፎ ሲከብር እናያለን።
ሰንበትም እንዲሁ ድርሳነ ሰንበት ፣ መልክአ ሰንበት ፣ ታቦተ ሰንበት ያለው እንዲያውም የበዓላት ኹሉ በኲር የሆነ በዓል ነው።
ከመልኩ ክፍል ይህን የሚያስረዳ መልእክት እንዲህ ሠፍሮ እናገኛለን
ሶበ አእመርኩ በስምኪ ከመ ታቦተ ይቄድሱ፡
ወድሶተኪ ወጠንኩ ለአእምሮትየ መጠነ ናእሱ፡
ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ንግሥተ መሳፍንት ስሱ፡
እለሰ ኪያኪ አርኰሱ፡
ፈቀዱ ሞተ ወኵነኔ ኃሠሡ፡፡
[በስምሽ እንደታቦት የሚቀደስ መሆኑን ባወቅኹ ጊዜ በትንሿ እውቀቴ ምስጋናሽን ጀመርኩ
ለስድስቱ መሳፍንት ንግሥት የምትሆኚ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ አንቺንስ ያረከሱ ሰዎች ሞትን ወደው መኮነንን የፈለጉ ናቸው።]
አንዳንዶች እግዚኣ ለሰንበት በሚል መጠሪያ የሰንበት ጌታ ስለሚል « ጌታ እንጂ ሰንበትን የሚወክል ታቦት የለም» ይላሉ። ይሁን እንጂ ሰንበት ራሱ ዕረፍት ነው ታቦተ ማርያም ተዝካረ ዕረፍቷ እንደሚታሰብበት ታቦታ ሰንበትም በሁለቱ ሰንበታት (ቅዳሜና እሑድ) ጌታችን ማረፉን የምንዘክርበት ጽላት/ታቦት ነው።
⇝ ቀዳሚት ሰንበት ፍጥረትን ፈጥሮ ያረፈበት በዓል ሲሆን ⇝ እሑድ (ሰንበተ ክርስቲያን) ደግሞ በሐዲስ ኪዳን ሁሉን ‘አዲስ’ ሊያደርግ ከልደቱ ጀምሮ ሲፈጽም የነበረውን የማዳን ሥራ በምድር ዕለተ ዓርብ ፈጽሞ እስከ እሑድ ነፍሳትን ከሲኦል አግዞ በትንሳኤው በሐዲስ ተፈጥሮ የመፍጠሩን ሥራ የፈጸመበት / ያረፈበት ዕለት ነው።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።” 【 ፪ኛ ቆሮ ፭፥፲፯
━━━━✦✿✦━━━━
በዓለ ደብረ ዘይት እኩለ ጾም ነው፤ የጌታችን ምጽኣቱ ዓለም በተፈጠረበት ዕለት በዕለተ ሰንበት መሆኑን ቅድስት ቤተክርስቲያን ታምናለች ታስተምራለችም! ቸሩ ጌታችን "በሰንበት ኢይኩን ጉያክሙ ⇨ ስደታችሁ በሰንበት አይሁን" ብሎ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰብስቦ በዕለተ ሰንበት አሕማላት (የለመለሙ ዕፀዋት) ካሉበት ቦታ ከ"ዐጸደ ሐምል" ተራራ ዐጸደ ዘይትም ወደበዛበት ሥፍራ አስጠግቶ ነገረ ምጽአቱን ያስተማረበት መታሰቢያ በዓለ ደብረ ዘይት ይባላል። ቀኑ ለኹዳዴ እኩለ ፆም ነው!
ባለቅኔው
"ተዝካሮ ግበሩ ባሕታውያን ደቂቁ፤
ለምውት ጾም እስመ ደብረ ዘይት መንፈቁ።" እንዳለ።
ገባሬ ሕይወት እግዚአ ለሰንበት ራሱ ጌታችን የቀደሳትና ከፍ ከፍ ያደረጋት ዕለት በመሆኗ "ቀደሳ ወአልዓላ" እያልን በእርሷ ደስ ብሎን ስናከብራትና ስናገናት እንውላለን።
በእርግጥ ጊዜው የእግዚአብሔርን በዓላት ከምድር ላይ እንሻር የሚሉ የበዙበት ዘመን መሆኑን ስናይ የዳዊት ትንቢት እያነሳን የትንቢቱ መፈጸሚያ በሆኑት እንደነቃለን።
“አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር አሉ።” ☞ 【መዝ ፸፬፥፰ 】
በዓለም ታሪክ እ.አ.አ. ከ1536 በፊት «በካቶሊካዊት» ቤተ እምነት በዐመት ውስጥ 95 የሚሆኑ የ«ቤተክርስቲያኗ» በዓላትና 52 ሰንበታት ይከሩ እንደነበር፤ ነገር ግን ከ1536 አንስቶ በተሃድሷውያኑ ጫና በዓላቱን ወደ 27 አውርደዋቸዋል።
ኋላ ላይ የተነሱት ከካተሊካዊ ባህል ፕሮቴስታንቱን እናነፃለን የሚሉ ወገኖች (The Puritans) በዓላቶችን በሙሉ (ገናና ፋሲካን ሳይቀር) በመሻር ዝክረ ዕለታትን ከሁለት ወገን ይከፍላሉ፦
① ችግር ጉዳትና አደጋ ከላይ የወረደ ቁጣ ተብለው የሚዘከሩባቸው ቀናት «ዕለታተ ፆም» ( Days of Fasting) ሲባሉ
② ልዩ በረከት ከአምላክ የሚሰጡባቸው ቀናት ዕለታተ ባርኮ/የምስጋና ቀናት (Days of Thanksgiving) ብለዋቸዋል።
【James W. Baker የተጻፈው "Thanksgiving: The Biography of an American Holiday" 】
ዛሬም የእኛዋን ቤተክርስቲያን አውቀው ይሁን ሳያውቁ በዚህ ወጀብ የሚንጧትን አበልጻጊዎች አስታግሶ ፣ ከመፍቀሬ ሁከት ሰይጣን ሰውሮ ፣ በመፍቀርያነ ምሕረት መላእክቱ ከልሎ ፈተናውን ሁሉ ያሻግርልን።
ወደዛሬው የመጀመሪያ ቀን ጉዳያችን እንለፍ፤ ትናንት በተሠጠው ጥቆማ መሠረት [https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=6005958766119252&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz]
ታቦተ ሰንበትን የሚመለከቱ ጥቂት ሐሳቦች እናሳለን። መነሻ ጥያቄው እንዲህ የሚል ነው
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይት» … መባሉ ስለምን ነው?
ቀድመን የሚከተለውን ጥያቄ እናንሳ
▶ ጽላት/ታቦት ለማን ይቀረጻል (በማን ይሰየማል) ?
በአጭር መልስ በስማቸው ጽላት የሚቀረጽላቸው ፣ መቅደስ የሚታነጽላቸው ፣ ጠበል የሚፈልቅና የሚሰየምላቸው ፣ ድርሳን ገድል መልክእ የሚጻፍ የሚደረስላቸው ቅዱሳን ናቸው።
▶ ቅዱሳንስ የምንለው ማንን ነው?
የኔታ ሐረገወይን አገዘ (ሊቀ ጠበብት) ነገረ ቅዱሳንን ሲያስረዱ ቅድስና የባህሪ ገንዘቡ የሆነ አምላክነትና ፈጣሪነትን ከማንም ያልተቀበለ ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ይሁንና ግን ከባህሪ ቅድስና በታች ያሉ በሥጦታ ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ቅዱሳንም አሉ ፤ እነዚህም ቅዱሳን/ቅዱሳት ዘበጸጋ ይባላሉ።
ለዚህ የጸጋ ቅድስና ምክንያቶች (ምንጮች) ደግሞ በጥቅሉ ሦስት ናቸው።
★ በመጽናት ቅዱሳን የምንላቸው አሉ ፦ ቅዱሳን መላእክት
★ በመመረጥ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ እመቤታችን፣ ንዋያት [ታቦት፣ መስቀል፣ መካናት/መቅደስ፣ ሥዕላት ፣ ንዋያተ ቅድሳት … ] ፣ ዕለታት ፣ መጻሕፍት፣ በጸሎት የከበሩ ቅብዓት [ቅብዓ ሜሮን ፣ ቅብዕ ቅዱስ፣ ቅብዓ ቀንዲል… ]
★ በተጋድሎ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ በቅድስናው ማዕረግ ከፍ ያሉ መስተጋድላን ጻድቃን ጽኑዓን …
መጽሐፍ ‘ሰብእ ይቄድሶ ለመካን ፤ ወመካን ይቄድሶ ለሰብእ’ ይላል፤ ደግሞም ቅዱሳን የረገጡትን ቦታ ብቻ ሳይሆን ገቢረ ተዓምራት የፈጸሙባቸውን ዕለታት ጭምር ቅዱስ ያሰኛሉ።
" ኀበ ቅዱሳን ይከውን ቅዱሰ ⇨ ከቅዱሳን ጋር የሚውል ቅዱስ ይኾናልና" 【ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፻፳፮】
ሰንበት ቅድስት ዕለት ናት። በእርግጥ በገዳማትና በአንድአንድ "ሊቃውንት" አንደበት የሰንበት ታቦት የሚባል የለም "እግዚኣ ለሰንበት" እንጂ ሲሉ ይደመጣል።
በአገባቡ «እግዚኣ ሰንበትና እግዚአ ለሰንበት» የሚሉት መልእክታት ፍቺና ምሥጢራቸው ለየቅል ነው።
እስኪ ደግመን አንድ ጥያቄ እናንሳ
▶ ለዕለታትና ለንዋያት ታቦት ይቀረጻል ወይ?
መልሱ፦ አዎ።
አስረጅ ፦ በእመቤታችን ስም ጽላት/ታቦት እንደሚቀረጽ ሁላችን እናውቃለን ፤ የዕረፍቷን መታሰቢያ መነሻ አድርጎ በ፳፩ ክብረ በዓሉ የሚታሰብ ሲሆን ሌሎቹን ታቦተ ልደታ ፣ ታቦተ በዓታ … እያሉ ለቀናቱ መታሰቢያ በመስጠት ዕለታት ይዘከሩባቸዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በቅዱስ መስቀሉ ስም ጽላት/ታቦት ተቀርጾ መቅደስ ታንጾ ድርሳን ተደርሶ መልክእ ተጽፎ ሲከብር እናያለን።
ሰንበትም እንዲሁ ድርሳነ ሰንበት ፣ መልክአ ሰንበት ፣ ታቦተ ሰንበት ያለው እንዲያውም የበዓላት ኹሉ በኲር የሆነ በዓል ነው።
ከመልኩ ክፍል ይህን የሚያስረዳ መልእክት እንዲህ ሠፍሮ እናገኛለን
ሶበ አእመርኩ በስምኪ ከመ ታቦተ ይቄድሱ፡
ወድሶተኪ ወጠንኩ ለአእምሮትየ መጠነ ናእሱ፡
ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ንግሥተ መሳፍንት ስሱ፡
እለሰ ኪያኪ አርኰሱ፡
ፈቀዱ ሞተ ወኵነኔ ኃሠሡ፡፡
[በስምሽ እንደታቦት የሚቀደስ መሆኑን ባወቅኹ ጊዜ በትንሿ እውቀቴ ምስጋናሽን ጀመርኩ
ለስድስቱ መሳፍንት ንግሥት የምትሆኚ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ አንቺንስ ያረከሱ ሰዎች ሞትን ወደው መኮነንን የፈለጉ ናቸው።]
አንዳንዶች እግዚኣ ለሰንበት በሚል መጠሪያ የሰንበት ጌታ ስለሚል « ጌታ እንጂ ሰንበትን የሚወክል ታቦት የለም» ይላሉ። ይሁን እንጂ ሰንበት ራሱ ዕረፍት ነው ታቦተ ማርያም ተዝካረ ዕረፍቷ እንደሚታሰብበት ታቦታ ሰንበትም በሁለቱ ሰንበታት (ቅዳሜና እሑድ) ጌታችን ማረፉን የምንዘክርበት ጽላት/ታቦት ነው።
⇝ ቀዳሚት ሰንበት ፍጥረትን ፈጥሮ ያረፈበት በዓል ሲሆን ⇝ እሑድ (ሰንበተ ክርስቲያን) ደግሞ በሐዲስ ኪዳን ሁሉን ‘አዲስ’ ሊያደርግ ከልደቱ ጀምሮ ሲፈጽም የነበረውን የማዳን ሥራ በምድር ዕለተ ዓርብ ፈጽሞ እስከ እሑድ ነፍሳትን ከሲኦል አግዞ በትንሳኤው በሐዲስ ተፈጥሮ የመፍጠሩን ሥራ የፈጸመበት / ያረፈበት ዕለት ነው።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።” 【 ፪ኛ ቆሮ ፭፥፲፯
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ስሙ ታቦቱ "እግዚኣ ሰንበት ⇨ ጌታዋ ሰንበት" እየተባለ ይጠራል በሌላ መጠሪያ እግዚአ ሰንበት አልያም እግዚኣ ለሰንበት ቢልም የሰንበት ጌታ ራሱ ሰንበት ነውና የዘይቤ እንጂ የምሥጢር ተፋልሶ የለውም። መጽሐፍ "ለሊሁ ርስቶሙ ⇨ርስታቸው እርሱ ራሱ ነው" ባለው መምህራን ሰንበታችን ሥሉስ ቅዱስ ዕረፍታችን እርሱ ራሱ እግዚአብሔር ነው ይላሉ። «ሰንበት ለሊሁ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ» እንዲል፤
በመልክአ እግዚአብሔር አብ ላይም
እሰግድ ለመለኮትከ ዘአእረፎሙ ለአይሁድ
በዕለተ ሰንበት ሳብዒት እምተግባረ አእጋር ወእድ
እግዚአብሔር አብ ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ
አግዕዘኒ እምቅኔ ሥጋ ለአብጽሖ ንስቲት ሰጊድ
ኀበ ኁልቆ ዕሥራ ወክልኤቱ ስሙያን አንጋድ
【ከእግርና ከእጅ ሥራ ፡ በሰባተኛው ቀን ሰንበት
አይሁድን ላሳረፋቸው ፡ ልስገድ ላንተ መለኮት
እሑድ የተባልክ እግዚአብሔር አብ ፡ የክርስቲያኖች ሰንበት
ለሥጋ ከመገዛት ነጻ አውጣኝ ፡ እንድሰግድልህ በጥቂት
‘ገናናው አባት አንተ ነህና’ ፡ ለሃያ ሁለቱም ፍጥረት】
ስለዚህ የሰንበት ታቦት/ጽላት የዕረፍት ታቦት ወደ ዕረፍት መግባትን ተስፋ በማድረግ ራሱ ማረፊያ!/ዕረፍት የሆነ የሰንበት ጌታ እንዳረፈባት የሚዘከርበት መታሰቢያ ነው።
የትኛው ሰንበት የሚለውን ለዕለተ ረቡዕ ባሳደርነው የመወያያ ነጥብ ላይ አንስተን የምንመካከር ይሆናል።
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር እንደቸርነቱ ነገ ማክሰኞ ደግሞ ለዚሁ ሠዓት ሰንበትና ስግደትን በሚመለከት ተከታዩን ጥያቄ እናያለን፦
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
✍ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ·ም·
በመልክአ እግዚአብሔር አብ ላይም
እሰግድ ለመለኮትከ ዘአእረፎሙ ለአይሁድ
በዕለተ ሰንበት ሳብዒት እምተግባረ አእጋር ወእድ
እግዚአብሔር አብ ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ
አግዕዘኒ እምቅኔ ሥጋ ለአብጽሖ ንስቲት ሰጊድ
ኀበ ኁልቆ ዕሥራ ወክልኤቱ ስሙያን አንጋድ
【ከእግርና ከእጅ ሥራ ፡ በሰባተኛው ቀን ሰንበት
አይሁድን ላሳረፋቸው ፡ ልስገድ ላንተ መለኮት
እሑድ የተባልክ እግዚአብሔር አብ ፡ የክርስቲያኖች ሰንበት
ለሥጋ ከመገዛት ነጻ አውጣኝ ፡ እንድሰግድልህ በጥቂት
‘ገናናው አባት አንተ ነህና’ ፡ ለሃያ ሁለቱም ፍጥረት】
ስለዚህ የሰንበት ታቦት/ጽላት የዕረፍት ታቦት ወደ ዕረፍት መግባትን ተስፋ በማድረግ ራሱ ማረፊያ!/ዕረፍት የሆነ የሰንበት ጌታ እንዳረፈባት የሚዘከርበት መታሰቢያ ነው።
የትኛው ሰንበት የሚለውን ለዕለተ ረቡዕ ባሳደርነው የመወያያ ነጥብ ላይ አንስተን የምንመካከር ይሆናል።
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር እንደቸርነቱ ነገ ማክሰኞ ደግሞ ለዚሁ ሠዓት ሰንበትና ስግደትን በሚመለከት ተከታዩን ጥያቄ እናያለን፦
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
✍ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ·ም·
ክፍል ፪] ሰንበትና ስግደት
━━━━ ✦✿✦ ━━━━
ለዛሬው በክፍል ሁለት በያዝነው ቀጠሮ መሠረት እንደ እግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ከነገረ ሰንበት [Sabbatarianism] ትምህርታችን መኻል ተከታዮቹን ጥያቄዎች መነሻ አድርገን ጥቂት ሐሳቦችን እናነሳለን
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
ዛሬ መጋቢት ፲፪ ቀን ሰጊድ ከሚከለከልባቸው የግዝት በዓላት መካከል የቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው። እንኳን አደረሳችሁ 🙏
ወደ ሐሳቡ ከመዝለቃችን አስቀድሞ ትናንት የሰንበትን ታቦት በሚመለከት ካነሳነው መልእክት ሁለት ተጨማሪ ፍሬ ነገሮችን እናክል
«በሳማ ሰንበት» ታሪክ ውሥጥ ቤተክርስቲያኑ በ1026 ዓ.ም. የተመሠረተ የሰንበት ታቦት ያለውና በሰንበተ ክርስቲያን ስም የተቆረቆረ ቀዳሚና ብቸኛ ገዳም እንደነበረ የቦታው ታሪክ ይነግረናል፤ ክብረ በዓሉም በዕለተ ደብረ ዘይት እንደሚውልና በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመነ ፓትርያርክና («ፕትርክና») አሁን ያለው አዲሱ ሕንጻ ተገንብቶ ቅዳሴ ቤቱ ሲከብር "ብሔረ ሕያዋን እግዚአ ለሰንበት" በሚል ተሰይሟል። 【የቤተክርስቲያን መረጃዎች ገጽ 95】ታቦቱ ግን እንደቀድሞ ታቦተ ሰንበት መሆኑን ልብ ይሏል።
ቤተክርስቲያናችን ቅዳሴ ማርያም ብላ የቅዱስ ሕርያቆስን ቅዳሴ እንደምትጠራው ሁሉ የቅዱስ አትናቴዎስን ቅዳሴ ደግሞ ቅዳሴ ሰንበት በማለት የሰንበትን ክብር ትገልጥበታለች ።
በዚህ ምስጋናም ልክ እንደ ሕያው ቅዱስ መስቀሉ ቅድስት ሰንበትን ለተማጽኖ ሕያውነቷን አምነን እንማጸናታለን ደጅ እንጠናታለን፤ መስቀሉን በመስተብቍዕ "ናስተበቊዖ ለዕፀ ቅዱስ መስቀል ጽኑዓ ሥልጣን" 【መጽሐፈ ሰዓታት】 እንዳልነው ሁሉ ሰንበትንም "ኦ ዛቲ ዕለት ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ሰዓሊ ለነ አስተምሕሪ ኀበ እግዚአብሔር አምላክነ ⇨ ይህች ቅድስት የክርስቲያን ሰንበት ምን ትደንቅ ፤ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምኚልን፤ ስለእኛ አማልጂ" 【ቅዳሴ አትናቴዎስ】 እንላታለን፤ የሰንበት ጌታ ስለቅድስት ሰንበት ብሎ ይማረን 🙏
ወደ ዛሬው ጉዳይ እንሻገር ፦ የዕለተ ሰንበት የአምልኮ ስግደት።
በዘመናችን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ከሚገዳደሩ ፈተናዎች መኻል ቀዳሚውን ቦታ የሚይዘው አዳስ ሕግ አርቃቂ ፣ ጠበል አፍላቂ ፣ ፈዋሽ አጥማቂ፣ ተኣምር አድናቂ ፣ ባህታዊ አጽዳቂ… መብዛቱ እንደሆነ ይሰማኛል።
ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ አንዳንድ ምዕመናን በግዝት በዓላትና ከቆረቡ በኋላ አብዝተው በመቅደስና በአውደ ምሕረት አካባቢ አብዝተው ሲሰግዱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፤ የሚያስቆማቸው ሲገኝ ለማስተማር እየቃጣቸው «የአምልኮ ስግደት ነው በበዓላት ምክንያት የማይቋረጥ ነው» የሚል ሙግት ያቀርባሉ! ትምህርቱን ከመምህር እገሌ ከአጥማቂ እገሌ አገኘን ከሚል በቀር ማስረጃ እንኳ የላቸውም።
በሥርዓተ አምልኮ ውሥጥ ለመንፈሳዊ ተግባራችን ሁሉ ምንጭ የሚሆኑን መነሻዎቻችን ተከታዮቹ ናቸው
☆ መጽሐፍ ቅዱስ በተለይም ፰ቱ የሥርዓት መጻሕፍት ፣ የሕገ ቤተክርስቲያን ድንጋጌ/አዋጅ [እንደ ፍትሐ ነገሥት ፣ ቀኖና ጉባኤያት ፣ ሥርዓተ አበው፣ ሕንጻ መነኮሳት ፣ አንቀጸ ንሰሐ ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ የየዘመናት ውሳኔ ፣ ሕገ ቤተክርስቲያንና ቃለ ዓዋዲ] በዋናነት ይጠቀሳል ከቤተ ጉባኤ መምህራን [የቤቱ አብነት የሚያትታቸው ሥርዓቶች)] በየቦታው ሊለያይ የሚችል ሥርዓተ ገዳም።
ከዚህ ውጪ ግለሰባዊ መመሪያና በካህን የሚታዘዝ ቀኖናን በመቀበል እደወል ሕግና የጋራ ሥርዓት አድርጎ ክብረ ሰንበትን መሻር የሚያስቀጣ ነው።
በሰንበት የሚቻል ስግደት አለ ወይስ የለም? የሚለውን ከማብራራታችን በፊት ጥቂት ጉዳይ ስግደትን በሚመለከት እናንሳ
ሰጊድ ማለት በቁሙ መስገድ መዋረድ ማጐንበስ መንበርከክ መድፋት በግንባር መውደቅ ግንባርን ምድር አስነክቶ መሬት ስሞ መመለስን የሚገልጽ ሲሆን ጸሎት ለማቅረብ ፣ ክብር ለመሥጠት ፣ ሰላምታ ለመለዋወጥ ፣ ሰውነትን ለመቅጣት የምንፈጽመው ተግባር ነው።
ይኸውም የአምልኮና የአክብሮ ተብሎ በሁለት መንገድ ይቀርባል።
የአምልኮ ስግደት አምላክነት የባህሪ ገንዘቡ ለሆነ እግዚአብሔር ፈጥረህ የምትገዛን አንተ ብቻ ነህ ብለን አሐቲ ☞ አንዲት[የተለየች] ስግደት በፊቱ እናቀርባለን።
የአክብሮ ስግደት ግን በጸጋ ቅድስናን ገንዘብ ላደረጉ ሁሉ ሊቀርብ የሚችል ነው።
ፍትሐ ነገሥቱ በአንቀጽ ፲፭ ስለ ጸሎት ሲያስረዳ
"ሰጊድ ለእግዚአብሔር ልዑል በጊዜ ጸሎት" በሚለው ክፍል ተከታዩን ማብራሪያ ትርጓሜ ሊቃውንቱ ያስቀምጣል
የሚጸልይ ሰው በሚጸልይበት ጊዜ ሰጊድን ከሚያነሳ አንቀጽ ሲደርስ ለልዑል እግዚአብሔር ይሰግድ ፤ ጸሎቱን በአንድ ሰጊድ ወይም በሦስትም ይጀምር ። ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜ አንዲህ ያድርግ በአንድ ጀምሮ እንደሆነ በአንድ በሦስት የጀመረም እንደሆነ በሦስት ይጨርስ [ወከማሁ ይግበር በተፍጻሜተ ጸሎቱ] ይላል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በዓላትን ምክንያት አድርጎ «ግዝት» ለመጠበቅ የተሠራውን የስግደት ሥርዓት መለያየት የአምልኮንና አክብሮን ስግደትን ለመፈጸም እንደ መለያ መጠቀሙ በምንም መንገድ ተገቢ አይደለም፤ ለምሳሌ አንዳንዶች ለእግዚአብሔር ሰጊድ ፣ ለእመቤታችን አስተብርኮ ለሌሎች ቅዱሳን አድንኖ እንደሚፈጸም ሲናገሩ ይሰማል።
ባይሆን ከአድኅኖና ከአስተብርኮ በቀር ግምባርን ምድር አስነክቶ ከመስገድ የሚከለክሉባቸው የታወቁ ጊዜያት አሉ፤ ፍትሐ ነገሥት "ወጊዜያት እሙራት ዘይኅድጉ ባቲ ስግደት እስከ ምድር ዘእንበለ አድንኖ ወአስተብርኮ ባቲ" የሚለው ይህን ነው።
እነዚህን ጊዜያት በዝርዝር ዕለት እሑድ ፣ በበዓለ ሃምሳ/ በበዓለ ጰንጠቆስጤ ፣ በጌታችን በዓል ፣ በእመቤታችን በዓል ፣ ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ እያለ ተቀምጧል። በሌሎች የሥርዓት መጻሕፍት ወርኃዊ የግዝት በዓላትን ቅዱስ ሚካኤል ፣ እመቤታችንና በዓለ ወልድ [በ፲፪፣ በ፳፩ እና በ፳፱] በሚል ሲጨምር ይታያል።
ፍትሐ ነገሥቱ በዚኹ ክፍል ሰጊድ ሦስት ወገን ነው ይላል፤ ሰጊድ ፣ አድንኖና አስተብርኮ ፤ አድንኖ በጌታ በዓላት አስተብርኮ በእመቤታችን በዓላት ብሎ መለያው ለዚህ እንደሚነገር ይገልጣል እንጂ በደረጃ ለመለየት የአምልኮ የአክብሮ ብሎ ለመከፋፈል እንዳልሆነ ያስቀምጣል። በተለየ መንገድ ሰንበትን የሚመለከተውን ደግሞ የአምልኮና የአክብሮ የሚል መለያ ሳይደረግ በቀኖና ኒቂያ አንቀጽ ፳ ላይ "ወይከውን ጸሎት በሰንበት ዘእንበለ ሰጊድ ውስተ ምድር አላ በደኒን ወአትሕቶ ርእስ ⇨ በዕለተ ሰንበት የሚፈጸመው ጸሎት ወደ ምድር ወድቆ ያለ መስገድ ይሁን ነገር ግን ራስን ዝቅና አንገትን ዘንበል በማድረግ ይሁን" ይላል።
መልክአ ሰንበትም በዕለቱ ስግደት ብቻ ሳይሆን ጾምም እንደሚከለከል እንዲህ ሲል ያስረዳናል።
ሰላም ለኵነትኪ እምቅድመ ኵሉ ፍጥረት፡
በዕለተ ተፈጥረ ብርሃን እማእከለ ግሩም ጽልመት፡
ለሰንበተ ሙሴ ካልዕታ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፡
ላዕሌኪሰ ከመ ባዕዳን ዕለታት፡
አልቦ ፆም ወአልቦ ስግደት፡፡
【ከፍጥረት ሁሉ በፊት በአስፈሪው ጨለማ መኻል ብርሃን በተፈጠረበት ዕለት ለነበረው መገኘትሽ ሰላም እላለሁ። ለቀዳሚዋ የሙሴ ሰንበት ሁለተኛዋ የሆንሽ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ እንደሌሎቹ ቀናት ፆምና ስግደት ባንቺ ላይ የለም】
የማይሰገደው ለምንድነው?
━━━━ ✦✿✦ ━━━━
ለዛሬው በክፍል ሁለት በያዝነው ቀጠሮ መሠረት እንደ እግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ከነገረ ሰንበት [Sabbatarianism] ትምህርታችን መኻል ተከታዮቹን ጥያቄዎች መነሻ አድርገን ጥቂት ሐሳቦችን እናነሳለን
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
ዛሬ መጋቢት ፲፪ ቀን ሰጊድ ከሚከለከልባቸው የግዝት በዓላት መካከል የቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው። እንኳን አደረሳችሁ 🙏
ወደ ሐሳቡ ከመዝለቃችን አስቀድሞ ትናንት የሰንበትን ታቦት በሚመለከት ካነሳነው መልእክት ሁለት ተጨማሪ ፍሬ ነገሮችን እናክል
«በሳማ ሰንበት» ታሪክ ውሥጥ ቤተክርስቲያኑ በ1026 ዓ.ም. የተመሠረተ የሰንበት ታቦት ያለውና በሰንበተ ክርስቲያን ስም የተቆረቆረ ቀዳሚና ብቸኛ ገዳም እንደነበረ የቦታው ታሪክ ይነግረናል፤ ክብረ በዓሉም በዕለተ ደብረ ዘይት እንደሚውልና በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመነ ፓትርያርክና («ፕትርክና») አሁን ያለው አዲሱ ሕንጻ ተገንብቶ ቅዳሴ ቤቱ ሲከብር "ብሔረ ሕያዋን እግዚአ ለሰንበት" በሚል ተሰይሟል። 【የቤተክርስቲያን መረጃዎች ገጽ 95】ታቦቱ ግን እንደቀድሞ ታቦተ ሰንበት መሆኑን ልብ ይሏል።
ቤተክርስቲያናችን ቅዳሴ ማርያም ብላ የቅዱስ ሕርያቆስን ቅዳሴ እንደምትጠራው ሁሉ የቅዱስ አትናቴዎስን ቅዳሴ ደግሞ ቅዳሴ ሰንበት በማለት የሰንበትን ክብር ትገልጥበታለች ።
በዚህ ምስጋናም ልክ እንደ ሕያው ቅዱስ መስቀሉ ቅድስት ሰንበትን ለተማጽኖ ሕያውነቷን አምነን እንማጸናታለን ደጅ እንጠናታለን፤ መስቀሉን በመስተብቍዕ "ናስተበቊዖ ለዕፀ ቅዱስ መስቀል ጽኑዓ ሥልጣን" 【መጽሐፈ ሰዓታት】 እንዳልነው ሁሉ ሰንበትንም "ኦ ዛቲ ዕለት ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ሰዓሊ ለነ አስተምሕሪ ኀበ እግዚአብሔር አምላክነ ⇨ ይህች ቅድስት የክርስቲያን ሰንበት ምን ትደንቅ ፤ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምኚልን፤ ስለእኛ አማልጂ" 【ቅዳሴ አትናቴዎስ】 እንላታለን፤ የሰንበት ጌታ ስለቅድስት ሰንበት ብሎ ይማረን 🙏
ወደ ዛሬው ጉዳይ እንሻገር ፦ የዕለተ ሰንበት የአምልኮ ስግደት።
በዘመናችን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ከሚገዳደሩ ፈተናዎች መኻል ቀዳሚውን ቦታ የሚይዘው አዳስ ሕግ አርቃቂ ፣ ጠበል አፍላቂ ፣ ፈዋሽ አጥማቂ፣ ተኣምር አድናቂ ፣ ባህታዊ አጽዳቂ… መብዛቱ እንደሆነ ይሰማኛል።
ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ አንዳንድ ምዕመናን በግዝት በዓላትና ከቆረቡ በኋላ አብዝተው በመቅደስና በአውደ ምሕረት አካባቢ አብዝተው ሲሰግዱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፤ የሚያስቆማቸው ሲገኝ ለማስተማር እየቃጣቸው «የአምልኮ ስግደት ነው በበዓላት ምክንያት የማይቋረጥ ነው» የሚል ሙግት ያቀርባሉ! ትምህርቱን ከመምህር እገሌ ከአጥማቂ እገሌ አገኘን ከሚል በቀር ማስረጃ እንኳ የላቸውም።
በሥርዓተ አምልኮ ውሥጥ ለመንፈሳዊ ተግባራችን ሁሉ ምንጭ የሚሆኑን መነሻዎቻችን ተከታዮቹ ናቸው
☆ መጽሐፍ ቅዱስ በተለይም ፰ቱ የሥርዓት መጻሕፍት ፣ የሕገ ቤተክርስቲያን ድንጋጌ/አዋጅ [እንደ ፍትሐ ነገሥት ፣ ቀኖና ጉባኤያት ፣ ሥርዓተ አበው፣ ሕንጻ መነኮሳት ፣ አንቀጸ ንሰሐ ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ የየዘመናት ውሳኔ ፣ ሕገ ቤተክርስቲያንና ቃለ ዓዋዲ] በዋናነት ይጠቀሳል ከቤተ ጉባኤ መምህራን [የቤቱ አብነት የሚያትታቸው ሥርዓቶች)] በየቦታው ሊለያይ የሚችል ሥርዓተ ገዳም።
ከዚህ ውጪ ግለሰባዊ መመሪያና በካህን የሚታዘዝ ቀኖናን በመቀበል እደወል ሕግና የጋራ ሥርዓት አድርጎ ክብረ ሰንበትን መሻር የሚያስቀጣ ነው።
በሰንበት የሚቻል ስግደት አለ ወይስ የለም? የሚለውን ከማብራራታችን በፊት ጥቂት ጉዳይ ስግደትን በሚመለከት እናንሳ
ሰጊድ ማለት በቁሙ መስገድ መዋረድ ማጐንበስ መንበርከክ መድፋት በግንባር መውደቅ ግንባርን ምድር አስነክቶ መሬት ስሞ መመለስን የሚገልጽ ሲሆን ጸሎት ለማቅረብ ፣ ክብር ለመሥጠት ፣ ሰላምታ ለመለዋወጥ ፣ ሰውነትን ለመቅጣት የምንፈጽመው ተግባር ነው።
ይኸውም የአምልኮና የአክብሮ ተብሎ በሁለት መንገድ ይቀርባል።
የአምልኮ ስግደት አምላክነት የባህሪ ገንዘቡ ለሆነ እግዚአብሔር ፈጥረህ የምትገዛን አንተ ብቻ ነህ ብለን አሐቲ ☞ አንዲት[የተለየች] ስግደት በፊቱ እናቀርባለን።
የአክብሮ ስግደት ግን በጸጋ ቅድስናን ገንዘብ ላደረጉ ሁሉ ሊቀርብ የሚችል ነው።
ፍትሐ ነገሥቱ በአንቀጽ ፲፭ ስለ ጸሎት ሲያስረዳ
"ሰጊድ ለእግዚአብሔር ልዑል በጊዜ ጸሎት" በሚለው ክፍል ተከታዩን ማብራሪያ ትርጓሜ ሊቃውንቱ ያስቀምጣል
የሚጸልይ ሰው በሚጸልይበት ጊዜ ሰጊድን ከሚያነሳ አንቀጽ ሲደርስ ለልዑል እግዚአብሔር ይሰግድ ፤ ጸሎቱን በአንድ ሰጊድ ወይም በሦስትም ይጀምር ። ጸሎቱን በጨረሰ ጊዜ አንዲህ ያድርግ በአንድ ጀምሮ እንደሆነ በአንድ በሦስት የጀመረም እንደሆነ በሦስት ይጨርስ [ወከማሁ ይግበር በተፍጻሜተ ጸሎቱ] ይላል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በዓላትን ምክንያት አድርጎ «ግዝት» ለመጠበቅ የተሠራውን የስግደት ሥርዓት መለያየት የአምልኮንና አክብሮን ስግደትን ለመፈጸም እንደ መለያ መጠቀሙ በምንም መንገድ ተገቢ አይደለም፤ ለምሳሌ አንዳንዶች ለእግዚአብሔር ሰጊድ ፣ ለእመቤታችን አስተብርኮ ለሌሎች ቅዱሳን አድንኖ እንደሚፈጸም ሲናገሩ ይሰማል።
ባይሆን ከአድኅኖና ከአስተብርኮ በቀር ግምባርን ምድር አስነክቶ ከመስገድ የሚከለክሉባቸው የታወቁ ጊዜያት አሉ፤ ፍትሐ ነገሥት "ወጊዜያት እሙራት ዘይኅድጉ ባቲ ስግደት እስከ ምድር ዘእንበለ አድንኖ ወአስተብርኮ ባቲ" የሚለው ይህን ነው።
እነዚህን ጊዜያት በዝርዝር ዕለት እሑድ ፣ በበዓለ ሃምሳ/ በበዓለ ጰንጠቆስጤ ፣ በጌታችን በዓል ፣ በእመቤታችን በዓል ፣ ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ እያለ ተቀምጧል። በሌሎች የሥርዓት መጻሕፍት ወርኃዊ የግዝት በዓላትን ቅዱስ ሚካኤል ፣ እመቤታችንና በዓለ ወልድ [በ፲፪፣ በ፳፩ እና በ፳፱] በሚል ሲጨምር ይታያል።
ፍትሐ ነገሥቱ በዚኹ ክፍል ሰጊድ ሦስት ወገን ነው ይላል፤ ሰጊድ ፣ አድንኖና አስተብርኮ ፤ አድንኖ በጌታ በዓላት አስተብርኮ በእመቤታችን በዓላት ብሎ መለያው ለዚህ እንደሚነገር ይገልጣል እንጂ በደረጃ ለመለየት የአምልኮ የአክብሮ ብሎ ለመከፋፈል እንዳልሆነ ያስቀምጣል። በተለየ መንገድ ሰንበትን የሚመለከተውን ደግሞ የአምልኮና የአክብሮ የሚል መለያ ሳይደረግ በቀኖና ኒቂያ አንቀጽ ፳ ላይ "ወይከውን ጸሎት በሰንበት ዘእንበለ ሰጊድ ውስተ ምድር አላ በደኒን ወአትሕቶ ርእስ ⇨ በዕለተ ሰንበት የሚፈጸመው ጸሎት ወደ ምድር ወድቆ ያለ መስገድ ይሁን ነገር ግን ራስን ዝቅና አንገትን ዘንበል በማድረግ ይሁን" ይላል።
መልክአ ሰንበትም በዕለቱ ስግደት ብቻ ሳይሆን ጾምም እንደሚከለከል እንዲህ ሲል ያስረዳናል።
ሰላም ለኵነትኪ እምቅድመ ኵሉ ፍጥረት፡
በዕለተ ተፈጥረ ብርሃን እማእከለ ግሩም ጽልመት፡
ለሰንበተ ሙሴ ካልዕታ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፡
ላዕሌኪሰ ከመ ባዕዳን ዕለታት፡
አልቦ ፆም ወአልቦ ስግደት፡፡
【ከፍጥረት ሁሉ በፊት በአስፈሪው ጨለማ መኻል ብርሃን በተፈጠረበት ዕለት ለነበረው መገኘትሽ ሰላም እላለሁ። ለቀዳሚዋ የሙሴ ሰንበት ሁለተኛዋ የሆንሽ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ እንደሌሎቹ ቀናት ፆምና ስግደት ባንቺ ላይ የለም】
የማይሰገደው ለምንድነው?
በግዝት በዓላት ዕለተ ሰንበትን ጨምሮ እንዲሁም ከቁርባን በኋላ የአምልኮ ይሁን የአክብሮ ስግደትን የሚከለክለው የቤተክርስቲያን ሥርዓት ምክንያቱን ሲነግረን ፦
✧ አክብሩ ያለውን ትእዛዝ ማፍረስ ስለሆነ፤
✧✧ በዚህ ቀን ዕረፍት ሥጋ አርፋችሁ ዕረፍተ ነፍስ ዕረፉበት ብሏል ያንን ተላልፈን ብንሰግድ በእመቤታችን ቃል ኪዳን ፣ በጌታ ካሳ … አልዳንም ስለሚያሰኝ፤
✧✧✧ የግዝት በዓላቱ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ናቸው በዚህ ቀን ሲሰግዱ መዋል መንግሥተ ሰማያት ከገቡ በኋላ ኃጢኣት ሠርቶ ንስሐ መግባት አለ ስለሚያስብል፤
✧✧✧✧ ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ መስገድ የማይገባው ወዙ ይንጠፈጠፋልና በዚያውም ላይ በሥጋው ደሙ አልዳንም በትሩፋታችን ዳንን እንዳንል።
እንግዲህ ከዚህ በተለየ ለአምልኮ በሚል ሰንበትን በመሻር በእርሱ ካሳ አልዳንም በትሩፋታችን እንጂ ብሎ በሞኝ አዋጅ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ቀኖና መጻሕፍትን መሻር ምን ይሉታል?
፨ ተከታዩን ምክር በመለገስ የዛሬውን ሐሳብ እንቋጭ ፨
ሰግላዊው ሊቅ መምህራችን አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ይላል "ወለእመሰ ፈቀድከ ታሥምሮ ለእግዚአብሔር አብዝኅ ጸሎተ ዘምስለ ሰጊድ ወጸዊም ዘምስለ ትሕርምት ወትሕትና ዘምስለ ትዕግሥት ወምንዳቤ ሥቃየ አጋንንት በውስተ ገዳማት ወምንዳቤ ሥቃየ ስምዕ በዐውደ ነገሥት ⇨ #እግዚአብሔርን_ለማገልገል _ከፈለግህ ጸሎትን ከስግደት ጋር አብዝተህ ጸልይ ጾምን ከቀኖና ጋር ትሕትናንም ከትዕግሥት ጋር በገዳመ ውስጥ በአጎንንንት መፈተንን በነገሥታት አደባባይ በሐሰት የመወንጀልን መከራ አብዛ"
ያን ማድረግ ባንችልስ ካላችሁ ደግሞ አባ ጊዮርጊስ ሌላም የተስፋ መንገድ አለ ይላል፦
"ወዘንተ ለእመ ኢክህልከ ግበር ተዝካሮሙ ለመስተጋድላን ከመ ትድኀን በኀይለ ጽድቆሙ ወበእንተዝ ንቤ ዘረከበ ሞገሰ አመ ፀአተ ነፍሱ ኢይረክብ ኀሣረ አመ ትንሣኤ ሙታን፡ ⇨ #ይህንን_ማድረግ_ባይቻልህ የሰማዕታትን መታሰቢያቸውን አድርግ በቃል ኪዳናቸው ትድን ዘንድ ስለዚህም ነፍሱ ከሥጋው በተለየች ጊዜ ክብርን ያገኝ በትንሣኤ ሙታን ጊዜ መከራ አያገኘውም"
【መጽሐፈ ምሥጢር】
እንደ ቅድስት ሥላሴ መልካም ፈቃድ ለነገው ደግሞ ክፍል ፫] ⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ ተከታዩን የቤት ሥራ ሠርተን ለመምጣት ያብቃን 🙏
ዕለተ ሰንበት የቷ ናት?
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
✍ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
✧ አክብሩ ያለውን ትእዛዝ ማፍረስ ስለሆነ፤
✧✧ በዚህ ቀን ዕረፍት ሥጋ አርፋችሁ ዕረፍተ ነፍስ ዕረፉበት ብሏል ያንን ተላልፈን ብንሰግድ በእመቤታችን ቃል ኪዳን ፣ በጌታ ካሳ … አልዳንም ስለሚያሰኝ፤
✧✧✧ የግዝት በዓላቱ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ናቸው በዚህ ቀን ሲሰግዱ መዋል መንግሥተ ሰማያት ከገቡ በኋላ ኃጢኣት ሠርቶ ንስሐ መግባት አለ ስለሚያስብል፤
✧✧✧✧ ሥጋውን ደሙን ከተቀበሉ በኋላ መስገድ የማይገባው ወዙ ይንጠፈጠፋልና በዚያውም ላይ በሥጋው ደሙ አልዳንም በትሩፋታችን ዳንን እንዳንል።
እንግዲህ ከዚህ በተለየ ለአምልኮ በሚል ሰንበትን በመሻር በእርሱ ካሳ አልዳንም በትሩፋታችን እንጂ ብሎ በሞኝ አዋጅ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ቀኖና መጻሕፍትን መሻር ምን ይሉታል?
፨ ተከታዩን ምክር በመለገስ የዛሬውን ሐሳብ እንቋጭ ፨
ሰግላዊው ሊቅ መምህራችን አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ይላል "ወለእመሰ ፈቀድከ ታሥምሮ ለእግዚአብሔር አብዝኅ ጸሎተ ዘምስለ ሰጊድ ወጸዊም ዘምስለ ትሕርምት ወትሕትና ዘምስለ ትዕግሥት ወምንዳቤ ሥቃየ አጋንንት በውስተ ገዳማት ወምንዳቤ ሥቃየ ስምዕ በዐውደ ነገሥት ⇨ #እግዚአብሔርን_ለማገልገል _ከፈለግህ ጸሎትን ከስግደት ጋር አብዝተህ ጸልይ ጾምን ከቀኖና ጋር ትሕትናንም ከትዕግሥት ጋር በገዳመ ውስጥ በአጎንንንት መፈተንን በነገሥታት አደባባይ በሐሰት የመወንጀልን መከራ አብዛ"
ያን ማድረግ ባንችልስ ካላችሁ ደግሞ አባ ጊዮርጊስ ሌላም የተስፋ መንገድ አለ ይላል፦
"ወዘንተ ለእመ ኢክህልከ ግበር ተዝካሮሙ ለመስተጋድላን ከመ ትድኀን በኀይለ ጽድቆሙ ወበእንተዝ ንቤ ዘረከበ ሞገሰ አመ ፀአተ ነፍሱ ኢይረክብ ኀሣረ አመ ትንሣኤ ሙታን፡ ⇨ #ይህንን_ማድረግ_ባይቻልህ የሰማዕታትን መታሰቢያቸውን አድርግ በቃል ኪዳናቸው ትድን ዘንድ ስለዚህም ነፍሱ ከሥጋው በተለየች ጊዜ ክብርን ያገኝ በትንሣኤ ሙታን ጊዜ መከራ አያገኘውም"
【መጽሐፈ ምሥጢር】
እንደ ቅድስት ሥላሴ መልካም ፈቃድ ለነገው ደግሞ ክፍል ፫] ⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ ተከታዩን የቤት ሥራ ሠርተን ለመምጣት ያብቃን 🙏
ዕለተ ሰንበት የቷ ናት?
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
✍ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ስብከት | ORTHODOX SIBKET
አቤቱ በእኔ በኩል እለፍ ፡፡
ተፆፋ በሥነልቦና ባለሞያ Bini Girmachew
ጌታ ሆይ በኢያሪኮው መንገደኛ በኩል እንዳለፍህ ይህች ዐመት ከማለቋ በፊት እባክህን በእኔም በኩል እለፍ፡፡
የጠፋውን በግ አዳምን የፈለግኸው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ እኔንም ፈልገኝ፤ ባገኘኸውም ጊዜ እንደተሸከምኸው እኔንም ተሸከመኝ፡፡
የቀደመ ፍጥረትህን አዳምን ቸል እንዳላልከው ከእርሱ አብራክ የተገኘሁ እኔ ደካማ ልጁንም ቸል አትበለኝ፡፡ ይልቁንም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንድ ሰው የተባለ አዳምን እንደተሸከምከው እኔንም ተሸከመኝ፡፡
አዎን ጌታ ሆይ በመንገድ ላይ የወደቀው ስም የለሽ አንድ ሰው እኔ እንደሆንኩ አውቂያለሁ፡፡
ከኢየሩሳሌም ልዕልና ነፍስ ወደ ኢያሪኮ የኃጢአት ቁልቁለት የወረድሁት እኔ እንደሆንኩ ገብቶኛል፡፡ አንተ ለእኔ ድኅነት የሠራኸውን አሸቀንጥሬ ጥዬ እኔን ካስቀመጥክበት ከፍታ ተንደርድሬ ለእኔ ፍላጎት ወደሚስማማው ቁልቁለት የወረድሁት በወንበዴዎች እጅም የወደቅሁት የኢያሪኮው መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በምሥጢራት ከሚኖርበት ተግባራዊ የክርስትና ከፍታ በማስመሰልና በውድድር ወደሚኖርበት ዝቅታ የወረድሁት ስም የለሽ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በእውነትና በፍቅር ከሚኖርበት የወንጌል ተራራ ጥቅሶችን ወደፍላጎታችን ወደሚለጥጥ ገደል የወረድሁት የተመታሁ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡
አንተን በሕይወቴ አሳድሬ አንተ በእኔ እንድትሠራ ከሚያደርግ ከፍታ እራሴን ለአንተ የሚሠራ ወታደር ወደሚያስመስል የሕይወት አዘቅት አውርጄ የጣልኩት የቁልቁለት መንገደኛው እኔ ነኝ፡፡
ሰለወደቀው በማዘን ስለእርሱም በመጸለይ እውነተኞቹ ልጆችህ ከኖሩበት ከፍታ ሁሉንም ወደሚያስንቅና ወደሚያስተች ዝቅታ የወረድሁት መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ ነገሮችን በመንፈስና በአስተውሎት ከመመርመር በስሜትና በግብታዊነት ወደማበላሽበት ጉድጓድ የወረድሁትም እኔ ነኝ፡፡ በእቅድና በጥበብ ከመሥራት በትችትና በነቀፌታ በእልህና በብስጭት ወደመናገር ብቻ የወረድሁት ከንቱ በእውነት እኔ ነኝ፡፡ ጥቂቶቹን ልዘርዝር ብዬ እንጂ ጌታ ሆይ እኔ ያልተውኩት ሰገነት፣ ያልወደቅሁበትም አዘቅት ምን አለና፡፡
ስወርድ ደግሞ እንደተጻፈው ወንበዴዎቹ አገኙኝና ደበደቡኝ፡፡ የነበረችኝንም ሁሉ ቀሙኝ፡፡ ጌታ ሆይ እየወረድኩም ይዠው ከነበረው ያልቀሙኝ ምንም የለም፡፡
መጀመሪያ የቀሙኝ ስንገዳገድ የምደገፍባትን፤ አቀበት ቁልቁለት የማቋርጥባትን፤ አራዊትን የማርቅባትን፣ ሰንቅና ጓዜን የምሸከምባትን አንዷን ዘንጌን ጸሎቴን ቀሙኝና ድጋፍ አልባ አደረጉኝ፡፡ ተነሥቼ ልጸልይ ስቆም አካሌ እንደ ሐውልት ቆሞ ነፍሴን ይዘዋት ይዞራሉ፡፡ አንዳንዴ ጥርሴን ያስነክሱኛል፡፡ አንዳንዴ ስለአንተ ተቆርቋሪ አስምስለው ጦርነት ውስጥ ይከቱኛል፡፡
ሌላ ጊዜ በአንተ በኩል ማግኘት የሚገባኝን ጥቅም ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ አንተ የማያስደስቱ የሚመስሉኝን እንድትቆርጥ እንድትጥል ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ የተረሳ ዘመድ ወዳጅ፣ የሞተ የጠፋ ቤተሰብእ ሳይቀር እያሳዩ ተመስጦ በሚመሰል ሕይወት ውስጥ ያጃጅሉኛል፡፡
የቀረ ሥራ የከሰረ ሀብትም አሳስበው ያናድዱኛል፡፡ ብቻ ነፍሴን የማይወስዱበት ቦታ የለም፡፡ ብሞት እንኳ መልአከ ሞት ነፍሴን ሊየንገላታት የማይችለውን ያህል ነፍሴን ያንከራትቷታል፡፡ ጸሎቴን ቀምተው ነፍሴን ማረፊያ ያጣች አሞራ አስመሰሏት፡፡
ስለዚህም የውስጥ ሰላሜ ተነጠቀ፡፡ እንኳን ከሌላው ከትዳር አጋሬ ከወላጅ ከቤተሰቤ በሰላም መነጋገሬን ሁሉ አከታትለው ቀሙኝ፡፡
ትዕግሥቴን ነጥቀዉ እንደ ፍየል ለፍላፊ፣ እንደ ጉጉት ጯሂ አደረጉኝ፡፡
ለሚናገረኝ ካልመለሰኩለት፣ የሚመለከተኝን ካልገላመጥኩት የተጠቃሁ እያስመሰሉ በመልካም የመመለስ ሀብቴን ዘረፉኝ፡፡ ይባስ በለው ልዩነቴን በእወቀት ከማስረዳት፣ ለመግባባት ከመወያየት አፋትተው የተለየለት ግልፍተኛ ተሳዳቢ አደረጉኝ፡፡
አሁንማ ካልተሳደብኩ ዐለም መሸነፌን አውቆ የሚስቅብኝ እያስመሰሉ እንኳን ይቃረኑኛል ለምላቸው በሀሳብ ይቀርቡኛል የምላቸውንም በእኔ መንገድ ስላልተናገሩ ብቻ የማላደላ ጀግና በማስመሰል እንድወርፋቸው ያደርጉኛል፡፡
ወደ ቀደመ ሕይወቴ እንዳልመለስም መንገዱን አጠሩብኝ፡፡ ጉባኤ ሔጄ እንዳልማር ጊዜ የማባክን ይመስለኛል፡፡
አንዳንድ መምህራንንም በትችት ስላስናቁኝ የመቀመጥ ትዕግሥቴ ራሱ የት እንደገባ አላውቅም፡፡ በጓደኛ ተጽእኖ ስቀመጥም ለእኔ ብሎ ከመስማት ይልቅ ይህ ለእነ እገሌ ነበር የሚያስፈልግ ያሰኘኛል፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ ዛሬም ይህን ይሰብካል እንዴ ያሰኘኛል፡፡ እኔ በማዘወትረው ኃጢአት ሳላፍር መምህሩ የሚታወቅ ትምህርት አስተማረ ብሎ አያፍርም ወይ ያሰኘኛል፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚነገረውም አሽሙርና የማይረባ ያስመስልብኛል፡፡ እዚህ ከምማር በቃ ቤቴ ተቀምጬዬ አነብባለሁ ብሎ ካስተዋኝ በኋላ ቤቴ ስገባ ቴሌቪዥን ጋር ያፋጥጠኛል፡፡
እርሱ ሲሰለቸኝ ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ የወጣ ነገር እንድመለከት በጓደኞቼ በኩል ያስደውልብኛል፡፡ እንደምንም ታግዬ ላነብብ ስነሣ እንቅልፍ እንደበረዶ ያዘንብብኛል፡፡
በቃ በጎው ነገር ካመለጠኝ በኋላ አልያዝ አልጨበጥ አለኝ፡፡ ምክር እንዳልጠይቅ ትልቅና አዋቂ ሰው ነው በሚባል የገጸ ባሕርይ ካባ ሸፍነው አሳፍረውኛል፡፡ ከዚህ ሁሉ የተነሣ በነፍሴ ሕመም ሥጋዬም ታማሚ ሆነ፡፡
እንደወፈረኩ ደከማ፣ እንደጠገብኩ ልፍስፍስ አደረጉኝ፡፡ እንዳልጾም ሰውነቴ ሁሉ እንቢ አለ፡፡ እንዳልሰግድም ጉልበቴ ሁሉ ተብረከረከ፡፡ በሁሉ ባዶ ሆኜ ቁጭ አልኩ፡፡
የነፍሴ መድኃኒት ጌታዬ ሆይ አፍ ማብዛቴን፣ ነገር መውደዴን አይተህ ነው መሰል አፍን በማስክ የሚያስይዝ የተግሣጽ ደዌ ብታመጣም የእኔ ነፍስ ግን አሁንም አላስታዋለችም፡፡
እጆቼ ማስኩን አፌ ላይ ቢያደርጉም ምላሴን ሊያስቆሟት ግን አልቻሉም፡፡ አንተ ለደቀመዛሙርትህ እንዳልከው አፍን የሚያረክሰው ከውጭ የሚገባው ሳይሆን ከውስጥ የሚወጣው ነውና ከነፍሴ ቁስል የተነሣ በአፌ የሚወጣው የነገር ጠረን አካባቢውን አሸተተው፡፡
እንኳን ለሌላው ለእኔም እየተሰማኝ ቢሆንም ነፍሴን የደበደቧት ወንበዴዎች ግን እንድነቃ አልፈቀዱልኝም፡፡ ስለዚህ ጌታ ሆይ የአፍ ብቻ ሳይሆን የልብና የኅሊና ማስክ እዘዝልኝ፡፡ እንደ ዳዊት ወዳጅህ ለአፌ ጠባቂ ሹምለት፤ ከንፈሮቼንም እንደ ቤተ መቅደስህ በር በምሕረትና በእውነት የሚከፈቱ አድርግልኝ፡፡
ጌታ ሆይ አሁን ችግሬ ገብቶኛል፤ ማስክ የሚያስፈልገኝ ለውጨኛው ሳይሆን ለውስጠኛው የኅሊና አፌ ነው፡፡ ጸረ ተሐዋሲ መድኃኒትም ከሥጋዬ ይልቅ ለነፍሴ እጆች እንደሚያስፈልጋቸው ገብቶኛል፡፡
አቤቱ ሰነድ በመደለዝ፣ ደም በማፍሰስ የረከሱ እጆቻችን በምን ይነጻሉ? የሐሰት ትርክት በመተረክ፣ የበለው ግደለው ቅስቀሳ በመጻፍ የዋሆችን በማነሣሣት ደም ያፈሰሱ የምሁር እጅ ነኝ የሚሉ የነፍስ እጆቻችንስ ቤትኛው ሳኒታይዘር ይነጻሉ? ጌታ ሆይ ዘንድሮ ሁሉንም ችግሮቼን ነግረኸኛል፡፡
በተለይ ርቀት ያለመጠበቅ፣ ቦታዬንም ያለማወቅ ችግር አስታውሼው አላውቅም ነበር፡፡ የእኔማ የተለየ ነው፡፡ እንኳን በሾምካቸው በጳጳሳት በካህናት በአንተ ወንበር ተቀምጬ ስፈርድ፣ ስገድል ሳድን፣ ስሰጥ ስነሣ ነው የኖርኩት፡፡
በወንጌል አልገባ ቢለኝ በበሽታ አስመስለህ ርቀትህን ጠብቅ ብትለኝም ልመለስ አልቻልኩም፡፡ ግን ወድቄያለሁና ተነሥቶ መቆም ርቀቴንም መጠበቅ እንዳይቻለኝ ደርገው ወንበዴዎቹ አጋንንት ስወርድ አግኝተው ደብደበውኛልና ተመልሶ መቆም ተሣነኝ፡፡
ተፆፋ በሥነልቦና ባለሞያ Bini Girmachew
ጌታ ሆይ በኢያሪኮው መንገደኛ በኩል እንዳለፍህ ይህች ዐመት ከማለቋ በፊት እባክህን በእኔም በኩል እለፍ፡፡
የጠፋውን በግ አዳምን የፈለግኸው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ እኔንም ፈልገኝ፤ ባገኘኸውም ጊዜ እንደተሸከምኸው እኔንም ተሸከመኝ፡፡
የቀደመ ፍጥረትህን አዳምን ቸል እንዳላልከው ከእርሱ አብራክ የተገኘሁ እኔ ደካማ ልጁንም ቸል አትበለኝ፡፡ ይልቁንም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንድ ሰው የተባለ አዳምን እንደተሸከምከው እኔንም ተሸከመኝ፡፡
አዎን ጌታ ሆይ በመንገድ ላይ የወደቀው ስም የለሽ አንድ ሰው እኔ እንደሆንኩ አውቂያለሁ፡፡
ከኢየሩሳሌም ልዕልና ነፍስ ወደ ኢያሪኮ የኃጢአት ቁልቁለት የወረድሁት እኔ እንደሆንኩ ገብቶኛል፡፡ አንተ ለእኔ ድኅነት የሠራኸውን አሸቀንጥሬ ጥዬ እኔን ካስቀመጥክበት ከፍታ ተንደርድሬ ለእኔ ፍላጎት ወደሚስማማው ቁልቁለት የወረድሁት በወንበዴዎች እጅም የወደቅሁት የኢያሪኮው መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በምሥጢራት ከሚኖርበት ተግባራዊ የክርስትና ከፍታ በማስመሰልና በውድድር ወደሚኖርበት ዝቅታ የወረድሁት ስም የለሽ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ በእውነትና በፍቅር ከሚኖርበት የወንጌል ተራራ ጥቅሶችን ወደፍላጎታችን ወደሚለጥጥ ገደል የወረድሁት የተመታሁ መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡
አንተን በሕይወቴ አሳድሬ አንተ በእኔ እንድትሠራ ከሚያደርግ ከፍታ እራሴን ለአንተ የሚሠራ ወታደር ወደሚያስመስል የሕይወት አዘቅት አውርጄ የጣልኩት የቁልቁለት መንገደኛው እኔ ነኝ፡፡
ሰለወደቀው በማዘን ስለእርሱም በመጸለይ እውነተኞቹ ልጆችህ ከኖሩበት ከፍታ ሁሉንም ወደሚያስንቅና ወደሚያስተች ዝቅታ የወረድሁት መንገደኛ እኔ ነኝ፡፡ ነገሮችን በመንፈስና በአስተውሎት ከመመርመር በስሜትና በግብታዊነት ወደማበላሽበት ጉድጓድ የወረድሁትም እኔ ነኝ፡፡ በእቅድና በጥበብ ከመሥራት በትችትና በነቀፌታ በእልህና በብስጭት ወደመናገር ብቻ የወረድሁት ከንቱ በእውነት እኔ ነኝ፡፡ ጥቂቶቹን ልዘርዝር ብዬ እንጂ ጌታ ሆይ እኔ ያልተውኩት ሰገነት፣ ያልወደቅሁበትም አዘቅት ምን አለና፡፡
ስወርድ ደግሞ እንደተጻፈው ወንበዴዎቹ አገኙኝና ደበደቡኝ፡፡ የነበረችኝንም ሁሉ ቀሙኝ፡፡ ጌታ ሆይ እየወረድኩም ይዠው ከነበረው ያልቀሙኝ ምንም የለም፡፡
መጀመሪያ የቀሙኝ ስንገዳገድ የምደገፍባትን፤ አቀበት ቁልቁለት የማቋርጥባትን፤ አራዊትን የማርቅባትን፣ ሰንቅና ጓዜን የምሸከምባትን አንዷን ዘንጌን ጸሎቴን ቀሙኝና ድጋፍ አልባ አደረጉኝ፡፡ ተነሥቼ ልጸልይ ስቆም አካሌ እንደ ሐውልት ቆሞ ነፍሴን ይዘዋት ይዞራሉ፡፡ አንዳንዴ ጥርሴን ያስነክሱኛል፡፡ አንዳንዴ ስለአንተ ተቆርቋሪ አስምስለው ጦርነት ውስጥ ይከቱኛል፡፡
ሌላ ጊዜ በአንተ በኩል ማግኘት የሚገባኝን ጥቅም ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ አንተ የማያስደስቱ የሚመስሉኝን እንድትቆርጥ እንድትጥል ያሳስቡኛል፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ የተረሳ ዘመድ ወዳጅ፣ የሞተ የጠፋ ቤተሰብእ ሳይቀር እያሳዩ ተመስጦ በሚመሰል ሕይወት ውስጥ ያጃጅሉኛል፡፡
የቀረ ሥራ የከሰረ ሀብትም አሳስበው ያናድዱኛል፡፡ ብቻ ነፍሴን የማይወስዱበት ቦታ የለም፡፡ ብሞት እንኳ መልአከ ሞት ነፍሴን ሊየንገላታት የማይችለውን ያህል ነፍሴን ያንከራትቷታል፡፡ ጸሎቴን ቀምተው ነፍሴን ማረፊያ ያጣች አሞራ አስመሰሏት፡፡
ስለዚህም የውስጥ ሰላሜ ተነጠቀ፡፡ እንኳን ከሌላው ከትዳር አጋሬ ከወላጅ ከቤተሰቤ በሰላም መነጋገሬን ሁሉ አከታትለው ቀሙኝ፡፡
ትዕግሥቴን ነጥቀዉ እንደ ፍየል ለፍላፊ፣ እንደ ጉጉት ጯሂ አደረጉኝ፡፡
ለሚናገረኝ ካልመለሰኩለት፣ የሚመለከተኝን ካልገላመጥኩት የተጠቃሁ እያስመሰሉ በመልካም የመመለስ ሀብቴን ዘረፉኝ፡፡ ይባስ በለው ልዩነቴን በእወቀት ከማስረዳት፣ ለመግባባት ከመወያየት አፋትተው የተለየለት ግልፍተኛ ተሳዳቢ አደረጉኝ፡፡
አሁንማ ካልተሳደብኩ ዐለም መሸነፌን አውቆ የሚስቅብኝ እያስመሰሉ እንኳን ይቃረኑኛል ለምላቸው በሀሳብ ይቀርቡኛል የምላቸውንም በእኔ መንገድ ስላልተናገሩ ብቻ የማላደላ ጀግና በማስመሰል እንድወርፋቸው ያደርጉኛል፡፡
ወደ ቀደመ ሕይወቴ እንዳልመለስም መንገዱን አጠሩብኝ፡፡ ጉባኤ ሔጄ እንዳልማር ጊዜ የማባክን ይመስለኛል፡፡
አንዳንድ መምህራንንም በትችት ስላስናቁኝ የመቀመጥ ትዕግሥቴ ራሱ የት እንደገባ አላውቅም፡፡ በጓደኛ ተጽእኖ ስቀመጥም ለእኔ ብሎ ከመስማት ይልቅ ይህ ለእነ እገሌ ነበር የሚያስፈልግ ያሰኘኛል፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ ዛሬም ይህን ይሰብካል እንዴ ያሰኘኛል፡፡ እኔ በማዘወትረው ኃጢአት ሳላፍር መምህሩ የሚታወቅ ትምህርት አስተማረ ብሎ አያፍርም ወይ ያሰኘኛል፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚነገረውም አሽሙርና የማይረባ ያስመስልብኛል፡፡ እዚህ ከምማር በቃ ቤቴ ተቀምጬዬ አነብባለሁ ብሎ ካስተዋኝ በኋላ ቤቴ ስገባ ቴሌቪዥን ጋር ያፋጥጠኛል፡፡
እርሱ ሲሰለቸኝ ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ የወጣ ነገር እንድመለከት በጓደኞቼ በኩል ያስደውልብኛል፡፡ እንደምንም ታግዬ ላነብብ ስነሣ እንቅልፍ እንደበረዶ ያዘንብብኛል፡፡
በቃ በጎው ነገር ካመለጠኝ በኋላ አልያዝ አልጨበጥ አለኝ፡፡ ምክር እንዳልጠይቅ ትልቅና አዋቂ ሰው ነው በሚባል የገጸ ባሕርይ ካባ ሸፍነው አሳፍረውኛል፡፡ ከዚህ ሁሉ የተነሣ በነፍሴ ሕመም ሥጋዬም ታማሚ ሆነ፡፡
እንደወፈረኩ ደከማ፣ እንደጠገብኩ ልፍስፍስ አደረጉኝ፡፡ እንዳልጾም ሰውነቴ ሁሉ እንቢ አለ፡፡ እንዳልሰግድም ጉልበቴ ሁሉ ተብረከረከ፡፡ በሁሉ ባዶ ሆኜ ቁጭ አልኩ፡፡
የነፍሴ መድኃኒት ጌታዬ ሆይ አፍ ማብዛቴን፣ ነገር መውደዴን አይተህ ነው መሰል አፍን በማስክ የሚያስይዝ የተግሣጽ ደዌ ብታመጣም የእኔ ነፍስ ግን አሁንም አላስታዋለችም፡፡
እጆቼ ማስኩን አፌ ላይ ቢያደርጉም ምላሴን ሊያስቆሟት ግን አልቻሉም፡፡ አንተ ለደቀመዛሙርትህ እንዳልከው አፍን የሚያረክሰው ከውጭ የሚገባው ሳይሆን ከውስጥ የሚወጣው ነውና ከነፍሴ ቁስል የተነሣ በአፌ የሚወጣው የነገር ጠረን አካባቢውን አሸተተው፡፡
እንኳን ለሌላው ለእኔም እየተሰማኝ ቢሆንም ነፍሴን የደበደቧት ወንበዴዎች ግን እንድነቃ አልፈቀዱልኝም፡፡ ስለዚህ ጌታ ሆይ የአፍ ብቻ ሳይሆን የልብና የኅሊና ማስክ እዘዝልኝ፡፡ እንደ ዳዊት ወዳጅህ ለአፌ ጠባቂ ሹምለት፤ ከንፈሮቼንም እንደ ቤተ መቅደስህ በር በምሕረትና በእውነት የሚከፈቱ አድርግልኝ፡፡
ጌታ ሆይ አሁን ችግሬ ገብቶኛል፤ ማስክ የሚያስፈልገኝ ለውጨኛው ሳይሆን ለውስጠኛው የኅሊና አፌ ነው፡፡ ጸረ ተሐዋሲ መድኃኒትም ከሥጋዬ ይልቅ ለነፍሴ እጆች እንደሚያስፈልጋቸው ገብቶኛል፡፡
አቤቱ ሰነድ በመደለዝ፣ ደም በማፍሰስ የረከሱ እጆቻችን በምን ይነጻሉ? የሐሰት ትርክት በመተረክ፣ የበለው ግደለው ቅስቀሳ በመጻፍ የዋሆችን በማነሣሣት ደም ያፈሰሱ የምሁር እጅ ነኝ የሚሉ የነፍስ እጆቻችንስ ቤትኛው ሳኒታይዘር ይነጻሉ? ጌታ ሆይ ዘንድሮ ሁሉንም ችግሮቼን ነግረኸኛል፡፡
በተለይ ርቀት ያለመጠበቅ፣ ቦታዬንም ያለማወቅ ችግር አስታውሼው አላውቅም ነበር፡፡ የእኔማ የተለየ ነው፡፡ እንኳን በሾምካቸው በጳጳሳት በካህናት በአንተ ወንበር ተቀምጬ ስፈርድ፣ ስገድል ሳድን፣ ስሰጥ ስነሣ ነው የኖርኩት፡፡
በወንጌል አልገባ ቢለኝ በበሽታ አስመስለህ ርቀትህን ጠብቅ ብትለኝም ልመለስ አልቻልኩም፡፡ ግን ወድቄያለሁና ተነሥቶ መቆም ርቀቴንም መጠበቅ እንዳይቻለኝ ደርገው ወንበዴዎቹ አጋንንት ስወርድ አግኝተው ደብደበውኛልና ተመልሶ መቆም ተሣነኝ፡፡
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ስብከት | ORTHODOX SIBKET
ደጉ ሳምራዊ ሆይ እንደ መንገደኛው በወደቅሁበት በረሃ ማለፍህን እየተጠባበቁ አሁንም በኢያሪኮ ጎዳና ቁልቁለቱ መካከል ላይ ነኝና አትለፈኝ፡፡
ጌታ ሆይ ከእኔ ተሽለው ያልወደቁት ቢያዩኝም ትተውኝ አለፉ እንጂ ሊያነሡኝ አልቻሉም፡፡ እንደ ቀደሙት መንገደኞች ፈርተው አይመስለኝም፡፡ ይልቁንስ ሸተተን ብለው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ደጉ ሳምራዊ ሆይ መበላሸቴ እውነታቸውን ነውና እባክህን አንተ ወደእኔ ተመለከት፡፡ ከወደቅሁበት ዛሬም አንሣኝ፡፡
እንደ ወንጌሉ በፍጹም ትሕትናህ በአህያህ ላይ ጫነኝ፡፡ ሰው መሆንን ወድደህ ሰው አለመሆንን ጠልተህ ስለእኔም ጭምር ሰው ሆነህ እንደ አህያ ደካማ የሆነ ባሕርያችን ገንዘብ አድርገሃልና ከወደቅሁበት አንሣኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ ስለእኔ ሰው ሆነሃልና በፈቃዴ ከሰውነት ባሕርይ ተራቁቼ ከእንስሳነትም ወርጄ በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን እኔን ለሰውነት መዓርግ አብቃኝ፡፡
ናከደበነፆርን ግብሩን አይተህ አረአያውን ለውጠህ አውሬ ካደረግኸው በኋላ ወደስውነነት እንደመለስከው እኔንም በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን ስለእኔ ሰው መሆንህን አስበህ ለሰውነት አብቃኝ፡፡
ስለእኔ በበረት ራቁትህን በብርድ ተወልደሃልና፤ የኃጢአት ብርዴን አርቅልኝ፡፡ ስለእኔም ጭምር ብለህ በከብቶች እስትንፋስ ተሟሙቀሃልና፤ በሙቀተ መንፈስ ቅዱስ እኔን ከኃጢአት ብርድ አላቅቀኝ፡፡
ስለእኔ ቅጠል ለብስሃልና አውልቄ የጣልሁትን ወንበዴዎቹም የዘረፉኝን የልጅነት ልብሰ ጸጋዬን መልሰህ አልብሰኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ የጠፋነውን ወደመንጋህ ለመመለስ አንተ ስለእኛ ተሰደሃልና አቤቱ እኔን መልሰኝ፡፡ የጠፋ በግህን ከቅዱሳን ኅብረት ከቅድስና ጉባኤህ ከመንጋህ ደርበኝ፡፡
እንርሱን አንድ ጉባኤ አንድ አካል ላደረገ ለቅዱስ ሥጋህና ለክቡር ደምህም አብቃኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ አቤቱ በአዲስ ዘመን ዋዜማ በአጠገቤ እለፍና አንሣኝ፡፡ ዘይትና ወይን ባልካቸው የመሥዋዕት ደምህ ቁስሌን ጥረግልኝ፡፡ ጨርቅ በተባለ ፍቅርህም ግጥም አድረገህ እሰርለኝና ከጥላቻ፣ ከከንቱነት፣ ከግብዝነት፣ ከለፍላፊነት፣ ከኩራትና ከትዕቢት፣ ከዝሙትና ከርኩሰት ቁስሌ ማገገምን ስጠኝ፡፡
በአገልጋይህ በኩል ስበህ የእንግዶች ማደሪያ ወዳልካት ቤትህ አስጠጋኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ እባክህን ለእኔ ለምስኪኑ ዛሬም ዲናርህን ክፈልልኝ፤ አቤቱ ሁለቱ ዲናሮችህ በተባሉ በብሉይና በሐዲስ እጅግ የደከመች ቁስለኛ ነፍሴን መግበህ አድንልኝ፡፡
የነፍሴ እረኛ ሆይ በአንተ ዘንድ ዝለት መሰልቸት የለምና የእኔ መቅበዝበዝ አይተህ ቸል አትበለኝ፤ ጠባቂዬ ሆይ በኃጢአቴ ምክንያት ካገኘኝ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፈስ ፈውሰህ ሰው አድርገህ አቁመኝ፡፡
ስለእኔ የእሾህ አክሊል የደፋኸው ጌታ ሆይ የአንተ ራስ ስለእኔ ተወግቷልና ኅሊናዬን ከሚወጋኝ የሀሳብና የኃጢአት እሾህ አድነኝ፡፡
በውኑ አንተ ለእኛ ብለህ ካልሆነ በከንቱ ተወግተሃልን? ስለዚህ ጌታ ሆይ ቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሜ እየጸለይኩ እያስቀደስኩ ሳይቀር እሾህ ነገር እያሰወጋ ከሚያቆስለኝ ክፉ ሀሳብ ስለደፋህልኝ የእሾህ አክሊል ብለህ እኔን አድን፡፡
አቤቴ እረኛዬ ሆይ በዘመነ ሥጋዌህ ኃጢአትህ ተተወልህ፣ ኃጢአትሽ ተተወልሽ እንዳልካቸው ኃጢአትህ ተትቶልሃል የሚለውን ድምጽህን አዲሱ ዘመን ከመግባቱ በፊት አሰማኝ፡፡
የልጆችን ለውሾች መስጠት አይገባም እንዳልካት ሴት ፈውስ ባይገባኝ እንኳ ጌታ ሆይ ውሾችም ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ ስትለህ እምነቷን አይተህ እንደፈወስክላት እኔንም በእምነት ፍጹማን ከሆኑት የተረፈውን የፈውስ ፍርፋሪ አቅምሰኝ፡፡
ቤዛዬ ሆይ ስለእኔ ተገርፈሃልና በመገረፍህ ቁስል ፈውሰኝ፡፡ በሙሴ ፊት ብርሃን በሳልከበት በአንተ ፊት ላይ አይሁድ የረከሰ ምራቃቸውን ሲተፉብህ የተጋሰከው ቤዛዬ ሆይ ዛሬም እኔ በየቀኑ በአንተ ፍጡር ላይ የምተፋውን አይተህ አላጠፋኸኝም፣ ነገር ግን ርኩሱን ምራቅ በብርሃናዊ ፊትህ ላይ ስለመቀበልህ እኔን ከርኩሰቴ አንጻኝ፡፡
አንተ ስለእኛ ስለሁላችን ተከሰህ በጲላጦስ ፊትህ ቀርበህልናልና አቤቱ ጌታ ሆይ እኛ ስለኃጢአታችን አንከሰስ አንወቀስ፤ በአንተ መከሰስ እኛ እንፈወስ እንጂ፡፡ ጌታ ሆይ ስለአንተ መንገላታታ የምእመናን መንገላታት ይበቃ፡፡ ስለአንተ መናቅ እኛ በድነቁርናና ባለማሰብ፤ ባለማቀድና ባለመሥራት የገጠመን መናቅና መገፋት በአዲሱ ዐመት ይከልከልልን፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ መስቀል ተሸክመህ ሦስት ጊዜ ወድቀሃልና፣ በግል በሠራነው ኃጢአት ከወደቅንበት ውድቀት፣ እንደተቋምም ተሰነካክለን ከወደቅንበት አዘቅት፣ የአባቶችን ገድልና ትሩፋት ይዘን ስለወደቅንበትም ታሪካዊ ውደቀት የአንተ መውደቅ ቤዛ ሆኖን እንነሣ፤ አቤቱ አንሣን፣ ቀጥ አድርገህም አቁመን፡፡
ተነሣ አልጋህን ተሸክመህ ተመላለስ እንዳልከው፤ ተነሡ ወንጌል እውነት ይዛችሁ፣ የተኛችሁበትን የታሪክ፣ የገድልና የፍቅር አልጋ ይዛችሁ በአገልግሎት ተመላለሱ ብለህ በኃጢአትና በድከመት የሰለሉ እግሮቻችንን አጽና፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ ተቸንከረሃልና ከተቸነከርንባቸው የጎሰኝነት፣ የድንቁርና የጥቅመኝነትና የአድሎ ችንካሮች አልላቀን፡፡
አቤቱ ጌታ ሆይ ስለእኛ የሆምጣጤውን መራራ ጽዋ ቀምሰሃልና በምትኩ ከፍቅርና ከይቅርታ፣ ከዕወቀትና ከምሕረት ጽዋ እኛን አቅምሰን፡፡
ሳይገባህ ስለእኛ ተገንዘህ ተቀብረሃልና አቤቱ ከድንዛዜ መግነዝ ፍታን፣ ከጥልቅ የድንቁርና መቃብርም አውጣን፡፡ ስለ ልዩ ትንሣኤህ ትንሣኤ ልቡና ወኅሊና አድለን፡፡
ስለ ቅድስት ዕረገትህም ዕርገተ ኅሊናና አልዕሎ ልቡናን አሳድርብን፡፡ ስለ ዳግም ምጽአትህም በቀኝህ የሚቆሙ ወዳጆችህ የሚሠሩትን ምግባረ ሃይማኖት ለመሥራት አብቃን፡፡
ጌታ ሆይ በዚህች በዿግሜ ኢዮብን በዮርዳኖስ ወንዘህ አጥበህ እንደፈወስነው እኛን ኢትዮጵያውያንን ከሚያጸይፍ ቁስለ ነፍሳችን ፈውሰን፡፡ እጠበን እንጠራለን፤ አንጻንም እንነጻለን፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ አይደለም መምጣትህን አስቀድመው ይነግሩ ዘንድ ስለነገርሃቸው አርእሰተ አበውና ነቢያት፣ መርጠህ አስተምረህ ሾመህ ዐለምን ወደአንተ ይመልሱ ዘንድ መስቀል መከራ ሞትን አሸክመህ ስለላክሃቸው ሐዋርያት፣ ኑፋቄ ዘርቶ መንጋውን ከአንተ ለመለየት የተጋውን የዲያብሎስን ሽንገላ ተቃውመው ሃይማኖትን በንጽህ ስለጠበቁ ሊቃውንት፣ ፍትወታትን ድል
ነሥተው በተጋድሏቸው ያለደም መፍሰስ ሰማዕትነትን ስለተቀበሉ ጻድቃን፣ የነገሥታትን ማስፈራራትና የሚያደርሱባቸውን መከራ ሳይሰቀቁ ነገሥታተ አሕዛብን ድል ስለነሡ ሰማዕታት፣ በንጽሕ እና በትጋት ሆነው ያለመታከት አንተን ስለሚያገለግሉ ሊቃነ
መላእከትና ሠራዊተ መላእክት ብለህ ይልቁንም ደግሞ ከሁሉም በላይ ስለሆነች ከእርሷ ሰው ትሆን ዘንድ ስለመርጥካት የንጽሕና መሠረት የባሕርየ አዳም መመኪያ ስለሆነች ስለንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን
ድንግል እናትህ ብለህ ጌታ ሆይ በወደቅሁበት አዘቅት እለፍና እኔን ምስኪኑን ቁስለኛ የዲያብሎስ ምርኮኛ ከወደቅሁበት አንሣኝ፤
በሚቀጥለው ዐመትና በመጪዎቹ ዘመናትም አንተን በመከተል ሕግህን በመጠበቅና ፈቃድህን በመፈጸም አንሣኝ፡፡
ለፈቃዴ አሳልፈህ አትሰጠኝ፣ ይልቁንም ለፈቃድህ የምገዛበትን ልቡና ሥጠኝ፡፡ አቤቱ አትተወኝ አትጣለኝም፣ አሜን፡፡
ጌታ ሆይ ከእኔ ተሽለው ያልወደቁት ቢያዩኝም ትተውኝ አለፉ እንጂ ሊያነሡኝ አልቻሉም፡፡ እንደ ቀደሙት መንገደኞች ፈርተው አይመስለኝም፡፡ ይልቁንስ ሸተተን ብለው ሳይሆን አይቀርም፡፡ ደጉ ሳምራዊ ሆይ መበላሸቴ እውነታቸውን ነውና እባክህን አንተ ወደእኔ ተመለከት፡፡ ከወደቅሁበት ዛሬም አንሣኝ፡፡
እንደ ወንጌሉ በፍጹም ትሕትናህ በአህያህ ላይ ጫነኝ፡፡ ሰው መሆንን ወድደህ ሰው አለመሆንን ጠልተህ ስለእኔም ጭምር ሰው ሆነህ እንደ አህያ ደካማ የሆነ ባሕርያችን ገንዘብ አድርገሃልና ከወደቅሁበት አንሣኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ ስለእኔ ሰው ሆነሃልና በፈቃዴ ከሰውነት ባሕርይ ተራቁቼ ከእንስሳነትም ወርጄ በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን እኔን ለሰውነት መዓርግ አብቃኝ፡፡
ናከደበነፆርን ግብሩን አይተህ አረአያውን ለውጠህ አውሬ ካደረግኸው በኋላ ወደስውነነት እንደመለስከው እኔንም በጠባዬ አውሬ የሆንኩትን ስለእኔ ሰው መሆንህን አስበህ ለሰውነት አብቃኝ፡፡
ስለእኔ በበረት ራቁትህን በብርድ ተወልደሃልና፤ የኃጢአት ብርዴን አርቅልኝ፡፡ ስለእኔም ጭምር ብለህ በከብቶች እስትንፋስ ተሟሙቀሃልና፤ በሙቀተ መንፈስ ቅዱስ እኔን ከኃጢአት ብርድ አላቅቀኝ፡፡
ስለእኔ ቅጠል ለብስሃልና አውልቄ የጣልሁትን ወንበዴዎቹም የዘረፉኝን የልጅነት ልብሰ ጸጋዬን መልሰህ አልብሰኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ የጠፋነውን ወደመንጋህ ለመመለስ አንተ ስለእኛ ተሰደሃልና አቤቱ እኔን መልሰኝ፡፡ የጠፋ በግህን ከቅዱሳን ኅብረት ከቅድስና ጉባኤህ ከመንጋህ ደርበኝ፡፡
እንርሱን አንድ ጉባኤ አንድ አካል ላደረገ ለቅዱስ ሥጋህና ለክቡር ደምህም አብቃኝ፡፡
ጌታዬ ሆይ አቤቱ በአዲስ ዘመን ዋዜማ በአጠገቤ እለፍና አንሣኝ፡፡ ዘይትና ወይን ባልካቸው የመሥዋዕት ደምህ ቁስሌን ጥረግልኝ፡፡ ጨርቅ በተባለ ፍቅርህም ግጥም አድረገህ እሰርለኝና ከጥላቻ፣ ከከንቱነት፣ ከግብዝነት፣ ከለፍላፊነት፣ ከኩራትና ከትዕቢት፣ ከዝሙትና ከርኩሰት ቁስሌ ማገገምን ስጠኝ፡፡
በአገልጋይህ በኩል ስበህ የእንግዶች ማደሪያ ወዳልካት ቤትህ አስጠጋኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ እባክህን ለእኔ ለምስኪኑ ዛሬም ዲናርህን ክፈልልኝ፤ አቤቱ ሁለቱ ዲናሮችህ በተባሉ በብሉይና በሐዲስ እጅግ የደከመች ቁስለኛ ነፍሴን መግበህ አድንልኝ፡፡
የነፍሴ እረኛ ሆይ በአንተ ዘንድ ዝለት መሰልቸት የለምና የእኔ መቅበዝበዝ አይተህ ቸል አትበለኝ፤ ጠባቂዬ ሆይ በኃጢአቴ ምክንያት ካገኘኝ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፈስ ፈውሰህ ሰው አድርገህ አቁመኝ፡፡
ስለእኔ የእሾህ አክሊል የደፋኸው ጌታ ሆይ የአንተ ራስ ስለእኔ ተወግቷልና ኅሊናዬን ከሚወጋኝ የሀሳብና የኃጢአት እሾህ አድነኝ፡፡
በውኑ አንተ ለእኛ ብለህ ካልሆነ በከንቱ ተወግተሃልን? ስለዚህ ጌታ ሆይ ቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሜ እየጸለይኩ እያስቀደስኩ ሳይቀር እሾህ ነገር እያሰወጋ ከሚያቆስለኝ ክፉ ሀሳብ ስለደፋህልኝ የእሾህ አክሊል ብለህ እኔን አድን፡፡
አቤቴ እረኛዬ ሆይ በዘመነ ሥጋዌህ ኃጢአትህ ተተወልህ፣ ኃጢአትሽ ተተወልሽ እንዳልካቸው ኃጢአትህ ተትቶልሃል የሚለውን ድምጽህን አዲሱ ዘመን ከመግባቱ በፊት አሰማኝ፡፡
የልጆችን ለውሾች መስጠት አይገባም እንዳልካት ሴት ፈውስ ባይገባኝ እንኳ ጌታ ሆይ ውሾችም ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ ስትለህ እምነቷን አይተህ እንደፈወስክላት እኔንም በእምነት ፍጹማን ከሆኑት የተረፈውን የፈውስ ፍርፋሪ አቅምሰኝ፡፡
ቤዛዬ ሆይ ስለእኔ ተገርፈሃልና በመገረፍህ ቁስል ፈውሰኝ፡፡ በሙሴ ፊት ብርሃን በሳልከበት በአንተ ፊት ላይ አይሁድ የረከሰ ምራቃቸውን ሲተፉብህ የተጋሰከው ቤዛዬ ሆይ ዛሬም እኔ በየቀኑ በአንተ ፍጡር ላይ የምተፋውን አይተህ አላጠፋኸኝም፣ ነገር ግን ርኩሱን ምራቅ በብርሃናዊ ፊትህ ላይ ስለመቀበልህ እኔን ከርኩሰቴ አንጻኝ፡፡
አንተ ስለእኛ ስለሁላችን ተከሰህ በጲላጦስ ፊትህ ቀርበህልናልና አቤቱ ጌታ ሆይ እኛ ስለኃጢአታችን አንከሰስ አንወቀስ፤ በአንተ መከሰስ እኛ እንፈወስ እንጂ፡፡ ጌታ ሆይ ስለአንተ መንገላታታ የምእመናን መንገላታት ይበቃ፡፡ ስለአንተ መናቅ እኛ በድነቁርናና ባለማሰብ፤ ባለማቀድና ባለመሥራት የገጠመን መናቅና መገፋት በአዲሱ ዐመት ይከልከልልን፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ መስቀል ተሸክመህ ሦስት ጊዜ ወድቀሃልና፣ በግል በሠራነው ኃጢአት ከወደቅንበት ውድቀት፣ እንደተቋምም ተሰነካክለን ከወደቅንበት አዘቅት፣ የአባቶችን ገድልና ትሩፋት ይዘን ስለወደቅንበትም ታሪካዊ ውደቀት የአንተ መውደቅ ቤዛ ሆኖን እንነሣ፤ አቤቱ አንሣን፣ ቀጥ አድርገህም አቁመን፡፡
ተነሣ አልጋህን ተሸክመህ ተመላለስ እንዳልከው፤ ተነሡ ወንጌል እውነት ይዛችሁ፣ የተኛችሁበትን የታሪክ፣ የገድልና የፍቅር አልጋ ይዛችሁ በአገልግሎት ተመላለሱ ብለህ በኃጢአትና በድከመት የሰለሉ እግሮቻችንን አጽና፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ ተቸንከረሃልና ከተቸነከርንባቸው የጎሰኝነት፣ የድንቁርና የጥቅመኝነትና የአድሎ ችንካሮች አልላቀን፡፡
አቤቱ ጌታ ሆይ ስለእኛ የሆምጣጤውን መራራ ጽዋ ቀምሰሃልና በምትኩ ከፍቅርና ከይቅርታ፣ ከዕወቀትና ከምሕረት ጽዋ እኛን አቅምሰን፡፡
ሳይገባህ ስለእኛ ተገንዘህ ተቀብረሃልና አቤቱ ከድንዛዜ መግነዝ ፍታን፣ ከጥልቅ የድንቁርና መቃብርም አውጣን፡፡ ስለ ልዩ ትንሣኤህ ትንሣኤ ልቡና ወኅሊና አድለን፡፡
ስለ ቅድስት ዕረገትህም ዕርገተ ኅሊናና አልዕሎ ልቡናን አሳድርብን፡፡ ስለ ዳግም ምጽአትህም በቀኝህ የሚቆሙ ወዳጆችህ የሚሠሩትን ምግባረ ሃይማኖት ለመሥራት አብቃን፡፡
ጌታ ሆይ በዚህች በዿግሜ ኢዮብን በዮርዳኖስ ወንዘህ አጥበህ እንደፈወስነው እኛን ኢትዮጵያውያንን ከሚያጸይፍ ቁስለ ነፍሳችን ፈውሰን፡፡ እጠበን እንጠራለን፤ አንጻንም እንነጻለን፡፡
ጌታ ሆይ ስለእኛ አይደለም መምጣትህን አስቀድመው ይነግሩ ዘንድ ስለነገርሃቸው አርእሰተ አበውና ነቢያት፣ መርጠህ አስተምረህ ሾመህ ዐለምን ወደአንተ ይመልሱ ዘንድ መስቀል መከራ ሞትን አሸክመህ ስለላክሃቸው ሐዋርያት፣ ኑፋቄ ዘርቶ መንጋውን ከአንተ ለመለየት የተጋውን የዲያብሎስን ሽንገላ ተቃውመው ሃይማኖትን በንጽህ ስለጠበቁ ሊቃውንት፣ ፍትወታትን ድል
ነሥተው በተጋድሏቸው ያለደም መፍሰስ ሰማዕትነትን ስለተቀበሉ ጻድቃን፣ የነገሥታትን ማስፈራራትና የሚያደርሱባቸውን መከራ ሳይሰቀቁ ነገሥታተ አሕዛብን ድል ስለነሡ ሰማዕታት፣ በንጽሕ እና በትጋት ሆነው ያለመታከት አንተን ስለሚያገለግሉ ሊቃነ
መላእከትና ሠራዊተ መላእክት ብለህ ይልቁንም ደግሞ ከሁሉም በላይ ስለሆነች ከእርሷ ሰው ትሆን ዘንድ ስለመርጥካት የንጽሕና መሠረት የባሕርየ አዳም መመኪያ ስለሆነች ስለንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን
ድንግል እናትህ ብለህ ጌታ ሆይ በወደቅሁበት አዘቅት እለፍና እኔን ምስኪኑን ቁስለኛ የዲያብሎስ ምርኮኛ ከወደቅሁበት አንሣኝ፤
በሚቀጥለው ዐመትና በመጪዎቹ ዘመናትም አንተን በመከተል ሕግህን በመጠበቅና ፈቃድህን በመፈጸም አንሣኝ፡፡
ለፈቃዴ አሳልፈህ አትሰጠኝ፣ ይልቁንም ለፈቃድህ የምገዛበትን ልቡና ሥጠኝ፡፡ አቤቱ አትተወኝ አትጣለኝም፣ አሜን፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
አባ ጊዮርጊስ በሦስትዮሽ ስልት (Trio) ራሱን ከጌታና ከእናቱ
ጋር የሚያዛምድበት ውብ ሥነ ጽሑፋዊ ሦስት ማዕዘንም አለ ፡-
‘እኔ የተጠማሁ ነኝ ፤
አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ ፣
ልጅሽ የሕይወት ውኃ ነው፡፡
እኔ ነጋዴ ነኝ ፤
አንቺ መርከብ ነሽ ፤
ልጅሽ ዕንቈ ነው፡፡
እኔ ገደል ተሻጋሪ ነኝ ፤
አንቺ ድልድይ ነሽ ፤
ልጅሽ የደስታ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ ደሃ ነኝ ፤
አንቺ የክብር ማከማቻ ነሽ ፤
ልጅሽ የከበረ ጌጥ ነው፡፡
እኔ ቁስለኛ ነኝ ፤
አንቺ የመድኃኒት ብልቃጥ ነሽ ፣
ልጅሽ መድኃኒት ነው፡፡
እኔ ዕርቃኔን ነኝ ፤
አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ ፣
ልጅሽ የማያረጅ ልብስ ነው’
የግዮን ወንዝ ገጽ 27-28
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
ጋር የሚያዛምድበት ውብ ሥነ ጽሑፋዊ ሦስት ማዕዘንም አለ ፡-
‘እኔ የተጠማሁ ነኝ ፤
አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ ፣
ልጅሽ የሕይወት ውኃ ነው፡፡
እኔ ነጋዴ ነኝ ፤
አንቺ መርከብ ነሽ ፤
ልጅሽ ዕንቈ ነው፡፡
እኔ ገደል ተሻጋሪ ነኝ ፤
አንቺ ድልድይ ነሽ ፤
ልጅሽ የደስታ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ ደሃ ነኝ ፤
አንቺ የክብር ማከማቻ ነሽ ፤
ልጅሽ የከበረ ጌጥ ነው፡፡
እኔ ቁስለኛ ነኝ ፤
አንቺ የመድኃኒት ብልቃጥ ነሽ ፣
ልጅሽ መድኃኒት ነው፡፡
እኔ ዕርቃኔን ነኝ ፤
አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ ፣
ልጅሽ የማያረጅ ልብስ ነው’
የግዮን ወንዝ ገጽ 27-28
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
Telegram
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1
በሌሊት ወደ ኢየሱስ
(ሽራፊ ሃሳብ 1 ከኒቆዲሞስ ምንባብ)
ኒቆዲሞስ በውድቅት ሌሊት ወደ ጌታችን መጣ። ሌሊት እንግዲህ በቂ ብርሃን የሌለበት ፣ እንቅፋት የሚበዛበት ፣ ጭልም የሚልበት ፣ ግራ ቀኝ ቢያዩ ሰው የሚታጣበት ፣ ማጅራት ከሚመቱ ወንበዴዎች በቀር በመንገድ ሌላ ሰው የማያጋጥምበት ፣ ብርድና ቆፈን ሰውነትን የሚያስጨንቅበት ሰዓት ነው። ይህ የአይሁድ መምህር በሌሊት የመጣበት ምክንያቱ ብዙ ሲሆን ለእምነት ማነስ ማሳያ የሚሆን ሰው ነው።
ዛሬ ደግሞ ለአፍታ ኒቆዲሞስን "በሌሊት ወደ ኢየሱስ በመምጣቱ" በጥቂቱ እናመስግነው። ብዙ እግሮች ወደ ኃጢአት በሚሮጡባት ሌሊት ወደ ክርስቶስ የሮጠውን ይህንን ሰው እስቲ እናድንቀው! ይህንን የሌሊት ግርማ ሳይበግረው ወደ ኢየሱስ የተጓዘ የጨለማ ተጓዥ ፣ ይህንን ሰዓታት ቋሚ ፣ ይህንን ማሕሌት ቋሚ በጥቂቱ ብናመሰግነው ምን አለ? ከጌታ ፊት ቆሞ ቅኔ የተመራውን ፣ ስለ ልደት እየተናገረ ስለ ጥምቀት የሚያመሰጥረውን የፈጣሪን ቅኔ ተቀብሎ ሊያዜም ከጀመረ በኋላ መቀበል ሲያቅተው ጌታችን "አንተ የአይሁድ መምህር ስትሆን ይህንን አታውቅምን?" ብሎ የገሠፀውን ኒቆዲሞስን እስቲ ዛሬ በበጎነቱ አርኣያ እናድርገው።
በሕይወታችን ውስጥ የተስፋ ብርሃን ጭልም ባለብን ጊዜ ፣ እንቅፋት በበዛብን ወቅት ፣ ግራ ቀኝ አይተን ሰው ባጣንበትና ብቸኝነት በዋጠን ሰዓት ፣ ክፉ ከማድረግ በማይመለሱ ጨካኞች በተከበብን ሰዓት እኛስ ወዴት እንሔዳለን?
ሕይወቱ "ሌሊት" የሆነበት ሰው ሁሉ ወደ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ቢሔድ እንደሚሻለው ከኒቆዲሞስ የተሻለ ምሳሌ የለም። ሕይወቱ የጨለመ ባይሆን እንኳን ልቡ የጨለመበት ፣ በኃጢአት ጠል የጠቆረ ፣ በበደል ብርድ ቆፈን እጅ እግሩ የታሰረ ከእኛ መካከል ስንት አለ?
እመነኝ ፣ ተስፋ ቆርጠህ ቁጭ ብለህ እስከሚነጋልህ ብትጠብቅ አይነጋም። ይልቅ ተነሥና "በሌሊት ወደ ክርስቶስ ሒድ" እርሱ ተስፋ ለቆረጠው ማንነትህ ዳግመኛ መወለድ እንዳለም ይነግርልሃል። ኒቆዲሞስ ጌታችንን ሊያየው ሔዶ ራሱ ታይቶ እንደመጣ አንተም ወደ እርሱ የቀረብህ እንደሆነ ራስህን ታያለህ።
በ"ሌሊት" ውስጥ ለሚኖር ሰው ነግቶ ፀሐይ ትወጣልኛለች ብሎ ከሚጠባበቅ ይልቅ በሌሊት እንደ ኒቆዲሞስ ተነሥቶ ወደ ጽድቅ ፀሐይ ወደ ክርስቶስ ቢሔድ ይሻለዋል። ወደ እርሱ ለሚሔድ ሰው ሌሊቱ ይነጋል ፣ ክርስቶስ ያለበት ሌሊት ከቀን ይልቅ ብሩሕ ነው ፣ እውነተኛው ብርሃን ያለበት ጨለማም ጨለማ አይደለም። ስለ እርሱ "ጨለማም በአንተ ዘንድ አይጨልምም" ተብሎ ተጽፎአልና።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 16 2010
ኒቆዲሞስ
ናይሮቢ ፣ ኬንያ
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
(ሽራፊ ሃሳብ 1 ከኒቆዲሞስ ምንባብ)
ኒቆዲሞስ በውድቅት ሌሊት ወደ ጌታችን መጣ። ሌሊት እንግዲህ በቂ ብርሃን የሌለበት ፣ እንቅፋት የሚበዛበት ፣ ጭልም የሚልበት ፣ ግራ ቀኝ ቢያዩ ሰው የሚታጣበት ፣ ማጅራት ከሚመቱ ወንበዴዎች በቀር በመንገድ ሌላ ሰው የማያጋጥምበት ፣ ብርድና ቆፈን ሰውነትን የሚያስጨንቅበት ሰዓት ነው። ይህ የአይሁድ መምህር በሌሊት የመጣበት ምክንያቱ ብዙ ሲሆን ለእምነት ማነስ ማሳያ የሚሆን ሰው ነው።
ዛሬ ደግሞ ለአፍታ ኒቆዲሞስን "በሌሊት ወደ ኢየሱስ በመምጣቱ" በጥቂቱ እናመስግነው። ብዙ እግሮች ወደ ኃጢአት በሚሮጡባት ሌሊት ወደ ክርስቶስ የሮጠውን ይህንን ሰው እስቲ እናድንቀው! ይህንን የሌሊት ግርማ ሳይበግረው ወደ ኢየሱስ የተጓዘ የጨለማ ተጓዥ ፣ ይህንን ሰዓታት ቋሚ ፣ ይህንን ማሕሌት ቋሚ በጥቂቱ ብናመሰግነው ምን አለ? ከጌታ ፊት ቆሞ ቅኔ የተመራውን ፣ ስለ ልደት እየተናገረ ስለ ጥምቀት የሚያመሰጥረውን የፈጣሪን ቅኔ ተቀብሎ ሊያዜም ከጀመረ በኋላ መቀበል ሲያቅተው ጌታችን "አንተ የአይሁድ መምህር ስትሆን ይህንን አታውቅምን?" ብሎ የገሠፀውን ኒቆዲሞስን እስቲ ዛሬ በበጎነቱ አርኣያ እናድርገው።
በሕይወታችን ውስጥ የተስፋ ብርሃን ጭልም ባለብን ጊዜ ፣ እንቅፋት በበዛብን ወቅት ፣ ግራ ቀኝ አይተን ሰው ባጣንበትና ብቸኝነት በዋጠን ሰዓት ፣ ክፉ ከማድረግ በማይመለሱ ጨካኞች በተከበብን ሰዓት እኛስ ወዴት እንሔዳለን?
ሕይወቱ "ሌሊት" የሆነበት ሰው ሁሉ ወደ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ቢሔድ እንደሚሻለው ከኒቆዲሞስ የተሻለ ምሳሌ የለም። ሕይወቱ የጨለመ ባይሆን እንኳን ልቡ የጨለመበት ፣ በኃጢአት ጠል የጠቆረ ፣ በበደል ብርድ ቆፈን እጅ እግሩ የታሰረ ከእኛ መካከል ስንት አለ?
እመነኝ ፣ ተስፋ ቆርጠህ ቁጭ ብለህ እስከሚነጋልህ ብትጠብቅ አይነጋም። ይልቅ ተነሥና "በሌሊት ወደ ክርስቶስ ሒድ" እርሱ ተስፋ ለቆረጠው ማንነትህ ዳግመኛ መወለድ እንዳለም ይነግርልሃል። ኒቆዲሞስ ጌታችንን ሊያየው ሔዶ ራሱ ታይቶ እንደመጣ አንተም ወደ እርሱ የቀረብህ እንደሆነ ራስህን ታያለህ።
በ"ሌሊት" ውስጥ ለሚኖር ሰው ነግቶ ፀሐይ ትወጣልኛለች ብሎ ከሚጠባበቅ ይልቅ በሌሊት እንደ ኒቆዲሞስ ተነሥቶ ወደ ጽድቅ ፀሐይ ወደ ክርስቶስ ቢሔድ ይሻለዋል። ወደ እርሱ ለሚሔድ ሰው ሌሊቱ ይነጋል ፣ ክርስቶስ ያለበት ሌሊት ከቀን ይልቅ ብሩሕ ነው ፣ እውነተኛው ብርሃን ያለበት ጨለማም ጨለማ አይደለም። ስለ እርሱ "ጨለማም በአንተ ዘንድ አይጨልምም" ተብሎ ተጽፎአልና።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 16 2010
ኒቆዲሞስ
ናይሮቢ ፣ ኬንያ
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
Telegram
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1
✝እንኳን አደረሳችሁ!
"ከሰውስ እንደኔ ኃጢአት የሚሠራ፤
ከመሐሪዎችስ እንዳንተ 'ሚራራ፤
አይገኝምና በዚያ የፍርድ ሥፍራ፤
ስለ ደምህ ብለህ ለኃጥኡ ራራ!"
"አልቦ ዘከማየ አበሳ ኃጢአት ገባሪ፤
ወአልቦ ዘከማከ እግዚአብሔር መሐሪ፤
፤
አመ ለኮንኖ ዓለመ ትመጽእ ደኃሪ፤
ቀደመ ገቦከ ኃጢአትየ አስተስሪ!"
(መልክአ መድኃኔ ዓለም)
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
"ከሰውስ እንደኔ ኃጢአት የሚሠራ፤
ከመሐሪዎችስ እንዳንተ 'ሚራራ፤
አይገኝምና በዚያ የፍርድ ሥፍራ፤
ስለ ደምህ ብለህ ለኃጥኡ ራራ!"
"አልቦ ዘከማየ አበሳ ኃጢአት ገባሪ፤
ወአልቦ ዘከማከ እግዚአብሔር መሐሪ፤
፤
አመ ለኮንኖ ዓለመ ትመጽእ ደኃሪ፤
ቀደመ ገቦከ ኃጢአትየ አስተስሪ!"
(መልክአ መድኃኔ ዓለም)
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw